ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem
الذهاب إلى القناة على Telegram
የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
إظهار المزيد1 721
المشتركون
+224 ساعات
-47 أيام
-1530 أيام
أرشيف المشاركات
በመጪው ጥቅምት 2013 በአዲስ አበባ ለኢትዮጵያውያን የፈጠራ እና የጥበብ ባለሙያዎች ብቻ ነጻ የስልጠና ፕሮግራም ለማዘጋጀት አቅደናል፡:
o በየትኞች ርዕሶች ላይ ብናተኩር ይሻላል ብለው ያስባሉ? o እርሶ የበለጠ ይጠቅማል ብለው የሚያስቡትን ርዕስ ይምረጡ፡፡ o ከዚያም ደግሞ እኛ በተሰጠው ድምጽ መሰረት የስልጠናውን መርሃ ግብር እናሰናዳለን:: እናመሰግናልን::
መንገደኛ
(ሰይፈ ተማም)
ከደመናት ቅድስናን የምቀዳ
በጉድንዳን መስመር ‘ምቀና
በልቤም በ’ግሬም ‘ማቀና
ረቂቅ የመንገድ ጀግና
ከየትም ወዴት ያልመጣሁ
ካለመኖር ውስጥ ኖሬ - ከመኖር መዝገብ የታጣሁ
መጣህብኝ ባይ የሌለኝ
መንገድ ነኝ - መንገደኛ ነኝ
ካልነበረውም ወደ ነበረው መጥቼ
ያልነበረውም ሲነብር አይቼ
እርጥበት ላይ ትኩሳትን
እርኩሰት ላይ ምርቃትን
እርግበት ላይ ክርራትን
እየበተንኩ የማቀና
በጉንዳን መስመር ‘ምቀና
ረቂቅ የመንገድ ጀግና
መ ን ገ ደ ኛ
በቅድስናም ሆነ በፍልስፍና ‘ምነጉድ
‘ሚያመጣ ‘ሚወስደኝ መንገድ
የሆንኩት ሁሉ ቢሰፈር
ቢመጣ ቢሄድ ቢቀመር
ቢለካ በሰፈር ባገር
ቢመተር በቀለም በዘር
ስዘረፍ ቅኔ ወርቅ አሰር
ስታሰር ስንኝ ምቋጠር
ስቋጠርም ስንቅ ‘ምካፈል
ስካፈል አሸዋ ‘ምገረፍ
ስገረፍ ቅኝት ‘ምካረር
ንዝረት ነኝ ያውታር በገና
በጉንዳን መስመር ‘ምቀና
በልቤም በ'ግሬም 'ማቀና
ረቂቅ የመንገድ ጀግና
መ ን ገ ደ ኛ
#ሰይፈተማም #ግጥምሲጥም #ጥበብበአደባባይ #ግጥማዊቅዳሜ
#seifetemam #gitemsitem #poeticsaturdays #tba #tibeb2020 #tibebbeadebabay #digitalartfestival #artinaddis
የጦቢያ ትንሳኤ
ምንድነው ማንባቱ ዕንባህን መዘርገፍ
ጠላትህ ሲጋልብ እንደማለት ዘራፍ
ከቶ አይችልምና መሞቱ ሊያባባህ
ሸልል ፎክር እና ስደደው አርቀህ
ግርማህን አሳየው ዝናርህን ታጥቀህ
ሰማይ ሆይ አድምጠኝ ስማኝ አስተውለህ
ከጷግሜ በኋላ ዝናብ ነው ጠላትህ
ወዝህን ማድረቂያ መርዛማ ነው ዕንባህ።
ፀሀይም አትሞኝ አትበይ አልወጣም
ቀንሽን ብሪበት ድመቂበት በጣም
ባክሽን ጦቢያዬ ልብሽን አይክፋው
አብቅቷል ወጀቡ የፀደይ ነው ተራው።
ደዌውን ሊያጠፋ ፌጦው ተፈትፍቷል
የእናቶችም አንጀት ለፀሎት ተፈቷል
ልጆች ሽክ ብለዋል አምረዋል በእጅጉ
አባቶች ባርከዋል ተሰውቷል በጉ።
ዕድልሽ ይታደል ደስታሽም ይደሰት
ችግርሽ ይቸገር ሞትሽ ቀድሞሽ ይሙት
እንደ አሸዋ ውሀ በኖ ተኖ ይጥፋ
ምድርሽ በአደይ እና በፍቅርሽ ይሰፋ
በአዲስ አመት መንበር በነገ ድልድይ ላይ
የፍቅር አክሊልን ደፍተሽ በላይሽ ላይ
ደምቀሽ ፈክተሽ ይታይ
መአዛሽ ይታወድ ከርቤሽ ያረስርሰን
በአዲስ እኛ አንኑር አሮጌውን ትተን።
ተፃፈ በ ግሩም ነን መቼም(ሮዛ)
የመለያ ቁጥር - ET-068
Like and join @eshidigital
@tibeb_drawing_and_poem
የቱ ጋር?
(ቶማስ አድማሱ)
ከአድዋ በፊት ያው ከድሉም ኋላ
ላንድ የዝና ታሪክ ላንድ የጋራ ጥላ
እንዴት ታጣ መላ?
እንደ ሰው ወደታች ያወረደን ማነው?
ከአድዋ ኋላ የቱ ጋር ነው የቆምነው?
*
እጃችን ማሸነፍ ረስቶ
ልባችን ወኔ ተነስቶ
ነፍሳችን ሃቅ እውነት ስቶ!
በካቻምና ታሪክ ዜማ
ልብ ባይን ሲደማ።
እዚያ ጋር ነው የቆምን እግር በእግር ሲወጋ?
ባንዲራ ላብ ማበስ ትቶ እግር ጠልፎ ሲያዋጋ፡፡
አያምም??
/ያማል/
ጎን ላይ እንደመወጋት
ተሰቅሎ በችንካር ቅጣት
ሆምጣጤ ከከርቤ ቅንጣት
ከሰፍነግ ላይ እንደመጋት፡፡
እሳት ላይ እንደቆመ እግር
እንደ ሰፋ የአራሽ ድግር
ያሸነፉት ሲያሸንፍ የጣሉት መልሶ ሲጥል
ሲያቃጥል!!!
*
“መንገዳችን ያሳዝናል”
የምንሄደው ያሰጋናል
አሁን ደሞ እንዲህ ሆነናል
/እንዲህ/
ይሁዳን እያሞገሱ ከዮሐንስ ጋር መጣለት
እዚህ በርባንን መስደብ በዚያ በኩል መስቀል መጥላት
በጉን ወዶ ተንከባክቦ ምን ይሉታል መጠየፍ ላት??
***
የጣልናቸው እየጣሉን
ያዘልናቸው እየጠሉን
እውነት?
አፈር አፈርን በላ?
ድንጋይ ድንጋይ ላይ ሰላ?
የቱ ጋር ነው የቆምን ከአድዋ ኋላ??
#ቶማስአድማሱ #ግጥምሲጥም #ጥበብበአደባባይ #ግጥማዊቅዳሜ
#ThomasAdmasu #tba #tibebbeqdebabay #digitalartfestival #artinaddis #gitemsitem
Who am I; Telling Migrating Stories
Take a peek 👀 at one of the many stories among the "My story" collection, a creative project by one of our talented artist @Yonas Hailu
This is the story of Tesfa, he graduated from Addis Ababa University in civil engineering as well as marketing at an early age. Highly influenced by his peers, he then migrated to Europe mainly to UK, Greece and Germany who spend 15 years in camp doing nothing.
Yonas says, he told me the biggest mistake that he believes he made was to pursue happiness and success from outside, when he already had it in the palm of his hands. After he spent so many years, he learned that the simple rumor and talk of migrating to Europe and the US almost destroyed his life.
Follow us:
Telegram: t.me/Tibeb_Be_Adebabay
Facebook Page: facebook.com/Tibeb2020
Twitter: twitter.com/TibebBe
YouTube: youtube.com/channel/UCmvDcNWiv8oNpzL7elz1fag
Website: http://tibebbeadebabay.org
#tibebbeadebabay #digitalart #digitalartfestival #artinaddis #tba
ኢትዯጲያ አገሬ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ መለያዬ.፣
የአያቶቼ አደራ የጥቁር ህዝብ አርማ ባንዲራዬ።
ሰሜንን ብናየው መቼም አንጠግበው፣
አክሱም ፈር ቀዳጅ ነው ለስልጣኔው፣
ወሎ ላሊበላ የቆነጆዎች አገር ፣
ጎጃም ጢስ አባይ ፋሲለደስ ጎንደር፣
አፈር ልምላሜው ቡናው ከወደ ጅማ፣
ወልቂጤ እነሞር ምድሩ ሰራተኛ፣
ደረስ ብለን ብናይ ወስጧን ከወለጋ፣
አላት እምቅ ሃብት መሬት ውስጥ የረጋ።
አገሬ አገሬ ኢትዯጲያ!!
https://t.me/rasja
#rasjany #gitemsitem
Did you participate in the Who am I #challenge by Gitem Sitem - ግጥም ሲጥም?
Find your word!😊😊
Thank you for your participation and STAY TUNED for more. KEEP PARTICIPATING IN THE CHALLENGES!!
'እኔ ማን ነኝ?' የሚለውን ጥያቄ ለራሳችሁ ጠይቁና መልሱን አቀብሉን ባልናችሁ መሰረት የሰበሰብናቸው ቃላት ይህን ይመስላሉ።
መልሳችሁን ምስሉ ውስጥ አገኛችሁት?
Follow us:
Telegram: t.me/Tibeb_Be_Adebabay
Facebook Page: facebook.com/Tibeb2020
Twitter: twitter.com/TibebBe
YouTube: youtube.com/channel/UCmvDcNWiv8oNpzL7elz1fag
Website: http://tibebbeadebabay.org
#gitemsitem #tibebbeadebabay #digitalart #digitalartfestival #artinaddis #tba
~የጠበበኝ እኔ
(ሀናን ሁሴን)
በጥልፍልፍ ጉያ የተሰነቀርኩ
በጥብቅ መቀነት የተሰረሰርኩ
በጎታች እትብት ወግ የተሰየምኩ
እኔ የታፈንኩኝ ...እኔ
ከስዬ አላበቃሁ ግና ነው መጫሬ
ከአመዱ ስር ነው ውሎና አዳሬ
በትኜ ለመውጣት ከተዳፈንኩበት
ለትንፋሽ የሚሆን አየር ልስብበት
አመድን ምቾቴ ከማለት በሩቅ ስርቅ
በደራው ሂደቴ ሙቀትን መኖሬን ማሳብቅ
እኔ.... የጠበበኝ እኔ
ብናኝ ሲውጠኝ ተከማችቶ
ዝቆ አስተንፋሽን ገፍቶ
ግለቴ ቢያጎላው መኖሬን
ሊያየኝ የዳዳው ከብናኝ መደበኝ
ቀርቦ ሳይምሰው ከአመድ አስጠጋኝ
እኔ....የጠበበኝ እኔ
በጥልፍልፍ ጉያ የተሰነቀርኩ
በጥብቅ መቀነት የተሰረሰርኩ
በጎታች እትብት ወግ የተሰየምኩ
እኔ....የታፈንኩኝ እኔ
ከባቢው ያፍናል
ላያፈናፍን ይጋፋል
በክብደቱ የውስጥ ጠሊቅን ያናጋል
ከሸክሙ አስማምቶ አየር ያሳጣል።
ሽቅብ ለመቃናት
በነፃነት ለመቃኘት
ከስር ቆሰቆስኩ
ውስጤን አጋልኩ
ክምሩን ብሰጋ
ከአመድ አልረጋ
ጠፍቼ ያልጠፋሁ እኔ ነኝ የተዳፈንኩ....
አመዱን ገርስሼ ብቅ ልል የደፈርኩ...
እኔ...የጠበበኝ እኔ
#hanan_hussen #ሀናን_ሁሴን #ግጥምሲጥም #ጥበብበአደባባይ #ግጥማዊቅዳሜ
#tba #tibebbeqdebabay #digitalartfestival #artinaddis
መ ነ ፅ ር ፤
"#Menetsir is a platform born of the conviction that now, more than ever, it is necessary for us, Ethiopians, to explore our own local thinking, ideologies, philosophies, and ways of life. We explore our local books, music, literature, school of thoughts, and of cultural idioms on diverse topics."
https://ketemajournal.com/story/%E1%88%98-%E1%8A%90-%E1%8D%85-%E1%88%AD-%E1%8D%A4/
Design for Humanity!
Stay Safe!
@NArcHomeArchitecture'እኔ ማን ነኝ?' የሚለውን ጥያቄ ለራሳችሁ ጠይቁና መልሱን አቀብሉን ባልናችሁ መሰረት የሰበሰብናቸው ቃላት ይህን ይመስላሉ።
መልሳችሁን ምስሉ ውስጥ አገኛችሁት?
#ግጥምሲጥም #ጥበብበአደባባይ #ግጥማዊቅዳሜ
#gitemsitem #tibebbeadebabay #tba #tba2020 #artinaddis #digitalartfestival #poeticsaturdays
Tibeb be Adebabay featured on Addis Zeybe!
“We believe art and creativity is a very important part of our society and we need artistic and creative expressions in all parts of our lives. Keep going, never give up on your creative side and believe in yourselves because we believe in you” Read the full article by clicking here: https://bit.ly/2QYCJPU
Follow us:
Telegram: t.me/Tibeb_Be_Adebabay
Facebook Page: facebook.com/Tibeb2020
Twitter: twitter.com/TibebBe
YouTube: youtube.com/channel/UCmvDcNWiv8oNpzL7elz1fag
Website: http://tibebbeadebabay.org
#tibebbeadebabay #digitalart #digitalartfestival #artinaddis #tba
OUT NOW: The Arts Mailing List newsletter – 7th Sep 2020 https://bit.ly/321oe46
Featuring the beautifully captivating work of Illustrator
https://www.instagram.com/hawi_kefale/
Click on the above link to find this week’s list of national and international open calls, competitions, funding and residencies etc… for you to apply to.
This week, we also bring you @seifetemam, @Theurbancenter, @PoeticSaturdays, @everythingaddis, @getz_mag, @LinkUpAddis, @aterira and so much more!!
@artsmailinglist
AWiB's 12th webinar series will take place on 09 September 2020 (Titled Awakening the Warroir Within), this time featuring Panos Hatziandreas (Professor), Head of Lebawi Academy.
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
