HOP Ministry
الذهاب إلى القناة على Telegram
HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28.
إظهار المزيدلم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
445
المشتركون
+224 ساعات
+237 أيام
+6630 أيام
أرشيف المشاركات
445
ሰሪያችን እግዚአብሔር ሆይ እጅህ ውስጥ ገብቶ እንደነበረ ሆኖ የሚወጣ ምንም የለም። ለሸክላ የመታደስ፣የመሰራት፣ እንደገና ውብ ሆኖና ሰሪው የሚፈልገውን ሌላ ቅርፅ ይዞ የመውጣት ዋስትናው የሸክላው ማንነት፣ ብልሽት፣ ተሰባሪነት ሳይሆን የሸክላ ሰሪው እጅ ነው፤ ምክንያቱም ሸክላው ምንም አይነት ሁኔታ ላይ ይሁን ሸክላ ሰሪው ባለቤት ነውና እንደገና፣ እንደወደደ አድርጎ ይሰራዋል።
ለዚህ ነው ሕይወታችንን፣ መንገዳችንን፣ ነገሮቻችንን የሰሪያችን እጅ ላይ አኑረን ማረፍ የሚገባን፤ ምክንያቱም እርሱ በእኛና በነገሮቻችን ሁሉ ላይ የወደደውን መስራት ይችላል። ስለዚህ እኛም ሁሉን ለእርሱ እያስገዛን፣ እኛንና የእኛ የሆነውን ሁሉ፦ ለሁሉን ቻይ እና ለታማኝ እጁ እየሰጠን በእረፍት እንኖራለን!!
ኤርምያስ 18 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ከእግዚአብሔር ወደ ኤርምያስ እንዲህ የሚል ቃል መጣ፦
² “ተነሥተህ ወደ ሸክላ ሠሪው ቤት ውረድ፤ በዚያ መልእክቴን እሰጥሃለሁ።”
³ እኔም ወደ ሸክላ ሠሪው ቤት ወረድሁ፤ ሸክላውንም በመንኵ ራኩር ላይ ይሠራ ነበር።
⁴ ከጭቃ ይሠራው የነበረውም ሸክላ በእጁ ላይ ተበላሸ፤ ሸክላ ሠሪውም በሚፈልገው ሌላ ቅርጽ መልሶ አበጀው።
⁵ የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፤
⁶ “የእስራኤል ቤት ሆይ፤ ሸክላ ሠሪው እንደሚሠራው፣ እኔ በእናንተ ላይ መሥራት አይቻለኝምን?” ይላል እግዚአብሔር፤ “የእስራኤል ቤት ሆይ፤ ጭቃው በሸክላ ሠሪው እጅ እንዳለ፣ እናንተም እንዲሁ በእጄ ውስጥ ናችሁ።
✍️ መክሊት አየለ
📆 December 13, 2023
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
445
የእግዚአብሔር ሕልውና የሌለበት የዓለም እልፍ ቀን የቱንም ያህል ለስጋችን ቢመች እረፍት የለበትም።
ስጋችን ሳይደላው፣ የምንፈልገውን ብዙ ነገር አጥተን ሳለን አብሮን ያለው የእግዚአብሔር ሕልውና ከብዙ ዓለማዊ ትርፍ ይበልጣል።
በዓለም ያለውን ነገር አሁን ባንጨብጠው እንኳን ብዙ እንደክማለን እንጂ ነገም ቢሆን ማግኘታችን አይቀርም፤ ባናገኘውም ያለ እርሱ መኖር እንችላለን። እግዚአብሔር ግን ትናንትን በአብሮነቱ ያሻገረን፣ የአሁን መኖሪያችን፣ ለነገም ተስፋችን የሆነ፤ መኖሩ ለእኛ መኖር ዋስትና የሆነ የመኖራችን ሕልውና ነው።
ከምንም በላይ ለእግዚአብሔር ሕልውና እና ከእርሱ ጋር ላለን ወዳጅነት ስፍራ እንስጥ! ከእርሱ ፊት እየራቅን ከእርሱ ጋር ያለን ሕብረት እየቀዘቀዘ በሄደ ቁጥር እየከሰምን፣ ሞገስ እያጣን፣ እየደረቅን ነው የምንሄደው።
"ከዓለም እልፍ ቀን ይልቅ
ከመኖር ከሕልውናህ ሩቅ
አንድ ቀን ቤትህ ይሻላል
መሸምገል ደግሞ እጅግ ይበልጣል
ግን አንድ ነገር እለምንሃለሁ
እርሷንም ደግሞ እጅግ እሻለሁ
በቤትህ ውስጥ ቀሪ ዘመኔን
እያየሁ መኖር ነው ውበትህን።"
👆🎶😇❤ Dawit Getachew
“በሌላ ስፍራ ሺህ ቀን ከመኖር፣ በአደባባይህ አንዲት ቀን መዋል ይሻላል፤ በክፉዎች ድንኳን ከመቀመጥ ይልቅ፣ በአምላኬ ቤት ደጅ መቆም እመርጣለሁ።”
— መዝሙር 84፥10 (አዲሱ መ.ት)
✍️ መክሊት አየለ
📆 June 26, 2022
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
445
#የአሳብ_ቅኝት!
አእምሮአችንን ከአሳብ ነጻ ልናደርገው አንችልም። ነገር ግን ምን ማሰብ እንዳለብን የመምረጥ መብቱ አለን። የሚያለማንን፣ የምናተርፍበትን፣ የሚያሳድገንን፣ ሕይወት ያለበትን ነገር መምረጥ የእኛ ድርሻ ነው።
በአእምሮአችን የሞላው አሳብ፦ ስሜት መውለዱ፣ ወደ ተግባርም መቀየሩ አይቀሬ ነው። ስለዚህ የምናስበው ነገር አሉታዊ በሆነ መጠን ከዚያ የሚመነጩት ስሜቶቻችንም አሉታዊና ሕይወታችንን ጽልመት የሚያለብሱ፣ ወደ ጥፋትም የሚመሩን መሆናቸው አይቀርም።
አብዛኞቻችን በማንፈልገው የስሜት ማዕበል ልንነዳ እንችላለን፤ ከስሜትም ነጻ የሆነ ሕይወት የለንም። ስሜቱ ግን፦ የሀዘን፣ የደስታ፣ የጭንቀት፣ የእረፍት፣ የብቸኝነት፣ የተፈላጊነት፣ ትኩረት የማጣት፣ በሰው የመከበብ፣ የባዶነት፣ የሙሉነት፣ የፍርሃትና የመሸማቀቅ፣ የድፍረትና በራስ የመተማመን....ወዘተ. አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ሊሆን ይችላል።
እነዚህ ሁሉ ስሜቶች እኛን ከፍ እና ዝቅ እያደረጉ፣ አንዴ ወደ ላይ አንዴ ደግሞ ወደታች ሲያደርጉን ትኩረት ነፍገናቸው፣ ምንጫቸው ምን እንደሆነ ሳናውቅና ሳንለይ፣ ደግሞም አሉታዊውን ስሜት ፈጣሪውን የችግር ምንጭ ለይተን፣ አውቀን ለማስተካከል ካልሰራንበት፦ ስሜታችን የእኛ ገዢ ሆኖ፣ እኛም በእርሱ እየተነዳን ስንንገላታ እንኖራለን።
በእኔ ምልከታ የስሜቶቻችንን ማዕበል ለመቆጣጠር፣ የስሜት መዋዥቅም ገንዘቡ እንዳያደርገን የችግሩ ዋና መሠረት፣ ምንጩ ላይ መስራት አለብን፤ ከውስጥ ሰውነት የሆነ ለውጥም ያስፈልገናል ባይ ነኝ።
ማንኛውም ከውጭ ወደ ውስጥ የምናስገባቸው ነገሮች፣ ለምሳሌ፦ ስሜቶቻችንን ለመቆጣጠር፣ ለማስተካከል፣ ካለንበት ስሜት ለመውጣት ወይንም ወደ አንድ ተፈላጊ የስሜት ክልል ውስጥ ለመግባት ይረዱናል ብለን ወደ ውስጣችን የምናስገባቸው ነገሮች፤ ለምሳሌ የተለያዩ አደንዛዥ እጾች በወሰድናቸው ቅጽበት የሚያመጡት ውጤት አለ፤ የፈለግነውንም ስሜት ለማግኘት ይረዱናል፤ ነገር ግን በጊዜ ሂደት የእነርሱ ጥገኛ እየሆንን እንሄዳለን። የምንፈልገውን ስሜት፣ ለምሳሌ ደስታን ለማግኘት የግድ ከውጭ ወደ ውስጣችን የምናስገባው ነገር መኖር አለበት። ከነገሩ ጋር ያለን ንክኪ ሲቋረጥ ደግሞ መልሰን ወደማንፈልገው የስሜት እስራት ውስጥ እንገባለን።
ይሄ አዙሪት ስር ነቀል ለውጥ ስለማያመጣ እውነተኛ መፍትሔ ከማይገኝበት ሀሰተኛ ምንጭ ጋር ተጣብቀን እንድንኖር፣ ሕያው የውሃ ምንጭ የሆነውን እግዚአብሔርን ትተን፣ ውሃ መያዝ የማይችሉትን ቀዳዳ የውሃ ማጠራቀሚያ ጉድጓዶች ለራሳችን ስንቆፍር ጊዜያችን እንዲባክን ያደርጋል።
ከእግዚአብሔር የሆነው ፍጹሙ፣ ቅዱሱ የእግዚአብሔር ቃል የሚያስተምረን ለውጥ፦ ከውጪ ወደ ውስጥ የሚደረግ ሳይሆን፦ በውስጥ ሰውነታችን የሚደረግ ደግሞ ከውስጥ ጀምሮ ሁለንተናችንን፣ የውጪውን ሕይወትና ተግባራችንን ሁሉ የሚቆጣጠር ለውጥ እንደሆነ ነው።
አሳባችንን፣ ስሜቶቻችንን፣ ተግባራችንን ለመግራት፣ የምናደርገው ጥረት ውጤታማ የሚሆነው ምንጫችንን፣ የተተከልንበትን መሠረት ስናስተካክል ነው።
ስለዚህ የውስጥ ሰውነታችንን ዘወትር ለእግዚአብሔር ክፍት ማድረግ፣ መንፈስ ቅዱስ እንዲቆጣጠረንና በአእምሮአችን፣ በልባችን መታደስ እንድንለወጥ እንዲረዳን መፍቀድ ቁልፍ ነገር ነው።
በተለምዶው ለሰው ልጅ መገልገያነት ከምንጠቀምባቸው ቁሶች መካከል፦ የጁስ መፍጫን እንደምሳሌ ብንወስድ የሚሰጠን ውጤት የሚመሰረተው በሰጠነው ጥሬ እቃ፣ ግብአት ላይ ነው። አቮካዶ ሰጥተነው የብርቱካን ጭማቂ አይሰጠንም። ግን ደግሞ ምንም ሰጠነው ምን የግብአት ምርጫውን ጉዳይ ለእኛ ትቶት መደበኛ ስራውን መስራቱን ይቀጥላል፤ ይፈጫል።
ልክ እንደዚህ ምሳሌ የእኛ አእምሮም የሰጠነውን ሁሉ ተቀብሎ ማጠንጠን፣ ማብላላት መፍጨት፣ ማሰቡን አይተውም፤ ወደድንም ጠላንም እንደተሰጠው ግብአት መልካምም ሆነ ክፉውን ማሰቡን፣ ስሜት መፍጠሩን፣ ወደ ተግባር መቀየሩንም አያቆምም።
ብልሆች ከሆንን መሠረታችንን፣ ምንጫችንን እግዚአብሔር ላይ፣ ቃሉ ላይ፣ የመንፈስ ፍሬ የሆኑት ነገሮች ላይ፦
( የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም፣ ትዕግሥት፣ ቸርነት፣ በጎነት፣ ታማኝነት፣ ገርነት፣ ራስን መግዛት ነው። እንደነዚህ ያሉትንም የሚከለክል ሕግ የለም። ---ገላትያ 5:22-23 (አዲሱ መ.ት))
መጽሐፍ ቅዱስ አስቡ የሚለን ነገር ላይ፦
(“በመጨረሻም ወንድሞች ሆይ፤ እውነት የሆነውን ሁሉ፣ ክቡር የሆነውን ሁሉ፣ ትክክል የሆነውን ሁሉ፣ ንጹሕ የሆነውን ሁሉ፣ ተወዳጅ የሆነውን ሁሉ፣ መልካም የሆነውን ሁሉ፣ በጎነት ቢሆን ወይም ምስጋና፣ እንደ እነዚህ ስላሉት ነገሮች አስቡ።”
— ፊልጵስዩስ 4፥8 (አዲሱ መ.ት))
በመትከል፣ በማጽናት በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ከውስጥ ሰውነት የሆነ ለውጥን መለወጥ፣ አሳባችንን እና ስሜቾቻችንን በእግዚአብሔር ቃል፣ በእግዚአብሔር መንፈስ የተቃኙ ማድረግ፣ ወደ ሞት ከሚነዳን ክፉ የአሳብና የስሜት ማዕበል ማምለጥ፣ ተግባራችንንም እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ማድረግ እና በእረፍት በፍጹም ሰላም ውስጥ መኖር እንችላለን።
“በመጨረሻም ወንድሞች ሆይ፤ እውነት የሆነውን ሁሉ፣ ክቡር የሆነውን ሁሉ፣ ትክክል የሆነውን ሁሉ፣ ንጹሕ የሆነውን ሁሉ፣ ተወዳጅ የሆነውን ሁሉ፣ መልካም የሆነውን ሁሉ፣ በጎነት ቢሆን ወይም ምስጋና፣ እንደ እነዚህ ስላሉት ነገሮች አስቡ።”
— ፊልጵስዩስ 4፥8 (አዲሱ መ.ት)
✍️ መክሊት አየለ
📆 June 25, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
445
አሳባችንን፣ ስሜቶቻችንን፣ ተግባራችንን ለመግራት፣ የምናደርገው ጥረት ውጤታማ የሚሆነው ምንጫችንን፣ የተተከልንበትን መሠረት ስናስተካክል ነው።
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
t.me/hopministry10
445
ከኢየሱስ ጋር የቆየ፣ ሳይታክት ኢየሱስ ላይ ያተኮረ፣ ኢየሱስን ካወቀው ይልቅ ለማወቅ የተጋ ሰው የተሰወረ የዕውቀትና የጥበብ መዝገብ ባለቤት ይሆናል። የእግዚአብሔር ምስጢር፣ የእግዚአብሔር ጥበብ የሆነው ክርስቶስ ኢየሱስ ይብራራለታል።
የተሰወረ የጥበብና የዕውቀት ሀብት ሁሉ በኢየሱስ ውስጥ አለ። ዕውቀት ወዴት አለ? ጥበብስ ከየት ይገኛል? ካልን አንድያ የእግዚአብሔር ልጅ ወደ ሆነው ወደ ኢየሱስ ዘንበል፣ ጥግት ማለት የግድ ያስፈልገናል። ምክንያቱም እግዚአብሔር አብ ዕውቀትንም ሆነ ጥበብን ከእርሱ ወዲያ ላይኖር በኢየሱስ ዘግቶታል!!
ፍጹም የሆነውን የመረዳት ብልጥግና ካገኘን ለሌላ ለምንም ሳይሆን የእግዚአብሔር ምስጢር የሆነውን ክርስቶስ ኢየሱስን ለማወቅ ነው!! እግዚአብሔር ኢየሱስን በምናውቅበት ፍጹም በሆነው የመረዳት ባለጠግነት ይባርከን!!
ቆላስይስ 2 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
² ደግሞም ልባቸው እንዲጽናናና በፍቅር እንዲተሳሰሩ፣ ፍጹም የሆነውን የመረዳት ብልጥግና አግኝተው የእግዚአብሔር ምስጢር የሆነውን ክርስቶስን እንዲያውቁ እተጋለሁ፤
³ የተሰወረ የጥበብና የዕውቀት ሀብት ሁሉ የሚገኘው በእርሱ ዘንድ ነውና።
✍️ መክሊት አየለ
📆 June 24, 2024
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
445
#አይዘገይም!!
2ኛ ጴጥሮስ 3 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ ወዳጆች ሆይ፤ በጌታ ዘንድ አንድ ቀን እንደ ሺህ ዓመት፣ ሺህ ዓመትም እንደ አንድ ቀን መሆኑን ይህን አንድ ነገር አትርሱ።
⁹ አንዳንድ ሰዎች የዘገየ እንደሚመስላቸው ጌታ የተስፋ ቃሉን ለመፈጸም አይዘገይም፤ ነገር ግን ማንም እንዳይጠፋ ፈልጎ፣ ሁሉ ለንስሓ እንዲበቃ ስለ እናንተ ይታገሣል።
¹⁰ የጌታ ቀን ግን እንደ ሌባ ይመጣል፤ በዚያች ቀን ሰማያት በታላቅ ድምፅ ያልፋሉ፤ የሰማይም ፍጥረት በእሳት ይጠፋል፤ ምድርና በእርሷም ላይ ያለ ነገር ሁሉ ይቃጠላል።
¹¹ እንግዲህ ሁሉም ነገር በዚህ ሁኔታ የሚጠፋ ከሆነ፣ እናንተ እንዴት ዐይነት ሰዎች ልትሆኑ ይገባችኋል? አዎን፣ በቅድስናና በእውነተኛ መንፈሳዊነት ልትኖሩ ይገባችኋል፤
¹² ደግሞም የእግዚአብሔርን ቀን እየተጠባበቃችሁ መምጫውን ልታፋጥኑ ይገባል። በዚያን ቀን ሰማያት በእሳት ተቃጥለው ይጠፋሉ፤ የሰማይም ፍጥረት በታላቅ ትኵሳት ይቀልጣል።
¹³ እኛ ግን ጽድቅ የሚኖርበትን አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር በተስፋ ቃሉ መሠረት እንጠባበቃለን።
¹⁴ ስለዚህ ወዳጆች ሆይ፤ እነዚህን ሁሉ ነገሮች የምትጠባበቁ ስለ ሆናችሁ፣ ያለ ነውርና ያለ ነቀፋ ከእርሱ ጋር በሰላም እንድትገኙ ትጉ።
¹⁵ የጌታችን ትዕግሥት እናንተ እንድትድኑ እንደሆነ አስቡ፤
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
445
“አንዳንድ ሰዎች የዘገየ እንደሚመስላቸው ጌታ የተስፋ ቃሉን ለመፈጸም አይዘገይም፤ ነገር ግን ማንም እንዳይጠፋ ፈልጎ፣ ሁሉ ለንስሓ እንዲበቃ ስለ እናንተ ይታገሣል።”
— 2ኛ ጴጥሮስ 3፥9 (አዲሱ መ.ት)
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
t.me/hopministry10
445
#ያለ_ቅድመ_ሁኔታ_የሆነ_እምነት!
ለአብርሃም ከእግዚአብሔር በመጀመሪያ የቀረበለት ጥሪ እንተዋወቅ የሚል አልነበረም። ምንም የመሰረቱት ግንኙነት፣ ትውውቅ ሳይኖር የራሴ የሚለውን ነገር ሁሉ የሚያስጥል፣ የሚያስክድ እንዲሁም እግዚአብሔር ወደሚያሳየው ምድር የመውጣት፣ እግዚአብሔርን የመከተል ጥሪ ነበር።
እግዚአብሔር ለአብርሃም ተለይቶ የመውጣት ጥሪ ሲያቀርብለት አብርሃም #WH_QUESTIONS? (What, why, How, who, when, Where, Which, whom) አላቀረበም፤ ቆም ብሎም አላሰበበትም፣ አላንገራገረም፣ አልተከራከረም፣ ስለ መንገዱም ማብራሪያ አልጠየቀም፤ ይልቁንም በደፈናው እግዚአብሔርን አመነውና እግዚአብሔር እንደ ነገረው ሄደ፣ ተከትሎት ሄደ፣ እግዚአብሔር ወደ ሚያሳየው ምድር ለመሄድ ወጣ።
የአብርሃም እምነት እጅግ ያስገርማል! የተናገረውን፣....ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ውጣ ያለውን እግዚአብሔርን የሰማበት መስማት ምን አይነት ይሆን? እርሱ ይናገር እንጂ፣ የእርሱ ይሁን እንጂ የትስ ቢሆን በሚል ልበ ሙሉነት፤ በመንገዴ ላይ፣ በመንገዴም መጨረሻ ላይ ምን ይገጥመኝ ይሆን? ብሎ ሳይጠይቅ የተናገረውን እግዚአብሔርን ለመከተል ወጣ። ከመንገዱ፣ ከማያውቀው አገር፣ ሊገጥመው ከሚችለው ችግር ፍርሃት በላይ የጠራውን እግዚአብሔርን አመነ።
እግዚአብሔር ከተናገረ፦ በምን፣ በማን፣ መቼ፣ እንዴት...የሚሉት ጥያቄዎች ሳያሳስቡት የተናገረውን ይፈጽማል። እኛስ ይህንን ከቅድመ ሁኔታ በላይ፣ ከእኛ ስጋት በላይ፣ ከእኛ አለመቻልና ውስንነት በላይ፣ ከምንለምነውና ከምናስበው በላይ መስራት የሚችለውን እግዚአብሔርን ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ፣ ያለማንገራገር ለማመን፣ እንደ ነገረን ተለይተን ለመውጣት ምን ያህል ቅርብ ነን?
✍️ መክሊት አየለ
📆 August 21, 2024
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
445
እግዚአብሔርን ማስረጃ ሳንጠይቅ፣ ቅድመ ሁኔታ ሳናስቀምጥ ማመን፣ ልባችንን እርሱ ላይ መጣል፤ የሕይወታችንን መሪ ሙሉ በሙሉ ለእርሱ መልቀቅ ይሁንልን!!
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
t.me/hopministry10
445
በታጠቁ፣ በተሰሩ፣ በተዘጋጁ ሰዎች መስራት የእግዚአብሔር ደስታው ነውና በእርሱ እንሰራ፣ እንታጠቅ፣ ለአገልግሎቱ እንደሚገባ እንዘጋጅ!!
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
t.me/hopministry10
445
#ምርጥ_ምርጡን_ለእግዚአብሔር!
አገልግሎት የእኛን ትጋት፣ ጥረት መጋደል ቢጠይቅም "Content wise" ከመልዕክት ይዘት አንጻር ግን የእኛን ምንም አይፈልግም። የምናቀርበው መልዕክት እግዚአብሔር ራሱ፣ የመልዕክቱ ሰጪም እርሱ ራሱ፣ መልዕክቱ የሚያወራውና የሚሰብከው እርሱን፣ ሥራውን፣ ማዳኑን፣ ፍቅሩን ነውና የእኛ የምንለው ምንም ነገር አያስፈልግም፤ ሊኖርበትም አይገባም።
"Presentation wise" ከአቀራረብ አንጻር፣ መልዕክቱን ከምናቀርብበት መንገድ (Technics) አንጻር ግን መማር፣ መሰልጠን አለብን።
የእግዚአብሔር የሆነውን ነገር ለማቅረብ ልህቀት (Excellence) ያስፈልገናል። ዘመኑ ያመጣቸውን የተለያዩ መንገዶች (Technologies) በጥበብ መጠቀም፣ በአግባቡ ለእግዚአብሔር ሥራ መዋጀት አለብን።
የመልዕክቱ ሰጪ እና መልዕክቱ ዘመን አመጣሽ፣ ደግሞም ዘመን ያለፈበትና ዘመን የሚሽረው አይደለም። የምናዘምነው እግዚአብሔርም የለም። እርሱ ከዘመናት በፊት የነበረ፣ ያለ፣ ለዘላለምም የሚኖር ሕያው አምላክ ነው። ነገር ግን ይሄን ዘላለማዊ አምላክ የምንገልጥበት፣ መልዕክቱንም ለትውልዶች የምናስተላልፍበት መንገድ እንደየ ዘመናቱ ሊቃኝ፣ ዘመን አመጣሽ ነገሮችን ዋጅቶ ሊጠቀም ይችላል።
እግዚአብሔርን ለማገልገል ሸክሙ ካለን፣ ጥሪውን እግዚአብሔር ካቀረበልን መልዕክቱንም ይሰጠናል፤ እድል፣ ጊዜ፣ ትውልድና መድረክም ይቸረናል።
ይሄ ሁሉ ሲሆን ግን እኛ ለአገልግሎቱ እንደሚገባ ያልተዘጋጀን፣ ያልታጠቅን፣ ያልተሰራን፣ ያልተገራን፣ ያልሰለጠንን፣ መማር የሚገባንን ነገር ሁሉ ያልተማርን ከሆንን ከእግዚአብሔር አሳብ ጋር እንተላለፋለን፤ የእግዚአብሔርንም አሳብ በልህቀት (Excellence) ለትውልዶች ማቅረብ አንችልም።
የእግዚአብሔር መንግሥት፣ ሥራውም ምርጥ የተባለ ነገር ሁሉ ይገባዋል። ምርጥ የተባሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን፣ መንገዶችን በጥበብ እየዋጀን ለመንግሥቱ ሥራ ልናውል ይገባናል።
እኛ የመንግሥቱ አገልጋዮችም የነቃን፣ የበቃን (የታጠቅን፣ የተማርን፣ የሰለጠንን)፣ ከእግዚአብሔር ጋር በመክረም፣ በመሰንበት ከእርሱ፣ ከቃሉ የተማርን፣ በጸሎት የተጋን፣ ከእግዚአብሔር ሥራ በፊት ሕይወታችን በእርሱ የተሰራ ልንሆን ይገባናል።
ስለዚህ ሰከን ሳንል፣ ለእግዚአብሔር ሳንገኝ፣ በእርሱ ለመሰራት ፈቃደኛ ሳንሆን፣ በትምህርት እና በስልጠና፣ በዝግጅትም ራሳችንን ሳናበቃ እናገለግላለን ብለን አንጋጋጥ። ለአገልግሎት ያለንን መሻት፣ ትጋት ያህል፤ ለመማር፣ ለመዘጋጀት፣ ለእግዚአብሔር ለመገኘት፣ በእርሱ ለመሰራት፣ ለመገራት፣ ከእርሱ ጋር ለመዋል፣ ከእርሱ ለመቅዳት መሻት፣ ትጋት ይኑረን።
ምርጥ ምርጡ ሁሉ ለእግዚአብሔር፣ ለመንግሥቱ ሥራም ያስፈልጋልና በጥበብ እየዋጀን ለመንግሥቱ ሥራ እናውለው። የእግዚአብሔርንም መንግሥት እናስፋበት!!
በታጠቁ፣ በተሰሩ፣ በተዘጋጁ ሰዎች መስራት የእግዚአብሔር ደስታው ነውና በእርሱ እንሰራ፣ እንታጠቅ፣ ለአገልግሎቱ እንደሚገባ እንዘጋጅ!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 June 21, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
445
ሊያገኘን፣ ከእኛ ጋር ሕብረት ሊያደርግ ናፍቆ እየጠበቀን ነው!!
“እግዚአብሔር በሚገኝበት ጊዜ ፈልጉት፤ ቀርቦም ሳለ ጥሩት።”
— ኢሳይያስ 55፥6 (አዲሱ መ.ት)
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
t.me/hopministry10
445
ሊያገኘን፣ ከእኛ ጋር ሕብረት ሊያደርግ ናፍቆ እየጠበቀን ነው!!
“እግዚአብሔር በሚገኝበት ጊዜ ፈልጉት፤ ቀርቦም ሳለ ጥሩት።”
— ኢሳይያስ 55፥6 (አዲሱ መ.ት)
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
t.me/hopministry10
445
#የዘላለም_ሕይወት እውነተኛ አምላክ ከሆነው ከእግዚአብሔር እንዲሁም የሕይወት ምንጭ ከሆነው ከልጁ ከኢየሱስ ክርስቶስ ውጪ በምንም አይገኝም።
እውነተኛ እና ብቸኛ አምላክ የሆነውን እግዚአብሔርን ፤ እርሱ የላከውንም ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅ ጊዜያዊ ጉዳይ ሳይሆን የዘላለም ሕይወት ነው።
እውነተኛ አምላክ የሆነውን እግዚአብሔር አብን፣ እርሱም የላከውን አንድያ ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅ እንደ ሌሎች የእውቀት አይነቶች አዕምሮን ለማስፋት፣ ለመረጃ ምንጭነት፣ ጠቢብ እና አዋቂ ለመባል፣ የተለያዩ ክህሎቶችን ለማግኘት ማወቅ ያለብን እውቀት ሳይሆን የሕይወት ጉዳይ ነው፤ ያውም የዘላለም ሕይወት ነው።
እግዚአብሔር አብን፣ ልጁንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያወቁ እርሱን ያዩ፣ ከእርሱ ሕይወትን የተካፈሉ ሰዎች ምስጉኖች ናቸው፤ የዘላለም ሕይወት አላቸው።
የዘላለም ሕይወት የሆነ፣ የዘላለም ሕይወት የሚገኝበት እውቀት እግዚአብሔርን ማወቅ ነው። እግዚአብሔርን ላለማወቅ ልባችንን ስናደነድን እና ቸልተኞች ስንሆን የዘላለም ሕይወትን ችላ እያልን እንደሆነ እናስተውል!!
አስተማሪ የሆነው፣ የእውነት መንፈስ፦ መንፈስ ቅዱስ ዕለት ዕለት እግዚአብሔርን እንድናውቅ፣ ከእርሱ ጋር ይበልጥ እንድንወዳጅ ይርዳን!!
“እውነተኛ አምላክ የሆንኸውን አንተንና የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።”
— ዮሐንስ 17፥3 (አዲሱ መ.ት)
✍️ መክሊት አየለ
📆 January 20 & August 19, 2022
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
