ar
Feedback
Fuad Muna (Fuya)

Fuad Muna (Fuya)

الذهاب إلى القناة على Telegram

የኛ እዉነታ የሌሎችን ስጋ ለብሶ ሲቀርብ! በፅሁፍ ያስነበብኳችሁን በድምፄ ስትሰሙት! ዩቲዩብ ቻናል http://Www.YouTube.com/c/FuadMuna የፌስቡክ አካውንቴን ለማግኘት www.facebook.com/fuadmuna14 ለፒዲኤፍ ብሎግ www.fuadmuna.wordpress.com

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Fuad Muna (Fuya)

تُعد قناة Fuad Muna (Fuya) (@fuadmu) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 635 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 453 في فئة المدوّنات والمرتبة 2 164 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 635 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 30 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 649، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 21، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 24.51‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 13.62‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 832 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 130 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 87.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የኛ እዉነታ የሌሎችን ስጋ ለብሶ ሲቀርብ! በፅሁፍ ያስነበብኳችሁን በድምፄ ስትሰሙት! ዩቲዩብ ቻናል http://Www.YouTube.com/c/FuadMuna የፌስቡክ አካውንቴን ለማግኘት www.facebook.com/fuadmuna14 ለፒዲኤፍ ብሎግ www.fuadmuna.wordpress.com

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 31 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة المدوّنات.

15 635
المشتركون
+2124 ساعات
+1577 أيام
+64930 أيام
أرشيف المشاركات
ስጦታ ሲማ ላይ የስጦታ ገፅ ተካቷል። ለምትወዱትም ሰው ግዙ! ስጦታ ተሰጣጡ! @sima_book ላይ 900 ብር መግዛት ትችላላችሁ። እያስተናገድን ነው። . @Fuadmu
+1
ስጦታ ሲማ ላይ የስጦታ ገፅ ተካቷል። ለምትወዱትም ሰው ግዙ! ስጦታ ተሰጣጡ! @sima_book ላይ 900 ብር መግዛት ትችላላችሁ። እያስተናገድን ነው። . @Fuadmu

በርካታ መልዕክቶችን በአንዴ ለማስተናገድ እየሞከርን ስለሆነ ቴሌግራም ትንሽ ያዝ እያደረገን ነው። @Sima_book ላይ መልዕክት ልካችሁ በትዕግስት ጠብቁን እንመልሳለን። 🥰 . @Fuadmu

ሲማ ረዥም ልብወለድ በፉአድ ሙና @Sima_book ላይ ይሸምቱ። . @Fuadmu
+2
ሲማ ረዥም ልብወለድ በፉአድ ሙና @Sima_book ላይ ይሸምቱ። . @Fuadmu

ሲማ 🥰 ከአሁን ጀምሮ @sima_book ላይ መግዛት ትችላላችሁ። . @Fuadmu

የሀምሌ ስጦታ! (ፉአድ ሙና) . ጊዜን የሚያገለባብጠው ጌታ ምስጋና ይገባው፡፡ ለመጨረሻ ጊዜ እንዲህ ማስታወቂያ አዘጋጅቼ ‹ሰርፕራይዝ› አለኝ ያልኩት ከዛሬ ሶስት ዓመታት በፊት የረመዳን መጠናቀቂያ ላይ ነበር፡፡ የዚያን ጊዜው ‹ሰርፕራይዛችን› ‹ኢፋዳ› የተሰኘችው የበኩር የረዥም ልብ-ወለድ ስራዬ ነበረች፡፡ የአላህ ፈቃድ ሆኖ ኢፋዳን እናንተም ወዳችኋት ከመፅሀፍነትም ተሻግራ ድርጅት መሆን ችላለች፡፡ ባለፉት ዓመታትም በኢፋዳ ኢስላማዊ ድርጅት በኩል በርካታ ስራዎችን ለመስራት ችለናል፡፡ በኢትዮጵያ ሙስሊም አዋርድ ላይም የዓመቱ ምርጥ ደራሲ ዘርፍ አሸናፊ ሆኜ ተሸልሜባታለሁ፡፡ የዛሬው ‹ሰርፕራይዛችን› በተመሳሳዩ መፅሀፍ ሊሆን ይችላል ብላችሁ የጠረጠራችሁ እንደነበራችሁ ተመልክቻለሁ፡፡ በእርግጥ አልተሳሳታችሁም፡፡ የሐምሌ 24 ‹ሰርፕራይዛችን› … ለእናንተ ያዘጋጀኋት የሀምሌ ስጦታ … ‹ሲማ› የተሰኘች የረዥም ልብወለድ ስራ ናት፡፡ ‹ሲማ› ለመወለድ ሁለት ዓመታትን ፈጅታለች፡፡ የአላህ ፈቃድ ሆኖ ውልደቷ እውን መሆን ችሏል፡፡ በእርግጥ ከጅምሩ የህትመት ዋጋ እንዲህ መናሩን ባወቅኩ ማሳተምን ባላሰብኩት ነበር፡፡ መፅሀፉን አዘጋጅቼ የህትመት ዋጋ ባጣራሁበት ሰዓት ሀሳቤን ስለመቀየርም አስቤያለሁ፡፡ ሆኖም በአላህ ችሮታ እንዲሁም ከጎኔ ሆነው አለንልህ ባሉኝ የቁርጥ ቀን ምርኩዞች ድጋፍ … ተወለድ ያለው እንዲሉ … ሲማ ተወልዳለች፡፡ ሲማ ክረምታችሁን የምትቆርጡባት የሀምሌ ስጦታዬ ናት፡፡ በጥቅሉ 320 ገፆች አሏት፡፡ እንደተለመደው የሙስሊሙን ዕሴት ያልተጣረሰ የልብወለድ ስራ ለማዘጋጀት ሞክሬያለሁ፡፡ ውድ አንባቢዎቼ ሲማን አንብባችኋት የተሰማችሁን ሀሳብ እስክታካፍሉኝ ጓጉቻለሁ፡፡ ሲማ ለውድ ቤተሰቦቼ ከዛሬ ጀምሮ ሽያጭ ላይ ትውላለች፡፡ አንባቢዎች ከአሁን ጀምሮ ከስድስተኛው ኮፒ ጀምሮ ያሉትን መፅሀፍት በቴሌግራም @sima_book ላይ 900 ብር በሞባይል ባንኪንግ በመክፈል በመግዛት የራሳችሁን ኮፒ ማስያዝ ትችላላችሁ፡፡ ከአንደኛ እስከ አምስተኛ ድረስ ያሉትን የመፅሀፉን ኮፒዎች ደግሞ ነገ ቅዳሜ ምሽት በሚኖረን የፈገግታ መጅሊስ መሰናዶ ላይ በጨረታ የምንሸጣቸው ይሆናል፡፡ ለአሸናፊዎች መፅሀፉን እኔ የማደርስ ይሆናል፡፡ መፅሀፉን የገዛችሁ ቤተሰቦች ኢፋዳ ላይ እንዳደረግነው በከተማችን በምናዘጋጃቸው የሲማ መፅሀፍ ፒካፕ ሎኬሽኖች በቀጣይ ሳምንታት መፅሀፋችሁን እንድትወስዱ እናደርጋለን፡፡ ከመጀመሪያዎቹ የሲማ ባለቤቶች መካከል ሁኑ! ከጥልቅ መውደድ ጋር! ፉአድ ሙና የማይነበብ ፊርማ . @Fuadmu @Sima_book

The post is Scheduled 📅 Stay Tuned 7:30 PM 2 hours left 🥰 . @Fuadmu

5 ሰዓታት ብቻ ቀሩ 🥰 . @Fuadmu

እነሆ ቀኑ ደረሰ! ዛሬ ምሽት ከምሽቱ 1:30 ሲል ሰርፕራይዛችን ይፋ ይደረጋል። ዛሬ በደንብ ማስታወቂያው ላይ እንበርታ! . @Fuadmu
እነሆ ቀኑ ደረሰ! ዛሬ ምሽት ከምሽቱ 1:30 ሲል ሰርፕራይዛችን ይፋ ይደረጋል። ዛሬ በደንብ ማስታወቂያው ላይ እንበርታ! . @Fuadmu

ከ24 ሰዓታት በታች ቀርተዋል! ነገ ቀኑ ጁሙዓ ሲል ... አማኝ ገላውን ተጣጥቦ መስጂድ ከሄደ በኋላ ... ጁሙዓ ተሰግዶ ... አስርና መግሪብ አልፈው ... በመግሪብና በኢሻ መሀል ... 1:30 ሲል ... ሰርፕራይዛችን ይፋ ይደረጋል! ሁላችሁም ነገ ጁሙዓ ከምሽቱ 1:30 ሲል ኦንላየን ጠብቁኝ። የማይደርስ የለም ... ደረሰ! እነሆ ሀምሌ 23 መሸ! ሀምሌ 24 ነገ ነው 🥰 ማስታወቂያው ላይ እንበርታ 🥰 . @Fuadmu

እነሆ ነገ ምሽት 1:30 ሲል ሰርፕራይዙ ይፋ ይደረጋል። ብዙ ግምቶ ተሰጥተዋል። እርስዎ የቱ ትክክል ይመስልዎታል?
Anonymous voting

2 ቀናት ብቻ! ሁላችሁም ፕሮፋይል፣ ስቶሪ፣ ፖስት በማድረግ ማስታወቂያው ላይ አግዙኝ! ዛሬና ነገ ብቻ ቀርተዋል። . @Fuadmu
2 ቀናት ብቻ! ሁላችሁም ፕሮፋይል፣ ስቶሪ፣ ፖስት በማድረግ ማስታወቂያው ላይ አግዙኝ! ዛሬና ነገ ብቻ ቀርተዋል። . @Fuadmu

እጥፋት አጭር ልብወለድ በፉአድ ሙና . @Fuadmu

ሰው አልባው ቤት በሰው ተሞላ፡፡ በህይወት ሳለ ሰው የራበው ሰው በድን ሆኖ በሰው ተከበበ፡፡ ልጆች በለሊት ተነስተው ጠዋቱን ወደ አባታቸው ቤት ደረሱ፡፡ ለአረፋ አርዶ ‹‹የተንቢ … ባፈር ንተን!›› ይላቸው የነበረው አባታቸው በብቸኝነት ብርድ ተቆራምዶ ወደ ቀጣዩ አለም ተሻገረ፡፡ እዚያ ናፍቆቱን ሳትሰለች የምትሰማው ሚስቱ አለች … አይበርደውም ይሆናል፡፡ የሰው ልጅ ወደ አፈር መከተቱ የተፈጥሮ ግዴታ ነውና … መዲናን የናፈቁት ሰው ወደ አፈር ተከተቱ፡፡ ልጆቹ ልክ እናታቸው ስታመልጣቸው እንዳሉት … ‹‹አመለጠን! … አመንጠንደም!›› እያሉ ተንሰቀሰቁ፡፡ ለእናታቸውም እንዲሁ ተንሰቅስቀው ነበር፡፡ ግን ከተማ ሲመለሱ ተረሳቸው፡፡ ገንዘብ ሲቆጥሩ አባታቸውም እንደ እናታቸው ሊያመልጣቸው እንደሚችል ዘነጉት! ሰደቃ እንዲሆንላቸው … የጥፋተኝነት ስሜታቸውን ለመሻርም ሊሆን ይችላል … ሰንጋ ወደ ቤቱ ነዱ፡፡ መንደርተኛ ሁሉ ሰደቃ ተጠራ፡፡ በየቀኑ ይታረዳል … ለከብት ብቻ ከግማሽ ሚሊየን በላይ አውጥተዋል፡፡ አሄሄ … ይኼ ገንዘብ በህይወት እያለ የአባታቸውን ናፍቆት አይቆርጠውም ነበር? ይቆርጠዋል፡፡ ግን ልብ ጠፋ … ወላጆቹን የሚያስታውስ ደህና ልብ! አጥተውስ ቢሆን ይሁን … ገንዘብ ተርፏቸው … እንዲህ ባይተዋር ሲያደርጓቸው! ለቀስተኛው ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡ እነሱም ቀስ በቀስ ወደ ከተማ መመለስ ጀመሩ፡፡ ታላቅ ወንድማቸው ብቻ ቀረ፡፡ ቤቱን ወደ መስጂድ ስለመለወጥ አስበዋል፡፡ ለማፅዳት ሲሞክር የአባቱን ቴፕ አገኘ፡፡ ካሴት እንደጎረሰች ናት፡፡ አጫወታት፡፡ ካቆመችበት ቀጠለች፡፡ ‹‹ሰላም ዘይኔ ለእናት እጅሁ፣ ሰው አንዴም ላልመታው፣ ጭነት ለከበደው ፈረስ፣ ለሚወርደው መንታው፣ ባለሟሉን የአላህ ደጌ፣ እንዴት ረሳህ አንተው፣ አስተዋዩ ይቅርና፣ እህ ግንዱም አይስተው፡፡ እያለፈ በጎዳናው፣ የቲም ‘ሚዳብሰው፣ ቢታወሰኝ የሱ ታሪክ፣ ሙች ውስጤን አመሰው፡፡ ድኩም አጽኚ ድሀ ወዳጅ፣ ለዑመት ‘ሚያለቅሰው፣ አልማዝ ሉል ሆኖ አከበረን፣ እንባው የሚፈሰው፡፡›› ከዓይኖቹ የእንባ ዘለላዎች ተሸቀዳደሙ፡፡ ድንገት የአባቱ ናፍቆት ታወሰው፡፡ ለመዲና መንሰፍሰፉ … መንገብገቡ ዓይኑ ላይ መጣበት፡፡ ልቡን ምን እንዲህ እንዳስረሳት እያሰበ እንደ አዲስ መንሰቅሰቅ ጀመረ፡፡ ምንም ሳይጎድለው ለአባቱ አለመድረሱ ውስጡን ፈጀው፡፡ ከዘገየ ነቃ! ካመለጡት በኋላ! እንደው ሄዶ ዑምራም … ሀጅም ያደርግላቸው ይሆናል፡፡ ግን እሳቸውን ወስዶ ቢያስደርጋቸው የሚያገኘውን ቅንጣት ታክል እርካታ አያገኝም፡፡ ከምንም ይሻላልና በስማቸው ሀጅና ዑምራ ለማድረግ ወሰነ፡፡ ካመለጡት በኋላ ባነነ … ናፍቆታቸውን ሳይቆርጥላቸው ከአባቱ ተለያየ፡፡ ሳያመልጡት ቢነቃ ይመኛል … ሳያጣቸው ቢደርስላቸው! ግን አምልጠውታል፡፡ ከቴፓቸው አጠገብ ተቀምጦ ያዳምጡት የነበረውን እንጉርጉሮ እየሰማ እየተነፋረቀ ‹‹አባኖ … አባኖ … እዮ እዮ … አባዎ አባኖ!›› ይላል፡፡ ለቅሶ ግን የሄደን አይመልስም! ተፈፀመ፡፡ ===== የእንጉርጉሮው ግጥም የቀደምት መሻዒኮች ስራ ነው። በድምፅ የተያያዘው እንጉርጉሮ ደግሞ ከቲክቶክ መንደር ከወንድም አይመን ዙልፊቃር ገፅ የተወሰደ ነው። . @Fuadmu

እጥፋት! (ፉአድ ሙና) . ‹‹አንተ ጦይባ ያለህ፣ ኧረ ወስፍም የለህ፣ ወዳጅ ትገድላህ፣ ከሩቅ ሰፍረህ ጦይባ፣ አህመደል ሙስጠፋ፣ ሸራቢ ሶፋ! አለቀሰች ዓይኔ፣ አይታ ሲሳፈሩ፣ የረውዳው መንደሩ፣ አሳሳኝ ብላ፣ አህመደል ሙስጠፋ፣ ሸራቢ ሶፋ! ጌታዬ እኔም ልየው፣ የጦይባን ሰፈር፣ ልቃም ያን አፈር፣ ልኽተም በሱ ስፍራ፡፡ አህመደል ሙስጠፋ፣ ሸራቢ ሶፋ! አላሁመሰሊ አላሙሀመዴ፣ አላሁመሰሊ አላሙሀመዴ፣ አህመደል ሙስጠፋ፣ ሸራቢ ሶፋ! ›› አንጀት የሚበላ የናፋቂ ድምፅ ከቴፑ ይስረቀረቃል፡፡ ፂማቸው በንጣት የተወረሰ … ከቴፓቸው ወዲያ አጫዋች የሌላቸው አባት የቤታቸውን በር ተደግፈው ያነባሉ፡፡ ይህ እንባ … የናፍቆት እንባ ነው … ከተማ ሄደው የጠፉባቸው ልጆቻቸው ናፍቆት አይደለም … ሳያዩ የናፈቋቸው ውዱ ነብይ ﷺ ናፍቆት እንጂ! ቢያዩት ይመኙ ነበር … የወደዷቸውን ነብይ ﷺ ሀገር … ሊረግጡት ይንሰፈሰፉ ነበር፡፡ ግን አልሆነላቸውም፡፡ ያለቻቸው ቴፓቸው ናት … ከደቡብ እስከ ሰሜን … ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ለውዱ ነብይ የተነቡ እንባዎችን እያስፈለጉ ቴፓቸውን ያጎርሳሉ፡፡ ቁስላቸውን ያኩላቸዋል መሰል … ለቅሷቸውን ያደምጣሉ፡፡ በርካታ ልጆች አሏቸው፡፡ ለአረፋ ተግተልትለው የሚመጡ … አመቱን ሙሉ ግን ባይተዋር ያደረጓቸው ቀልብ አልባ ልጆች! በዚህ የማረፊያ ዕድሜያቸው ወደ ጓሮ ወርደው ከአትክልቱ ጋር ይታገላሉ፡፡ ይጎለጉላሉ … ይኮተኩታሉ … የደረሰውን ያወጣሉ! ሰፊ የጫት እርሻም አላቸው፡፡ ሲደርስ እሱን ሽጠው … ልጆቻቸው ላይ ጥገኛ ላለመሆን ይታገላሉ፡፡  የተወሰኑ ከብቶች አሏቸው፡፡ እነሱን ለእረኛ እየከፈሉ ያሰማሩላቸዋል፡፡ ውሀ አቀባይ የሌለው ጎሮሯቸውን በወተት ጥሙን ይቆርጣሉ፡፡ ልጆቻቸው የገንዘብ ችግር የለባቸውም፡፡ እንኳን ዑምራ … ሀጅም ሊያስደርጓቸው ቢፈልጉ ገንዘብ አላጠራቸውም፡፡ ገንዘቡ ሳያጥር … ልብ አጠረ! ከዱንያ ኮተት ተፋቶ ለአፍታ የውዱን ነብይ ﷺ ሀገር የሚያስታውስ ልብ አነሳቸው፡፡ አባታቸውን እንኳን የሳር ቤቱን አፍርሰው በጭቃ ቤት ከመተካት ውጪ በሌላ አላስታወሱም፡፡እሱም የታወሳቸው ለአረፋ ገጠር ሲገቡ አልመች ብሏቸው ነው፡፡ ለራሳቸው ምቾት! ገንዘብ እንኳን ነበር … ልብ ጠፋ፡፡ ቴፑ የጎረሰውን የሲቃ ድምፅ ይተፋል፡፡ ሽማግሌው ሰው አብረውት በናፍቆት ይነፋረቃሉ፡፡ የማይቆረጥ ጥም ሆኖባቸው ይብሰለሰላሉ! ‹‹አቤት ባየውህ ማሳዘኔ፣ ይህ ጎጆ ሲል ወና፣ ይፅናናብኛል ታማሚ፣ ህመሜን ያይና፡፡ ውዴ የቀልቤ ጀምበሩ፣ ፋኖስም ሻማዬ፣ ሳስብ ለዑመት መቅለጥሁን፣ ጠናኝ በሽታዬ፡፡ ባልመልስም ውለታሁን፣ እኔም በተራዬ፣ ከጥልቁ ቀልቤ ምንጩ ስር፣ ያንቱ ነው እንባዬ፡፡ ሰላቱሏህ ሰላሙሏህ፣ አላ ኑሪል ቁሉብ፣ ሙሀመዲን ወአሊሂ፣ ሃባኢቢል መህቡብ!›› ያኔ ሚስታቸው በህይወት ሳለች … ናፍቆታቸውን ያወጓት ነበር፡፡ ደጉን ሰው መናፈቃቸውን ይተርኩላት ነበር፡፡ እሷም አትሰለችም፡፡ አፏን ከፍታ ታደምጣቸዋለች፡፡ ጠዋት ቁርስ እየበሉ ድንገት ተነስተው ወደ በሩ ይኼዱና ‹‹ሀቢቢ ናፈኬም … ምሽራና!›› ይላሉ፡፡ ‹‹አይዞዎት ቢትወደድ … ጎይታ የስደኸ፡፡›› ታፅናናቸዋለች፡፡ ‹‹ምሩ አቴርኸም … ቀብራቸውን ሳልዘይር መሞቴ ሆነ እኮ!›› ‹‹ጎይታ የፈዘዘ ቃር አሰበንኸምታ ይኽርሸ፡፡›› ልታረጋጋቸው ትሞክራለች፡፡ አሁን አፅናኛቸውም አፈር ከተንተራሰች ቆየች፡፡ ጠዋት ተነስተው ‹‹ሀቢቢ ናፈቁኝ … ምሽራና!›› የሚሉት እንኳን ሰው የላቸውም፡፡ በራቸው ስር ተቀምጠው ለቅሷቸውን የሚያለቅስላቸውን ድምፅ ከቴፑ ያደምጣሉ፡፡ ቴፓቸው ባትሪ ድንጋይ ሲያልቀው ወለላዬን የተቋረጡ ይመስላቸዋል፡፡ ሳይውል ሳያድር ከተማ ሰው ይልካሉ … ሰውም ከጠፋ ራሳቸው በደከመ ጉልበታቸው ተጉዘው የቴፓቸውን ቀለብ ይገዛሉ፡፡ ዛሬ ከጠዋት ጀምሮ ለየት ያለ ስሜት እየተሰማቸው ነው፡፡ ደሞ እንደመቁረጥም ያደርጋቸዋል፡፡ በጠዋቱ ምግብ ስላልቀመሱ ከሆነ ብለው አሰቡ፡፡ እሳት አቀጣጥለው ከምድጃቸው ላይ ቆጯቸውን መጥበስ ጀመሩ፡፡ የታለበ ወተት ስላላቸው … ቆጮው ከተጠበሰ … በወተት ከበሉ ይበቃቸዋል፡፡ ምግብ እንደ ድሮ አይደሉም፡፡ ሚስታቸው እያለች ደህና እየተከታተለች ታበላቸው ነበር፡፡ ቴፑ ሲቃውን ቀጥሏል፡፡ ከውጋታቸው ጋር እየታገሉ … ቆጯቸውን እየጠበሱ … ልባቸው ግን ቴፓቸው ላይ ነው፡፡ ‹‹ነፍርቄ እንጂ አልፃፍኩልሆም፣ አንዷንም ደብዳቤ፣ እያቃሰትኩ በጤናዬ፣ እየመታ ልቤ፡፡ ምነው ግርዶ ቢገልጡልኝ፣ ሲብስ መንገብገቤ፣ ብንደፋደፍ እግርሁ ስር፣ ሀይባሁን ተስቤ፡፡ ንገስበት በዓለሜ፣ ባሻህ ተዘናፈል፣ ለቅሶ የሰራውን ባህሬን፣ በበትርህ ክፈል፡፡ ሙሳዬ ነህ አንተው ዒሳ፣ ካንተ እንዴት ይገፈል፣ መሻሪያም ነህ መታመምያ፣ ምን ባታውቅም በደል፡፡ ሰላቱሏህ ሰላሙሏህ፣ አላ ኑሪል ቁሉብ፣ ሙሀመዲን ወአሊሂ፣ ሃባኢቢል መህቡብ!›› ወጣት ሳሉ ልጆቻቸውን አቀማጥለው አሳድገዋል፡፡ የአካባቢው ማህበረሰብ ከሚያሳድግበት መንገድ የተሻለ አድርገው እንጂ አጉድለው አላሳደጉም፡፡ ስለ ውዱ ነብይ ﷺ ፍቅርም ነግረዋቸዋል … ከንግግርም በላይ በተግባር ልጆቻቸው መንሰፍሰፍን ከአባታቸው ላይ አይተዋል፡፡ ግን ከተማ ከገቡ ወዲያ ገንዘብ እንጂ ሙሀባ ጠፋቸው፡፡ ሳንቲም ከእጃቸው ሳይጠፋ የአባታቸውን ናፍቆት መቁረጥ ተረሳቸው፡፡ ቆጯቸውን ለመንከስ ሲሞክሩ አምልጣ ከእጃቸው ወደቀች፡፡ እርሳቸውም  ጉልበት ከድቷቸው ወደ ጎን ተፈነገሉ፡፡ ምናልባት ይህች ቆጮ ከርዝቃቸው ላይ አልተከተበችም ይሆናል፡፡ የተፃፈላቸውን ርዝቅ በልተው ስለጨረሱም ሊሆን ይችላል፡፡ የልብ ምታቸው ፈጠነባቸው፡፡ አተነፋፈስ ጠፋቸው፡፡ ይህችን ምድር እንዳሰቡት የውዱን ነብይ ﷺ ሀገር ሳይዘይሩ እየለቀቋት መሆኑ ገባቸው፡፡ በልጆቻቸው የማዘን ስሜት ውስጣቸውን በላው፡፡ ሩሀቸው ጎሮሯቸው ላይ ደረሰች፡፡ ጆሯቸው እየሞቱም ቴፑ ላይ ተቀስሯል፡፡ ‹‹የአሚነቱ ያሲን ጠሀ፣ የናፍቆቴ ውሀ፣ ትውስታሁ የአህባብ ቀለብ፣ የሩህ ጅስሙ ረሀ፡፡ ያዕቁቡህ ነኝ ሆነው ዩሱፍ፣ የጀማሉ ዱሀ፣ ግንስ ያንቱ ውበትሁ፣ ያለፈው ሙንተሀ፡፡ ሰላም ላይኑህ ዐይነ ኩሌ፣ ለተጠማው ዓይኔ፣ ሙሂቡህ ሚስባህ ይልኋል፣ ጌጤ መኮንኔ፡፡ ትዝ ሲለኝ በድሬ ወጅሁ፣ አልተኛም በጎኔ፣ እንደነኚህ ባልሆንሁም፣ ላንብብሎ እኔ፡፡ ሰላቱሏህ ሰላሙሏህ፣ አላ ኑሪል ቁሉብ፣ ሙሀመዲን ወአሊሂ፣ ሃባኢቢል መህቡብ!›› አመሻሹን እረኛቸው ከብቶቹን ለመመለስ ወደ ቤታቸው ጎራ አለ፡፡ ‹‹ቢትወደድ …›› መልስ የለም፡፡ ‹‹ቢትወደድ …›› ዝም … ጭጭ! ነገሩ አላማረውም፡፡ ወደ ጎጇቸው ዘለቀ፡፡ እኒያን የውዱን ነብይ ﷺ አፍቃሪ መሬት ላይ ተከንብለው አገኛቸው፡፡ ቴፓቸው ብቻዋን ትስረቀረቃለች፡፡ ጮኸ፡፡ ‹‹እዮ እዮ … አባኖ አባኖ … እዮ እዮ እዮ … አባዎ …›› ቀርቦ ትንፋሻቸውን አረጋገጠ፡፡ ሲነካቸው ቀዝቅዘዋል፡፡ ጩኸቱን ካቋረጠበት ቀጠለ፡፡ ‹‹ቢትወደድ ሞተም … ባሪቀንዳ ሞተም … አትሻካቸንዳ ሞተም … የጎይታ ሰብ ሞተም!›› ጩኸቱን እያቀለጠ ከቤት ወጣ፡፡ የቀዬው ሰው ‹‹እዮ እዮ … አባኖ አባኖ …›› እያለ ተሰበሰበ፡፡ ብቻቸውን መሆናቸው የሁሉንም አንጀት ይበላቸው ነበር፡፡ በተወሰነ ጊዜ ልዩነት ቡና እየያዙ ወደ ቤታቸው ጎራ እያሉ ያጫውቷቸዋል፡፡ የብቸኝነታቸውን ዳገት ሊያዋጧቸው ሞክረዋል፡፡ እንደፈሩት … ውሀ እንኳን የሚያቀብላቸው ሰው ከጎናቸው ሳይኖር ተፈነገሉ፡፡ ከዱንያ ተቆራረጡ፡፡

የዛሬውን ልብወለድ የምለቀው በፅሁፍና በድምፅ ነው። ድምፁን እየሰማችሁ ፅሁፉ ላይ ብትከታተሉት የተሻለ የሚሆን ይመስለኛል። እንደዚያ ሞክሩት! እንጉርጉሮ ስላለው በፅሁፍ ብቻ ካነበባችሁት ስሜቱን እንዳታጡት ብዬ ነው። ሁለቱንም 12:00 ሲል እለቃለሁ። 🥰 . @Fuadmu

ዛሬ በተለመደው ሰዓት ባለ አንድ ክፍል ልብወለድ አለኝ 🥰 12:00 ላይ 🥰 . @Fuadmu

ገደልሽኝ... ጨረስሽኝ! ግጥም በፉአድ ሙና 🥰 . @Fuadmu

3 ቀናት ብቻ ቀርተዋል! የሀምሌ ሰርፕራይዛችን ይፋ ሊደረግ ቀርቧል። በደንብ እናስተዋውቀው ወገን 🥰 . @Fuadmu
3 ቀናት ብቻ ቀርተዋል! የሀምሌ ሰርፕራይዛችን ይፋ ሊደረግ ቀርቧል። በደንብ እናስተዋውቀው ወገን 🥰 . @Fuadmu

ማለት ነው፡፡ደራሲው በዚህ ውስጥ መጠቀም ያለበትን በአግባቡ ሳይጠቀም በቀጣይ መፅሀፍ የማሳተም ሞራሉ ይሞታል፡፡ የህትመት ወጪ ጎሮሮውን እየረገጠው ስንት ደራሲ ያሳተመውን መፅሀፍ መሸጥ አቅቶት በኪሳራ ከጨዋታ ውጪ ሆኗል፡፡ በርካቶች መፅሀፋቸውን አቅፈው ተቀምጠዋል፡፡ በዚህ መሀል መፅሀፉ በፒዲዔፍ ተሰራጨ ማለት ጨዋታው አለቀ … ኪሳራ ማለት ነው፡፡ ያለ ደራሲው ፈቃድ የተለቀቀ ፒዲኤፍ በምታነቡበት ሰዓት የተሰረቀ ምግብ እየበላችሁ መሆኑን እወቁ፡፡ ክብራችሁን አይመጥንም፡፡ በቻላችሁት መጠን በገንዘባችሁ ግዙ፡፡ ደራሲው ይበረታታል፡፡ በተለይ አሁን ደግሞ የህትመት ዋጋ ቢቀርስ በሚያስብል ደረጃ ጣራ ስለነካ መፅሀፍ በመግዛት ደራሲዎችን አበረታቱ፡፡ ደግማችሁ ፒዲኤፍ እንዳትጠይቁኝ አደራ! በጥቅሉ የተጠየቁትን ጥያቄዎች ለመመለስ ሞክሬያለሁ፡፡ በቀጣይ ደግሞ ሀሳቦቻችሁን እንደ ግብዓት ወስጄ አሻሽዬ ለመምጣት እሞክራለሁ፡፡ እወዳችኋለሁ! ከጥልቅ መውደድ ጋር! ፉአድ ሙና የማይነበብ ፊርማ . @Fuadmu

የጥያቄዎቻችሁ ምላሾች (ፉአድ ሙና) . ማለፊያ ልብወለድን በተመለከተ ከቀረቡት ጥያቄዎች ውስጥ በቀጥታ ከልብወለዱ ጋር የሚገናኙትን እንዲሁም ቢመለሱ መልካም ነው ያልኳቸውን ጥያቄዎች እንደሚከተለው መልስ ሰጥቼባቸዋለሁ፡፡ 1. ልብወለዱ ላይቭ ፊክሽን እንደመሆኑ ኮመንት ላይ የሚፃፉ ነገሮችን እንደ ግብዓት ተጠቅመህ ታውቃለህ ወይስ ሆን ብለህ ኮመንት ላይ አድርግ ከተባልከው በተቃራኒው ታደርጋለህ? አስተያየት መስጫው ላይ በአንባቢዎች የሚሰጡ አስተያየቶች አንባቢዎቼ ፅሁፌን እንዴት እየተረዱት እንደሆነ ስለሚያሳዩኝ ለፅሁፉ በጣም ጠቅመውኛል፡፡ ለምሳሌ ብንወስድ ስለ አብደላ ሁለተኛ ሚስት ማግባት በተፃፈበት ጊዜ አብዛኛዎቹ ሴት አንባቢዎቼ ከውሰር አብደላን እንድትገድለው የሚደግፍ ወይም እነሱ ቢሆኑ እንደሚገሉት የሚያሳይ አዝማሚያ ያላቸው አስተያየቶችን ሲሰጡ ተመለከትኩ፡፡ ይህ ከመጀመሪያ የያዝኩት አላማ ባይሆንም እነሱ እንደሚሉት ከውሰር ልትገድለው ብትሞክር ምን ሊፈጠር እንደሚችል ማሳየትና ህይወታቸው ላይ ይህን ውሳኔ እንዲከልሱት ማድረግ እንዳለብኝ ተሰማኝ፡፡ የከውሰር መታሰርም ሆነ ባሏን ለመግደል መሞከር የአንባቢዎቼን አስተያየት ተመልክቼ ለማስተማር ያካተትኩት እና የታሪኩን ፍሰት የቀየርኩበት እንጂ መነሻ ሀሳቤ ሙሉ ለሙሉ ቤተሰብን አልፈን ስንሄድ ሊፈጠር የሚችለውን መጥፎ ነገር ሲሀምን በመጉዳት ማሳየት ላይ ያተኮረ ነበር፡፡ 2. ማለፊያ ለምን አልከው? ልብወለዱ አንድ ሀሳብ ላይ ብቻ ከማተኮር ይልቅ በተለያዩ ሀሳቦች ውስጥ እንዲያልፍ በማሰብ የተጠናቀረ ስለነበር ነው፡፡ የሆነውም እንደዛው ነው፡፡ በማለፊያ በርካታ ሀሳቦች ውስጥ አልፈናል፡፡ 3. አጨራረሱ ላይ ከውሰር ላይ ለምን በረታህ? አምረላህንስ አልተለሳለስክለትም ወይ? በተቻለኝ መጠን የታሪኩ ድምዳሜ ላይ ማሳየት የፈለግኩት በእውነታው ዓለም ላይ ሊሆን የሚችለውን ነው፡፡ እንደ አምረላ አይነት ሰዎች ይጎዳሉ እንጂ እነሱ በቀላሉ አይጎዱም፡፡ ያጠፋሉ እንጂ አይጠፉም፡፡ እንደ ከውሰርና ሲሀም ያሉ ሴቶች ግን የመከራን ገፈት ይቀምሳሉ፡፡ በተለይ አሁን ባለንበት ተጨባጭ ወንድ ሆነው ደረታቸውን ነፍተው ሚስት እንዳላቸው አሳውቀው ከሚያገቡ ጨዋ ወንዶች ይልቅ እንደ አምረላና አብደላ አይነቶቹ በርካታ ሴቶች ላይ ጉዳት እያደረሱና የገፈቱ ቀማሾች ደግሞ በታሪኩ ላይ እንደተመለከትነው ሴቶቹ እየሆኑ በመሆኑ ያንን ለማሳየት ያደረግኩት ነው፡፡ ከውሰርን ከእስር አስፈትቶ ድጋሚ ከአብደላ ጋር አብሮ ማኖር በጣም ቀላሉ ነገር ነበር፡፡ ግን ከእውነታው ዓለም ጋር በጣም ይጣረሳል፡፡ እንደ አምረላ ያለ ሰው የእጁን አኼራ ላይ ማግኘቱ አይቀርም፡፡ 4. ምክንያትና ውጤትን በተመለከተ ይኼ ብዙ ተመሳሳይ ጥያቄዎች በታሪክ መዋቅሩ ውስጥ የተጠየቁትን አንድ ላይ ለመመለስ የፈጠርኩት አርዕስት ነው፡፡ በታሪኩ ውስጥ ያሉት ድርጊቶች በእውነታው ዓለም እንዳሉ እርግጠኛ የሆንኩባቸው ናቸው፡፡ ለምሳሌ የሲሀምን ከዚያ ሁሉ ነገር በኋላ ወደ አብደላ መመለስ … የከውሰር መበደል … መቆጣት … የአምረላ ተፅዕኖ … ሳይናገሩ ማግባት … ሲታወቅባቸው መፍታት ስራቸው ሁሉ ሳይቀር … በእውነታው ዓለም በደንብ ገጦ የሚታይ ነው፡፡ አንዳንዶቹ ስም ተቀየረላቸው እንጂ የእኔ ታሪክ የሚሏቸው ሰዎች አሏቸው፡፡ 5. የሴቶችን ህይወት ሁሌ ለምን ታከብዳለህ? የሴት ልጅ ህይወት ትንሽ መንሻፈፍ ሲገጥመው ብዙ ይጎዳል፡፡ የማከብደው በትንሹ ህይወታችሁ ችግር ውስጥ ሊገባ ስለሚችል አረማመዳችሁን እንድታስተካክሉ ለማጠንቀቅ እንጂ ለሌላ አይደለም፡፡ 6. ስልጤ ገፀ-ባህሪ የልብ-ነገርና እዚህ ላይ በመጥፎ ወክለሀል ለምንድነው? የልብነገር ላይ በመጥፎ አልወከልኩም፡፡ አንድ አፍቅራ የተሳሳተች ቆንጅዬ ሴት መጥፎ መባል የለባትም፡፡ ሲጀመር የአዲስ አበባ ልጅ ናት … ኢክራም ቤብ! በጥቅሉ ግን ስልጤ ሙሉ ለሙሉ ሙስሊም ማህበረሰብ እንደመሆኑ ውክልና ከማካተት አንፃር ነው፡፡ እኔ በልብወለድ ብቻ ሳይሆን በግጥምም በርካታ ቋንቋዎችን እጠቀማለሁ፡፡ ከዚህ ቀደም ኦሮምኛ፣ ትግርኛ፣ ሱማልኛ፣ አረብኛ፣ እንግሊዘኛ ቋንቋዎችን ተጠቅሜያለሁ፡፡ የሁለተኛ ሚስትን ጉዳይ ደግሞ በስልጤ ማህበረሰብ ቢወከል ሙሉ ለሙሉ ሙስሊም እንደመሆኑ ከሌላው የተሻለ ተዓማኒነት ይኖረዋል ብዬ አስባለሁ፡፡ ሁለተኛ በማግባት የተሻለ ልምምድ ያለው ይመስለኛል፡፡ ስልጤ አንባቢዎቼ … እናንተ የኢስላም ባንዲራ ያዦች … እወዳችኋለሁ፡፡ ይኼ አቀሳሳሪ ጥያቄ ነው፡፡ በጥቅሉ ሙስሊም እንደመሆኔ በዲኔ እስካልመጣ ድረስ አንድን ብሔርን ነጥዬ ልጠላ አልችልም፡፡ ስልጤ ደሞ በዲን ጉዳይ ቤብ ነው፡፡ 7.  አብደላን ለምን መልዓክ አደረግከው? የሰው ልጅ ብዙ ጎኖች እንዳሉት ማሳየት ፈልጌያለሁ፡፡ ይህንን አፃፃፍ ከዚህ ቀደምም የልብ-ነገር ላይ ተጠቅሜዋለሁ፡፡ አብደላ አንድ ጥፋት ሰራ ማለት ሙሉ ለሙሉ መጥፎ ነው ማለት ላይሆን ይችላል፡፡ በሂደት ተፀፅቶ ለሚስቱም ጥሩ ባል ሆኗል፡፡ ህይወት ላይም አንዳንድ ሁለተኛ ዕድሎች መልካም ሰውን ይሰራሉ፡፡ 8. በነፃ ለማስነበብ ይህን ያክል ረዥም ልብወለድ ቁጭ ብሎ ለመፃፍ ሰብር ከየት ታገኛለህ? ከዛሬ ዘጠኝ አስር ዓመት ገደማ ጀምሮ በርካታ ልብወለዶችን አስነብቤያለሁ፡፡ በሰዎች ህይወት ላይ የሚፈጥሩት መልካም ነገር ሲኖር ከክፍያም በላይ ነው፡፡ አንዳንዴ መጥፎ አሻራ ካላቸውም ከባድ ነው፡፡ ውስጤ ያለ ነገር ስለሆነ ማስነበቡ ደስ ይላል፡፡ ግን በጣም ያስቀምጣል፡፡ ረዥም ሰዓት መቀመጥንና ማሰብን ይፈልጋል፡፡ የአንባቢዎችን ቀልብ ለመጠበቅ በሰዓቱ በቋሚነት ለማድረስ ኃላፊነት መውሰድን ይጠይቃል፡፡ ላያስችል አይሰጥም አይደል የሚባለው? ለዚያ ይመስለኛል፡፡ 9. ታሪኩን ለምን አሳጠርከው? ታሪኩ ማስተላለፍ የፈለገውን መልዕክት ከጨረሰ በኋላ ለታሪክ ፍሰት ብዬ ማስረዘምን አልፈለግኩም፡፡ ከምታስቡት በላይ ብዙ ገፅ አንብባችኋል፡፡ በየቀኑ ሲለቀቅ ትንሽ ቢመስልም ብዙ ነበር፡፡ ስለዚህ ዋናውን ግብ ከመታ እዚህ ላይ ማቆም የተሻለ እንደሆነ ስላሰብኩ ነው፡፡ 10. አንዳንድ ገፀ-ባህሪያት ለምን መጨረሻቸው አልተነገረም?  እንደ ሰላሀዲን፣ ምህረትና ቤቲ አይነቶቹ መሀል ላይ ለምን ተረሱ? ሰላሀዲን ያስፈለገበትን ድርጊት ፈፅሞ ከሲሀም ጋ ስለተለያየ ለታሪኩ አስፈላጊ አልነበረም፡፡ መመረቁ ስለተነገረ ከዚህ በኋላ ለአንባቢ የሚያስፈልግ ታሪክ የለውም፡፡ ቤቲና ምህረትን መጥፎ ነገር ላይ ወድቀው እንዳሳይ የጠበቃችሁ ነበራችሁ፡፡ ግን እሱን በሰፊው የሂባዋ ናርዶስ ላይ ስለሰራነው እዚህ ላይ ዋና ገፀ ባህሪ ባልሆኑ ሰዎች ማሳየት አልፈለግኩም፡፡ ሁሌም ያረግዛሉ፣ በሽታ ይሸምታሉ ላይሆንም ይችላል፡፡ በተለይ ዶክተር ከመሆናቸው ጋር ያሉበት ውርደት ከቅጣት በኩል በቂ እንደሆነ ይሰማኛል፡፡ 11. ኢፋዳን ለምን በፒዲዔፍ አትለቅልንም? ይህ ጥያቄ በተደጋጋሚ አስተያየት መስጫ ላይ የታዘብኩት ስለነበር ለምን በዚሁ አልመልስም ብዬ አስቤ ነው፡፡ በጣም ብሽቅ የሚያደርገኝ ጥያቄ ነው፡፡ ምናልባት ካለማወቅ ከሆነ እስኪ ላብራራው! አንድ ደራሲ መፅሀፍ ለመፃፍ በተለይ ልብወለድ ከሆነ ከፍተኛ የአዕምሮ ድካም አለው፡፡ ለበርካታ ወራት መቀመጥ አለበት፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከፍተኛ ገንዘብ ያወጣል፡፡ ምናልባት ለረዥም ወራት ገና ለማሳተም ያወጣውን ገንዘብ ለማካካስ ይሆናል የሚሸጠው፡፡ ኢፋዳ ተፅፋ ተስተካክላ እስክትታተም ብቻ ከሶስት በላይ ዓመታት ፈጅታለች፡፡  የታተመውን መፅሀፍ 2000 ኮፒ ለመሸጥ ደግሞ ተጨማሪ ሁለት ዓመታት ወስዷል፡፡ በድምሩ አምስት ዓመታት