ar
Feedback
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

الذهاب إلى القناة على Telegram

የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com

إظهار المزيد
1 718
المشتركون
-124 ساعات
-47 أيام
-1330 أيام
أرشيف المشاركات
photo content

Scar's If I could I would sacrifices my soul, my being just to avoid falling for you If I could I would cut my eyes out just to avoid seeing you smile If I could I would die earlier before meeting you I am afraid of height and falling too but some how in some ways I fall for you Not knowing what would happen at the bottom Whether I land on my feet or break my back, That is how much I trusted you I touched you infinity, I tattooed you deep in my heart, I wispered you to the stars, I treated you like the rarest thing in the earth, I had butterflies in my stomach, I was good to you Loving you was the last thing I done And I was good at it Most of the times I smile And gave you a thousand second chances, just to prove I am wrong and you right I did Olympic worth back flip and believe you are the one One, you left me One, you used me One, like you never had memories of me even the little you had , that is a big may be, you scattered them like the stars One, sometimes when I see a couples in the streets I wish it would have been us One, one, you smile with her like I never existed One, I hate her Ten, I hope she smiles with your jokes but you would remember me instead of her Nine, I hope she would feel my infinity touch's, smell my perfume on your body and leave you Eight, may be then you would want to know how I get my scar's Seven, you would want to know how time heal the pain and what would you do when those days come, when you don't feel like yourself, when it is upside down Six, you would wander, when you feel worthless, you would wander, How I get my scar's Five, see I ripped you out of my heart, I ripped you out of my smile, I spoke to you in to my shadows, so you would vapor to thin air See, I stopped my heart so i could breath again Four, see I swallowed my pride, but it clues back to my mouth Three, to her, to the random girl you start dating, I think I saw her in your smile but I cried and washed her too Two, see I scratched you, from my chest, i used my finger nails One, that is how I gat my scar's. One , that is how I smile everyday One , that is how l smile everyday 🦋🦋🦋🦋 @freetalkk

አንሶሻል ዘለዓለሜ አካል ሥጋ ጠቦሻል ረቂቅ ነፍስ በግዘፍሽ ከአንቺ በልጦ ምን ይዘሻል? (ጥልመት ድ'ቅድቅ ብርሃን ድ'ብቅ እ'ርስት ዝን'ግት . ሕዋ ዐይንሽ ላይ ንጋቴን ልታጋፍሪበት ያንቺን ጀንበር
አንሶሻል ዘለዓለሜ አካል ሥጋ ጠቦሻል ረቂቅ ነፍስ በግዘፍሽ ከአንቺ በልጦ ምን ይዘሻል? (ጥልመት ድ'ቅድቅ ብርሃን ድ'ብቅ እ'ርስት ዝን'ግት . ሕዋ ዐይንሽ ላይ ንጋቴን ልታጋፍሪበት ያንቺን ጀንበር መሸበት.... ዝም ዝም ዝም ጭልም!) አንቺን አልፌ ሁሉን ሁሉን ሳልፈው ተመለስሁኝ መኖሪያሽ ነኝ የምለው ለካስ ነዋሪሽ ነበርሁኝ (አድማስ እኔ ብርሃኔ እ'ጥፍ ጥልመት አንቺ ጥ'ልፍ ብ'ርር ክ'ንፍ! አልነገሩኝ አልተረዳሁ ስበት ብርሃንን እንዲያሸንፍ! ሳብሺኝ! ል'ጥፍ! ቦግ...እልም ዳግም ዝም!) ዘለዓለሜ አንሶሽ መሆኔ ጠቦሽ ከእኔ ገዝፈሽ እኔን ያዝሺኝ። ጥልመትሽ ሁሉን ቢሞላ አድማስ ሙሉ አበራሺኝ። ..ተንጸባረቅሁ ..ነገሥሁብሽ! (የማይሆንን አደረግነው በቅጽበት ሁሌን ኖርነው ...ከዕለታት ጠይም መልከ መልካሙ ላይ ሁሉን የሚያህልን አንድ ነጥብ ሰማይ አቅፈነው አደርን ነቅተን ሕልሞች ሆንን አንቺን አልፌ ዓለሙን ዓለሙን ሳልፍ ተመለስሁ አንቺን ሳልፍ - አንቺ ሁሉን ቀኔ ሲያልፈኝ አንቺ ሁሌ - አንቺ አሁን ሆንሁሽና ሆንሁት ሁሉን! ከዕለታት አንቺ ዕለት ሰማዩን አቀፍሁት ተሸከምሁ ሁለንታ ደቃቃ አሁን ላይ ዘለዓለም ተረታ...) አንሶሻል ዘለዓለሜ (በማን ዐይን ተመዝኖ) ጠቦሻል ሥጋ አካሌ (በማን አንጻር ተነጻጽሮ) የመውደዴን ልኬት ከመዘንሽው በእነሱ አቅም ከአሁን ሌላ አልወድሽም (በእነሱ ዘለዓለም አሁን የለም!) ማርቆስ ዘመንበረ ልዑል #ማርቆስ_ዘመንበረ_ልዑል #MarkOs #ግጥምሲጥም #gitemsitem #ግጥማዊቅዳሜ #poeticsaturdays

''ኧረ እሰየው ተመስገን ተመስገን አዲስ ፀሐይ ወጣ ሞት የለህም ከእንግዲህ ችግር ምናምንቴ በል ከቤቴ ውጣ ከእንግዲህ አትችለኝም ጠንካራ ነኝ እኔ ሰንቄያለሁና ከብረት የላቀ የብርሃን ወኔ እስከመቼ
''ኧረ እሰየው ተመስገን ተመስገን አዲስ ፀሐይ ወጣ ሞት የለህም ከእንግዲህ ችግር ምናምንቴ በል ከቤቴ ውጣ ከእንግዲህ አትችለኝም ጠንካራ ነኝ እኔ ሰንቄያለሁና ከብረት የላቀ የብርሃን ወኔ እስከመቼ ነፍሴ ከእውነት ቤት እርቃ ዘልቀህ ላታዛልቅ ካንተ ጋር ተጣብቃ ከሚወፍር በኃጥያት እንጀራ ገላዬ መርጫለሁ መክሳት በንጹህ ህሊናዬ ልታለማምደኝ እርኩሰት ተጠቅመህ በቴሌቭዢን መስኮት ባህል ሐይማኖቴን እንድረሳ ሞክረሃል ተሞልተህ ብዙ ተስፋ እርግጥ እልፍ አእላፎች ይዘሃል እንደምትገዛም እቺን ምድር ተጽፏል ግን እብሪትህ በጣም አየለና እቺን ቁድስ አገር አዓይኑ አየና ባምናው ቤቴ ላይ ነግሰህ ስታሸኝ ኖረሃል ያ ክንድህ በርትቶ ‘ምታለብሰኝ ያለም ካባ የሚያልፍ የሚነጥፍ የተንኮል ድሪቶ ከእንግዲህ ግን ይብቃ ጠንካራ ነኝ እኔ ሰንቄያለሁና ከብረት የላቀ የብርሃን ወኔ . . . '' በቃ በቃ - አማን ኪያሞ / Aman Kiyamo #አማን_ኪያሞ #Aman_Kiyamo #ግጥምሲጥም #gitemsitem #ግጥማዊቅዳሜ #poeticsaturdays

photo content

Lyrics by: Moel and Seife Temam #Moel #seifetemam #Gitemsitem

ያ ዕድሜ ላይ ሰው በተሰበሰበበት ወይን ጭስ ጨዋታ ዳንስ ሴት እስክስታ ዳንኪራ ሁካታ ቡንቧታ ግርግር ጫጫታ ነገር ማኪያቶ የቆንጆ ሴት ከንፈር ሲቀራርብ ተፈለኩ ብዬ ሰው ጠራኝ ብዬ ራሴን ገፍትሬ ራሴን ቀጥሬ ወደ ቤቴ ምበር ጫማዬን ከበሬ የ ምወረውር ከአልጋዬ ትራሴ ስር ቀዝቃዛ ሙዚቃ ነገር ከፍቼ ከራሴ ሃሳብ የምቀበር ። (ያ ዕድሜ ላይ ። ) ____ ሰው ሁሉ ጓጉቶ መንገድ ጉዞ ተዘጋጅቶ ስንቅ ተዘጋጅቶ ጠጅ ተይዞ ቆሎ ተይዞ ባጋጣሚ ምክነያት ባለቀ ሰዓት ጉዞ ተሰርዟል !! ሲባል ፈገግ የሚያስብለኝ (ያ ዕድሜ ላይ ) .... ብዙ የፈረሱ ህልሞች _ ከአመድ የገቡ ከምስጥ ጉድጓድ የጠበቡ ሰው እየቀነስኩ ሰው እየቀነሰኝ አነስኩ ስል ገዝፌ የምገኝ ____( ያ ዕድሜ ላይ ) _ ሴት ቀጥሬ ከወንበሬ ስትደርስ _ ተነስቼ ስሜ ከወጠራት ልብስ _ዳሌ ይልቅ ህልሟ የሚስበኝ (ያ ዕድሜ ላይ ) ትርጉም በሌላት ዓለም _ ትርጉም የምፈልግ የክብ ጉዞ የምስብ ጠፍቼ _ስለመገኘት_ የማስብ (ያ ዕድሜ ላይ ) _ የሲሲፈስን ርግማን _ኑሮዬ አርጌ የተቀበልኩ ለራሴው እርድ _ ቢላ ስዬ ያቀረብኩ በሞቱት የምቀና መኖር የሚያስፈራኝ _ (ያ ዕድሜ ላይ ) _ ብናኝ መሆኔ የገባኝ አዋራ መሆኔ የገባኝ 'አውራ ነኝ' የምል __ ከመሞት ይልቅ መኖር የሚያስፈራኝ ሰው ያረገው የሚያስጠላኝ ራሴው ያደረኩት የሚያስጠላኝ በትልቁ ተጋድሜ ትንሹ ነገር የሚያስፈራኝ _ (ያ ዕድሜ ላይ ) _ የራሴን ህይወት ማሳመር ባልችል ለማበላሸት የማላንስ (ካደረኩት ይልቅ የማደርገው የሚያጓጓኝ የማያጓጓኝ ይቅር እንዴ ? ላርገው እንዴ ? ልሂድ እንዴ ? ልምጣ እንዴ ? ላግባ እንዴ ? ልውለድ እንዴ ? ልሙት እንዴ ? የሚያስብለኝ የማያስብለኝ (ያ ዕድሜ ላይ ) 1ዱ ጌታቸው #1ዱ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ

ትዝታሽን ለእኔ፣ ትዝታዬ ለአንቺ ኂሳዊ ንባብ በማርቆስ ዘመንበረ ልዑል

የመጻሕፍት ሕብረ - ቀለም ::
+9
የመጻሕፍት ሕብረ - ቀለም ::

1. አንድ ሰው ፈጣሪውን የማይፈራ 2. ሰውን የማያፍር (ህሊናው የማይከብደው) 3. ህግን የማያከብርና፤ቢያጠፋ እንኳን ከህግ ተጠያቂነት ሊያመልጥ የሚችልበት መንገድ እንዳለ የሚያስብ ከሆነ። ወዳጄ #
1. አንድ ሰው ፈጣሪውን የማይፈራ 2. ሰውን የማያፍር (ህሊናው የማይከብደው) 3. ህግን የማያከብርና፤ቢያጠፋ እንኳን ከህግ ተጠያቂነት ሊያመልጥ የሚችልበት መንገድ እንዳለ የሚያስብ ከሆነ። ወዳጄ #አጥፍቶ_ጠፊ ነው ይህ ሰው! ማናችንንም ከነዚህ ገመዶች አንዱ ነው፤ ከጥፋት መንገድ መልሶ የያዘን። እዚ ምድር ላይ እኚህ #ሶስቱ_ገመዶች የተበጠሱበት ሰው፤ እጅግ አደገኛ #ፍረት_ነው ሚሆነው። ማለቴ እራሱ ላይ እንኳን ሳይቀር በቀላሉ አደጋ ሊጥል ይችላል ይህ አይነት ሰው። እኔ ቢያንስ አንዱ እንደቀረው እርግጠኛ ካልሆንኩት ሰው ጋር በምንም ተአምር አብሬ ለመስራት ፍቃደኛ አይደለሁም። ከመቃብር በላይ፤ በህያዋን አለም ስትኖር ከሰዎች ጋር ከሶስቱ በአንዱ ገመድ ነው ልትተሳሰርና ልትግባባ የምትችለው። በአንድ አጋጣሚ ማንነቱ እስኪገለጥ እንጂ፤ እኚ ሶስቱን በጥሶ ሚኖር ሰው ፤ #ሁኔታና #ስፖንሰር_ያጣ_አጥፍቶ_ጠፊ_ነው። ሰው #ሃይማኖቱ፣ብሄሩ፣የኑሮው ሁኔታ፣የትምህርት ደረጃው ምንም ይሁን ፈጣሪውን የማይፈራ፣ህሊናውን የማያፍር፣ህግን የማያከብር ከሆነ፤ ዳግመኛ ሊያገናኛችሁ የሚችል ነገር ከዚህ ሰው ጋር ፈጽሞ አይስፈልግም። ለዚ ምስኪን ሰው #ስጦታ እንጂ #ብድር እንዳትሰጡት፤ እናንተም እንዳትበደሩት ተጠንቀቁ። #አላህን_ፍራ/ #ስለ_እግዚአብሄር፣ በህግ አምላክ አልያም ለዘመድ ወዳጆችህ እነግርብሃለሁ የማይባል ሰው #በጣም_አደገኛ_ፍጥረት ነው። #ከኖራችሁ_አይቀር ከቻላችሁ ሶስቱም ገመድ ይኑራችሁ፤ ካልሆነ ግን #ቢያንስ አንዱን አስቀሩ። እኚ ሶስቱ ከተበጠሱብህ ግን #በአራዊትና በሰው መሃል ያለውን ልዩነት ነው በሂደት እያጣህ ምትሄደው። እንደ ተቋም፤ የሞቱና በከባድ የህይወት ልምምድ ውስጥ አልፈው የደነዘዙ ህሊናዎችን የማነቃቃት ስራ በትውልድ መሃል እንሰራለን።

ዕድሜ ለጨረቃ የቀትሯ ፅሃይ ግዜዋን ጠብቃ ምሽጓን ስትመሽግ ከኔ ተደብቃ አዕዋፍ ጥለውኝ ጎጇቸው ሲሰፍሩ ሰዎች በየቤቱ በሳቅ በጨዋታ ፈንድቀው ሲዳሩ ብኩኑ ብቸኛው 'የት ደረስክ' የሚለኝ ጠያቂ የሌለ
ዕድሜ ለጨረቃ የቀትሯ ፅሃይ ግዜዋን ጠብቃ ምሽጓን ስትመሽግ ከኔ ተደብቃ አዕዋፍ ጥለውኝ ጎጇቸው ሲሰፍሩ ሰዎች በየቤቱ በሳቅ በጨዋታ ፈንድቀው ሲዳሩ ብኩኑ ብቸኛው 'የት ደረስክ' የሚለኝ ጠያቂ የሌለኝ ብቻየን ወጥቼ በሀሳብ ዋትቼ ሳልተኛ ተኝቼ በህልም አለም ሞቼ በብርድ ስንሰፈሰፍ በውርጭ ስንቃቃ ዕድሜ ለጨረቃ ከሰዎች ተሽላ መጣች ተደብቃ የሀሳብ ባትሞላም አብልታ አጠጥታ ጭንቀትን ተጋርታ ዕድሜ ለጨረቃ ስቃ አሳሳቀችኝ ብርሀንን ዘርግታ። #ዮሃንስ_ጋሻው #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ

ጀንበር ሳትጠልቅ እንባ ስታቀሪ፣ በሰቆቃ ስትሞሸሪ፣ ሰላም እየጠማሽ ፣ ባለመኖር መኖር እየተቆራመድሽ፣ አለሁኝ አትበይኝ ቆፈን ሲገርፍሽ፣ ጠኔ ሲፈጅሽ፣ የነፃነት አየር አጥቢያ ምትናፍቂ፣ በዛሬ ውጥን
ጀንበር ሳትጠልቅ እንባ ስታቀሪ፣ በሰቆቃ ስትሞሸሪ፣ ሰላም እየጠማሽ ፣ ባለመኖር መኖር እየተቆራመድሽ፣ አለሁኝ አትበይኝ ቆፈን ሲገርፍሽ፣ ጠኔ ሲፈጅሽ፣ የነፃነት አየር አጥቢያ ምትናፍቂ፣ በዛሬ ውጥን ኦና አልባ መንገድ ላይ የምትሳቀቂ፣ ታድያ ለምንድን ነው ? ደህና ነኝ እያልሽኝ ወሬ የምትሰብቂ፣ መአልቱ ሌሊቱ እንደ ሰጋር ፈረስ እየነጎደ፣ ጎህ ይቀዳል አትበይ በፅልመት ተውጧል እየተራመደ። ህመምሽ ህመሜ በደሙ ጠበል እያጠመቀኝ፣ ምድር ቆቧን ሳ'ጥል መለኮት በመጣ ቅኔውን እንዲቀኝ። ሀብታሙ ፍቃዴ (የጁ) #ሀብታሙ_ፍቃዴ #ግጥምሲጥም

Much Needed Conversations - Art vs. Artist 📅 Sunday October 11, 2020 at 7 PM 📍 IG Live 🙏 @KeTsenat Join us this week as we
Much Needed Conversations - Art vs. Artist 📅 Sunday October 11, 2020 at 7 PM 📍 IG Live 🙏 @KeTsenat Join us this week as we discuss Art vs. Artist - should we differentiate between the two? @ketsenatmagazine @eventsethiopia

እንዴትም ---------- እንዴት ናችሁ ላላችሁን አለን አንደምጥ ስቀን በማይለቅ ጉንፋን ታፍነን የማያልቅ ንፍጥ ተናፍጠን የማያልቅ ነፍጥ ተናፍጠን ወደራሳችን ደግነን ... እንዴት ናችሁ ላላችሁ እንዴት እንመልስላችሁ 'አለን' ለማለት ፈርተን ያለን መስሎን የሌለን የሌለን መስሎን አለን አይባል ነገር ለሰው አንዴት ናችሁም ያሉን መቼም ያለን መስለን ነው ...ምን ሊውጠን ልንል ስንል ምን ልንውጥ ነው 'ምንል ምኑን እንዴት ነህ ይባላል ሊጥ መጥለቂያ የራስ ቅል ሰይፈ ተማም 2009 #ሰይፈተማም #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ

Here comes the Arts Mailing List newsletter - 12th Oct 2020 https://bit.ly/3jKunYW This week, we bring you the amazing work o
Here comes the Arts Mailing List newsletter - 12th Oct 2020 https://bit.ly/3jKunYW This week, we bring you the amazing work of visual artist https://www.instagram.com/abel_fine_arts/ With so many open calls, competitions, residencies etc ... there is something for each one of you to apply for. In this week's newsletter, you will also find news and opportunities from @Ahadubeatz, @seifetemam @ethiopianrecords, @Theurbancenter, @WallpapersETdaily and so much more @artsmailinglist

A call for poets ! We are looking for amateur poets who deserve a stage. Gitem Sitem is organizing a monthly poetry event. Ea
A call for poets ! We are looking for amateur poets who deserve a stage. Gitem Sitem is organizing a monthly poetry event. Each month, we give the opportunity for two upcoming poets if their sample work got selected by our experienced group of poets. Please send us an audio through @seifdman or @Tominu and be part of our event. #gitemsitem