cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ETHIO MEREJA

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدلم يتم تحديد اللغةالفئة غير محددة
مشاركات الإعلانات
2 642
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

Photo unavailableShow in Telegram
ተደራዳሪዎቹ እነማን ናቸው? የፌደራሉ መንግሥት ከትግራይ ኃይሎች ጋር የሚነጋገሩ አባላት ከዚህ ቀደም ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። ይህ ተደራዳሪ ቡድን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ደመቀ መኮንን የሚመራ ሲሆን ሰባት አባላትን ያካተተ ነው። ከአቶ ደመቀ በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንግሥት መንግሥትን የሚወክሉት የፍትሕ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር)፣ ብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ተመስገን ጥሩነህ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንት ጉዳዮች አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን፣ የመከላከያ ሠራዊት የመረጃ ደኅንነት ኃላፊ ሌ/ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ፣ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ጌታቸው ጀምበር (ዶ/ር) እና በብልጽግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ማዕከል ዘርፍ ውስጥ በከፍተኛ ኃላፊነት እየሰሩ የሚገኙት አምባሳደር ሐሰን አብዱልቃድር ናቸው። የትግራይ ኃይሎች በበኩላቸው ሁለት ተወካዮቻቸውን ለድርድር እንደሚልኩ ከዚህ ቀደም ገልጸው ነበር። የመጀመሪያው የህወሓት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል እና የፓርቲው ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ ሲሆኑ ሁለተኛው ደግሞ የትግራይ ኃይሎችን ከሚመሩት ከፍተኛ የጦር መኮንኖች መካከል አንዱ የሆኑት ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳይ ናቸው። ወደ ደቡብ አፍሪካ ግን ያቀኑት በቁጥር 9 መሆናቸዉንና ደቡብ አፍሪካ መድረሳቸዉን መረጃዎች አመላክተዋል፡፡ የሕወሃት የውጪ ግንኙነት አባል ክንደያ ገብረሕይወት እንዳስታወቁት ድርጅታቸው አስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ፣ የሰብዓዊ ዕርዳታ ያለ እንቅፋት ለተረጂዎች እንዲደርስና የኤርትራ ሰራዊት ከትግራይ እንዲወጣ መጠየቅ የድርጅታቸው ቀዳሚ ፍላጎት መሆኑን አስታውቀዋል። የፌደራል መንግስት እስካሁን ምንም ያለዉ ነገር የለም፡፡ በአባቱ መረቀ ጥቅምት 14 ቀን 2015 ዓ.ም
إظهار الكل...
ተደራዳሪዎቹ ደቡብ አፍሪካ ገብተዋል! በኢትዮጵያ ፌዴራል መንግሥትና በህወሓት መካከል ዛሬ፤ ሰኞ ይጀመራል ለተባለው የሠላም ንግግር የሁለቱም ወገኖች ተደራዳሪዎች ደቡብ አፍሪካ መግባታቸው እየተሰማ ነው። ምንም እንኳ ድርድሩ የሚካሄድበት ትክክለኛ ቦታና ሰዓት በጥብቅ ምሥጢር የተያዘና እስካሁንም ያልተገለፀ ቢሆንም የህወሓት ቃል አቀባይ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት ዛሬ ባወጡት ትዊት ተደራዳሪዎቻቸው ደቡብ አፍሪካ መግባታቸውን አስታውቀዋል። “በአፍሪካ ኅብረት በሚመራው የኢትዮጵያ ትግራይ የሠላም ንግግር ላይ ለመገኘት የትግራይ መንግሥት ልዑካን ቡድን ደቡብ አፍሪካ ገብቷል” ብለዋል።ቃል አቀባዩ በዚሁ ትዊታቸው ላይ አክለውም “እጅግ አንገብጋቢ ጉዳዮች” (Pressing) ሲሉ ባሠፈሩት ዝርዝር “ፀቡ [ውጊያ] ፈጥኖ እንዲቆም፣ ያልተገደበ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦትና የኤርትራ ኃይሎች መውጣት” ብለዋል። ይሁን እንጂ እነዚህ ነጥቦች ቅድመ ሁኔታ ይሁኑ አይሁኑ የጠቆሙት ነገር የለም። ፕሮፌሰር ክንደያ ትዊታቸውን የዘጉት “ወታደራዊ መፍትኄ ሊኖር አይችልም” በሚል መልዕክት ነው።ከህወሓት ተደራዳሪዎች መካከል ጄነራል ፃድቃን ገብረትንሳይ እና አቶ ጌታቸው ረዳ እንደሚገኙበት ተዘግቧል። ይህ ዜና እስከተጠናቀረበትና እስከወጣበት ደቂቃ ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል የተሰማ የመጨረሻ ይፋ መረጃ ወይም መግለጫ ባይኖርም የተደራዳሪው ቡድን አባል እንደሚሆኑ ቀደም ሲልም ተገልፆ የነበረው የብሄራዊ ፀጥታና ደኅንነት አማካሪው አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ሃሙስ፣ ጥቅምት 10/2015 ዓ.ም. ባወጡት ትዊት ድርድሮቹ ጥቅምት 14/2015 እንዲካሄዱ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን እንዳሳወቃቸው ጠቁመው ለመሳተፍም ያላቸውን ቁርጠኛነት በድጋሚ ማረጋገጣቸውን አመልክተዋል። አምባሳደር ሬድዋን በዚሁ ትዊታቸው ላይ አያይዘው በስም ያልጠሯቸውና “አንዳንድ” ያሏቸው “ከሰላም ንግግሮች አፈንግጠው በመከላከያ እርምጃዎቹ ላይ የሃሰት ክሶችን መንዛታቸው አስደምሞናል” ብለዋል። የድርድሩ ነጥቦችና ጭብጦች ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ እስካሁን የወጣ መረጃ የለም። የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ዩናይትድ ስቴትስን በእጅጉ እንደሚያሳስባት የተናገሩት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ አንተኒ ብሊንከን የሰኞው የደቡብ አፍሪካ ድርድር በቅን መንፈስ እንዲካሄድ ጥሪ አድርገው ተኩስ በአስቸኳይ እንዲቆም፣ ያልተገደበ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት እንዲኖር፣ የኤርትራ ኃይሎች ከሰሜን ኢትዮጵያ እንዲወጡ ማሳሰባቸውን ቃል አቀባያቸው ኔድ ፕራይስ ገልፀዋል። ከአፍሪካ ኅብረት በይፋ የተሰጠ መግለጫ እስካሁን የለም። Via VoA #ዳጉ_ጆርናል
إظهار الكل...
በማላዊ በጅምላ ተቀብረው የተገኙ ኢትዮጵያዊያን ቁጥር 29 ደረሰ ባሳለፍኑው ማክሰኞ እለት በማላዊ ሚዚምባ በተባለ ስፍራ የ25 ኢትዮጵያዊያን በጅምላ ተቀብረው መገኘታቸው ይታወሳል። ማላዊ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለሚደረግ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር መተላለፊያ መሆኑን ተከትሎ ኢትዮያውያኑ የህገ ወጥ ስደት ሰለባ ሳይሆኑ አይቀሩም ተብሏል። አሁን ደግሞ አራት ተጨማሪ ኢትዮጵያውያን ሳይሆኑ እንዳልቀረ የተገመተ አስከሬን ባንድ ቦታ መገኘቱን የማላዊ ፖሊስ አስታውቋል። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በማላዊ በተገኘው አስከሬን ጉዳይ ከሀገሪቱ መንግስት ጋር ጉዳዩን እየተከታተለ መሆኑን አስታውቋል። ለወቅታዊ እና ለፈጣን መረጃዎች የሁሌ አዲስ ሚዲያ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ይቀላቀሉ። Facebook : https://www.facebook.com/Huleadissmedia/ Telegram : https://t.me/Hulaadiss YouTube Channel https://www.youtube.com/channel/UCk934znIu60LV3czcIVZ9Bg
إظهار الكل...
Log in to Facebook

Log in to Facebook to start sharing and connecting with your friends, family and people you know.

Photo unavailableShow in Telegram
መከላከያ የሽሬ ኤርፖርትን መቆጣጠሩ ተነገረ፡፡ የኢትጵያ ጥምር ጦር በህወሃት ቁጥጥር ስር የነበሩ ሽሬና አላማጣ የመሳሰሉ ከተሞችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ተናግሯል፡፡ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ባወጣዉ አጭር መግለጫ ጦሩ ለሰብአዊ እርዳታ ድጋፍ ትልቅ ጠቀሜታ ያለዉን የሽሬ ኤርፖርትን መቆጣጠሩን አስታዉቋል፡፡በመሆኑም ይህን በመጠቀም የሰብአዊ እርዳታዎችን ተደራሽ ለማድረግ ጥረት አደርጋለሁ ብሏል፡፡ መከላከያ በከተሞች አካባቢ ጦርነት ሳያካሂድ መቆጣጠር እንደቻለም ተነግሯል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ክልል ለሚገኙ ዜጎች የሰብአዊ እርዳታ ለማቅረብ ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር እንደሚሰራም ነዉ የገለፀዉ፡፡ የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦቱን ለማስፋት ሰሜን ጎንደርን ከሽሬ የሚያገናኘዉን መስመር ሊጠቀም እንደሚችልም መግለጫዉ እትቷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የሰብአዊ እርዳታ በኮምቦልቻ ፤ደሴ፤ ቆቦና አለማጣ መስመር እንዲሰላጥ ይደረጋል ነዉ ያለዉ፡፡ ከሰብአዊ እርዳታ በተጨማሪም በግጭቱ የተጎዱ አካባቢዎች ተለይተዉ የመልሶ ማቋቋም ስራዎች እንደሚከናወኑም በመግለጫዉ ተጠቅሷል፡፡ https://t.me/ethiogeeks https://t.me/ethiogeeks
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
ኔቶ ከሩሲያ ጋር ጦርነት ውስጥ መግባቱን አምኗል - ሜድቬዴቭ የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) ከሩሲያ ጋር ጦርነት ውስጥ መግባቱን የኔቶ ዋና ጸሐፊ ዬንስ ስቶልተንበርግ በተዘዋዋሪ ማመናቸውን የቀድሞው የሩሲያ ፕሬዚዳንት ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ ገለጹ፡፡ ማክሰኞ ዕለት በጉዳዩ ላይ ስቶልተንበርግ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ÷ “ሩሲያ በጦርነቱ ባለድል ከሆነች ለኔቶ ሽንፈት ይሆናል” ማለታቸው ይታወሳል። የኖርዌዩ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዬንስ ስቶልተንበርግ ለጋዜጠኞች አስተያየታቸውን የሠጡት በዛሬው ዕለት የኔቶ አባል ሀገራት ሚኒስትሮች ከዩክሬን መከላከያ ሚኒስትር አሌክሲ ሬዝኒኮቭ ጋር ለመገናኘት በተዘጋጁበት ወቅት ላይ መሆኑን አር ቲ ዘግቧል፡፡ https://t.me/ethiogeeks https://t.me/ethiogeeks
إظهار الكل...
ወቅታዊ መረጃ በቅርቡ ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው የሰላም ንግግር ከሀገር ሉዓላዊነትና ሕገ መንግስታዊ ሥርዓት አንፃር መታረም የሚገባቸው ጉዳዮች፡-
إظهار الكل...
00:35
Video unavailableShow in Telegram
በካዛኪስታን አነጋጋሪው ሌባ ⚡  ሰሞኑ በካዛክስታን አንድ ሌባ ወደ አንድ የሃርድዌር መደብር  ጎራ አለ ።  ወደ መደበሩ መጋዘን  አምርቶ ለመስረቅ ሲዘጋጅ ሰው እንደመጣበት  ተመለከተ።  ማቀዝቀዣው ወስጥም ተደበቀ ። የተደበቀበት ማቀዘቀዣ ተሽጦ በካርቶን ሲታሸግ ሌባው እዛ ነበር ።ኋላ ግን ጭር ሲል  ከማቀዝቀዣ ወጥቶ ሰርቆ ሄዷል።
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
⚡️ኳታር በመጪው ህዳር አጋማሽ ለሚጀመረው የ2022 የአለም ዋንጫ የእግር ኳስ ደጋፊዎች መመሪያ አውጥታለች። መመሪያው ከሚያግደው ውስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል፡- ▪️አልኮል በመንገድ ላይ መጠጣት ▪️ ግብረ ሰዶማዊነት ▪️የሴቷ አካል ክፍሎችን የሚያሳይ አለባበስ ▪️መሳደብ ▪️ለመስጂዶች ክብር አለመስጠት ▪️ከፍተኛ ሙዚቃ እና ድምፆች ▪️የፍቅር ቀጠሮ ▪️ሰዎችን ያለፈቃዳቸው ፎቶግራፍ ማንሳት የሚሉት ይገኙበታል
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
ሰሜን ኮሪያ ወደ በጃፓን ላይ ባልስቲክ ሚሳኤል ተኮሰች ሰሜን ኮሪያ የቶኪዮ እና የዋሽንግተንን ትኩረት ለመሳብ ነዉተብሎ የተጠረጠረ ሚሳኤል በጃፓን ላይ ተኩሳለች።የባሊስቲክ ሚሳኤሉ ወደ ፓስፊክ ውቅያኖስ ከመውደቁ በፊት 4,500 ኪ.ሜ ያህል የተጓዘ ሲሆን በሌላ አቅጣጫ ቢወነጨፍ የጉዋም ደሴትን ለመምታት በቂ ሀይል እንደነበረዉ ተገልጿል፡፡ ከ2017 ወዲህ ሰሜን ኮሪያ ወደ ጃፓን ሚሳኤል ስታስወነጭር የአሁኑ የመጀመሪያው ነው።ጃፓን ዜጎቿ እንዲጠነቀቁ ጥሪ አቅርባለች፡፡የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰሜን ኮሪያ የባሊስቲክ እና የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎችን እንዳትሞክር ቢከለክላትም ተግባራዊ መሆን ግን አልቻለም። ያለ ምንም ቅድመ ማስጠንቀቂያ ወይም ምክክር ወደ ሌላ ሀገር የሚደረግ የሚሳኤል ማስወንጨፍ አለም አቀፍ ደንቦችን የሚቃረን ነዉ፡፡ የተወነጨፈዉን ሚሳኤል ተከትሎ የመንግስት ባለሥልጣናት እንደተናገሩት መካከለኛ ርቀት ያለው ባለስቲክ ሚሳኤል መሆኑን በመግለጽ ከጃፓን ርቆ በፓስፊክ ውቅያኖስ ውስጥ መውደቁን እና ምንም ዓይነት ጉዳት እንዳልደረሰም ገልጸዋል፡፡የጃፓኑ ጠቅላይ ሚንስትር ፉሚዮ ኪሺዳ ድርጊቱ “ጸብ ጫሪ” ያሉት ሲሆን የአሜሪካ ብሄራዊ ደህንነት ምክር ቤት ቃል አቀባይ አድሪያን ዋትሰን ድርጊቱን "አደገኛ እና የግዴለሽነት ውሳኔ" ለአካባቢው "መረጋጋት" አደጋ ሲሉ ጠርተውታል። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
የዩጋንዳው የረዥም ጊዜ ፕሬዝዳንት ሙሴቬኒ ልጅ ናይሮቢን ለመያዝ፣ የኔ ሰራዊት እና እኔ 2 ሳምንት አይፈጅብንም ሲሉ ተናግረዋል።የዩጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ልጅ ሌተናል ጄኔራል ሙሁዚ ካይኔሩጋባ በአወዛጋቢነታቸው ይታወቃሉ። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
إظهار الكل...