አል ፋሩቅ ጀመዓ
Islamawi yemereja makel
إظهار المزيدلم يتم تحديد البلدلم يتم تحديد اللغةالفئة غير محددة
201
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
"ውዴታ እስከ ጀነት"
በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት ለተለዩት ሙንሺድ መሐመድ አወል መሐመድ ሷላህ "ውዴታ እስከ ጀነት" በሚል መሪ ቃል የምሥጋና ፕሮግራም ተዘጋጀ።
ዝግጅቱ በወዳጆቹና ለዚህ ፕሮግራም በተቋቋመ ጊዜያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
የኮሚቴው ዋነኛ ተግባር መሐመድ አወል መሐመድ ሷላህ ቤተሰቦች መደገፍና ማቋቋም ነው ተብሏል።
ኮሚቴው የተለያዩ መርሀ ግብሮችም ነድፎ ኮ እየተንቀሳቀሰ ሲሆን ከዚህ ተግባር ውስጥ አንዱ የፊታችን እሁድ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ትያትር የተዘጋጀው ዝግጅት ነው።
ዝግጅቱ ጠዋት 3 ሰዓት ጀምሮ የሚካሄድ ሲሆን የመግቢያው ዋጋ 300 ብር መሆኑ ተገልጿል።
ዝግጅቱ ላይ ሙንሺዶች ሥራቸውን ያቀርባሉ ልዩ ሙሐመድ አወልን የሚያስታውሱ ነሺዳ በጋራ ይሠራል የተመረጡ ፕሮግራሞች ይኖራል ተብሏል።
ከእሁዱ ፕሮግራም በተጨማሪ መሐመድ አወል መሐመድ ሷላህ ቤተሰቦች እንዲቋቋሙ እና እንዲደገፉ የጎ ፈንድ ሚ አካውንት https://www.gofundme.com/f/j294mw?utm_source=customer&utm_medium=copy_link&utm_campaign=p_cf+share-flow-1 መከፈቱ ተገልጿል።
መሐመድ አወል መሐመድ ሷላህ ባለፉት ከ12 በላይ ዓመታት የሠሯቸው የነሺዳ ሥራዎች ተወዳጅና ተመራጭ ሆነው በሙስሊሙም ሆነ ሙስሊም ያልሆኑ አድናቂዎቹ ዘንድ ቢሠራጩም ከሥራዎቹ ተጠቃሚ ሳይሆኑ ነው ያለፉት።
@tikvahethiopia
የጎርፍ መሄጃ ቦዮች ተደፍነዋል፤ መተላለፊያ መንገዶች በተመነጠሩ አረሞችና በተቆረጡ ዛፎች ተዘግቷል፤ ኃይለኛ ዝናብ ጥሎ ጎርፍ ወደ ለህድ ዘልቆ ሙታኖቻችንን አጉል አድርጎብን ከንፈር ከምንመጥና ጣት ከምንቀስር ኑ የአቅማችንን እናበርክት።
ለሌሎች ወንድሞቻችን ሼር በማድረግ ብዙ ሰው እንዲገኝ እናድርግ። ዛሬም ትላንትም ያለውን ነገር ለማየት ሞክሬ ነበር ወላሒ አሳዛኝ ሁኔታ ውስጥ ነን
እንደ ልብ ወዳጅ ሌት ተቀን ተናፍቃ
እንደ እናት ጉርሻ በስስት ተጠብቃ
ምድሩን አፍክታ ሰማዩን አድምቃ
ብቅ አለች
ብቅ አለች ጨረቃ
ብቅ አለች
ብቅ አለች ጨረቃ!
#ተናፋቂው_ወር_ረመዳን❤️