ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
الذهاب إلى القناة على Telegram
የቀድሞ አበው እና እመት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ጥበብ... 👇👇👇👇👇👇👇👇 👉 @behlateabew 👈 👆👆👆👆👆👆👆👆 https://t.me/+RICJUxY54uwNbPXe
إظهار المزيد8 549
المشتركون
-124 ساعات
-137 أيام
-8930 أيام
أرشيف المشاركات
#ስለ #ዓለማዊ #ግርግርና #ስለ #ነፍስ>>_*
"ነፍስህ ከሥጋህ እንደምትበልጥ ሁሉ፣
ለነፍስህ የምታደርገው ጥንቃቄም
ለሥጋህ ከምታደርገው መብለጥ አለበት።
ለሰውነትህ ምግብ ትፈልጋለህ፣
ለነፍስህስ ቃለ እግዚአብሔርን ትመግባታለህ?
ለሰውነትህ ልብስ ትገዛለህ፣
ነፍስህንስ በምግባርና በሃይማኖት ታስጌጣታለህ?
ይህ ዓለም እንደ ሆቴል ነው፤
ጥቂት ቆይተህ ትወጣዋለህ።
*እንደ እንግዳ እንጂ እንደ ባለቤት* አትኑር።
ንብረትህንም ቢሆን እንደ አደራ እንጂ እንደ ቋሚ ሀብት አትቁጠረው፤
ምክንያቱም ስትሄድ ይዘኸው የምትሄደው
*በልብህ የሰነቅከውን ፍቅር ብቻ ነው።"*
ቅዱስ ባሲልዮስ
«ጌታ ሆይ! አንተ በመስቀል ላይ ሆነህ የሰቀሉህን ሰዎች በይቅርታ ተመለከትካቸው፤ እኔ ግን ከእኔ የተሻለውን ሰው እንኳ በቅናት እመለከታለሁ። አንተ ለእኔ ስትል የሞት ፍርድን በጸጥታ ተቀበልክ፤ እኔ ግን ጥቂት ስድብን እንኳ ችዬ ማሳለፍ አቃተኝ። አቤቱ የተሰቀልከው ስለ እኔ፣ የሞትከው ስለ እኔ ነውና፣ ይህን ደንዳና ልቤን በፍቅርህ ችንካር ውጋው፤ ከዓለም ፍቅር ለይተህ፣ ከመስቀልህ ሥር አስጠጋኝ»
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
ክርስቶስ እንዲህ ይላል፦ “እኔ ነኝ፤ ስለዚህ እናንተ በኃጢአት የረከሳችሁ የሰው ወገኖች ሁሉ ኑና የኃጢአትን ይቅርታ ተቀበሉ። እኔ ነፃነታችሁ ነኝና። እኔ የመዳኛችሁ ፋሲካ ነኝ፤ ስለ እናንተ የታረድኩ በግ እኔ ነኝ፤ እኔ ቤዛችሁ ነኝ፤ እኔ ሕይወታችሁ ነኝ፤ እኔ ብርሃናችሁ ነኝ፤ እኔ መድኃኒታችሁ ነኝ፤ እኔ ትንሳኤያችሁ ነኝ፤ እኔ ንጉሣችሁ ነኝ። በቀኝ እጄ ወደ ላይ አነሣችኋለሁ፤ ወደ ሰማያዊው ከፍታ እመራችኋለሁ፤ በዚያም የዘላለም አባትን አሳያችኋለሁ።”
ቅዱስ ሜሊጦ ዘሰርዴስ
"ጥቂት ደም ዓለምን ሁሉ ዳነ፤ እርሱ በገዛ ደሙ እኛን ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከምድር ወደ ሰማይ አሻገረን።"
ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዝናዙ
እንኳን ለብርሀነ ትንሳኤው አደረሳችሁ!
ሞት ሆይ! መውጊያህ ወዴት አለ? ሲዖል፥ መቃብርም ሆይ! ድል መንሣትህ ይዞም ማስቀረትህ ወዴት አለ?
#ክርስቶስ_ተነሣ፤ ሞት ሆይ፥ አንተም ጠፋህ!
#ክርስቶስ_ተነሣ፣ አጋንንትም አዘኑ!
#ክርስቶስ_ተነሣ፤ መላእክትም ሐሴት አደረጉ!
#ክርስቶስ_ተነሣ፤ የሰው ሕይወትም ነጻ ወጣች!
#ክርስቶስ_ተነሣ፤ መቃብርም ባዶ ኾነች!
ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶ ለአንቀላፉት ኹሉ በኵር ኾኖላቸዋልና፡፡
(#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ)
"ክርስቶስ ተነሥቷል፤ ሞትም ተሸንፏል! ክርስቶስ ተነሥቷል፤ ሕይወትም ነግሣለች! በመቃብርም አንድም ሙት አልቀረም፤ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ በመነሣቱ ለሞቱት ሁሉ በኩር ሆኖላቸዋልና።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"የሁሉ ጌታ የሆነው እርሱ የሁሉንም ዕዳ ይከፍል ዘንድ ሥጋውን ለሞት አሳልፎ ሰጠ፤ በዚህም በሥጋው አማካኝነት ለሁላችንም የትንሣኤን መንገድ ከፈተልን።"
ቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ
"ስለ ስሙ (ስለ ክርስቶስ) የታሰርኩ ብሆንም እንኳ፣ በኢየሱስ ክርስቶስ ገና ፍጹም አልሆንኩም።"
ቅዱስ ኢግናጥዮስ
"ትዕቢት ማለት ዓለምን በራስህ ሃሳብ ለመፍጠር መሞከርና በዚያው ውስጥ መኖር ነው። ትሕትና ግን ዓለምን እግዚአብሔር እንደፈጠራት አድርጎ መቀበል ነው።"
ቅዱስ ሶፍሮኒ ዘኤሴክስ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
