ar
Feedback
ከቃሉ ማዕድ

ከቃሉ ማዕድ

الذهاب إلى القناة على Telegram

☀️ ክርስቶስን መስለን በመኖር ፣ ላልተደረሱት የሕዝብ ክፍሎች በመፀለይ ፣ ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ የሚፈልገውን እግዚአብሔርን የሙጥኝ የምንልበት ቻነል ነው። 1ጢሞ 2:1-4 ☀️ ደግሞም አብ የሰጠንን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በልተን ደግሞም ጠትተን ዕለት ዕለት ደግሞ 💥በሁለንተናችን የሚያሳድገንን የቃሉን🎯 ማዕድ የምንቆርስበት ትምህርታዊ እና መንፈሳዊ ቤት ነው። ዮሐ6:35

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
322
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+67 أيام
+6630 أيام
أرشيف المشاركات
አለመብሰል የወንጌልን በጎ ተፅዕኖ ይቀንሳል፣ ብስለትና ምግባር የሌለበት ተሳትፎ ከጥቅሙ ጉዳቱ ከአስከባሪነቱ እንቅፋቱ ያመዝናል።
📖መንፈሳዊ ብስለት📝ማሙሻ ፈንታ(ዶ/ር) ገፅ66
@kekalu_Maid

photo content

👉ዘማሪ ዮሴፍ አስቻለው ▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▿▵▿▵▿ ➫ 2008 ዓም አዲስ አመት መግብያ እንደማንኛውም፡ቤት እኛም ቤት ድፎ ይደፋ ነበር ለእንቁጣጣሽ አጥብያ ቅዝቃዜ በሞላበት አየርና ዝናብ ባራሰው እንጨት የቤታችን ብርቅዬ ሙያተኛዋና ጎበዝ አብሳይ እህት ድፎውን ከላይም ከታችም እንጨት ማግዳበት ከረጅም፡አመት ሙያዋ የተነሳ መቼ እንደሚበስል ስለምታውቅ ወጣወጥ ለመስራት ክፍል ትቀይርና ወጥዋን ጣጥዳ ድፎው ይደርሳል ብላ ከምታስብበት በግማሹ ሰዓት እሳቱ በቦታው በሚገባ እየነደደ እንዳለ ለማረጋገጥ ድፎው ወደሚጋገርበት ክፍል ጎራ አለች። ➫              እሳቱ የለም የላይኛውም የታችኛውም እንደገና ማቀጣጠል እስኪያስፈልገው ድረስ ሙሉ ለሙሉ ጠፍቷል በዚ ፍጥነት በእሳት የማገደቸው እንጨት ጠፍቶባት ስለማያውቅ ደንግጣለች ከብዙ ብስጭት ጋር እንደገና ለማቀጣጠል ክብሪት መለኮስ ጀመረች በክብሪቱ ቀፎ ውስጥ በጣት የሚቆጠሩ የክብሪት መጫርያ ዘለላዎች አሉ ልምድ ስላላት አንድ ፍሬ የክብሪት ዘለላ ብትቀር እንኳን ብዙ አያሳስብም። ➫              እናም የመጀመርያዋን ክብሪት ጭራ ለማቀጣጠል ካዘጋጀችው ከወረቀቱ ልታገናኘው ስትል ጠፋባት፣ ይህ ሊፈጠር ይችላል ብላ ሁለተኛም ጫረች ይሄም፡ወረቀቱን ሳይነካው ጠፋ፣ለሶስተኛ ግዜ ለኩሳ ወደ ወረቀቱ ስታስጠጋ እሱም ጠፋ። አሁን ስሜታዊ መሆን ጀመረች መሃል መሃል ላይ የጌታን ስም እየጠራች እየተቃወመችም ሞከረችው አልሰራም በስተመጨረሻም አንድ የክብሪት ዘለላ ብቻ ቀረ ይሄስ ውግያ ነው ብላ የክብሪት እንጨቷን ይዛ እንዲህ ብላ ጸለየች "ጌታ ሆይ ይህንን ክብሪት አንዲነድልኝና እኚህ ልጆች ድፎ እንዲበሉ አድርግ" ብላ የመጨረሻዋን የክብሪት ዘለላ ጫረችው በሚገርም ሁኔታ እሱም ጠፋ። ➫               ከነፍሷ ተበሳጨች፣ጠራችንና በቁጣ ድምጽ ይሄንን ነገር ከዚ ውሰዱልኝ ከዚህ በላይ ምንም ማድረግ አልችልም ከፈለጋችሁ ቡኮንም ምታረጉትን አርጉት ብላ በብስጭት አዛን ሄደች እኛም ተሸክመን ወደሚቀመጥበት ክፍል ወስደን ካስቀመጥነው ኋላ እያጉረመረመች ድፎው የተሸፈነበትን ቅጠል ገፈፍ ስታደርገው አታምኑኝም ለካ ድፎው  ይህንን ባየች ግዜ ይህች የቤታችን፡ሙያተኛ፡ሴት ወደ ላይ ወደ ጌታዋ ቀና ብላ "ውይ ጌታ ሆይ እንኳን ጸሎቴን፡አልሰማኸኝ እንኳን እንቢ አልከኝ ብትሰማኝ ኖሮ ደህና የበሰለው አሮብኝ ነበር" ብላ አመሰገነች ሚገርማችሁ እንደዛ ሾላ የሆነ ድፎ ከዛ አመት ኋላ የበላን ሁሉ አይመስለኝም። ➬    እና ተወዳጆች ጌታን እሺ ስላላችሁ ነገር ብዙ ዘመን አመስግናችሁታል ዛሬ ግን ከትልቅ፡ፍቅሩና ከኛ በላይ ለኛ ከማሰቡ የተነሳ እምቢ ስላለን፡ነገርም ጌታን እናመስግነው እየከለከለ አልሰማም እያለ እየጨከነብን ወዶናልና አድኖናልና። 📢YD✨ @Kekalu_Maid

〰〰〰〰〰〰ከ⃠ቃ⃠ሉ⃠ማ⃠ዕ⃠ድ⃠〰〰〰〰〰〰 አጭር ታሪክ ላጋራችሁ◦◦◦ 📌 በአንድ አገር የአገሩን ንጉሥ🤴 ለማየት ዘወትር የምትመኝና የምትፈልግ ሴት👩🏾 ነበረች አንድ ቀን ቆርጣ ንጉሱን ፍለጋ ወጣች። በድፍረት እሰከ ቤተ መንግሰት🏰 ድረስ ከብዙ ውጣ ውረድና ክልከላ በኃላ ደርሳ በመንበረ ዙፋኑ ፊት ቆመች ፤ ሰዎች "ለምን መጣሽ? ምን ትፈልጊያለሽ?" ሲሏት ፤ እሷም "የምፈልገውን እኔው ራሴ አውቃለሁ ፤ እሱንም ለንጉሡ እነግረዋለሁ" አለቻቸው። ወደ ንጉሡ የመቅረብ ተራው ደረሳትና ቀርባ እንዲህ አለቻቸው፦ "እርስዎን ማየት አንዱና የመጀመሪያው መሻቴ ነው፤ ሁለተኛው ደግሞ አንድ ቀን ወደ እኔ ቤት መጥተው እንደጎበኙኝ እፈልጋለሁ " አለቻቸው። ንጉሡ ተገረመና ፈገግ ብሎ "እሺ ወደ ቤትሽ መጥቼ እጎበኝሻለሁ"ብለው የመንገድ ባለስልጣኑን አስጠርተው "እኔ አንድ ቀን ይህችን ሴት ለመጎብኘት ቤቷ ስለምሄድ ሁኔታዎችን ሁሉ አመቻች" የሚል ትዕዛዝ ሰጥተው ሸኟት። ከዚያች ቀን ጀምሮ ከቤተመንግስት ጀምሮ አስከ መኖሪያ ቤቷ ድረስ ያለው መንገድ ተሰርቶ አስፋልት🛣 ለበሰ። ንጉሡ ከባለሥልጣኖቻቸው ጋር ሄደው የሚያርፉበት የእንግዶች ማረፊያ ቤት በሴትዋ ግቢ ተሠራ ለእንግዳ አስተናጋጆች ማረፊያ ቤት ለእርስዋና ለቤተሰቦቿ ቀለብ ተዘጋጀ ለንጉሱ ጉብኝትና አብረው ለሚመጡ እንግዶች ተገቢ ወጪ ሁሉ ተመደበ ፣ ለእርሷ ዋና መኖሪያ ቤት በቤተመንግስቱ አጠገብ ተዘጋጀላት። ዘወትር ስትገባና ስትወጣ ለማየት የተመኘችውን ንጉሡን እያየች እንድትኖር ተፈቀደላት፤ ቀን ወጣላት ማለት ነው።💠እኛም መንግስቱንና ፅድቁን ብንሻ የተመኘነው መንግስት ለዘላለም የእኛ ይሆናል። 📌የእግዚአብሔርን መንግሥትና ፅድቁን መፈለግ ይብዛልን🙌ማቴ 6:33
ከመጋቢ ዶ/ር ዮሐንስ ባሰና መድብለ ስብከት የተቀነጨበ
#ንጉሡን_መፈለግ @Kekalu_Maid

✔️        〘ከ〙〘ቃ〙〘ሉ〙 ◄►〘ማ〙〘ዕ〙〘ድ〙       ✔️ 📌ቆንጆ መዝሙር ነው❣ስሙት🧏‍♂ 💫 ጆሲ ፣ ህሊና እግዚአብሔር ይባርካቸው። ድንቅ የሕይወት እና የፀሎት መዝሙር ነው ያካፈሉን።🙏 https://youtu.be/DAgPW4CB08o?is=IDAJ6jKw0OVTys9H

☑️ "Ron Wyatt" ይባላሉ የክርስቶስን ደም🩸 በላቦራቶሪ እንዳጠኑት ይናገራሉ እንዲህ ሲሉ.....🧏 #ከቃሉ_ማዕድ Join|Follow|Share¶ @Kekalu_Maid

🔆 እግዚአብሔር የፅድቅ ሕይወትን የሰጠን ያለምንም የፅድቅ ስራ ነው። አዲስ ኪዳን የሚያስተምረን ለማይሰራ ኃጢአተኛውን በሚያፀድቅ ፣ ለሚያምን ሰው እምነቱ ፅድቅ ሆኖ ይቆጠርለታል። ሮሜ 4:5
📖መንፈሳዊ ብስለት📝ማሙሻ ፈንታ(ዶ/ር)
@Kekalu_Maid

Repost from Purity center
"ቅድስና የዘመን ክፋት ቀሎልን ሳይሆን የእግዚአብሔር ፀጋ በዝቶልን የምንኖረው ህይወት ነው።"
📖መንፈሳዊ ብስለት📝ማሙሻ ፈንታ(ዶ/ር) ገፅ52
#purity_center

"ማክስ ሎክድ የተባለ ዕውቅ ፀሐፊ የልጁን መልክ መምሰል በሚል መፅሐፋቸው አንድ ምናባዊ ጥያቄን ያቀርባሉ። አንድ ቀን ለ24 ሰዓታት ኢየሱስ አንተን መሆን ቢፈልግ እና ሁሉ ነገር እንዳለ ሆኖ ልብ ብቻ ብትቀያየሩስ? ይህ ምን ማለት እንደሆነ በጥያቄዎቹ ሲያብራራ በዚያን ቀን ያንተ ልብ ዕረፍት ወስዶ ህይወትህ በእርሱ ልብ ቢመራስ? የዕለት ባህርይህ ሁሉም የቀኑ ውሳኔዎች በዚህ ልብ ቢንቀሳቀሱ ምን ይፈጠር ይሆን?በዙሪያህ ያሉ ወዳጆችህስ ምን ለውጥ ያዩ ይሆን?በዚያ ዕለት ለማድረግ አቅደህ የነበረውን ሁሉ ታደርገው ነበር? ወደ ያዝካቸው ቀጠሮዎች ታቀና ነበር?ወይስ ልብህን ኢየሱስ ስለያዘው የሚቀየሩ አስተሳሰቦች እና እርምጃዎች ይኖሩ ይሆን? በማለት የልጁን መልክ መምሰል ይህ መሆኑን ያስረዳል።ፊል2:5 በመጥቀስ ሲያብራራ #እርሱ ኢየሱስ እንደማያስብ ማሰብ እራሱ እንደሚያደርግ ማድረግ ነው ይላል። በማስከተልም እግዚአብሔር ባለህበት ሁኔታ ይወድሃል ባለህበት ሁኔታ ግን ሊተውህ አይፈልግምኢየሱስንም እንድትመስል ነው የሚፈልገው።"
📖መንፈሳዊ ብስለት📝ማሙሻ ፈንታ(ዶ/ር)
#ከቃሉ_ማዕድ ¶Join | Follow | Share 🚩@Kekalu_Maid

#የመስቀል ሞት የሚካሄደው በሚሰቀለው ሰው ላይ በውርደት ላይ ውርደትን ፣ በዕረፍት ላይ ዕረፍትን እየከመሩ ከሰዎች  ተነጥሎ እንዲወገድ ማድረግ ነው። የመስቀል ሞት በቀዳሚነት #በአዋርጅነቱ ነው የሚመረጠው።...በተለይ በሮማውያን የሚሰቀሉ ሰዎች አስቀድመው ይገረፋሉ።...ተገራፊው የጀርባው ቆዳ እየተገሸለጠ የቆዳው ነጩ ክፍል መታየት የሚጀምረው ገና #በመጀመሪያዎቹ ግርፊያዎች ነው። ግርፋቱ ሲቀጥል የቆዳው ነጩ ክፍል ተተልትሎ የአጥንት ጡንቻዎቹ መቀደድ ይጀምራሉ። ይህ እጅግ ከባድ ሥቃይን ከማስከተሉም በላይ ለከባድ የደም ፍሰት ይዳርገዋል። የግርፋቱ ዓላማ የሚሰቀለውን ሰው ከስቅላቱ በፊት ክፉኛ እንዲዳከም ማድረግ ነው። በዚህም ላይ ከግርፋቱ ጋር በተገራፊው ላይ ማላገጥና መሳለቅ አይቀሬ ነው። ከዚህ ሁሉ በኃላ ፍርደኛው መስቀሉን ተሸክሞ ወደ መስቀያ ስፍራው እንዲሄድ ይደረጋል።
📖የተሰቀለው📝ጳውሎስ ፈቃዱ
📌📌📌 ፬፤ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው። 📌📌📌 👐 የማይገባንን ክብር ያከበረን እግዚአብሔር ይባረክ❕ #ሞተልኝ #ከቃሉ_ማዕድ@Kekalu_Maid

✔️        〘ከ〙〘ቃ〙〘ሉ〙 ◄►〘ማ〙〘ዕ〙〘ድ〙       ✔️ ---------------- ወደ ሮሜ ሰዎች ፱:፳፮-፳፱ ---------------- ፳፮፤ እናንተ ሕዝቤ አይደላችሁም በተባለላቸውም     ስፍራ በዚያ የሕያው እግዚአብሔር ልጆች ተብለው ይጠራሉ ይላል። ◦◦◦◦◦ ፳፱፤ ኢሳይያስም እንደዚሁ፦     ጌታ ፀባዖት ዘር ባላስቀረልን እንደ     ሰዶም በሆንን ገሞራንም በመሰልን ነበር ብሎ አስቀድሞ ተናገረ። ▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▿▵▿▵▿▵▿ ☣ በበደላችን እና በኃጢአታችን ምክንያት ሙታን በነበረን ጊዜ እኛ ሁላችን በአንድ ወቅት የሥጋችንን ምኞት እያረካን፣ መንገዱንም እየተከተልን በመካከላቸው እንኖር ነበር፤ እንደ ሌሎቹም የቍጣ ልጆች ነበርን። ነገር ግን እግዚአብሔር ያለፈን እንደ ሰዶም እና ገሞራ ጠፍተን ያልቀረነው ኃጢአት ስላልተገኘብን ሳይሆን በምሕረቱ ባለጠጋ የሆነ እግዚአብሔር ለእኛ ካለው ከታላቅ ፍቅሩ የተነሣ፣ በበደላችን ሙታን ሆነን ሳለን፣በፀጋው በክርስቶስ በኩል ሕያዋን አደረገን❕ 💥ሕዝቤ አይደላችሁም በተባልነው በዚያ ስፍራ የሕያው እግዚአብሔር ልጆች ተብለን የተጠራነው ከእኛ ባልሆነ ማዳን የፀጋው ባለጠግነት ይታይ ዘንድ ፀጋው በእምነት አድኖን ነው እንጂ ደሙን ሲያይ አለፈን እንጂ...📌የእኛ ነው ሰዶም የእኛው ነው ጎሞራ።💯💯💯 🤲በምህረቱ ባለጠጋ የሆነ፣ እውነትና ምህረት የታረቁበት፣ ልጆቹ ያደረገን፣ ፍቅር❤️‍🔥 የሆነው እግዚአብሔር አምላክ ስሙ ይባረክ‼️ #ባለምህረት ¶Join | Follow | Share 🚩@Kekalu_Maid #ከቃሉ_ማዕድ

sticker.webp0.32 KB