ar
Feedback
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

الذهاب إلى القناة على Telegram

የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com

إظهار المزيد
1 721
المشتركون
+224 ساعات
-47 أيام
-1530 أيام
أرشيف المشاركات
''ኧረ እሰየው ተመስገን ተመስገን አዲስ ፀሐይ ወጣ ሞት የለህም ከእንግዲህ ችግር ምናምንቴ በል ከቤቴ ውጣ ከእንግዲህ አትችለኝም ጠንካራ ነኝ እኔ ሰንቄያለሁና ከብረት የላቀ የብርሃን ወኔ እስከመቼ
''ኧረ እሰየው ተመስገን ተመስገን አዲስ ፀሐይ ወጣ ሞት የለህም ከእንግዲህ ችግር ምናምንቴ በል ከቤቴ ውጣ ከእንግዲህ አትችለኝም ጠንካራ ነኝ እኔ ሰንቄያለሁና ከብረት የላቀ የብርሃን ወኔ እስከመቼ ነፍሴ ከእውነት ቤት እርቃ ዘልቀህ ላታዛልቅ ካንተ ጋር ተጣብቃ ከሚወፍር በኃጥያት እንጀራ ገላዬ መርጫለሁ መክሳት በንጹህ ህሊናዬ ልታለማምደኝ እርኩሰት ተጠቅመህ በቴሌቭዢን መስኮት ባህል ሐይማኖቴን እንድረሳ ሞክረሃል ተሞልተህ ብዙ ተስፋ እርግጥ እልፍ አእላፎች ይዘሃል እንደምትገዛም እቺን ምድር ተጽፏል ግን እብሪትህ በጣም አየለና እቺን ቁድስ አገር አዓይኑ አየና ባምናው ቤቴ ላይ ነግሰህ ስታሸኝ ኖረሃል ያ ክንድህ በርትቶ ‘ምታለብሰኝ ያለም ካባ የሚያልፍ የሚነጥፍ የተንኮል ድሪቶ ከእንግዲህ ግን ይብቃ ጠንካራ ነኝ እኔ ሰንቄያለሁና ከብረት የላቀ የብርሃን ወኔ . . . '' በቃ በቃ - አማን ኪያሞ / Aman Kiyamo #አማን_ኪያሞ #Aman_Kiyamo #ግጥምሲጥም #gitemsitem #ግጥማዊቅዳሜ #poeticsaturdays

photo content

Lyrics by: Moel and Seife Temam #Moel #seifetemam #Gitemsitem

ያ ዕድሜ ላይ ሰው በተሰበሰበበት ወይን ጭስ ጨዋታ ዳንስ ሴት እስክስታ ዳንኪራ ሁካታ ቡንቧታ ግርግር ጫጫታ ነገር ማኪያቶ የቆንጆ ሴት ከንፈር ሲቀራርብ ተፈለኩ ብዬ ሰው ጠራኝ ብዬ ራሴን ገፍትሬ ራሴን ቀጥሬ ወደ ቤቴ ምበር ጫማዬን ከበሬ የ ምወረውር ከአልጋዬ ትራሴ ስር ቀዝቃዛ ሙዚቃ ነገር ከፍቼ ከራሴ ሃሳብ የምቀበር ። (ያ ዕድሜ ላይ ። ) ____ ሰው ሁሉ ጓጉቶ መንገድ ጉዞ ተዘጋጅቶ ስንቅ ተዘጋጅቶ ጠጅ ተይዞ ቆሎ ተይዞ ባጋጣሚ ምክነያት ባለቀ ሰዓት ጉዞ ተሰርዟል !! ሲባል ፈገግ የሚያስብለኝ (ያ ዕድሜ ላይ ) .... ብዙ የፈረሱ ህልሞች _ ከአመድ የገቡ ከምስጥ ጉድጓድ የጠበቡ ሰው እየቀነስኩ ሰው እየቀነሰኝ አነስኩ ስል ገዝፌ የምገኝ ____( ያ ዕድሜ ላይ ) _ ሴት ቀጥሬ ከወንበሬ ስትደርስ _ ተነስቼ ስሜ ከወጠራት ልብስ _ዳሌ ይልቅ ህልሟ የሚስበኝ (ያ ዕድሜ ላይ ) ትርጉም በሌላት ዓለም _ ትርጉም የምፈልግ የክብ ጉዞ የምስብ ጠፍቼ _ስለመገኘት_ የማስብ (ያ ዕድሜ ላይ ) _ የሲሲፈስን ርግማን _ኑሮዬ አርጌ የተቀበልኩ ለራሴው እርድ _ ቢላ ስዬ ያቀረብኩ በሞቱት የምቀና መኖር የሚያስፈራኝ _ (ያ ዕድሜ ላይ ) _ ብናኝ መሆኔ የገባኝ አዋራ መሆኔ የገባኝ 'አውራ ነኝ' የምል __ ከመሞት ይልቅ መኖር የሚያስፈራኝ ሰው ያረገው የሚያስጠላኝ ራሴው ያደረኩት የሚያስጠላኝ በትልቁ ተጋድሜ ትንሹ ነገር የሚያስፈራኝ _ (ያ ዕድሜ ላይ ) _ የራሴን ህይወት ማሳመር ባልችል ለማበላሸት የማላንስ (ካደረኩት ይልቅ የማደርገው የሚያጓጓኝ የማያጓጓኝ ይቅር እንዴ ? ላርገው እንዴ ? ልሂድ እንዴ ? ልምጣ እንዴ ? ላግባ እንዴ ? ልውለድ እንዴ ? ልሙት እንዴ ? የሚያስብለኝ የማያስብለኝ (ያ ዕድሜ ላይ ) 1ዱ ጌታቸው #1ዱ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ

ትዝታሽን ለእኔ፣ ትዝታዬ ለአንቺ ኂሳዊ ንባብ በማርቆስ ዘመንበረ ልዑል

የመጻሕፍት ሕብረ - ቀለም ::
+9
የመጻሕፍት ሕብረ - ቀለም ::

1. አንድ ሰው ፈጣሪውን የማይፈራ 2. ሰውን የማያፍር (ህሊናው የማይከብደው) 3. ህግን የማያከብርና፤ቢያጠፋ እንኳን ከህግ ተጠያቂነት ሊያመልጥ የሚችልበት መንገድ እንዳለ የሚያስብ ከሆነ። ወዳጄ #
1. አንድ ሰው ፈጣሪውን የማይፈራ 2. ሰውን የማያፍር (ህሊናው የማይከብደው) 3. ህግን የማያከብርና፤ቢያጠፋ እንኳን ከህግ ተጠያቂነት ሊያመልጥ የሚችልበት መንገድ እንዳለ የሚያስብ ከሆነ። ወዳጄ #አጥፍቶ_ጠፊ ነው ይህ ሰው! ማናችንንም ከነዚህ ገመዶች አንዱ ነው፤ ከጥፋት መንገድ መልሶ የያዘን። እዚ ምድር ላይ እኚህ #ሶስቱ_ገመዶች የተበጠሱበት ሰው፤ እጅግ አደገኛ #ፍረት_ነው ሚሆነው። ማለቴ እራሱ ላይ እንኳን ሳይቀር በቀላሉ አደጋ ሊጥል ይችላል ይህ አይነት ሰው። እኔ ቢያንስ አንዱ እንደቀረው እርግጠኛ ካልሆንኩት ሰው ጋር በምንም ተአምር አብሬ ለመስራት ፍቃደኛ አይደለሁም። ከመቃብር በላይ፤ በህያዋን አለም ስትኖር ከሰዎች ጋር ከሶስቱ በአንዱ ገመድ ነው ልትተሳሰርና ልትግባባ የምትችለው። በአንድ አጋጣሚ ማንነቱ እስኪገለጥ እንጂ፤ እኚ ሶስቱን በጥሶ ሚኖር ሰው ፤ #ሁኔታና #ስፖንሰር_ያጣ_አጥፍቶ_ጠፊ_ነው። ሰው #ሃይማኖቱ፣ብሄሩ፣የኑሮው ሁኔታ፣የትምህርት ደረጃው ምንም ይሁን ፈጣሪውን የማይፈራ፣ህሊናውን የማያፍር፣ህግን የማያከብር ከሆነ፤ ዳግመኛ ሊያገናኛችሁ የሚችል ነገር ከዚህ ሰው ጋር ፈጽሞ አይስፈልግም። ለዚ ምስኪን ሰው #ስጦታ እንጂ #ብድር እንዳትሰጡት፤ እናንተም እንዳትበደሩት ተጠንቀቁ። #አላህን_ፍራ/ #ስለ_እግዚአብሄር፣ በህግ አምላክ አልያም ለዘመድ ወዳጆችህ እነግርብሃለሁ የማይባል ሰው #በጣም_አደገኛ_ፍጥረት ነው። #ከኖራችሁ_አይቀር ከቻላችሁ ሶስቱም ገመድ ይኑራችሁ፤ ካልሆነ ግን #ቢያንስ አንዱን አስቀሩ። እኚ ሶስቱ ከተበጠሱብህ ግን #በአራዊትና በሰው መሃል ያለውን ልዩነት ነው በሂደት እያጣህ ምትሄደው። እንደ ተቋም፤ የሞቱና በከባድ የህይወት ልምምድ ውስጥ አልፈው የደነዘዙ ህሊናዎችን የማነቃቃት ስራ በትውልድ መሃል እንሰራለን።

ዕድሜ ለጨረቃ የቀትሯ ፅሃይ ግዜዋን ጠብቃ ምሽጓን ስትመሽግ ከኔ ተደብቃ አዕዋፍ ጥለውኝ ጎጇቸው ሲሰፍሩ ሰዎች በየቤቱ በሳቅ በጨዋታ ፈንድቀው ሲዳሩ ብኩኑ ብቸኛው 'የት ደረስክ' የሚለኝ ጠያቂ የሌለ
ዕድሜ ለጨረቃ የቀትሯ ፅሃይ ግዜዋን ጠብቃ ምሽጓን ስትመሽግ ከኔ ተደብቃ አዕዋፍ ጥለውኝ ጎጇቸው ሲሰፍሩ ሰዎች በየቤቱ በሳቅ በጨዋታ ፈንድቀው ሲዳሩ ብኩኑ ብቸኛው 'የት ደረስክ' የሚለኝ ጠያቂ የሌለኝ ብቻየን ወጥቼ በሀሳብ ዋትቼ ሳልተኛ ተኝቼ በህልም አለም ሞቼ በብርድ ስንሰፈሰፍ በውርጭ ስንቃቃ ዕድሜ ለጨረቃ ከሰዎች ተሽላ መጣች ተደብቃ የሀሳብ ባትሞላም አብልታ አጠጥታ ጭንቀትን ተጋርታ ዕድሜ ለጨረቃ ስቃ አሳሳቀችኝ ብርሀንን ዘርግታ። #ዮሃንስ_ጋሻው #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ

ጀንበር ሳትጠልቅ እንባ ስታቀሪ፣ በሰቆቃ ስትሞሸሪ፣ ሰላም እየጠማሽ ፣ ባለመኖር መኖር እየተቆራመድሽ፣ አለሁኝ አትበይኝ ቆፈን ሲገርፍሽ፣ ጠኔ ሲፈጅሽ፣ የነፃነት አየር አጥቢያ ምትናፍቂ፣ በዛሬ ውጥን
ጀንበር ሳትጠልቅ እንባ ስታቀሪ፣ በሰቆቃ ስትሞሸሪ፣ ሰላም እየጠማሽ ፣ ባለመኖር መኖር እየተቆራመድሽ፣ አለሁኝ አትበይኝ ቆፈን ሲገርፍሽ፣ ጠኔ ሲፈጅሽ፣ የነፃነት አየር አጥቢያ ምትናፍቂ፣ በዛሬ ውጥን ኦና አልባ መንገድ ላይ የምትሳቀቂ፣ ታድያ ለምንድን ነው ? ደህና ነኝ እያልሽኝ ወሬ የምትሰብቂ፣ መአልቱ ሌሊቱ እንደ ሰጋር ፈረስ እየነጎደ፣ ጎህ ይቀዳል አትበይ በፅልመት ተውጧል እየተራመደ። ህመምሽ ህመሜ በደሙ ጠበል እያጠመቀኝ፣ ምድር ቆቧን ሳ'ጥል መለኮት በመጣ ቅኔውን እንዲቀኝ። ሀብታሙ ፍቃዴ (የጁ) #ሀብታሙ_ፍቃዴ #ግጥምሲጥም

Much Needed Conversations - Art vs. Artist 📅 Sunday October 11, 2020 at 7 PM 📍 IG Live 🙏 @KeTsenat Join us this week as we
Much Needed Conversations - Art vs. Artist 📅 Sunday October 11, 2020 at 7 PM 📍 IG Live 🙏 @KeTsenat Join us this week as we discuss Art vs. Artist - should we differentiate between the two? @ketsenatmagazine @eventsethiopia

እንዴትም ---------- እንዴት ናችሁ ላላችሁን አለን አንደምጥ ስቀን በማይለቅ ጉንፋን ታፍነን የማያልቅ ንፍጥ ተናፍጠን የማያልቅ ነፍጥ ተናፍጠን ወደራሳችን ደግነን ... እንዴት ናችሁ ላላችሁ እንዴት እንመልስላችሁ 'አለን' ለማለት ፈርተን ያለን መስሎን የሌለን የሌለን መስሎን አለን አይባል ነገር ለሰው አንዴት ናችሁም ያሉን መቼም ያለን መስለን ነው ...ምን ሊውጠን ልንል ስንል ምን ልንውጥ ነው 'ምንል ምኑን እንዴት ነህ ይባላል ሊጥ መጥለቂያ የራስ ቅል ሰይፈ ተማም 2009 #ሰይፈተማም #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ

Here comes the Arts Mailing List newsletter - 12th Oct 2020 https://bit.ly/3jKunYW This week, we bring you the amazing work o
Here comes the Arts Mailing List newsletter - 12th Oct 2020 https://bit.ly/3jKunYW This week, we bring you the amazing work of visual artist https://www.instagram.com/abel_fine_arts/ With so many open calls, competitions, residencies etc ... there is something for each one of you to apply for. In this week's newsletter, you will also find news and opportunities from @Ahadubeatz, @seifetemam @ethiopianrecords, @Theurbancenter, @WallpapersETdaily and so much more @artsmailinglist

A call for poets ! We are looking for amateur poets who deserve a stage. Gitem Sitem is organizing a monthly poetry event. Ea
A call for poets ! We are looking for amateur poets who deserve a stage. Gitem Sitem is organizing a monthly poetry event. Each month, we give the opportunity for two upcoming poets if their sample work got selected by our experienced group of poets. Please send us an audio through @seifdman or @Tominu and be part of our event. #gitemsitem

ስራቸውን በመድረክ ለማቀረብ ዕድል አግኝተው የማያውቁ ብቁ ገጣሚያንን ፍለጋ የዋጣ ጥሪ። ግጥም ሲጥም በወርሃዊ የግጥም ዝግጅቱ ላይ በየወሩ ለሁለት ገጣሚያን ይህን ዕድል የሚሰጥ በመሆኑ መሳተፍ የምት
ስራቸውን በመድረክ ለማቀረብ ዕድል አግኝተው የማያውቁ ብቁ ገጣሚያንን ፍለጋ የዋጣ ጥሪ። ግጥም ሲጥም በወርሃዊ የግጥም ዝግጅቱ ላይ በየወሩ ለሁለት ገጣሚያን ይህን ዕድል የሚሰጥ በመሆኑ መሳተፍ የምትፈልጉ ገጣሚያን ስራችሁን በድምጽ ቀድታችሁ በ @seifdman ወይንም በ @Tominu ብትልኩልን ስራችሁ ልምድ ባላቸው ገጣሚዎች ተመዛዝኖ ይበልጥ ይጥማሉ ያልናቸውን እናሳውቃለን። #ግጥምሲጥም

አይ ባልና ሚስት! ጥንትማ ከአንድ ወንዝ ይቀዱ ነበረ የኔና ያንቺ ግን መልኩ ተቀየረ የትዳራችን ቅል ይዞት ክፉ አባዜ አንቺን ከዓባይ ቀዳሽ እኔን ከተከዜ ሰይፈ ተማም 1999 #ሰይፈተማም #ግጥማዊቅዳሜ #ግጥምሲጥም

ምህረት -------- (ለ ኒኪ ጂዮቫኒ) ሸረሪቷን ግደላት እንጂ አለችኝ ግና መግደል ቢሰቅቀኝ የሰላም መንጃ ተቸረኝ አሮጌ ጣሳ ደፍቼ ብጣሽ ጨርቅ ላይ ዘግቼ የያዝኳትን የነፍሳት ነፍስ ወደ ውጪ ለቀኳት በነጻነት እንድትነፍስ አለም ምድሯን እንድታስስ ማንም ላይ ባልደርስም እንኳን ድንገት ከተገኘሁኝ በማይገባኝ ድንኳን ሩሄን እያሰነበትኩ ያለቦታዬ ብከሰት ባልታሰብኩበት ቦታ በማይገባኝ ሰዓት እላለሁ 'አቤቱ ምኞቴን አደራ' ሸረሪቷን እንዳዳንኳት ለእኔም ቀን ም’ረትን ስራ ሩዲ ፍራንሲስኮ (ትርጉም፦ ሰይፈ ተማም) ሂሊየም #ሩዲ #ሰይፈተማም #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ