Ethio Matric
Ethio Matric ለ12ኛ ክፍል ኢንትራንስ ፈተና የሚያዘጋጅ የሞባይል አፕሊኬሽን ነው። አፕሊኬሽኑን ከዚህ ሊንክ https://play.google.com/store/apps/details?id=com.addismatric.addismatric ዳውንሎድ አድርጋቹ መጠቀም ትችላላቹ ከአፕሊኬሽኑ ጋር ለተያያዘ ጥያቄ @ethiomatric_support
إظهار المزيد32 862المشتركون
+9124 hour
+3847 يوم
+1 20230 يوم
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
#Update
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
የ2016 የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆኗል።
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ፤ ከሐምሌ 9 እስከ ሐምሌ 11/2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል።
በወረቀት ላይ የሚፈተኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 01/2016 ዓ/ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ከሐምሌ 6 እስከ 7/2016 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ይሆናል።
መረጃው የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ ፣ የአራዳ ክ/ከተማ የሶሻሎች 2016ዓም 2ኛ ሴሚስተር ሞዴል ፈተና ⬇️፡፡ መልሶቹን ኮሜንት ላይ አስቀምጠናል፡፡
English እና SAT ከናቹራሎች ጋር አንድ አይነት ነው፡፡
" የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ይሰጣል " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ
የ2016 ዓ.ም 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፤ " ፈተናው ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ለመስጠት ባይቻልም በክልሎች በተመረጡ ከተሞች ለመስጠት እየተሠራ ነው " ብለዋል።
በሁሉም ክልሎች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን ይወስዳሉ ሲሉም አሳውቀዋል።
ቀሪዎቹ ደግሞ በተለመደው አግባብ ፈተናቸውን እንደሚወስዱ ገልጸዋል።
የሀገር አቀፍ ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎትም ፈተናው በኦንላይን ለመሥጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ ነው ብሏል።
ተማሪዎች በሙከራ ፈተና እንዲለማመዱ እንደሚደረግ ገልጿል።
የአሰልጣኞች ስልጠና በመሥጠት ተማሪዎች ተደጋጋሚ ስልጠና እንደሚሠጣቸው ተገልጿል።
ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ይጀመራል ተብሏል።
#MoE
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ ፣ የአራዳ ክ/ከተማ የናቹራሎች 2016ዓም 2ኛ ሴሚስተር ሞዴል ፈተና መልሶች (Model Answer) ⬇️፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ፣ የአራዳ ክ/ከተማ የናቹራሎች 2016ዓም 2ኛ ሴሚስተር ሞዴል ፈተና መልሶች (Model Answer) ⬇️፡፡