ምድርን ማሳመር
የተለያዩ የዳዕዋ እና ወቅታዊ ምስል , ፅሁፍ እና ቪዲዎች የሚለቀቁበት ቻናል መጪው ግዜ የኢስላም ነው!
إظهار المزيد934
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-930 أيام
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
Repost from N/a
Photo unavailableShow in Telegram
⌛3 ቀን ብቻ ቀረ!⌛
ኢስላምን ለመተግበር ህግጋቱን ማወቅ አስፈላጊ ነው። የኢስላማዊ ህግጋት ጥናት ዘርፍ ፊቅህ ይባላል። ታዋቂ ከሆኑ የፊቅህ መዝሀቦች (አስተሳሰብ ትምህርት ቤቶች) መሀከል የሆነው ፊቅህ አሻፊዒያ የመጀመሪያ ኪታብ የሆነችውን ሰፊነቱ ነጃ መማር ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ብዙ ምሁራን መስክረዋል።
ሰፊነቱ ነጃ ማለት የመዳኛይቱ መርከብ ማለት ሲሆን በአምልኮ ተግባራቶቻችን ስኬታማ ሆነን እንድን ዘንድ ሁነኛ ሚና ያላት ኪታብ ነች። በሀገራችንም የሀይማኖት ትምህርት ጀማሪዎች የሸሪዓ እውቀትን የሚጀምሩባት ኪታብ ነች።
በኪታቧ አንድ ሙስሊም ሊያከናውናቸው የሚገቡ መሰረታዊ አምልኳዊ ተግባራት ህግጋት በግሩም ሁኔታ ቀርበዋል።
እርስዎም ሀይማኖታዊ ግዴታዎትን በእውቀት ላይ ተመስርተው ያከናውኑ ዘንድ ለማገዝ አልገዛሊ አካዳሚ ይህን አድል አመቻችቶላችኋል።
የትምህርት አሰጣጡ ሙሉ በሙሉ በኦንላየን የቀጥታ ስርጭት (LIVE) ሲሆን በተጨማሪም ለትምህርት አሰጣጥ ሂደቱ ውጤታማነት አጋዥ የሆኑ የትምህርት ግብአቶችን ያገኛሉ።
ትምህርቱ የሚጀምረው ጁን 22/2024 ወይም ሰኔ 15/2016 ዓ ል ሲሆን ለተከታታይ 12 ሳምንታት ዘወትር ቀዳሜ ማታ 2:30–3:15 በቀጥታ ስርጭት ይተላለፋል። በትምህርቱ ማጠናቀቂያም ፈተና የሚኖር ይሆናል።
በስኬት የሚያጠናቅቁ ተማሪዎች ሰርተፍኬት የሚያገኙ ሲሆን ወደቀጣይ ምዕራፍ በመሸጋገር የእውቀት አድማሳቸውን የሚያሰፉበት እድል ተመቻችቷል።
ያለን ቦታ ውስን በመሆኑ ዛሬውኑ ተመዝግበው ቦታዎትን ይያዙ።
ለመመዝገብ ከስር ያለውን ሊንክ ይጫኑ
https://forms.gle/35MjjTBNxhkyiBH66
ለተጨማሪ መረጃ በቴሌግራም @algazaliacademyadmin
ወይም በዋትስአፕ https://wa.me/251984109507 ያናግሩን
የኡድሒያ በሬ አስተራረድ ትምህርት
1/ መጀመሪያ ገበያ ወጥተን በሬውን search እናደርጋለን።
2/ ካገኘነው በኋላ: በተስማማነው መሰረት ዋጋውን ከፍለን በሬውን save ማድረግ ነው።
3/ ወደቤት እናመጣውና በ group በመሆን: መሬት ላይ በግራው download እናደርገዋለን።
4/ ከዛም የተቀደሰውን የጌታችንን የአላህን ስም በማውሳት shortcut እናደርገዋለን።
5/ ከዛም የበሬው ህይወት እስትንፋሱ swith off እስኪሆን እንጠብቀዋለን።
6/ ሲቀጥል ደግሞ ቆዳውን ከበሬው ሰውነት ላይ remove በማድረግ እናራቁተዋለን።
7/ በመቀጠል ወደ ሰውነቱ hack አድርገን እንገባለን።
8/ ከዚያም ከውስጡ ያሉትን applications አንድ በአንድ እናወጣቸዋለን።
8/ ያወጣናቸውን applications በፎልደር ላይ እንደረድራቸዋለን።
9/ ከዚያም ዘመድና ጎረቤት invite በማድረግ እንቃመሳቸዋለን።
10/ ምስኪኖችን ጠርተን ደግሞ share እናደርጋለን።
ትስማማላችሁ???
በአቡ ሀይደር
🤩 1
የሸህ ሚናስ ልጅ ሼህ ከረም በጠና ታመው ለማሳከሚያ ለተጠየቀው እርዳታ እስከአሁን የተባበራችሁ ወንድምና እህቶች አላህ ኸይር ጀዛ ይክፈላችሁ።
ሼህ ከረም በ ታዝማ ሜዲካል እና ሰርጂካል የሕክምና ማእከል ከግንቦት 21 ጀምሮ ተኝተው ከባድ ክትትል እየተደረገላቸው ነው። አሁን ያሉበትን ሁኔታ በተመለከተ፣ አልጋ ይዘዉ እየታከሙ ያለ ቢሆንም ሃኪሞቹ “ICU Room ገብተዉ ህክምናዉን ካልተከታተሉ በስተከቀር በሽታው እየተባባሰባቸዉ ይሄዳል” ለዚህ ደግሞ በየግዜዉ ማሲያዢያ እየተባለ የሚከፈል በርከት ያለ ገንዘብ ያስፈልጋችኋል ስላሉና በገንዘብ እጥረት ምክንያት በሆስፒታሉ ዉስጥ የሚሰጠውን ህክምና ለማቋረጥ ጫፍ ላይ የደረሱበት ሁኔታ ዉስጥ ነዉ ያሉት ፡፡
በተጨማሪም በተጠየቀው አካውንት የገባላቸው ብር በጣም አነስተኛ ከመሆኑም በላይ ካሉበት ሁኔታ አንጻር በሳቸው ፊርማ አካውንቱን ማንቀሳቀስ አልተቻለም።
በመሆኑም በሶስት ቅርብ ዘመዶቻቸው በጋራ የሚንቀሳቀስ አዲስ አካውንት የተከፈተ በመሆኑ ለሚያስፈልገው ከፍተኛ ህክምና የቻላችሁትን ታበረክቱ ዘንድ በአላህ ስም እንጠይቃለን።
CBE Account
1000631136641
Hassen Tahir
Mahmoud Teyib
Mezid Abdella
:
:
بسم الله ، الحمدلله ، والصلاة والسلام على رسول الله
እኝህ አባታችን ሸይኽ ከረም ሸይኽ ዐብዱልባሲጥ ይባላሉ። ላፍቶ፣ ሀና ማርያምና ሰፈራ አካባቢ ባሉ መስጊዶች ለረዥም ዓመታት ነሕዉና ሌሎች ፈኖችን ሲያቀሩ የኖሩ ዓሊም ናቸው። ካለፉት አምስት ወራት ወዲህ ግን ሐኪሞች እንደሚሉት በልብ እና በኩላሊት ችግር የተነሳ በጽኑ ታመው የአልጋ ቁራኛ ሆነዋል። ከሚወዱት የዒልም ማእድ ከተነጠሉም ይህንኑ ያህል ጊዜያት ተቆጥረዋል። ሸይኽ ከረም ከአባታቸው የወረሱትን ሀይማኖታዊ ዕውቀት በማሠራጨት ሲባትሉ የኖሩ
Photo unavailableShow in Telegram
የፍልስጤም ነቅባ (መከራ) ከተፈፀመ ከ76 ዓመታት በኋላም ፍልስጤም በፅናት መቆሟን ትቀጥላለች ወረራውም መክሸፉ አይቀርም 🇵🇸✌🏼
©Embassy of Palestine in Addis ababa
😢 3
Photo unavailableShow in Telegram
ኢና ሊላሂ ወኢና ኢላይሂ ራጂዑን
በተለያዩ ከተሞች በመዘዋወር የጎዳና ላይ ዳዕዋ ያደርግ የነበረው ኡስታዝ ፈቂ ገለቶ ወደ አኼራ ሄደ!
...
(ሀሩን ሚዲያ፦ግንቦት 06/2016)
...
በተለያዩ ከተሞች እየተዘዋወረ በተለይ በአሳሳ፣ሮቤ፣አዳማ ፣ አርሲ ፣ባሌ፣ሻሸመኔ ፣ሀረር፣ድሬዳዋ፣አዲስአበባን በመሳሰሉ ከተሞች በወዘዋወር የጎዳና ላይ ዳዕዋ ያደርግ የነበረው ኡስታዝ ፈቂ ገለቶ በዛሬው ዕለት በሻሸመኔ ከተማ በድንገት ወደአኼራ መሻገሩ ተሰምቷል።
..
ኡስታዝ ፈቂ ገለቶ ምንም የማይፈራ ሙጃሂድ ከልጅነት እስከ ወጣትነትና ጎልማሳነት ምናልባት እስካዛሬዋ እስከመጨረሻዋ የዱንያ ላይ ቀኑ ድረስ ሐያቱን በሙሉ በደዕዋ አሳልፏል፡፡ኢስላምን ለማድረስ ብዙ የለፋ የጎዳና ላይ ዳዕዋ የሚያደርግበት ስፒከሩ በተዳጋጋሚ ታስሮበት በተለያዩ የሀገሪቷ ከተሞች በሚገኙ የፖሊስ ጣቢያቢያዎች በመንከራተት ብዙ መስዋዕትነት ይከፍል እንደነበረ "ኑ ወደ አላህ"እያለ በሚያደርገው ጥሪ ብዙ ድብደባ እና እስርና እንግልት ይፈፀምበት እንደነበርም ወዳጆቹ ገልፀዋል።
...
ኡስታዝ ፈቂ ገለቶ እሁድ ዕለት ግንቦት 4/2016 ዓ.ል በሻሸመኔ ከተማ የተካሄደውን የቁርአን ውድድር ታድሞ የነበረ ሲሆን ዛሬ ሻሻመኔ ላይ ድንገት ወደአኼራ መሄዱ ተሰምቷል።
...
¤ሀሩን ሚዲያ አላህ ለእርሱ ጀነትን ለወዳጅዘመዶቹ ሰብርን እንድወፍቃቸው ይመኛል!
...
©ሀሩን ሚዲያ
Photo unavailableShow in Telegram
ሙጅመእ አት ተቅዋ መስጅድ
________
ልዩ የቂርዓት ፕሮግራም አሰናድቶ የኢልም ገበታ ተቋደሱ ! እያለን ነው 🙏
SHARE
❤ 5
Tet abba cajji mucammad Nur Nacwi kee Tesfsiir berseenak sugee
. Usuk biyaakiteh yan widdir ina marin sara kalqisak orbissah tan dagiinat aqeeshuk sugen. Waysi alsaay sanat 2013 i.l.l qunxuk baaxok akah tewqem ken catta^gadik sugte. Dubayal sugtem takkay immay Awropa koo beenno axcuk dallaala dirab oyti teetil cayuk tet duquurussa heenih Etyopiya temeeteeh, akah temeete gexoh gita qimbisseek lakal liibiyal tet yibbixeenih uma weelot tan. Tet caboonuh 800 alfi esseran, ayroorah addat esseren lakqo gee weenik tet qideloonum warsan. Tet abba lakimi numuh yan, ken cattaamak tuh elle xayi malon, yablem faxa mari yablem xiqa karaakare Ansuar Masjidih dariifa kinni buxa keenik.
Ossotinah oyta
Cajji Mucammad Nur
Telefoon Ne 0913- 333659
Ina Lubaaba Ayalew
Telefoon Ne: 0964-046713
Tet catam faxa mari yenek tet ina Lubaaba Ayalew migaaqal yan Banki cisaabih ixxima: 1000413996493
Photo unavailableShow in Telegram
የሱና ዩኒቨርስቲ ተመራቂዎች የቢላሉል ሐበሺን ማእከል ጎበኙ
=============================
የሱና ዩኒቨርስቲ አሰተምሮ ያስመረቃቸዉን እና ተመርቀዉ በስራ ላይ ያሰማራቸዉን ኢማሞች ፣ ዳእዮች፣ አስተማሪዎች፣ መሻይኸች እና የዩኒቨርስቲዉ ስታፎች በትናትናዉ እለት ሳር ቤት በሚገኘዉ የቢላሉል ሐበሺ ማእከል በመገኘት ቢላሉል ሓበሺ እየሰራቸዉ ያሉትን ስራዎች ጎብኝተዋል፡፡
በጉብኝቱ ወቅት የዩኒቨርስቲዉ መስራች እና ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶ/ር ሸይኸ መሐመድ ሓሚዲን የተገኙ ሲሆን በጉብኝታቸዉም ቢላሉል ሐበሺን ከበርካታ አመታት በፊት እንደሚያዉቁት እና ለትዉልድ የሚተላለፍ ስራን እየሰራ ያለ ፋና ወጊ ሃገር በቀል ተቋም እንደሆነ አስተያታቸዉን ሰጥተዋል፡፡
በጉብኝቱ በአጠቃላይ 45 የሚሆኑ ኢማሞች ፣ ዳእዮች፣ አስተማሪዎች እና መሻይኸች የተገኙ ሲሆን ኡስታዝ መሓመድ ጀማል ጎናፍር እነዚህን ጎብኝዎች በመቀበል የቢላልን ስራዎች በማስጎብኝት ሁሉም ጎብኝዎች በተሰማሩበት ቦታ እና ስራ ለሃገር እና ለወገን የሚጠቅም ስራ እንዲሰሩ በማሳሰብ ዝግጅቱን በዱአ አጠናቀዋል፡፡