cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

የፊቅሪ ነገሪ

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدلم يتم تحديد اللغةالفئة غير محددة
مشاركات الإعلانات
230
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

❤️ፍቅር በዚህ መንገድ📖 😘ምዕራፍ ➊➊ ✍ደራሲ ዘሪሁን ገመቹ . . . ‹‹እቤት መዋል ስትጀምሪ ባለሞያ ወጥቶሻል›› አለ ሁሴን የቀረበለትን ምግብ በልቶ ጨርሶ እጁን እየታጠበ፡፡ ‹‹ባክህ ድሮም ባለሙያ ነኝ፡፡ በእጄ የተሠራውን ምግብ ለመቅመስ እድሉ ስላልገጠመህ እንጂ›› አለችው ትንግርት የተበላበትን ዕቃ አነሳስታ ከጨረሠች በኋላ ለሁለቱም ተጨማሪ ቢራ ጠረጴዛ ላይ በማስቀመጥ ፊት ለፊቱ እየተቀመጠች፡፡ ‹‹መጠጥ አሁንም አልተውሽም ማለት ነው›› ‹‹መተው አልተውኩም ግን በጣም ቀንሻለሁ፡፡ አንዳንዴ ሲያሠኘኝ ብቻ ነው ቀመስ የማደርገው›› ‹‹ይህቺ ቀመስ እራስን መሸወጃ እንዳትሆን?›› ‹‹አይመስልህ፡፡ አልፎ አልፎ መጠጣቱ ያን ያህል መጥፎ መስሎ ስላልተሰማኝ ነው እንጂ ለማቆም ከብዶኝ አይደለም፡፡ ጫት፣ ሲጋራ እና አንተን በአንዴ እርግፍ አድርጌ መተው የቻልኩ ሠው እኮ ነኝ፡፡›› ሁሴን በንግግሯ ፈገግ አለና ንግግሩን ቀጠለ ‹‹ እኔም ሱስሽ ነበርኩ ማለት ነው?፡፡ ለዛውም ከጫትና ከሲጋራ እኩል ውስጥሽን የምጎዳ መጥፎ ሱስ … ለማንኛውም እፈልግሃለሁ ብለሽ ያስጠራሸኝ ለምን እንደሆነ ለማወቅ ጓጉቻለሁ›› ‹‹ያን ያህል?›› ‹‹ከምትገምቺው በላይ፡፡ አንቺን መፍራት ከጀመርኩ ሠነበትኩ እኮ፡፡ ነገረ ስራሽ ሁሉ ተዓምራዊ ነው፡፡ የዛሬው ደግሞ ምን እንደሆነ ልስማዋ!›› ከመቀመጫዋ ተነሳችና ወደ መኝታ ክፍሏ እየተውረገረገች ገባች፡፡ አተኩሮ ተመለከታት ውበቷ ከቀድሞው በጣም የጨመረ መሰለው፡፡ አንዳንዴ የማያቃት አዲስ ሴት ትሆንበታለች፡፡ እርጋታዋ ያስፈራዋል፡፡ ብስለቷ ያስደነግጠዋል፡፡ በፊት ተሸፍነው የነበሩ ምርጥ ስብዕናዎቿ ዛሬ ጎልተውና አብበው መታየት ሲጀምሩ የማያውቃት ሠው መስላ ብትታየው ምኑ ይገርማል፡፡ ተመልሳ መጣችና አንድ አበጥ ያለ አሽግ ካኪ ወረቀት አቀበለችውና መቀመጫዋ ላይ ተመልሳ ተቀመጠች፡፡ ‹‹ምንድነው?›› ግራ በመጋባት ጠየቃት፡፡ ዝም አለችው ‹‹ልክፈተው?›› መልሶ ጠየቃት፡፡ ‹‹ምን አስቸኮለህ መጠጥህን ጨርሰህ ወደ ቤትህ ሄደህ ተረጋግተህ ታየዋለህ፡፡ ያን ያህል የሚያስቸኩል ጉዳይ አይደለም›› አሁኑኑ እቤቱን ለቆ ወጥቶ አሽጉን ለመክፈት እና ውስጡ ያለውን ዕቃ ምንነት ማወቅ ፈለገ፡፡ ደግሞም ስሜቱን እንደምንም ተቆጣጥሮ ሃሳቡን ቀየረ፡፡ ከእሷ አጠገብ መቀመጥ ከእሷ ጋር ማውራት ፈልጎል፡፡ አሁን ውድ ሆናበታለች፡፡ ሻይ ለመገባበዝ እንኳን እሷ በፈለገችና ባሰኛት ጊዜ እንጂ እሱ ሲፈልግ ሊያገኛት አይችልም፡፡ ስለዚህ ታግሶ ወደ ወሬው ተመለሠ፡፡ ‹‹… ያንን የጠየኩሽን ነገር ምን ወሠንሽ?›› ቢራውን ከነጠርሙሱ አንስቶ ተጎነጨና ጠየቃት ‹‹የቱን?›› ‹‹የሕይወት ታሪክሽን በጋዜጣዬ ላይ በተከታታይ አምድ ማሳተም እፈልጋለሁ ብዬሽ ነበር እኮ›› ‹‹አስታውሳለሁ .. ግን አልወሰንኩም›› ‹‹ብዙ ብር እኮ ነው የሚያስገኝልሽ .. የፈለግሽውን ያህል እከፍልሻለሁ›› የንዴት ፈገግታ ፈገግ አለች፡፡ ‹‹በቃ አንተ ከእኔ የምትፈልጋቸውን ነገሮች ሁሉ በብር ብቻ ነው ለመግዛት የምትጥረው፡፡ ፍቅሬን ወይንም ገላዬን በገንዘብ ስሸጥልህ ኖርኩ፡፡ ዛሬም ታሪኬን በገንዘብ ልሽጥልህ፡፡ ያን ያህል አታውቀኝም ማለት ነው?›› ሁሴን ባላሠበው መንገድ ስለመጣችበት ተሸበረ፡፡ ትንግርት የሕይወቷን አቅጣጫ ከተቀየረ ቡኋላ ያስተዋለባት አንድ ለውጥ ይሄ ነው፡፡ በፊት ሲያውቃት ቻይ፣ ሆደ ሠፊ፣ ማንኛውን ንግግር የማያስከፋት፤ ቢያስከፋትም መከፋቷን ሳትገልፅ በሳቅ ማሳለፍ የምትችል ነበረች፡፡ አሁን ግን የተለየች ሆናለች:: ‹‹እንደዛ ማለቴ አይደለም፡፡ ልዩ ታሪክ ስላላሽ ይሄ ታሪክ ደግሞ ተዳፍኖ መቅረት የለበትም ብዬ ስለማስብ ነው፡፡ እስቲ እንዲታተም ባትፈቅጂ እንኳን ለራስሽ ፅፈሽ አስቀምጪው::›› ‹‹ጽፌዋለሁ… በተለይ ባለፉት ሠባት አመት ያሳለፍኳቸውን በህይወቴ የተከሠቱ አንኳር ድርጊቶች በዲያሪዎቼ ላይ አስፍሬያቸዋለሁ›› ‹‹በቃ እኔ የፈለኩት ይሄን ነው፡፡ አየሽ ያልተጻፈ ነገር እየደበዘዘ ሄዶ ከእለታት አንድ ቀን መረሳቱ አይቀርም›› ‹‹አይዞህ የሚረሳ ነገር አይኖርም፡፡ መታተም አለበት ብዬ ስወስን ወደ አንተ ቢሮ እንደምመጣ ቃሌን እሠጥሃለሁ›› ‹‹አመሠግናለሁ፡፡ ቃልሽንም እንደምትጠብቂ አምናለሁ›› ብቻ አሁን አንድ ነገር ላስቸግርሽ ነው፡፡ መጀመሪያ እሺ በይኝ፡፡›› ‹‹ሳላውቅ እንዴት እሽ እልሃለሁ?›› ‹‹በቃ እሽ በይኝ፡፡ ማረግ የማትችይውን ነገር አልጠይቅሽም›› ‹‹ለማድረግ እኮ ማድረግ መቻል ብቻ በቂ አይደለም፡፡ ፍላጎትም ያስፈልጋል›› ‹‹ባክሽ ክርክሩን አቁመሽ እሺ በይኝ፡፡›› ‹‹ውጪልኝ እንዳትለኝ እንጂ ለሌላው ችግር የለም›› ትክዝ ብሎ ሃሳብ ውስጥ ገባ፡፡ እራቁት ገላዋ፣ ቅብጠቷ፣ የወሲብ ብቃቷ በዓይነ ህሊናው ተመላለሰበት፡፡ ከት ብላ ሳቀችና ‹‹ ተነቅቶብሃል፡፡ በፍፁም እሺ አልልህም፡፡የእሱ ጉዳይ ተዘግቶ ፋይሉ ወደ መዝገብ ቤት ተመልሷል›› አለችው፡፡ ‹‹ግምትሽ የተሳሳተ ነው፡፡ እርግጥ ፍላጎቱ የለኝም ብዬ ልዋሽሽ አልፈልግም፡፡ በጣም ተርቤሻለሁ፡፡ አሁን ቃል ግቢልኝ ያልኩሽ ግን ለእሱ አይደለም›› ‹‹ለእሱ ካልሆነ ቃሌን ሠጥቼሃለሁ፡፡ ጠይቀኝ›› ጉሮሮውን በመጠኑ ካረጠበ በኋላ ‹‹ከዲያሪሽ ላይ የአንዱን ቀን ውሎሽን እንድታነቢልኝ እፈልጋለሁ›› ‹‹መቼ?›› ‹‹አሁን ነዋ›› ‹‹አይሆንም .. አይሆንም .. ሌላ ጊዜ›› ‹‹ቃል ገብተሸል›› እንደማሰብ አለችና ‹‹እሺ... ምን ቸገረን.. ስለምንድነው መስማት የምትፈልገው? የዩኒቨርስቲ የህይወት ገጠመኜን፣ የቡና ቤት ህይወት ገጠመኜን .. የቱን? ‹‹ደስ ያለሽን ግን ስለ ቡና ቤት ቢሆን እመርጣለሁ›› ወደ መኝታ ቤቷ በመሄድ ስለ ቡና ቤት የሕይወት ገጠመኟ ካሰፈረችባቸው ድያሪዎቿ መካከል አንዱን መዛ ወደ ሣሎን በመመለስ መቀመጫዋ ላይ ቁጭ አለች፡፡ ‹‹እንግዲህ አዚህ ዲያሪ ላይ ከተፃፈው የአንዱን ቀን ውሎዬን ወይም አዳሬን አነብልሃለሁ፡፡ ግን መርጬ አይደለም፡፡ ዝም ብዩ እከፍተዋለሁ፡፡ አነብልሃለሁ፡፡›› ‹‹ተስማምቻለሁ›› አለ በጉጉት ተስተካክላ ተቀመጠችና ዲያሪዋን ከፈተች ወደ መሃከል ገደማ ነው፡፡ ርዕሱን አነበበች ‹‹40 ፐርሰንት›› ይላል ይሄንንማ አላነብልህም በጣም ይሰቀጥጣል፡፡ ‹‹እድሌ ነው አንብቢልኝ›› ‹‹በናትህ ደባሪ እኮ ነው›› ‹‹ምንም ቢሆን ምንም መስማት እፈልጋለሁ›› እሺ ምን ቸገረኝ በማለት ማንበብ ጀመረች ሚያዚያ 20/2002 ‹‹40 ፐርሰንት›› ቀድሞ ገባ፡፡ ተከተልኩት፡፡ የቤርጎው ስፋት መታጠቢያ ክፍሉን ሳይጨምር አራት በሦስት ይሆናል፡፡ የከፈለኝ የጠየኩትን ያህል ብር ነው፡፡ ዝምተኛ፣ ጭምትና የከፋው ቢጤ ነው፡፡አንድ የተለየ ነገር አይታጣባቸውም ብዬ ስለማስብ ከእንዲህ ዓይነት ወንዶች ጋር ማደር ደስ ይለኛል፡፡ የቤርጎውን በር ከቀረቀርኩ በኋላ ወደ ውስጥ ዘለኩ፡፡ ቀድሞኝ አልጋው ላይ ጋደም አለ ከነልብሱ፡፡ እኔም በእጄ ይዤ የነበረውን ኮንዶም ኮሞዲኖው ላይ ጣል አድርጌ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመ
إظهار الكل...
​​ተሠናብቷት ወጣ፡፡ እሷም በተቀመጠችበት በስስት በሚንከራተቱ አይኖቿ ሸኘችው፡፡ የሠጠችውን ፖስታ ለመቅደድ እቤቱ እስኪደርስ አላስቻለውም፡፡ ከሠፈሩ ትንሽ ወጣ እንዳለ ነበር ወደ አንድ ሆቴል ጎራ በማለት መኪናውን አቁሞ ከውስጥ ሳይወጣ የከፈተው፡፡ የሚያየው ነገር ግራ ገብቶታል፡፡ አንድ ወረቀት እና መዓት ብሮች! ባለ መቶ፤ ሃምሳ እና አስር ብር በየመጠናቸው ለየብቻ በብር ላስቲክ ተጠፍንገዋል፡፡ አንድ ወረቀት አብሮ አለ፡፡ አወጣና ማንበብ ጀመረ፡፡ አንተን ከመጀመሪያ ጀምሬ የቀረብኩህ ሸርሙጣ ስለሆንኩ ሳይሆን ስለማፈቅርህ ነው፡፡ ብር የምቀበልህ ከአንተ ፍቅር እንደያዘኝ በፍፁም እንድታውቅ ስለማልፈልግ ነበር፡፡ ከተጠቀምኩትማ ፍቅር ሳይሆን ሽርሙጥና ይሆናል እና ለሁለት ዓመት ደንበኛዬ ነበርክ፡፡ በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ሠላሳ ዘጠኝ ቀን አብረኸኝ አድረሃል፡፡ ከዚህ ውስጥ አስራ አምስቱን ቀን ብር ስላልነበረህ አልከፈልከኝም፡፡ ለዘጠኝ ቀን -› 300 ብር ከፈልከኝ -› 300x9 -› 2700 ብር ይሆናል አስራ ሁለት ቀን -› 200 ብር ከፈልከኝ -› 200x12 -› 2400 ብር ይሆናል ሦስት ቀን -› 150 ብር ነው የከፈልከኝ -› 150x3 -› 450 ብር ይሆናል፡፡ እንግዲህ በድምሩ አምስት ሺ አንድ መቶ ሃምሳ ብር መሆኑ ነው፡፡ ይሄ ብር እንግዲህ ለመውጫ የምትከፍለውን ሃያ ሃያ ብር አያጠቃልልም፡፡ ቸው ይላል፡፡ አንብቦ ሲጨርስ ወረቀቱን ጨምድዶ አፉ ውስጥ ከተተው፡፡ ይቀጥላል ╔═══❖•🌺🌸•❖═══╗ @fikerdertogada ╚═══❖•🌺🌸•❖═══╝ 4 any comment @fikerdertogada_bot ❥............🍃🌹🍃..............❥
إظهار الكل...
❤️ፍቅር በዚህ መንገድ📖 😘ምዕራፍ ➊❷ ✍ደራሲ ዘሪሁን ገመቹ . . . ሠዓቱ ከምሽቱ 2፡30 ሆኗል፡፡ ሠሎሞንና ኤደን ቦሌ በሚገኘው ታዋቂው አቢሲኒያ ሬስቶራንት እራት በአክሱማይት ወይን እያወራረዱ በመመገብ ላይ ናቸው፡፡ የተገናኙት በቀጠሮ አልነበረም፡፡ ሁለቱም በጋራ የሚያውቁት ሠርግ ላይ በመታደማቸው ነበር ድንገት የተገጣጠሙት፡፡ ሠሎሞን እንደ ወትሮው ሙሉ ሱፍ ከሠማያዊ ሸሚዝና ጥቁር መደብ ኖሮት በነጭ መስመር ከተዥጎረጎረ ክራባት ጋር ለብሶ ሙሽራ ባይሆንም ሚዜ መስሏል፡፡ ኤደንም ከሱ ባልተናነሰ ሁኔታ ዘንጣለች፡፡ ጥቁር ቀለም ያለው ከጉልበቷ በላይ የሚቀር ጉርድ ቀሚስ ለብሳለች፡፡ከላይ ከሠውነቷ ጋር የተጣበቀ ሮዝ ከለር ያለውና የጡቷን ቅርፅ አጉልቶ የሚያሳይ በተጨማሪም ግማሽ የሚሆን የጀርባዋን ክፍል አጋልጦ የሚያሳይ ‹ፓክ አውት› ለብሳለች፡፡ ጆሮዋ ላይ ያንጠለጠለችው ጌጥ አርቲፊሻል ቢሆንም ለውበቷ የራሱ የሆነ ድርሻ ነበረው፡፡ በፊትም ጎላ ጎላ ብለው ሚታዩ አይኖቿን በስሱ ተኩላቸው ይበልጥ ቀልብ ሳቢ ሆነዋል፡፡ የፀጉር አሠራሯም ልዩ ነው፡፡ ‹‹ቬሎ ስላለበሽ ነው እንጂ ሙሽራዋ እኮ አንቺ መስለሽኝ ነበር፡፡›› ‹‹ኸረ ባክህ! ለእንደዛማ አይነት ወግ መች ታደልን›› ‹‹ምን ማለት ነው?›› አላት ሠሎሞን በግራ እጁ አንገቱ ላይ የተሸመቀቀውን ክራባት እያላላ፡፡ ‹‹እብድ አፍቅረን ከእሱ ጋር ስንጃጃል ውዱ ጊዜያችን በከንቱ አልፎ በፈነዳንበትም ወቅት የነበረንን አንፀባራቂ ውበት መጠቀም አቅቶን ዛሬ ከጠወለግን ቡኃላ ካንቀላፋንበት ስንባንን ረፍዶብን አገኘነው፡፡ ምን ማድረግ እንችላለን፡፡ አረጀን! ማን ይፈልገናል ያው ቆመን መቅረታችን ሳይሆን ይቀራል?›› በትካዜ ከምግቡ ቆንጠር አድርጋ ወደ አፏ ላከች፡፡ ሠሎሞን መናገር ጀመረ ‹‹ለመሆኑ እቤትሽ ፊትሽን የምትመለከቺበት መስታወት የለሽም እንዴ? የአስራ ስድስት አመት ልጃገረድ ነኝ ብትይ እኮ ማንም የሚጠረጥርሽ አይኖርም ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ ሆኖ ነው እንጂ መች ላንቺ የሚሆን ባል ጠፋ ብለሽ ነው … ለማንኛውም ምግቡን ብይ›› ‹‹ባክህ በቃኝ›› ‹‹ምነው? መች ተነካና›› ‹‹ግድ የለህም ይብቃኝ ባይሆን ወይኑን እደጋግማለሁ፡፡›› ‹‹ኸረ ይቻላል! በስንት ወራችን እኮ ነው የተገናኘነው፡፡ ዛሬማ መላቀቅ የለም›› ‹‹ተስማምቼያለሁ›› አለች ኤደን የወይን ብርጭቆዋን አንስታ እየተጎነጨችለት፡፡ሠሎሞን የዘወትር ገረሜታው አሁንም እንደገና አገርሸቶበት የኤደንን ውበት በጎሪጥ እየቃኝ በውስጡ ያብሠለሠላል፡፡ ‹‹የሠው ፍላጎት እንዴት ነው? ይህቺን የመሠለች ውብ እና አፍቃሪ ሴት ገፍቶ እንዴት የማያውቀውን ሴት አፍቅሬያለሁ ብሎ ይሄን ያህል ይሠቃያል፡፡ እዚህ አጠገቤ ያለችው ኤደን ምን ይጎላታል? መልክ አላት፣ ፀባይ አላት፣ ብር አላት … ከዚህ በላይ ምን ማሟላት ይጠበቅባታል?››ከወራት በፊት ስለዚህ ጉዳይ ሁሴንን ጠይቆት የመለሠለት መልስ ትዝ አለውና ፈገግ አለ፡፡ ‹‹ወረት ነው አይደል እንዲህ የሚያንቀዠቅዠህ አጠገብህ በጣም የሚያፈቅሩህ ሴቶች እያሉልህ አንተ ሌላ ፍለጋ ምትሠቃየው?›› የሚል ጥያቄ ነበር ያቀረበለት፡፡ ‹‹ትክክለኛ ሄዋኔን ፍለጋ ላይ ነኝ›› ብሎ መለሠለት ‹‹ታዲያ እነሱስ ሄዋንህ መሆን አይችሉም?›› ‹‹አይመስለኝም፡፡ አየህ የሠው ልጅ አፈጣጠርን መለስ ብለን ስንመለከት እግዚአብሔር መልኩን ወይም መሠሉን ማየት ፈለገና ጭቃ አድቦልቡሎ እስትንፋሱን እፍ አለበት እና አዳምን ፈጠረው፡፡ ልብ በልልኝ ለአዳም መፈጠር ዋናው ምክንያት እግዚአብሔር በአዳም ውስጥ የራሱን መልክ ለማየት ስለፈለገ ነበር፡፡ቆየት አለና አዳም ደበረው፡፡ በብቸኝነቱ አጉረመረመ፡፡ እግዚአብሔርም ሠማው፡፡ እንቅልፍ ጣለበት እና ከግራ ጎኑ አንድ አጥንት መዘዘና ሄዋንን አበረከተለት፡፡ የሄዋን የመፈጠር ምክንያት ደግሞ ምንድነው ብትለኝ የአዳም ድብርት ውስጥ መግባት ነው፡፡ አዳም ባይደብረው እግዚአብሔር ሄዋንን ለመፍጠር ሃሳብ አይመጣለትም ነበር፡፡ወደ ነጥቤ ልመልስህ እና በእያንዳንዱ አዳም የግራ ጎን ከእኔ እና ከአንተም ጭምር እግዚአብሔር አንድ አንድ አጥንት ወስዶ አንድ አንድ ሴት ፈጥሮልናል፡፡ ፍቅር የሚባለው ነገር ምን እንደሆነ ታውቃለህ ያለ ፍቃድህ ከግራ ጎንህ በእግዚአብሔር የተወሠደብህን የራስህን አጥንት ለማስመለስ የምታደርገው ውጣ ውረድ ነው፡፡ ታዲያ ብዙውን ጊዜ ፍቅር እንከን የተሞላ የሚሆነው ለምን እንደሆነ ታውቃለህ፡፡ክህደት፣ ውስልትና፣ ፍቺ የመሳሰሉት ለምን እንደሚከሰቱስ ይገባኻል? እንዷን በአጋጣሚ ትቀርባታለህ፡፡ ይህቺ ከእራሴው አጥንት የተሠራች ነች ብለህ ትወስናለህ ፡፡አፈቀርኩሽ ትላታለህ፡፡ ታገባታለህ፡፡ አሁን ሙሉ ሠው ነኝ ሙሉ አካልም አለኝ የተወሠደብኝን የግራ ጎኔን መልሻለሁ ብለህ ትኩራራለህ፡፡ ጥቂት ቆይቶ ግን ያ አጥንት ካንተ ጎን የተወሠደ ሳይሆን ከሌላ አዳም ጎን የተወሠደ ሆኖ ይገኛል፡፡ ያ ማለት አጥንቱ አንተ ላይ በትክክል ገብቶ አይገጥምም ማለት ነው፡፡ ወይ ይሠፋል አሊያም ይጠባል፡፡ ወይ ያጥራል ወይ ደግሞ ይረዝምብሃል፡፡ ያ ደግሞ ምቾትህን ይነሳሃል፡፡ በሽተኛ ያደርግሃል፡፡ ይቆረቁርሃል፡፡ ይጎረብጥሃል፡፡ በመጨረሻ ስቃዩ ሲበዛብህ ያ ቦታ እንደድሮ ባዶ ቢሆን ይሻለኛል ብለህ ትወስናለህ፡፡ አውጥተህ አሽቀንጥረህ ትጥለዋለህ ሌላ ያንተኑ ትክክለኛ ግጣምህን ፍለጋ ዳግመኛ ትኳትናለህ፡፡እና ማጠቃለያዬ ምን መሠለህ የራሴውን አጥንት እንዳገኘሁ እርግጠኛ እስክሆን ድረስ ተረጋግቼ መቀመጥ አልፈልግም፡፡ ካለበለዚያ ያ ያንተ ዕጣ ነው የሚደርሠኝ፡፡›› በማለት ነበር ያስረዳው፡፡ በትውስታው ፈገግ ብሎ ወደ ሌላ ትካዜ ሊሸጋገር ሲል የኤደን ጥያቄ መለሠው፡፡ ‹‹ልጆችህ ደህና ናቸው?›› ‹‹ደህና ናቸው እግዜር ይመስገን›› ‹‹የውብዳርስ?›› ‹‹እኔ እንጃላት›› ‹‹እንዴት እኔ እንጃላት … ወንዶች ስትባሉ በቃ ሁላችሁም አንድ አይነት ናችሁ፡፡ ሴትን ልጅ ቀምሳችሁ... ልሳችሁ ጣዕሞን ከጨረሳችሁ በኋላ ተፍታችሁ ካፈር ስትደባልቁ ጥቂት እንኳን ፀፀት አይሠማችሁም፡፡ ግርም የሚለኝ እግኢአብሔር ለምን እናንተን እንደፈጠራችሁ ነው?›› ‹‹የፈጠረንማ አንደኛ አቶ ሁሴን እንደሚለው መልኩን በእኛ በኩል ለማየት ነው፡፡ ምክንያቱም እኛ እሱን እንመስላለን፡፡ ሁለተኛው ምድርን እንድናበዛለት ወይም እንድናስተዳድርለት ነው፡፡ ሦስተኛው እንድናመሰግነው ይመስለኛል፡፡ እንደ እኔ ሦስተኛው ብዙም የተሳካ አይመስለኝም፡፡ እናንተን ከፈጠረ በኋላ አይናችንን ወደ ፈጣሪ እንዳናነሳ እንቅፋት እንደሆናችሁን ነው የምረዳው፡፡ እንደ እኔ እግዚአብሔር ያደረገው ነገር ሁሉ ትክክል ነው፡፡ ስህተት የለበትም ብዬ ባስብም ትልቁ አደጋ ወንድን መፍጠሩ ሳይሆን ሴትን መፍጠሩ ይመስለኛል፡፡››ሁለቱም ምግቡን ስላቆሙ አስተናጋጅ መጥቶ መአዱን አነሳውና ጠረጴዛውን አፀዳዳው፡፡ ‹‹ግን እውነት ደህና ነች?›› ጠየቀችው ኤደን ‹‹እኔም እውነቴን እኮ ነው አላውቅም›› ‹‹ምን ማለት ነው?›› ‹‹ተፋተናል›› ‹‹ምን?›› በድንጋጤ አፏን በእጇ ሸፍና ከመቀመጫዋ ተነሳችና መልሳ ቁጭ አለች፡፡ ‹‹አዋ አራት ወር አለፈን›› ‹‹እንዴት
إظهار الكل...
​​ሳልሰማ? ምን አለበት ደውለህ እንኳን ብትነግረኝ?›› ‹‹ምን የሚነገር ነገር አለው ለሰርጉም ጠርቼሽ ለፍቺውም ጠርቼሽ እችላለው... ድግስና ጥሪ ለጋብቻ ብቻ ነው›› ‹‹ለምን የለውም? የዛሬን አያድርገውና ስንት ጥሩና መጥፎውን ነገር አብረን አሳልፈናል እኮ ሃይ የሚላችሁ ሠውም የለ እንዴ? ዳሩ ከእብድ ጋር የሚውል ምን ጤና ይኖረዋል፡፡ ከአህያ ጋር የዋለች ጊደር...› እንደሚባለው ቢጤ እኮ ነው›› ‹‹እንደምታስቢው እኔ ጠልቻት ወይም ሌላ አፍቅሬ እንዳይመስልሽ›› ‹‹እና እንዴት ሆኖ ነው?›› ‹‹ሠለቸኋት … ድብብቆሽ ጫዋታ ውስጥ ገባች፡፡ እጅ ከፍንጅ ያዝኳት .. በቃ ይሄው ነው፡፡›› ‹‹እኔ አላምንም … የውብዳር ከሌላ ወንድ ጋር... ምቀኛ በመሃከላችሁ ገብቶ እንዳይሆን?›› ‹‹አመንሽም አላመንሽም በወሬ ወይ በጥርጣሬ አንዳይመስልሽ፡፡ እራሷም ባመነችበት አሳማኝ ማስረጃ ነው›› ‹‹ወይ ጉድ!›› አለች ኤደን ግራ ገብቷት፡፡ ሠሎሞን ብርጭቆውን አነሳና ውስጥ ያለውን ጅው አድርጎ ከጨለጠው በኋላ ለሁለቱም ቀድቶ ጠርሙሱ ውስጥ ያለውን አሟጦ ሌላ እንዲጨምርላቸው ለአስተናጋጁ ትዕዛዝ አስተላልፎ ንግግሩን ቀጠለ፡፡ ‹‹አየሽ ኤደን ምን አልባት አንቺ ነገሮችን ከራስሽ አንፃር ስትገመግሚያቸው በወንድ በደል ደርሶብኛል ወይም ተገፍቼያለሁ ብለሽ ስለምታስቢ ጠቅላላ ወንዶች ላይ ያለሽ ግንዛቤ አሉታዊ ጎኑ ስለሚያመዝን ወንዶች ሁሉ በዳይ ሴቶች ደግሞ ተበዳይ ሆነው ሊታዩሽ ይችላሉ፡፡ ሀቁ ግን እንደዛ አይደለም ስንት መሠሪና አለሌ ሴቶችም አሉ ፡፡ እና ምን መሠለሽ …››ንግግሩን የስልኩ መጮህ አቋረጠው፡፡ ከኪሱ አወጣና ደዋዩ ማን እንደሆነ አየው፡፡ ሁሴን ነበር፡፡ አነሳው፡፡ ‹‹እሺ ጌታው›› ‹‹አለሁ ባክህ ፡፡ሠርጉ እንዴት ነበር?›› ሁሴን፡፡ ‹‹አሪፍ ነው፡፡ አሁን ወጥቼያለሁ፡፡ ፍንድቅድቅ ያልክ ትመስላለህ ደግሞ ምን አገኘህ?›› ‹‹ደወለች ባክህ›› ‹‹ማ?›› ሁሴን ተበሳጨ ‹‹ማን ትላለህ እንዴ? ማን እንድልህ ትፈልጋለህ›› ‹‹ይቅርታ እሺ ደራሲዋ ደውላልሃለች ማለት ነው?›› ኤደን ሁሴን እንደደወለ አወቀች፡፡ ሌላ ነገር የምታስብ መስላ ከወይኑ እየተጎነጨች በጽሞና ቃለ ምልልሳቸውን እያዳመጠች ነው፡፡ ‹‹ትክክል ነህ ፡፡እሷን ለማግኘት ማድረግ የሚገባኝን ነገረችኝ፡፡›› ‹‹አትለኝም ምን አለችህ?›› ‹‹አግባኝ›› ‹‹በተሠቀለው ንጉስ አግባኝ? የምሯን ነው!›› ‹‹ኸረ ከምሯ ነው፡፡›› ‹‹ታዲያ ምን ችግር አለው እሺ በላታ፡፡ ከዛም አግኛትና ካልተመቸችህ ቃልህን ታጥፋለህ፡፡ ቃል ማጠፍ እንደሆነ ላንተ የሚከብድ አይመስለኝም›› የኤደን ስሜት ይበልጥ እየተነቃቃ ውስጧ በቁጣና በቅናት እየነደደ መጣ፡፡ ትቼዋለሁ ወጥቶልኛል ብላ ከሁሴን አጠገብ ከራቀች... እሱን ማግኘት ከተወች ስድስት ወር ቢሆናትም ውስጧ ግን ዛሬም ይራበዋል፡፡ መሸነፍ ልቧን ያቆስለዋል፡፡ንግግራቸው ቀጥሏል፡- ‹‹ባክህ የዋዛ እንዳትመስልህ የእውነት ከወደድከኝ ቆማጣም ሆንኩ ሸፋፋ የማትተወኝ ከሆነ እና ልታገባኝ ከወሠንክ በመጀመሪያ ሠርግ ደግስ ለምታውቃቸው ሠዎች ሁሉ የሠርግ ጥሪ በትን ከዛ በሠርጉ ቀን ሽማግሌዎችህን ሚዜዎችህንና አጃቢዎችህን አዘጋጅ ልክ በሠዓቱ እደውልልሃለሁ ያለሁበት ትመጣና ይዘኸኝ ትሄዳለህ፡፡››አለችኝ ‹‹እንዲህ ነችና … ልጅቷ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ፊልም እየሠራች ነው እንዴ …? እኔ ይሄንን ጉዳይ ከዚህ በላይ በስልክ ማውራት አልፈልግም ነገ ጥዋት እቢሮ እመጣለሁ ታወራኛለህ›› ‹‹እጠብቅሃለሁ ለማንኛውም ሚዜ ለመሆን ተዘጋጅ›› ‹‹እሱን እናያለን .. ለማንኛውም አሁን ከኤደን ጋር ነኝ፡፡ሰርግ ቤት ተገናኘን፡፡ ሠላም ትልሃለች›› ‹‹ኤደን በተቃውሞ ፊቷን አኮሳተረች፡፡›› ‹‹ተመችቶሃላ .. ላናግራት›› አለ ሁሴን ሠሎሞን ሞባይሉን ዘረጋላት .. ፍቃደኛ አልሆነችም፡፡ ‹‹በል ቻው፡፡ በአየር ላይ ሠላም ብላሃለች፡፡›› በማለት ስልኩን ዘጋው፡፡ ‹‹በቃ አሁንም ስለዛች ደራሲ የቀን ህልም እያለመ ነው፡፡›› ‹‹ባክሽ እኔም ግራ ገብቶኛል›› ‹‹እኔ እኮ የሚገርመኝ ቆይ ማን ትሆን እንዲህ የሚጫወትበት?›› ‹‹እሱ አይደል እንቆቅልሹ፡፡ አሁን እኮ የሚለኝ ልታየኝ ከፈለክ ድግስ ደግስና አግባኝ አለችኝ ነው›› በ ‹‹በቃ በቃ እኔ እንዲህ አይነት ቅራቅንቦ መስማት አልፈልግም፡፡ እንደውም መጠጣት ሁሉን መርሳት እፈልጋለሁ ሞቅ ያለ ቤት ውሠደኝ›› አለችው፡፡ ‹‹ኸረ እስማማለሁ›› በማለት ሂሳቡን ከፍሎ ቀጫጭን የእጆቿን ጣቶች በፈርጣማው ጣቶቹ አቆላልፎ በመያዝ ወደ ጭፈራ ቤት ይዟት ለሜሄድ መኪናው ውስጥ ይዘዋት ገባ፡፡ መኪናውን ከማንቀሳቀሱ በፊት የሞባይል ስልኩን ካስቀመጠበት ኪሱ አውጥቶ የጹሁፍ መልክት መፃፍ ጀመረ ‹‹ኤደን ጭፈራ ቤት ውሠደኝ እያለችኝ ነው፡፡ ባንተ የተበሳጨች ይመስለኛል፡፡ ስሰክር ማስተዋሌ እንደሚቀንስ ታውቃለህ፡፡ ምን አልባት አንተን የማያስደስት ነገር በእኔ እና በእሷ መሀከል ይፈጠር ይሆን? ብዬ ፈራሁ፡፡ ምን ትመክረኛለህ?››መልዕክቱን ወደ ሁሴን ሞባይል ላከና የመኪናውን ሞተር አስነስቶ መንዳት ጀመረ፡፡ ወዴት እንደሚሄዱ አያውቅም፡፡ ከሁሴን መልስ እስኪመጣለት ጊዜ ለማግኘት ነው፡፡ ሠዓቱ 3፡45 ሆኗል፡፡ ከዚህ ሠዓት በኋላ ለብታን ወደ ስካር ለማሸጋገር፤ ለዛውም ከሴት ጋር ጭፈራ ቤት መግባት መጨረሻውን መገመት አዳጋች ነው፡፡ ሞባይሉ ምልክት አሳየው፡፡ መኪናውን ጥግ ይዞ አቆመና የመጣለትን መልስ ከፍቶ ማንበብ ጀመረ፡፡ ‹‹ቀሽም አትሁን፡፡ ምንም ቅር የሚያሰኝ ነገር የለም፡፡ ግን አደራ በቦርጭህ ሙሉ ተከምረህባት እንዳታፈነዳት፡፡ በል ይመቻችሁ፡፡ በጥዋት ቢሮ ና፡፡ ባይሆን የአልጋ መውረጃ ደህና ቁርስ ጋብዝሃለሁ፡፡›› አንብቦ ሲጨርስ ፈገግ አለና መኪናውን አስነስቶ ተፈተለከ ወደ ጭፈራ ቤት፡፡ እሷ ግን በዝምታዋ ውስጥ ሠምጣለች... ይቀጥላል ╔═══❖•🌺🌸•❖═══╗ @fikerdertogada ╚═══❖•🌺🌸•❖═══╝ 4 any comment @fikerdertogada_bot ❥............🍃🌹🍃..............❥
إظهار الكل...
❤️ፍቅር በዚህ መንገድ📖 😘ምዕራፍ ➓ ✍ደራሲ ዘሪሁን ገመቹ . . . ሃያ ሁለት አካባቢ ነው፡፡ ሠዓቱ ከምሽቱ 4፡45 ሆኗል ያሉበት ጭፈራ ቤት በጠጪዎች እና በቡና ቤት ሴቶች ተሞልቷል፡፡ በዲጄው ፍላጎት በሚለቀቁ ሙዚቃዎች የተወሠኑ ሠዎች ይውረገረጋሉ፡፡ ሠሎሞንና ሁሴን አንድ ጥግ ይዘው መጠጣታቸው ከጨዋታ ጋር እያወራረዱት ነው፡፡ ‹‹ቆይ አንተ ጨክነህ እንደ እኔ ወንደላጤ ሆንክ ማለት ነው›› ሁሴን ነበር ጠያቂው፡፡ ‹‹ኸረ ትቀልዳለህ እንዴ! አስከዛሬም የተጃጃልኩት ለልጆቼ ስል ነበር፡፡›› ‹‹ቆይ በቤተክርስቲያን ስርዓት አይደል እንዴ ያገባሀት? እና ዝም ብሎ መፋታት ይቻላል፡፡ ከምትፈርውስ ከፈጣሪ ጋርስ አያቀያይምህም፡፡›› ‹‹ዝም ብለህ አትበለኝ፡፡ ዝም ብዬ አይደለም የፈታኋት፡፡ በእኛ ሃይማኖት ፍቺ የሚፈቀዱባቸው ሦስት መሰረታዊ ሁኔታዎች አሉ፡፡ አንደኛው ከተጋቢዎቹ አንዱ ሲሞት፣ ሁለተኛ ከሁለት አንዱ በዝሙት ኃጥያት ከወደቀ ሲሆን ሦስተኛው ደግሞ የማይድን የአዕምሮ በሽተኛ ሲሆን ነው፡፡›› ሁሴን ከአፉ ተቀበለው፡፡ ‹‹ገባኝ... ገባኝ... ታዲያ እኔ እስከማውቀው ድረስ ያንተዋ አልሞተች ወይም የአዕምሮ ህመምተኛ አልሆነችም የቀረው ዝሙት ያልከው ጉዳይ ደግሞ አንተም እየተንቦራጨክበት ነው፡፡ ›› ‹‹ቢሆንም እኮ እኔ ወንድ ነኝ›› ‹‹መፅሐፉ ለወንዶች ልዩ ፍቃድ ይሰጣል ማለት ነው?›› ‹‹ባክህ ነገር አታጣም፡፡ ያው እንደምታውቀው እኔ ሆነ ብዬ ሳይሆን አንዳንዴ ስጠጣ እና ስበሳጭ የምፈፅመው ስህተት ነው፡፡ ለዛውም ከቡና ቤት ሴቶች ጋር ነው፡፡ አንዴ ያወጣኋትን ሴት መልሼ እንደማልደግማት ታውቃለህ፡፡ ይሄንን የማደርገው ለምን እንደሆነ ታውቃለህ ከማንም ከሌላ ሴት ጋር ፍቅር እንዳይዘኝ ስለምፈራ ነው፡፡እሷ ግን ሥጋዋንም ልቧንም ጠቅላላ እሷነቷንም ነው ያስረከበችው፡፡ ስለዚህ ለእኔ ምን ይተርፈኛል?፡፡ ምንም … ባዶ በድን ገላ እና የተራቆተ ልብ... በቃ፡፡›› ‹‹እኔ በበኩሌ ውሳኔህ አልተዋጠልኝም፡፡ የሃይማኖቱን አላውቅም፡፡ በሞራል በኩል ግን ኢፍትሃዊ ይመስለኛል፡፡›› ሠለሞን ተበሳጨ ‹‹አቦ በቃ ጨዋታ ቀይር… ልዝናና ነው የመጣሁት፡፡በደስታ ልጠጣበት …›› ሁለቱም ፊት ለፊታቸው ያለውን የቢራ ጠርሙስ አነሱና ወደ ጉሮሮአቸው ካንቆረቆሩለት በኃላ መልሰው አስቀመጡ፡፡አዲስ የጨዋታ ርዕስ ለማምጣት የቀደመው አሁንም ሠሎሞን ነበር፡፡ ‹‹ለመሆኑ የመጽሃፉ ሽያጭ እንዴት ነው?›› ‹‹አትጠይቀን ባክህ … የተአምር ያህል ነው፡፡ በቅርብ ሁለተኛ ዕትም ማሳተማችን አይቀርም፡፡በየጋዜጣውና የየሬዲዬ ጣቢያው መነጋገሪያ ርዕስም ሆኗል፡፡ የድርሰቱ ምርጥነት ብቻም ሳሆን የደራሲዋ ማንነት አለመታቅ ያልተለመደ ክስተት በመሆኑ ዝነኛ እንዲሆን የራሱን አስተዋጽኦ ሳያደርግ አይቀርም፡፡›› ‹‹ቆይ ደውላልህ አታውቅም›› ‹‹ማ? ›› ‹‹ጣኦትህ ነቻ፡፡ ደራሲዋ›› ‹‹መፅሐፉ ከታተመ ወዲህ አንዴ ደውላልኝ ነበር፡፡ በጣም የሚገርመው ስሜት የለሽ ሆና ነበር ያናገረችኝ፡፤ መቼም አንድ ጤነኛ ሠው የመጀመሪያ ልጁን ሲወልድ እንደሚፈነጥዝ ሁሉ አንድም ደራሲ የመጀመሪያ መፅሐፉ ሲታተምለት በደስታ መፈንጠዙ የሚጠበቅ ነው፡፡ እሷ ግን ደንታም የሠጣት አይመስለኝም፡፡ ስለ ሌላ ነገር ነበር የምታወራልኝ፡፡›› ‹‹አሁንም ልታገኝህ አትፈልግም ማለት ነው?›› ‹‹እሷን ለማግኘት አንድ አማራጭ ብቻ እንዳለ ነግራኛለች›› ‹‹ምንድነው .. እንዴት አይነት አማራጭ?›› ‹‹አልነገረችኝም፡፡ ትንሽ ታገስ አለችኝ›› ‹‹አሁንስ አበዛችው፡፡ ቆይ እሷ አንደኛው ሠው አይደለችም እንዴ? ነው ወይስ የመላዕክት ዝርያ አለባት ይሆን?... ብቻ እኔን ለማየት አርባ ቀንና ለሊት ጹም እንዳትልህ!›› ‹‹ምን ችግር አለው፡፡ እጾማለኋ፡፡ ጣኦቴ አይደለች? ሠው ለጣኦቱ ነፍሱንስ ይሰዋ የለ፡፡›› ‹‹ወይ ጉድ በሕወቴ ማየት እፈልግ የነበረው አንድ ነገር ያንተን በሴት ፍቅር ተንበርክከህ ስትንገላወድ ማየት ነበር፡፡ አንድ ቀን እንደሚሆን እምነቴ ቢሆንም እንዲህ መላ ቅጡ በጠፋ መልኩ ይሆናል ብዬ ግን ፍፁም ግምቱ አልነበረኝም፡፡ በነገራችን ላይ ይህቺ ደራሲህን ሳስብ አንድ ነገር ትዝ አለኝ፡፡ የመጽሐፍ ምረቃው ቀን ፎዚያን በጣም ስከታተላት ነበር፡፡ ስታነብ ታሪኩ የራሷ ይመስል ተመስጣ ነበር፡፡›› ‹‹አዋ እኔም ያንን ታዝቤዋለሁ›› ‹‹ቆይ የሥነ ጽሁፍ ችሎታ አላት እንዴ?›› ‹‹እኔ እስከማውቀው ድረስ የላትም፡፡ ግን አንባቢ ነች›› ‹‹ግን ምነው ጠየከኝ?›› ‹‹አይ የሆነ ጥርጣሬ ነገር በውስጤ ተጭሮ ነው፡፡ ሁሴን ተንከትክቶ ሳቀ፡፡ ‹‹ደራሲዋ ፎዚያ ነች ልትል ነው?›› ‹‹ነች አላልኩም፤ ተጠራጠርኩ እንጂ፡፡ አንዳንዴ በዚህ ዓለም ላይ ሊሆን አይችልም የምትለው ነገር ሆኖ ታገኘዋለህ፡፡›› ‹‹እሱ ትክክል ነህ፡፡ግን ጥርጣሬህ ምክንያተ ቢስ ሆነ እንጂ …›› ንግግሩን ሳይጨርስ በዙሪያቸው ስትሽከረከር የቆየች አንዲት የ18 ዓመት ውብ ወጣት እጎናቸው ባለው ባዶ ወንበር ላይ ሳታስፈቅድ ተቀመጠችና በመኮሳተር ንግግሯን ጀመረች፡፡ ‹ቆይ እናንተ የመጣችሁት ልትዝናኑ ነው ወይስ የፓርላማ ውይይት ላታካሂዱ?›› ሁለቱም በአግራሞት አፍጥጠው ቢመለከቷትም መልስ ለመስጠት የቀደመው ግን ሠለሞን ነበር፡፡ ‹‹እስከ አሁን ስትሰልይን ነበር እንዴ?›› ‹‹ምን እሰልላችኋለሁ ገርማችሁኝ እንጂ … አሁንም እስቲ በደረቁ አታድርቁኝ፡፡ ጋብዙኝ፡፡›› ‹‹እዘዢ›› ሁሴን ነበር የፈቀደላት፡፡ አስተናጋጁን ጠርታ ዳሽን ቢራ አዘዘች፡፡ ‹‹ቆንጆ ነሽ›› አላት ሠሎሞን፡፡ ትላልቅ አይኖቿን አንከባለለችበትና ፈገግ ብላ ‹‹ሊበሏት ያሠቧትን ወፍ ጅግራ ነሽ ይሏታል አለ ያገሬ ሠው›› ‹‹እንዴት ማለት›› አላት ሠሎሞን፡፡ ‹ ‹‹አይገባህም፡፡ ቅኔ አልተማርክም እንዴ?›› ‹‹ተይው እሱ ስለ ስሚንቶና ድንጋይ ብቻ ነው የሚያውቀው›› የሁሴን ንግግር ነበር፡፡ ‹‹ግምበኛ ነው እንዴ?›› ከቢራዋ እየተጎነጨች በፈገግታ ጠየቀች፡፡ ‹‹ትክክል ነሽ፡፡ የግንበኞች አለቃ ነው›› ‹‹እሺ አንተስ?›› ሠለሞን ብድሩን ለመመለስ ተሽቀዳደመ፡፡ ‹‹እሱማ ያው ወሬ ለቃቃሚ ነው … ወሬ ይገዛል፡፡ ይሸጣል፡፡›› ‹‹ኸረ እኔ ጋር ብዙ ወሬ አለ፡፡ ብትገዛኝ .. ግን ደስ የምትሉ ጓደኛሞች ናችሁ፡፡ ተረባችሁ ደስ ይላል፡፡ ሠሎሞን እጁን አንስቶ ጭኗ ላይ በማስቀመት ጨመቅ እያደረጋት ወሬውን ቀጠለ ‹‹ተረብ እኮ አይደለም የወሬ ነጋዴ ነው እሱና መሰሎቹ ግን ለራሳቸው ቆንጆ ስም ሠይመዋል፡፡ ስራችሁ ምንድነው ሲባሉ ጋዜጠኛ ይላሉ ደረታቸውን ነፍተው፡፡›› ሁሴን ተቀበለው፡፡ ‹‹ልክ እናንተም ስትጠየቁ ኢንጅነር እንደምትሉት ሁሉ›› ‹‹በቃ ይበቃችኋል እኔ ስለማንነታችሁ በቂ መረጃ አግኝቼያለው›› ‹‹ኮሚሽን እፈልጋለሁ›› አላት ሁሴን፡፡ ‹‹ለምኑ?›› ‹‹አያያዙን ሳየው የሚለቅሽ አይመስለኝም፤ ታዲያ ስትደራደሩ ምን ያህል መክፈል እንደሚችል እንድታውቂ መረጃ ሠጥቼሻለሁ›› ‹‹ባክህ ስንት ቀብቃባ ኢንጅነር አይተናል መሠለህ›› እንዲህ እንዲህ እየተጫወቱ
إظهار الكل...
ጥኩ፡፡ ሠረቅ አድርጌ ተመለከትኩት አይኑን ጣሪያ ላይ ሠክቶ ይቆዝማል፡፡ ነገር የገባው ፈላስፋ ይመስላል፡፡ ‹‹የዚህ አገር ልጅ ነህ?›› የጥያቄውን መልስ ፈልጌ ሳይሆን እንዲያወራኝ ስለፈለኩ ነበር መጠየቄ፡፡ ‹ምነው?›› መልሶ በግድየለሽነት ጠየቀኝ፡፡ ‹‹እዚህ ሠፈር አይቼህ ስለማላውቅ ነው›› ‹‹ከአሁን በኋላም አታይኝም›› ደረቅ መልስ መለሰልኝ፡፡ ‹‹ኡ. ኡ .ቴ እሱን እንኳን እናያለን›› አልኩ አስቤ አልነበረም እንደዛ ያልኩት፤ እንዲሁ ለመቀለድ ስለፈለኩ እንጂ፡፡ ድብርቱን ላላቅቅለት ወስኛለሁ፡፡ ቢያንስ ለዚች ለሊት እንኳን ቢሆን ችግሩን እንዲረሳ በደስታ ላንሳፍፈው ቆርጬ ነበር፡፡ ‹‹ዝምተኛ ነህ?›› ‹‹ብንተኛ ምን ይመስልሻል?›› አለኝ ታጥቦ እንዳልተተኮሰ ሱፍ ጨርቅ የተጨማደደ ፊቱን እንደቋጠረ፡፡አልከፋኝም፡፡ አይነጥላው እስኪገለጥለት ነው ስል አሠብኩ፡፡ ከደቂቃዎች በኋላ የሕይወት ታሪኩን እንደሚዘከዝክልኝ እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ እንደእሱ አይነት ብዙዎች ገጥመውኛል፡፡ መጨረሻቸውንም በሃዘኔታና በትዝብት ተመልክቼያለሁ …ቀይ ፒኪኒ ፓንቴ ሲቀር የተቀረውን ልብሴን አንድ ባንድ አወለኩ፡፡ አንሶላውን ገልጬ ከውስጥ ገባሁና እሱን መመልከት ጀመርኩ፡፡ ከተጋደመበት ተስፈንጥሮ ተነሳና ማወላለቅ ቀጠለ፡፡ እፍረቱን መሸፈኛ እንኳን አላስቀረም፡፡ መለመላውን ወንበር ስቦ ተቀመጠ፡፡ ከተኛሁበት ሳልንቀሳቀስ አፍጥጬ እየተመለከትኩት ነው፡፡ አወላልቆ ካስቀመጠው የሱሪ ኪስ ሲጋራ አወጣና ለኩሶ ማጬስ ጀመረ፡፡ ገረመኝ … ‹‹በሽተኛ ነው እንዴ?›› ሁሴን አላስችል ብሎት ጣልቃ ገብቶ ጠየቀ፡፡ ‹‹እያነበብኩልህ እኮ ነው፡፡ ሠለቸህ እንዴ?›› አለችው ትንግርት ከንባቧ ስላደናቀፋት ተበሳጭታ፡፡ ‹‹ኸረ በፍፁም፡፡ መጨረሻው አጓጉቶኝ እንጂ›› ‹‹ታገስ ካሁን በኋላ ካቋረጥከኝ አላነብልህም፡፡›› አለችና ከቢራው አንዴ ተጎንጭታ ካቆመችበት ቀጠለች፡፡ ከሴቶች ጋር ተኝቶ አያውቅም ወይስ ስልብ ነው ስል አሰብኩ፡፡ አጢሶ ሲጨርስ ከኪሱ ሌላ ነገር አወጣ እና ወደ እኔ አመራ፡፡ ሠፋ ያለ ፕላስተር እና የተጠቀለለ ገመድ ነበር የያዘው፡፡ ግምቴን ሳልጨርስ ኪራይ እንዳልተከፈለበት የቀበሌ ቤት በሚገርም ፍጥነት አፌን አሸገኝ፡፡ ፋታ ሳይሰጠኝ የለበስኩትን ብርድ ልብስ ከላዬ ላይ ገፎ ወደ ወለሉ ወረወረውና ከተኛሁበት ጎትቶ አስነሳኝ፡፡ እጆቼን ወደ ኃላ ጠመዘዘና በመንግስት እጅ እንደወደቀ አሸባሪ አንድ ላይ አጣምሮ ጠፈራቸው....መታገል አልቻልኩም፡፡ በፍራቻ ቀስ በቀስ መደንዘዝ ጀምሬለው፡፡ ሊገለኝ እንዳሰበ ገመትኩ፡፡ አይኖቹን ተመለከትኳቸው የሲኦል እሳት ውስጣቸው መንቦግቦግ ጀምሯል፡፤ ለበርካታ ደቆቃዎች ፊት ለፊቴ ቆሞ አስተዋለኝ፡፡ እነዛ ደቂቃዎች ለእኔ ከእድሜ ልክ በላይ ነው የረዘሙብኝ፡፡ አንዴ ጡቶቼን ከዛም ጭኔን ጠቅላላ ሠውነቴን በማፈራረቅ እስኪጠግብ ተመለከታቸው፡፡ መመልከቱ ሲበቃው የለበስኩትን ቀይ ፓንት በእርጋታ አውልቆ ወደ አፍንጫው አስጠጋው፡፡ የፈረንሳይ ሽቶ እንደተነሰነሰበት ውድ መሃረብ በተመስጦ ወደ ውስጥ እየማገ አጣጣመው፡፡በኋላም በጥንቃቄ አጣጠፈውና ኮመዲኖው ላይ አስቀመጠው፡፡ ወዲያው ሃሳቡን ቀየረና ካስቀመጠበት አንስቶ የጃኬት ኪስ ውስጥ ከተተው ፡፡ፓንቴን፡፡ በዚህ ጊዜ የስነልቦና በሽተኛ መሆኑ በደንብ ገባኝ፡፡ ፍራቻዬ በእጥፍ ጨመረ፡፡ ብዙ የወሲብ በሽተኞች አጋጥመውኝ ያውቃሉ፡፡የዛሬው ግን የተለየ ነው የሆነብኝ፡፡ ነገሩን የከፋ ያደረገው ደግሞ የሆነ ነገር ተናግሬ እንዳላረጋጋው ካልሆነም ያቅሜን ያህል ጮኬ ከውጭ እርዳታ እንዳይመጣልኝ የአፌ መታሸግና የእጄ መታሰር ነው፡፡ሁለት እግሮቼን ይዞ ወደ አልጋው ጫፍ ሳበኝ፡፡ ወንበሩን አስጠጋና እግሮቼ መካከል ተቀመጠ፡፡ ልክ ከማህፀን የሚወጣ ህፃን ልጅ እንደምትጠብቅ አዋላጅ ብልቴን አትኩሮ ይመለከት ጀመር፡፡ እንደመባነን አለና ሌላ ሲጋራ መዞ አቀጣጠለ፡፡ በዚህ ጊዜ ይበልጥ ሠውነቴ መንቀጥቀጥ ጀምሮ ነበር፡፡ ‹‹ሊያበላሸኝ ነው›› ስል ደመደምኩ፡፡ ብልቴን በሲጋራ እሳት ሊተረኩሰው እንደሆነ ገመትኩ፡፡ በዓይኖቼ ተማፀንኩት፡፡ ፍራቻዬ አየለ፡፡ ፊኛዬ ተነፋፋና የሽንት መቆጣጠሪያዬ ተተረተረ፡፡እሱም በተራው በመገረም አስተዋለኝ፡፡ አዲስ እንደፈለቀ ምንጭ ከሚንጎለጎለው ሽንቴ በጣቱ አጥቅሶ ወደ ምላሱ ሠደደው... እናም አጣጣመው፡፡ ልክ የሠራችውን እንደምትቀምስ ባለሞያ ወጠ ሠሪ፡፡ ደግነቱ ምንም የቃጠሎ አደጋ ሳያደርስብኝ ሲጋራውን አጪሶ ጨረሠና ወረወረው፡፡ አወራወሩ የንዴት ይመስላል፡፡ ‹‹ከሌላ ፕላኔት የመጣ ፍጡር ይሆን እንዴ?›› ስል አሰብኩ፡፡ መጨረሻዬም አጓጓኝ፡፡ በዚህ ቅፅበት እጁን ወደ ጃኬት ኪሱ ሲሠድ በጨረፍታ ተመለከትኩ፡፡ ብሞት ግድ የሌለኝ መስሎ ይሠማኝ ነበር፡፡ ይህቺን አለም ገና እንዳልጠገብኳት የተረዳሁት ግን በዚህ ክስተት ነው፡፡የሚያብረቀርቅ ጩቤ አወጣ ፤የራሱን እጅ በጭካኔ ሸረከተው፡፡ ደሙ መስመር ሰርቶ መንጠባጠብ ጀመረ፡፡ የተለያዩ ህብረ - ቀለማት አይኖቼ ላይ ተመላለሱብኝ ቀስ በቀስ ተከደኑ፡፡ ወደ ጥልቅ ገደል እየተንሸራተትኩ ምጓዝ መስሎ ተሠማኝ፡፡ለምን ያህል ጊዜ እራሴን ስቼ እንደቆየሁ ትዝ አይለኝም፡፡ አይኖቼን በፍራቻ ስከፍተው ባዶ ክፍል ውስጥ ባዶ ሆኜ ብቻዬን ነው ያለሁት፡፡ ዙሪያ- ገባውን በጥንቃቄ ቃኘሁት፡፡ የቤቱ ግድግዳ በቀይ ቀለም ተዥጎርጉሯል፡፡ ፅሁፍ ነው፡፡ የሚነበብ ፅሁፍ፡፡ ፊት ለፊት ግድግዳ ላይ ‹‹አፈቅርሻለሁ .. አምርሬም እጠላሻለሁ›› የሚል ፅሁፍ አነበብኩ፡፡አይኖቼን ወደ ራቁት ሠውነቴ ስመልስ እንደ ግድግዳው በፅሑፍ ሳይሆን በምልክት ተዥጎርጉሯል፡፡ ሁለቱ ጡቶቼ የራይት ምልክት አለባቸው፡፡ እንብርቴ አካባቢ የኤክስ ምልክት ይታያል፡፡ ግራ ገባኝ እስከዛን ግዜ እጆቼ እንደተጠፈሩ አፌ እንደተለጎመ ነበር፤ የተለየው ነገር የአእምሮዬ በመጠኑ መረጋጋት ነው፡፡ እጁን ሲቆርጥ ያየሁትን ምስል ወደ ኃላ ተመልሼ ሳስታውስ ይሄ ሁሉ ግድግዳው ላይ እና ሠውነቴ ላይ ያቀለመው በራሱ ደም እንደሆነ ገባኝ፡፡ ሠውነቴ ላይ ያረፉት የራይትና የኤክስ ምልክቶች ፍቺ ግን በቀላሉ ሊገለፅልኝ አልቻለም፡፡እንደ ድንገት ወደ ጎኔ ስዞር በቀኝ በኩል በሚገኘው ግድግዳ ላይ ሌላ ፅሑፍ አነበብኩ፡፡ ‹‹40 ፐርሰንት ብቻ ካንቺ ጋር ትመሳሰላለች፡፡ ስለዚህ አንቺን አትወክልም ማለት ነው...ያበሳጫል...ሳልገላት ትቼያት ሄጃለሁ፡፡››ዳግም አዞረኝ፡፡ የሚገላትን ሴት በመፈለግ ላይ ያለ ወፈፌ ነው ያጋጠመኝ፡፡ የምልክቶቹም ፍቺ ተገለፀልኝ፡፡ ከሚያውቃት ወይም ካስከፋችው ሴት ጋር እያመሳሰለኝ ነበር፡፡ እየተንፏቀኩ ሄጄ በራፉን በደከመ ጉልበቴ ደበደብኩ፡፡ ዘበኛው ሠምቶ ከፈተልኝ፡፡ ከእስሬ ነፃ አደረገኝ፡፡ እየተንቀጠቀትኩ ልብሴን እየለበስኩ ሳለ ቅድም ያለየሁት ሌላ ምልክት ብልቴ አካባቢ አየሁ፡፡ ጥያቄ ምልክት አስቀምጦበታል፡፡ ኮንትራት ታክሲ አስጠርቼ እቤቴ አደረሠኝ፡፡ እቤቴ ስገባ ልክ ስምንት ሠዓት ነበር፡፡ ሠውነቴን ታጠብኩ፡፡ከፍራቻዬ ለመገላገል ለሊቱን ሙሉ ስጠጣ አደርኩ፡፡ይሄው ነው አለችው እያነበበችለት ያለውን ዲያሪ አጥፋ እያስቀመጠች፡፡ ‹‹ልብ ወለድ ነው እውነት?›› በጉንጮቹ ላይ ያለ ፍቃድ የወረደ እንባውን እየጠረገ ‹‹ልብ ወለድ በዲያሪ ይፃፋል እንዴ?›› ‹‹በቃ ምንም አላውቅሽም ማለት ነው፡፡ እራሴን አመመኝ ልሂድ›› በማለት ከመቀመጫው ተነሳና ግንባሯን ስሟት
إظهار الكل...
​​የሚበቃቸውን ያህል ከጠጡና የሚበቃቸውን ያህል ካመሹ በኋላ ሁለት ሆነው የገቡበትን ቤት ሦስት ሆነው ለቀቁ፡፡ ሠሎሞን ወጣቷን ሸጉጦ በራሱ መኪና ገብቶ ሁሴንን ተሠናበተና ተፈተለከ፡፡ ሁሴን የራሱ መኪና ውስጥ ገብቶ ጉዞ ጀመረ፡፡ ብቸኝነት ተሠማው፡፡ ተንቀሳቃሽ ስልኩን አንስቶ ደወለ፡፡ ከአራት ጥሪ በኋላ ተነሳ፡፡ ‹‹ምነው ጋሼ?›› ‹‹እንዴት ምነው?›› ‹‹እኩለ ለሊት እኮ ተቃርቧል›› ‹‹ተኝተሸ ነበር እንዴ?›› ‹‹ነገሩ እንኳን አልተኛሁም … ለመሆኑ የት ነህ? መኪና እየነዳህ መሠለኝ፡፡›› ‹‹አዎ ከዛ ቦርጫም ጋር ዘና ብዬ ወደ ቤት እየገባሁ ነው›› ‹‹ጥሩ ነዋ …›› ‹‹አሁን የደወልኩት ላገኝሽ ስለፈለኩ ነው›› ‹‹ምን?›› ‹‹ምነው ደነገጥሽ ..?›› ‹‹አሁን እኮ እንደበፊቱ ሸርሙጣ አይደለሁም፡፡ በፈለክ ሠዓት ገንዘብህን ከፍለህ ልታገኘኝ አትችልም›› በማለት ጆሮው ላይ ጠረቀመችበት፡፡ ግር አለው እሷ ባሰበችው መልኩ ፈፅሞ አስቦት አልነበረም፡፡ እንዲህም ሆደ ባሻ እና ቁጡ ስትሆን አይቷት አያውቅም፡፡ ይቀጥላል ╔═══❖•🌺🌸•❖═══╗ @fikerdertogada ╚═══❖•🌺🌸•❖═══╝ 4 any comment @fikerdertogada_bot ❥............🍃🌹🍃..............❥
إظهار الكل...
‍ ተዘጋጀ፡፡ ግራ ገባት ከእሷ ጋር አብሮ ለማየት የሚጓጓለት ፊልም ከዚህ ቀደም አጋጥሟት አያውቅም፡፡ ‹‹እየቀለድክ ነው?›› አለችው ‹‹በፍፁም እንደዛሬም አምርሬ አላውቅም፡፡ አንቺ መሪ ተዋናይ ሆነሽ የተወንሽበትን ፊልም አብረን ብናይ ምን አለበት? ምንም ቢሆን እኮ ታማኟና ተወዳጇ ባለቤቴ ነሽ›› በማለት ከፈተውና ወደ እሷ አስጠጋላት፡፡ በፍራቻ እና ግራ በመጋባት መመልከት ጀመረች፡፡ አፏን የምታረጥብበት ምራቅ አጣች፡፡ ጉሮሮዋ ደረቀባት፡፡ ሠውነቷ ሲንቀጠቀጥና እየዛለ ሲሄድ ለራሷ ይታወቃታል፡፡ መንቀሳቀስም ሆነ መናገር አልቻለችም፡፡ ከምትመለከተው ፊልም ላይም ፊቷን ዞር ማድረግ አልሆነላትም፡፡ እስኪጠናቀቅ አየች፡፡ ሠሎሞን ማለቁን ሲያይ ዘጋውና ከጎኗ ተነስቶ ፊት ለፊቷ ተቀመጠ፡፡ ‹‹እሺ አሁን መነጋገር የምንችል ይመስለኛል›› ለመናገር ከንፈሯን ማላቀቅ አልቻለችም፡፡ በፍራቻ የቀዘቀዙ ዓይኖቿን አንከባለለችበት፡፡ ‹‹መልስ ስጪኝ እንጂ?›› ‹‹ምን ል..በልህ?›› ‹‹መነጋገር አለብን እኮ ነው የምልሽ›› ‹‹መ..ቼ?›› ‹‹ዛሬ .. አሁን … እዚሁ›› ‹‹አልችልም ነገ›› እየተጎተተችበት ከተቀመጠችበት ለመነሳት ስትሞክር ተንጠራርቶ ክንዷን ጨመቀና መልሶ አስቀመጣት፡፡ ‹‹ትሰሚያለሽ! እንደውም ካንቺ ጋር መነጋገር አልፈልግም፡፡ ውሳኔዬን ግን በጥሞና እንድታደምጪኝ እፈልጋለሁ፡፡ ከአሁን ሠዓት ጀምሮ እቤቱን ለቅቄልሽ እወጣለሁ፡፡ የግል ዕቃዎቼን ብቻ ይዤ ፡፡ የምትጠቀሚበትን መኪና አንዴ ገዝቼልሻለሁ አሁንም ያንቺው ነው፡፡ እቤቱንም ከጎረምሳሽ ጋር ቅበጪበት፣ ጨፍሪበት፣ እንዳሻሽ ሸርሙጪበት፡፡ ስሙ ባንቺ ስላልሆነ የመሸጥ የመለወጥ መብት ግን የለሽም፡፡ ከዛ በተረፈ ለልጆቼ ከሚያስፈልገው ውጪ በስተቀር ሠባራ ሳንቲም ከእኔ አታገኝም፡፡ ወደ ክስ እሄዳለሁ ብትይ ግን ይሄንን ጉድሽን በአስር ሺ ኮፒ አባዝቼ ፣ለእነዛ ተመፃዳቂና ጉረኛ ዘመዶችሽ በነፍስ ወከፍ አድልልሻለሁ፡፡ በጠበቃዬ በኩልም ለፍርድ ቤቱም በማስረጃነት አቀርበዋለሁ፡፡ ከዛ በኋላ ምን አልባት ከእኔ ንብረት መካፈል ብትችይ እንኳን ከዘመዶችሽና ከጎረቤቶችሽ የሚደርስብሽን ውርደት ተቋቁመሽ እዚህ ከተማ ውስጥ መኖር የምትችይ አይመስለኝም፡፡ ለማንኛውም የሚሻልሽን ከውሽማሽ ጋር ተማክረሽ መወሰን ትችያለሽ ››በማለት ተነስቶ እርምጃ ከጀመረ በኃላ ቆሞ ንግግሩን ቀጠለ፡፡ ‹‹…ሌላ አንድ ነገር ይቀረኛል፡፡ በማንኛውም ሠዓት ልጆቼን ማየት ስፈልግ መኪና እልካለሁ ፣ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ትልኪልኛለሽ፡፡ ሁኔታዎችን አመቻችቼ ወደ ራሴ እስክውስዳቸው ድረስ ማለት ነው፡፡ ሳስብሽ ትክክለኛ ሚስት ብቻ ሳይሆን ትክክለኛ እናትም የመሆን ብቃቱ ያለሽ አይመስለኝም›› እንባዋን እያረገፈች ፣አንደበቷ ተሳስሮ ፣ሠውነቷ በድንጋጤ እና በፀፀት ተኮማትሮ እያያት ያለ ምንም ሀዘኔታ ጥሏት ወደ መኝታ ቤቱ ገባ፡፡ እቃዎቹን ሠብስቦ ቤቱን ጥሎላት ሊወጣ። ********* ይቀጥላል ╔═══❖•🌺🌸•❖═══╗ @fikerdertogada ╚═══❖•🌺🌸•❖═══╝ 4 any comment @fikerdertogada_bot ❥............🍃🌹🍃..............❥
إظهار الكل...
​​ናኘት ለጊዜው ምንም አይነት ፍላጎት እንደሌላት አስረግጣ ነገረችኝ፡፡ እንዳለችውም ውክልናውን በፖስታ ቤት ላከችልን በዚህም መሠረት መጽሐፍ በእኔ አማካይነት እና በጓደኞቼም እገዛ እነሆ ዛሬ ለህትመት በቃ›› ‹‹እኔም ጋዜጠኛ እንደመሆኔ መጠን እዚህ ያላችሁ ጋዜጠኞች መዓት ጥያቄ በአዕምሮአችሁ እየተጉላላ መሆኑ ቢገባኝም አሁን ወደ ዝግጅቱ በቀጥታ እንድንገባ እየጠየቅኩ በስተመጨረሻ ላይ ግን በተቻለ መጠን ለጥያቄያችሁ መልስ ልሠጣችሁ እንደምሞክር ቃል እገባለው፡፡ በመቀጠል የእለቱን የክብር እንግዳ የሆኑት የደራሲያን ማህበር ፕሬዘዳንት በንግግር እንዲከፍቱልን በክብር እጠይቃለሁ›› በማለት መድረኩን ለፕሬዘዳንቱ አስረከበ፡፡,ፕሬዘዳንቱም ንግራቸውን በመገረም ጀምረው በመደነቅ ጨረሱ እና መድረኩን መልሠው ለሁሴን አስረከቡ፡፡ ሁሴን ንግግሩን ቀጠለ ‹‹በመቀጠል የተወሰኑ ግለሠቦች ከመጽሐፉ የተወሠነ ጽሁፍ በመቀነጫጨብ ለዕድምተኞቻችን ያቀርቡልናል፡፡ የመጀመሪያዋ አቅራቢ ትዕንግርት ትሆናለች፡፡ ትዕንግርት ወደ መድረኩ ብትመጪልን፡፡ በነገራችን ላይ ትዕንግርት በሞያዋ ሠዓሊ ነች፡፡ በሚቀጥለው ሳምንት በአልያንስፍራንስ የመጀመሪያ የሥዕል ኤግዚብሽኖን ታቀርባለች ጋዜጠኞች ይህቺን ልጅ ብትከታተሏት ድንቅ ታሪክ ከጀርባዋ እንደምታገኙ በሚሥጥር ሹክ ልላችሁ እወዳለሁ›› በማለት ነጭ የአበሻ ቀሚሷን ለብሳ በቄንጠኛ እርምጃ ወደ መድረኩ ለተቃረበችው ትዕንግርት ለቀቀላት፡፡ እሷም ያለምንም የመግቢያ ንግግር ቀጥታ መጽሐፉን ገልጣ ወደ ማንበብ ነበር የገባቸችው፡፡ ‹እናቴ› በሚል ርዕስ የሠፈረውን አጭር ልቦለድ ነበር የምታነበው፡፡ አዳረሹ በፀጥታ ተሸበበ፤ ጋዜጠኞች ሳይቀሩ መቁነጥነጣቸውን አቁመው በተመስጦ በማዳመጥ ላይ ናቸው፡፡ የታሪኩ ፍሠትና የቃላቶቹ ውበት ብቻ አልነበረም እንዲመሠጡ ያስገደዳቸው፡፡ የተራኪዋም ድንቅ ችሎታ አፍ ያስከፍታል፡፡ የምታነበው ድርሠት በሦስት ገፀ ባሕርያት የተዋቀረ ነው፡፡ አንድ ወጣት ሴት፣ አንድ አዛውንት እናት እና ጎረምሳ ወንድ፡፡ የሦስቱንም ንግግር በተለያየ የድምፅ ቅላፄ ሳታምታታ እየቀያየረች ስታቀርብ ሕይወት ላለው ድርሠት ድርብ ሕይወት ዘራችበት፡፡ በዚህም ችሎታዋ እድምተኛውም ሆነ ጋዜጠኞች በሙሉ እጅጉን ተደነቁባት፡፡ ሠሎሞንና ሁሴንም በመገረም ፈዘው ነበር፡፡ የሙዚቃ እረፍት ከተደረገ በኋላ ሌሎች ሦስት አንባቢዎች ፎዚያንም ጨምሮ የመረጡትን በንባብ አሠሙ፡፡በአጠቃላይ የመጽሃፍ ምረቃ በዓል ከተለመደው የተለየ ብዙ አስገራሚ ነገሮች የተመቁበት ነበር፡፡ እያንዳንዱ ጋዜጠኛ ያገኞቸውን መረጃዎች በቅደም ተከተል አጠናቅሮ በየሚሠሩበት ሚዲያ ላይ ለማቅረብ ከፍተኛ ጉጉትና መቻኮል ይታይባቸው ነበር፡፡ ሁሴንም እንዲህ ያንሠፈሠፈውን እያንዳንዱን ጋዜጠኛ ነገሮችን በምንም መልኩ እንደተረዱት እና በምን መልኩም ለሕዝብ ለማስተጋባት እንደወሠኑ ለማወቅ ጓጓ፡፡ መጽሃፉም በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያገኛል ወይስ አንባቢ አጥቶ በየመጽሃፍ መሸጫ መደብሩ የብል ሲሳይ ሆኖ ይቀራል የሚለውን ጥያቄ ሌላ ያስጨነቀው ጉዳይ ነበር፡፡ መልሶቹን ለማግኘት ግን የተወሠኑ የጊዜ ሽክርክሮሾችን በትዕግስት መጠበቅ እንዳለበት ተረዳ፡፡ ይቀጥላል ╔═══❖•🌺🌸•❖═══╗ @fikerdertogada ╚═══❖•🌺🌸•❖═══╝ 4 any comment @fikerdertogada_bot ❥............🍃🌹🍃..............❥
إظهار الكل...
❤️ፍቅር በዚህ መንገድ📖 😘 ምዕራፍ ➑ ✍ደራሲ ዘሪሁን ገመቹ . . . ሁሴን ቤቱ የገባው በጊዜ ነው፡፡ እራሱን በመጠኑ ስላመመው በእንቅልፍ እንዲያልፍለት ሳሎን ሶፋ ላይ ጋደም ቢልም እንቅልፍ ግን አልወሰደውም፡፡ ፎዚያ ከጓዳ በር ብቅ አለች፡፡ ‹‹ትምህርት ቤት አልሄድሽም እንዴ?›› ‹‹ ዛሬ የለንም ምነው አንተ ጠቋቆርክ?›› ‹‹ደህና ነኝ፡፡ ትንሽ ብቻ ተጫጭኖኛል›› ‹‹ቡና ላፍላልህ?›› ‹‹ስራ ከሌለሽ ደስ ይለኛል›› ‹‹ኸረ የለኝም›› በማለት እየተንደረደረች ወደ ኩሺና ገባች፡፡ ሁሴን ስለ ፎዚያ ሲያስብ ይገርመዋል፡፡ አንድ ላይ መኖር ከጀመሩ ሦስት ዓመት አልፎአቸዋል፡፡ አንድም ቀን አስከፍታው ወይንም የማያስደስተውን ነገር ለመስራት ሞክራ አታውቅም፡፡ በመጀመሪያ የተገናኙበት አጋጣሚ ትዝ አለው፡፡ ትክክለኛ ቀኑንና ወሩን አያስታውሰውም ብቻ ከሦስት ዓመት በፊት ነው፡፡ ቢሮ አምሽቶ ጨለምለም ሲል በዝግታ እየነዳ ወደ ቤቱ እያመራ ሳለ ሲጋራ አሠኘውና ኪሱን ቢዳብስ ማግኘት አልቻለም፡፡ መኪናውን ጥግ አሲዞ አቆመና ወደ ኪዎስክ ጎራ አለ፡፡ ሊገዛ፡፡ ገዝቶ ሲመለስ ግን ዓይኑ አንድ ነገር አየ፡፡ የመብራት ምሰሶ ስር አንድ ልጅ እግር ወጣት ሴት ቁጭ ብላ ታለቅሳለች፡፡ ያረጀ ሻንጣ አጠገቧ አለ፡፡ ሻንጣው ላይ የተወሰኑ ደብተር እና መጽሐፎች ይታያሉ፡፡ እሷ የትምህርት ቤት ዩኒፎርም ነው የለበሠችው፡፡ አልፏት መሄድ ስላልቻለ ተጠጋት፡፡ ቀናም ብላ አላየችውም፡፡ እንባዋ በቀጥታ ከአይኖቿ ወደ መሬት ይንጠባጠባል፡፡ ‹‹ምን ሆነሽ ነው የእኔ እህት?›› ጠየቃት ዓይኖቿን ወደ ላይ በልጥጣ ተመለከተችው፡፡ ጎንበስ አለና ቀኝ እጁን ትከሻዋ ላይ ጣል አድርጎ ‹‹ከቤት ተጣልተሽ ነው?›› ሁለተኛ ጥያቄ ጠየቃት ‹‹አዎ›› መለሠችለት በደከመ ድምፅ ‹‹ታዲያ ጎዳና ላይ ምን ትሠሪያለሽ? ጎረቤት ወይም ዘመድ ጋር ለምን አትሄጅም?፡፡ ያስታርቁሻል፡፡›› ‹‹ዘመድ የለኝም›› ‹‹እናትና አባት ብቻ ነው ያለሽ?›› ‹‹እናትም አባትም የለኝም፡፡ አንድ አክስት ብቻ ነው ያለችኝ እሷው ነች ያ.ባ..ረ..ረ..›› ሳግ ስለተናነቃት መቀጠል አልቻለችም፡፡ ከኪሱ ሶፍት አወጣና አጠገቧ በርከክ ብሎ ፊቷ ላይ የተረጨ እንባዋን አበሠላት፡፡ ትንሽ ካረጋጋት በኋላ አጇን ይዞ አነሳት፡፡ በጥርጣሬ እያየችው በዝግታ ተነስታ ቆመች፡፡ ‹‹ይኸውልሽ አሁን መሽቷል፡፡ ለዛሬ እኔ ቤት ታድሪና ነገ የሚሆነውን ነገር እንነጋገራለን፡፡ በዚህ ሁኔታ ላይ የዱርዬ መጫወቻ እንድትሆኚ ጥዬሽ ልሄድ አልችልም፡፡›› እንደተገተረች አፍጥጣ አየችው፡፡ ምን መወሠን እንዳለባትም ግራ ገብቷታል፡፡ የማታውቀውን ሠው ተከትላ መሄድ ጨነቃት፡፡ እምቢ ብላም ከጨለማው ጋር መፋጠጥም ይበልጥ አስጨናቂ ሆነባት፡፡ሁሴን ፍራቻዋ ስለገባው ስለ ራሱ ያብራራላት ጀመር፡፡ ‹‹እኔ ሁሴን ሙሀመድ እባላለሁ፡፡ የፍኖተ ጥበብ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ነኝ፡፡ጋዜጣውን ታውቂዋለሽ ብዬ እገምታለሁ፡፡››በማለት መታወቂያውን አውጥቶ ዘረጋላት፡፡ አልተቀበለችውም፡፡ ‹‹አውቅኩህ .. ማለት በአጋጣሚ ጋዜጣው እጄ ሲገባ አንዳንዴም ከጓደኞቼ በመዋስ የማንበብ ዕድል ገጥሞኛል፡፡ በጣም የምወደው ጋዜጣ ነው፡፡ አሁን ጋዜጣው ላይ ያየሁት ፎቶም ትዝ አለኝ›› በማለት ጎንበስ ብላ ደብተሯንና መፅሃፍቶቿን አስተካክላ በቀኝ እጇ ይዛ በግራ እጇ ሻንጣዋን ልታነሳ ስትሞክር እሱ ቀደሟት አነሳውና ወደ መኪናው ጉዞ ጀመረ፡፡ ከኋላው ተከተለችው፡፡ ቀጥታ ወደ ቤት ከመሄዳቸው በፊት ራስ-ሆቴል ጎራ ብለው እራት በሉ፡፡ ስለ ተለያዩ ነገሮች እያወራት ትንሽ ዘና እንድትል ካደረጋት በኋላ ወደ ቤት ይዟት ገባ፡፡ልደታ፡፡ ሳሎን አረፍ ብለው ትንሽ ከወሩ በኋላ … ‹‹በነገራችን ላይ ስምሽ ማን ይባላል?›› ሲል ጠየቃት ‹‹ፎዚያ›› ‹‹እሺ ፎዝያ..ደክሞሻል መሠለኝ፤ እዛ ጥግ የሚታይሽ ክፍል ገብተሸ ተኚ፡፡ ምንም ነገር አትፍሪ፡፡ እንደቤትሽ ቁጠሪው፡፡ ዘና በይ፡፡ የእኔ ክፍል ይሄኛው ነው፡፡ የምትፈልጊው ነገር ካለ አንኳክተሸ ልትጠይቂኝ ትችያለሽ፡፡ ሽንት ቤት ወይም ሻወር ከፈለግሽ ከክፍልሽ ፊት ለፊት ያለው ክፍል ነው፡፡ ምን እንዳጋጠመሽ ጥዋት በዝርዝር ትነግሪኛለሽ›› አላት፡፡ እሷ ግን ይሄንን የታመቀ ብሦቷን ለሊቱን ሙሉ አፍና መቆየት አልፈለገችም፡፡ መተንፈስ... ማውራት ፈልጋለች፡፡ እንኳን እንዲህ ችግሯን ሊረዳላት የሚችል ሠው አግኝታ ይቅርና እንሠማሻለን ካሏት ለጨረቃ እና ለከዋክብቶችም ብታወራላቸው ደስታዋ ነው፡፡ ‹‹እኔ እንኳን አልደከመኝም፡፡ አሁን ልነግርህ እችላለሁ›› አለችው፡፡ ‹‹እንደዛ ከሆነ ቀጥይ እኔም እንዳላጨናንቅሽ ብዬ ነው እንጂ ችግርሽን አሁኑኑ ብሠማ ደሳ ይለኛል፡፡›› ማውራት ጀመረች ‹‹እናትና አባቴ ከአምስት አመት በፊት ነው በሚጓዙበት መኪና ላይ በደረሠ የመገልበጥ አደጋ በአንድ ላይ የሞቱት፡፡ በወቅቱ የእናቴ ታናሽ እህት የሆነችው ይህቺ አክስቴ እኛ ጋር ነበር የምትኖረው፡፡ ከእሷ በስተቀር ሌላ የሥጋ ዘመድ አላውቅም፡፡ ስለዚህ ከእሷው ጋር አብሬ መኖር ቀጠልኩ፡፡ ወላጆቼ ከተወሠነ ቁሳቁስ እና ጥቂት ብሮች በስተቀር የረባ ነገር ጥለውልኝ አላለፉም፡፡ የምንኖርበትም ቤት የኪራይ ነበር፡፡ ብዙም ሳይቆይ አክስቴ በዕድሜ በጣም የሚበልጥትን አንድ አስተማሪ አገባች፡፡ይሄ አስተማሪ ይጠጣል... ያጨሳል... ይረብሻል... ይደባደባል፡፡ በቃ ፀባዩ መላ ቅጥ የሌለው ነው፡፡ ከቆይታ በኋላ ግን የእሱ ብቻ ሳይሆን የእሷም ፀባይ እየተበላሸ መጣ፡፡ በተለይ ልጆች ከተወለዱ በኋላ በጣም ትጨክንብኝ ጀመር፡፡ ስቃዬ በዛ፡፡ ትምህርት ቤት ከምሄድበት ቀን ይልቅ የማልሄድበት ይበልጥ ጀመር፡፡ የልጆቹን ልብስ አጥባለሁ፤ ለቤተሰብ ምግብ አበስላለሁ፤ እቤት አፀዳለሁ፡፡ የማልሠራው ስራ የለም፡፡ እንዲያም ሆኖ ሠላም የለኝም፡፡ከስድስት ወር ወዲህ ደግሞ ነገሮች በጣም እየከፉብኝ መጡ፡፡ የአክስቴ ባል አዲስ ፀባይ አመጣ፤ የአክስቴን ወጣ ማለት እየጠበቀ መቀመጫዬን ይመታኛል፤ ጡቴን ሳላስበው ጨምቆ ያስለቅሰኛል፤ ፀያፍ ቃላቶች ይናገረኛል፡፡ በቃ ጣሬን አበዛው፡፡ ምን ልሁን ለአክስቴ እንዳልነግራት ምን ብዬ...፡፡ በኋላ እያደፈጠ ሊደፍረኝ መሞከር ጀመረ፡፡ ሁለት ሦስት ቀን በመከራ አመለጥኩት፡፡ የዛሬውም ችግር መነሻው ይሄው ነበር፡፡ አስራ አንድ ሠዓት ከትምህርት ቤት ሲመጣ እቤት ያለሁት እኔ ብቻ ነበርኩ፡፡ አክስቴ ትንሿን ልጅ አዝላ ጎረቤት ለቅሶ ሄዳለች፡፡ ትልቁ ልጅ ደግሞ ጎረቤት ለመጫወት ሄዶ ነበር፡፡ እንደመጣ አለመኖሯን ጠይቆ ካረጋገጠ በኋላ ‹ውሃ ጠምቶኛል ውሃ ስጪኝ› አለኝና ወደ መኝታ ቤት ገባ፡፡ ውሃውን በብርጭቆ ቀድቼ በራፍ ላይ ቆሜ ሳንገራግር … ‹ጠምቶኛል እኮ ነው የምልሽ አምጪ እንጂ›በማለት ሺጮኽብኝ በድንጋጤ ተርበትብቼ ወደ ውስጥ ዘለኩና ስሰጠው ብርጭቆውን ትቶ እጄን ለቀም አደረገው፡፡ ሳላስበው ብርጭቆ ከእጄ ሾለከና ወለሉ ላይ ተከሠከሠ፡፡ ባለችኝ ጉልበት እጄን አስለቅቄ ለማምለጥ መታገል ጀመርኩ፡፡ እሱ ግን ባለ በሌለ ሀይሉ ተሸክሞኝ አልጋ ላይ ወረወረኝና ተከመረብኝ፡፡ ታገልኩት ..ታገልኩት…እስኪደክመኝ ታገልኩት... በጥፊ መታኝና በቦክስ ደገመኝ፡፡ እኔን ለማድከም ማድ
إظهار الكل...
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.