ar
Feedback
የቀጠናው ተመልካች

የቀጠናው ተመልካች

الذهاب إلى القناة على Telegram

በአለማችን ቀጠናዎች የሚከሰቱ ክስተቶችን ይዘግባል፣ ሳይቀዘቅዝ በትኩሱ። ለጥያቄና ለአስተያየቶች በኢሜል asuleyma246@Gmail.com ብላችሁ ፃፉልኝ።

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
4 308
المشتركون
-324 ساعات
-237 أيام
-8630 أيام
أرشيف المشاركات
⚡🇺🇸🇮🇷 ፕሬዝዳንት ትራምፕ፣ 60 ቀናት የሚባለው የድርድር የጊዜ ገደብ ብዙም የሚያሳስበው እንዳልሆነ ተናገረ። "
ከዚያ በላይ ሊወስድ ይችላል፣ በ60 ቀናት ውስጥ ካልሆነ ብዬ የሙጥኝ የምል አይደለሁም። ሲሆን ይሆናል፣ ዋናው ነገር ተግባራቸው ጥሩ ይሁን። ከዛ በተረፈ ብዙ አላስብም።"

🇷🇺🇮🇷⚡️ - የኢራን ቀይ ጨረቃ ማህበር (IRCS) ለአደጋ ጊዜ ምላሽ እና እፎይታ የሚሰጡ 20 M-171 ሄሊኮፕተሮችን ለመግዛት ከሩሲያ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርማለች። ሄሊኮፕተሮቹ፣
🇷🇺🇮🇷⚡️ - የኢራን ቀይ ጨረቃ ማህበር (IRCS) ለአደጋ ጊዜ ምላሽ እና እፎይታ የሚሰጡ 20 M-171 ሄሊኮፕተሮችን ለመግዛት ከሩሲያ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርማለች። ሄሊኮፕተሮቹ፣ ለነብስ አድን፣ ለህክምና፣ ለእሳት አደጋ መከላከያ እና ለሌሎች የአደጋ ጊዜ ስራዎች ያገለግላሉ። የምሽት እይታ አቅም እና ልዩ የህክምና መሳሪያዎችን ጨምሮ ዘመናዊ ሥርዓቶችንም የታጠቁ ሄሊኮፕተሮች ናቸውም ተብሏል። የመጀመሪያዎቹ አራት ሄሊኮፕተሮች በመጪው ወራቶች እንዲደርሱ መርሐግብር ተይዞላቸዋል። *-*--* ጦርነቱ በቆመ በማግሥቱ፣ 20 ሄሊኮፕተር፣ እረ እነዚህ ሀብታም ናቸው ባክህ። አስቡት፣ ይሄን የሚያደርጉት ከዓለም ኃያላን ጦር ኃይሎች ጋር ጦርነት አድርገው 'ከደቀቁ' በኋላ ነው። እኛ ብንሆን ብላችሁ አስቡት፣ ሂሮሽማ ሆነን ነበር፣ አይደለም በማግስቱ ቀና ብለን፣ ለቀይ መስቀላችን ወጪ ልናወጣ ይቅርና። ትዝ ይላችኋል የዛሬ ሦስት ዓመት ገደማ ሰሜን ተራሮች ላይ እሳት ተነስቶ? እሳቱን የሚያጠፋልን አጥተን እንደ አንቡላንስ ዋይ ዋይ ስንል? ከስንት ዲፕሎማሲያዊ ዋይታ በኋላ ነበር ከእስራኤል መንግሥት የሆነች አንዲት ሚጢጢ ሄሊኮፕተር መጥታ ውሃ በባሊ እየዛቀች ያጠፋችልን። ያቺ ሚጢጢ እንኳ አልነበረችንም። እኛማ'ኮ ደሃ ነን! አስተዳዳሪዎቻችን የአእምሮ ደሃዎች፣ የማሰብ ችሎታቸው ኔጌቲቭ የሆነ ስለሆኑ፣ ሀገራችንም እንደዛ ሆናለች። ያጣች የገረጣች በአጥንቷ የምትሄድ ደሃ! መከላከያ የሚባለውም ተቋም ቢሆን በጣት የሚቆጠሩ፣ ከታጃኪስታን ግምዣ ቤት የሚነዳቸው አጥተው የበሰበሱ ሄሊኮፕተሮች ናቸው ያሉት። እንዲያውም አንዱ በትግራይ ጦርነት ጊዜ ተከስክሷል መሰለኝ። እነሱን በያመቱ አንዴ አረንጓዴ፣ አንዴ ውሃ ሰማያዊ እየቀቡ … እረ ተውት የኛን ነገር።

🇷🇺🇮🇷⚡️ - የኢራን ቀይ ጨረቃ ማህበር (IRCS) ለአደጋ ጊዜ ምላሽ እና እፎይታ የሚሰጡ 20 M-171 ሄሊኮፕተሮችን ለመግዛት ከሩሲያ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርማለች። ሄሊኮፕተሮቹ፣
🇷🇺🇮🇷⚡️ - የኢራን ቀይ ጨረቃ ማህበር (IRCS) ለአደጋ ጊዜ ምላሽ እና እፎይታ የሚሰጡ 20 M-171 ሄሊኮፕተሮችን ለመግዛት ከሩሲያ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርማለች። ሄሊኮፕተሮቹ፣ ለነብስ አድን፣ ለህክምና፣ ለእሳት አደጋ መከላከያ እና ለሌሎች የአደጋ ጊዜ ስራዎች ያገለግላሉ። የምሽት እይታ አቅም እና ልዩ የህክምና መሳሪያዎችን ጨምሮ ዘመናዊ ሥርዓቶችንም የታጠቁ ሄሊኮፕተሮች ናቸውም ተብሏል። የመጀመሪያዎቹ አራት ሄሊኮፕተሮች በመጪው ወራቶች እንዲደርሱ መርሐግብር ተይዞላቸዋል። *-*--* ጦርነቱ በቆመ በማግሥቱ፣ 20 ሄሊኮፕተር፣ እረ እነዚህ ሀብታም ናቸው ባክህ። ትዝ ይላችኋል የዛሬ ሦስት ዓመት ገደማ ሰሜን ተራሮች እሳት ተነስቶ? እሳቱን የምታጠፋ አንዲት ሄሊኮፕተር ከስንት ዲፕሎማሲያዊ ምልልስ በኋላ ከእስራኤል መንግሥት መጥታ ነበር ውሃ በባሊ እየዛቀች ያጠፋችልን። እኛማ'ኮ ደሃ ነን! አስተዳዳሪዎቻችን የአእምሮ ደሃዎች፣ የማሰብ ችሎታቸው ኔጌቲቭ የሆነ ስለሆኑ፣ ሀገራችንም እንደዛ ሆናለች። ያጣች የገረጣች እና በአጥንቷ የምትሄድ! መከላከያ የሚባለውም ተቋም በጣት የሚቆጠሩ፣ ከታጃኪስታን ግምዣ ቤት የሚነዳቸው አጥተው እየበሰበሱ የነበሩ ሄሊኮፕተሮች ናቸው ያሉት። እነሱን በያመቱ አንዴ አረንጓዴ፣ አንዴ ውሃ ሰማያዊ እየቀቡ … እረ ተውት የኛን።

🇮🇷| የኢራን ዋና ተደራዳሪ እና ፓርላማ መሪ፡ ጋሊባፍ፡ የፊት መስመሩን ተረክበው በጽናት በመቆም ጦርነቱን በአመርቂ ሁኔታ እንደተወጡት ሚሳዬል ኦፕሬተሮቻችን ሁሉ፣ እኛም፣ ሕዝባችንን ከኢኮኖሚ ጫና ለማላቀቅ እንደ እነሱ በጽናት መቆም እና ተግባራችንን መወጣት አለብን።

🇧🇬❗️የአውሮፓ ኮሚሽን በሩሲያ ላይ 21ኛውን የማዕቀብ ዙር ፓኬጅ አሳልፏል። የሩሲያ ፓትሪያርክ ኪርልን፣ ማዕቀብ ውስጥ ለማካተት ሐሳብ አቅርቧል። ማዕቀቡ ካለፈ፣ ፓትርያርኩ በአውሮፓ በየትም እን
🇧🇬❗️የአውሮፓ ኮሚሽን በሩሲያ ላይ 21ኛውን የማዕቀብ ዙር ፓኬጅ አሳልፏል። የሩሲያ ፓትሪያርክ ኪርልን፣ ማዕቀብ ውስጥ ለማካተት ሐሳብ አቅርቧል። ማዕቀቡ ካለፈ፣ ፓትርያርኩ በአውሮፓ በየትም እንዳይዘዋወሩ፣ መንፈሳዊ አገልግሎት በሀገራቱ እንዳይሰጡ ያግዳል፣ እንደ POLITICO ዘገባ። ይህን በሩሲያ ፓትርያርክ ላይ የተጣለውን ማዕቀብ ቡልጋርያ መቃወሟን አሳይታለች፣ POLTICO ሁለት ዲፕሎማቶችን ጠቅሶ እንደዘገበው። በቅርብ ቀናት ውስጥ፣ የቡልጋሪያ ሚዲያዎች ቡልጋሪያ የሩስያ መንፈሳዊ መሪን ለመጠበቅ እንደምትሞክር ዘግቧል። 

🇺🇸🇮🇳⚡️ - የሕንድ ዘጋቢ - ሚስተር ፕሬዝዳንት፣ በኢራን ግጭት ውስጥ ሰላም በማምጣት ታሪክ ሊሰሩ ጫፍ ላይ ነዎት... ትራምፕ፡ ይህን ሰው ወድጄዋለሁ። ጋዜጠኞቻችሁ ከኛ የበለጡ በጣም አሪፎች ናቸው (የኛማ አሉ፣ ነቋሪዎች!)።

🇺🇸 / 🇮🇳 ፕሬዝዳንት ትራምፕ በሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ላይ ሙድ ይዞበታል - 'እሱ በጣም ቆንጆ መልክ ያለው ሰው ነው። እንደ መልአክ ነው። በእውነቱ ግን እሱ ገዳይ ነው፣ አደገኛ ገዳይ።

🇷🇺🇺🇦⚡️ - ሩሲያ ባልተለመደ መልኩ፣ በዚህ ወር ቤንዚን በባህር ለማስመጣት በዝግጅት ላይ መሆኗ ተነገረ። የዩክሬን ድሮኖች በማጣሪያዎች፣ በቧንቧ መስመሮች እና በማከማቻ ተቋማት ላይ ባደረሱት
🇷🇺🇺🇦⚡️ - ሩሲያ ባልተለመደ መልኩ፣ በዚህ ወር ቤንዚን በባህር ለማስመጣት በዝግጅት ላይ መሆኗ ተነገረ። የዩክሬን ድሮኖች በማጣሪያዎች፣ በቧንቧ መስመሮች እና በማከማቻ ተቋማት ላይ ባደረሱት ተከታታይና ቀጣይነት ባለው ጥቃት ምክንያት የሚፈጠረውን የነዳጅ እጥረት ለማቃለል ያለመ እርምጃ ነው ሲል ሮይተርስ ዘግቧል። ➡️ ሩሲያ በሰኔ ወር በአንዱ ምዕራባዊ ወደቦቿ በኩል የነዳጅ ጭነት ትቀበላለች ተብሎ ይጠበቃል፣ ምናልባትም ከእስያ የሚመጣ ሊሆን ይችላል። ➡️ ሩሲያ ነዳጅ ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ፊቷን ወደ ቤላሩስ አዙራለች፣ ከዚህ ቀደምም ከካዛኪስታን ለማስገባት ጥረት አድርጋለች። ቢሆንም፣ ሁለቱም ሀገሮች የአቅርቦት እጥረቱን ለማካካስ የሚያስችል በቂ ትርፍ አቅም እንደሌላቸው ምንጮች ይናገራሉ። በባሕር ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶች በሎጂስቲክስ ተግዳሮቶች እና ከፍተኛ ወጪዎች ምክንያት የተወሰነ እፎይታ ብቻ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። *-*-* ሩሲያንማ በደንብ አድቅቀዋታል። እስከ 40% የሚደርስ የነዳጅ ማውጣትና ማጣራት አቅሟን ነው ያወደሙባት። አሁንም እደግመዋል፣ ፑቲን በስልጣን እስካለ፣ ሩሲያ እንደ ዶሮ ተገነጣጥላ ትሸነፋለች። ሰውዬው በኃይል ጦርነቱን መቋጨት ይችል ነበር፣ አሁንም ይችላል። ምንነቱ ላልታወቀ ግራ ለሚገባ ምክኒያት ግን፣ ይሄን ለማድረግ ፈቃደኛ አይደለም፣ እንደ አንዳንድ ሪፖርቶች ዘገባ በወር 35ሺ የሩሲያ ወታደሮች በጦር ሜዳ እየሞቱ ባለበት ሁኔታ እንኳ።

+1
🇮🇷🇮🇱 ፕሬዝዳንት ትራምፕ በእስራኤል የአሜሪካ አምባሳደር ማይክ ሃከቢ "ያለ እስራኤል አሜሪካ አትኖርም ነበር" ንግግሩ ዛሬ ምላሽ ሰጥቶበታል፡
"ያለ አሜሪካ፣ እስራኤል አትኖርም ነበር። ያለ እኔ፣ እስራኤል አትኖርም ነበር።
የማይክ ሃከቢ ንግግር በአሜሪካ ባለስልጣናት እና ሚዲያ ፐርሰናሊቲዎች አካባቢ ቁጣን ቀስቅሷል። አምባሳደሩ ከስልጣኑ ይነሳ ድምፆችም ተበራክተው ተሰምተዋል። ይህ ንግግር፣ በተለይ አሜሪካ 250ኛ የልደት በዓሏን ለማክበር በምትሰናዳበት ወቅት እና ትራምፕ፣ 'እስራኤል ዋይት ሃውስን' እያዘዘችበት ነው የሚለውን ብዥታ ለማጥራት በሚጣጣርበት ጊዜ የመጣ በመሆኑ፣ ቁጣው በአምባሳደሩ ላይ ሊያይል ችሏል።

+1
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በእስራኤል የአሜሪካ አምባሳደር ማይክ ሃከቢ "ያለ እስራኤል አሜሪካ አትኖርም ነበር" ንግግሩ ዛሬ ምላሽ ሰጥቶበታል፡
"ያለ አሜሪካ፣ እስራኤል አትኖርም ነበር። ያለ እኔ፣ እስራኤል አትኖርም ነበር።
የማይክ ሃከቢ ንግግር በአሜሪካ ባለስልጣናት እና ሚዲያ ፐርሰናሊቲዎች አካባቢ ቁጣን ቀስቅሷል። አምባሳደሩ ከስልጣኑ ይነሳ ድምፆችም ተበራክተው ተሰምተዋል። ይህ ንግግር፣ በተለይ አሜሪካ 250ኛ የልደት በዓሏን ለማክበር በምትሰናዳበት ወቅት እና ትራምፕ፣ 'እስራኤል ዋይት ሃውስን' እያዘዘችበት ነው የሚለውን ብዥታ ለማጥራት በሚጣጣርበት ጊዜ የመጣ በመሆኑ፣ ቁጣው በአምባሳደሩ ላይ ሊያይል ችሏል።

🇺🇸🇮🇷 - የኢራን የመጨረሻ ሻህ (ንጉሥ) ልጅ፣ ረዛ ፓህላቪ፣ ትራምፕን ተቆጥቶታል። "ምን አስነክተዎት ፈረሙ?" ሲል ትራምፕን ጠይቆታል። ‹‹ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የኢራን ሕዝብ ለነጻነት የ
🇺🇸🇮🇷 - የኢራን የመጨረሻ ሻህ (ንጉሥ) ልጅ፣ ረዛ ፓህላቪ፣ ትራምፕን ተቆጥቶታል። "ምን አስነክተዎት ፈረሙ?" ሲል ትራምፕን ጠይቆታል።
‹‹ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የኢራን ሕዝብ ለነጻነት የሚያደርገውን ትግል መደገፍ አለበት። በማንኛውም ድርድር እና በኢራን ፖሊሲያቸው ውስጥ እና መሃል፣ የኢራን ሕዝብ ሊካተት ይገባል። ግን ግልጽ ላድርግ - ዓለም አቀፍ ድጋፍም ይኑር አይኑር፣ ይህ አገዛዝ ይወድቃል። የኢራን ህዝብ እራሱን ከአምባገነንነት ነፃ ያወጣል።
ትራምፕ ከዚህ በፊት ረዛ ፓህላቪን፣ የኢራን ሕዝብ የሚወዱህ አይመስለኝም፣ ምክኒያቱም ለስልጣን ቋምጠሃል፣ አትልፋ! እንዳለው ይታወሳል። ምክትሉ JD Vanceም ዛሬ እንደተናገረው፣ ረዛ ፓህላቪን በምንም የወደፊት የኢራን ቀመር እንደማይፈልገው ገልጿል።

🇺🇸🇮🇱⚡️🇺🇸በእስራኤል የአሜሪካ አምባሳደር ማይክ ሃካቢ - እስራኤል ባትኖር ኖሮ አሜሪካ አትኖርም ነበር። - ለህልውናችን መገኘት፣ የእስራኤል መገኘት ምክኒያቱ ነው። ለዚህች ምድር ያልከፈ
🇺🇸🇮🇱⚡️🇺🇸በእስራኤል የአሜሪካ አምባሳደር ማይክ ሃካቢ - እስራኤል ባትኖር ኖሮ አሜሪካ አትኖርም ነበር። - ለህልውናችን መገኘት፣ የእስራኤል መገኘት ምክኒያቱ ነው። ለዚህች ምድር ያልከፈልነው ተራራ ዕዳ አለብን።

🇺🇸🇮🇷 ትራምፕ የኢራንን የተብላላ ዩራኒየም ከመውሰድ እያፈገፈገ ነው።
ይሄን ያህል ምን ያሳስባል? የሚካበድለት ነገር አይደለም፣ ብዬ ልከራከር እችላለሁ።

🇺🇸 ❌ 🇮🇷 ⚡️ - JD VANCE፡ የኢራን ስምምነት ተቺዎች (እስራኤል እና ጦርነት አራጋቢዎች) "እያንዳንዱ ቦምብ እስኪጣል ድረስ ወይም እያንዳንዱ ኢራናዊ እስኪሞት ድረስ ጦርነቱ እንዲቀጥል ይፈልጋሉ።" 🔴 "የሚያቀርቡትን ሐሳብ ከተመለከትክ፣ ማለቂያ የሌለው ግጭትን ነው።" 🔴 "የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት የሚፈልገው ደግም፣ ይህን አይደለም።"

🇮🇷🇵🇸⚔️🇺🇸🇮🇱🇶🇦🇸🇦 ኢራን የጋዛ ፋይል ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በተደረገው ድርድር ውስጥ እንዲካተት ጠይቃለች፣ ነገር ግን ሳዑዲን ጨምሮ በአካባቢው ያሉ የአረብ ሀገሮች፣ ይህንን ሀሳብ ሙሉ በሙሉ ውድቅ በማድረግ የጋዛ ጉዳይ ኢራንን እንደማይመለከት እና እነሱ የያዙት ጉዳይ እንደሆነ ተናግረዋል ተብሏል። ኢራን በጉዳዩ በመግባት ጋዛን በስምምነቱ ለማካለል ያደረገችውንም ጫና እንደ 'ጣልቃ መግባት' ቆጥረው ውድቅ አድርገውታል መባሉ ተሰምቷል። ጋዛውያን፣ ኢራን በድርድሯ ለምን እነሱን ማካተት እንደዘነጋች ሲጠይቁ ከርመዋል።

🇮🇷🇱🇧⚡🇮🇱🇺🇸|| የኢራን ማዕከላዊ ወታደራዊ ማዘዣ ጣቢያ (ካቲመ'ል-አንቢያ) 'እስራኤልን' አስጠንቅቋል። ባለፉት 2 ቀናት ውስጥ፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጦርነቱ ማብቃቱን ካወጁ በኋላ፣
🇮🇷🇱🇧⚡🇮🇱🇺🇸|| የኢራን ማዕከላዊ ወታደራዊ ማዘዣ ጣቢያ (ካቲመ'ል-አንቢያ) 'እስራኤልን' አስጠንቅቋል። ባለፉት 2 ቀናት ውስጥ፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጦርነቱ ማብቃቱን ካወጁ በኋላ፣ የጽዮናውያን አገዛዝ አሸባሪ ጦር፣ በደቡባዊ ሊባኖስ የተኩስ አቁሙን 84 ጊዜ ጥሷል፣ የተጨቆነውን ሕዝብንም መግደሉን ቀጥሏል" ብሏል። ኢራን፣ 'የጽዮናውያን ህጻናት ገዳይ ጦር' በደቡባዊ ሊባኖስ የሚያደርገውን ተንኮል አዘል ድርጊት ካላቆመ፣ ከኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ኃያል ጦር ኃይሎች፣ ከባድ ምላሽ መጠበቅ ይኖርበታል፣ ብሏል በመግለጫው።

🇮🇷🇱🇧⚡🇮🇱🇺🇸|| የኢራን ማዕከላዊ ወታደራዊ ማዘዣ ጣቢያ (ካቲመ'ል-አንቢያ) 'እስራኤልን' አስጠንቅቋል። ባለፉት 2 ቀናት ውስጥ፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጦርነቱ ማብቃቱን ካወጁ በኋላ፣ የጽዮናውያን አገዛዝ አሸባሪ ጦር፣ በደቡባዊ ሊባኖስ የተኩስ አቁሙን 84 ጊዜ ጥሷል፣ የተጨቆነውን ሕዝብንም መግደሉን ቀጥሏል" ብሏል። ኢራን፣ 'የጽዮናውያን ህጻናት ገዳይ ጦር' በደቡባዊ ሊባኖስ የሚያደርገውን ተንኮል አዘል ድርጊት ካላቆመ፣ ከኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ኃያል ጦር ኃይሎች፣ ከባድ ምላሽ መጠበቅ ይኖርበታል፣ ብሏል በመግለጫው።

🇮🇷🇱🇧⚡☠️🇺🇸|| የኢራን ማዕከላዊ ወታደራዊ ማዘዣ ጣቢያ (ካቲመ'ል-አንቢያ) 'እስራኤልን' አስጠንቅቋል። ባለፉት 2 ቀናት ውስጥ፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጦርነቱ ማብቃቱን ካወጁ በኋላ፣ የ
🇮🇷🇱🇧⚡☠️🇺🇸|| የኢራን ማዕከላዊ ወታደራዊ ማዘዣ ጣቢያ (ካቲመ'ል-አንቢያ) 'እስራኤልን' አስጠንቅቋል። ባለፉት 2 ቀናት ውስጥ፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጦርነቱ ማብቃቱን ካወጁ በኋላ፣ የጽዮናውያን አገዛዝ አሸባሪ ጦር በደቡባዊ ሊባኖስ የተኩስ አቁሙን 84 ጊዜ ጥሷል፣ የተጨቆነውን ሕዝብንም መግደሉን ቀጥሏል" ብሏል። እና ወንጀሉን እና የተጨቆኑትን የሊባኖስ ህዝብ መግደሉን ቀጥሏል። ኢራን፣ 'የጽዮናውያን ህጻናት ገዳይ ጦር' በደቡባዊ ሊባኖስ የሚያደርገውን ተንኮል አዘል ድርጊት ካላቆመ፣ ከኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ኃያል ጦር ኃይሎች፣ ከባድ ምላሽ መጠበቅ ይኖርበታል፣ ብሏል በመግለጫው።

🇺🇸🇮🇱🇮🇷 — እስራኤል፣ አሜሪካ ከኢራን ጋር የደረሰችበትን ስምምነት ይዘት እንድታጋራት ጠይቃለች። አሜሪካ ግን፣ እስከአሁን ለእስራኤል ይዘቱን ለማሳወቅ ፈቃደኛ እንዳልሆነች ነው። — Israeli Channel 12 |

🇸🇾 የተክፊር/ወሃቢ አክራሪ አንጃ የሆነው ISIS፣ በሶሪያ ራቃ ግዛት ውስጥ፣ በመንግሥት የፀጥታ አካላት ላይ፣ ለተሰነዘረው ጥቃት ኃላፊነቱን ወስዷል። በጥቃቱ በርካቶች፣ ሲቪሊያንን ጨምሮ፣ ሕይወ
+1
🇸🇾 የተክፊር/ወሃቢ አክራሪ አንጃ የሆነው ISIS፣ በሶሪያ ራቃ ግዛት ውስጥ፣ በመንግሥት የፀጥታ አካላት ላይ፣ ለተሰነዘረው ጥቃት ኃላፊነቱን ወስዷል። በጥቃቱ በርካቶች፣ ሲቪሊያንን ጨምሮ፣ ሕይወታቸው አልፏል። "የመንግሥት ኃይሎች" የሚባሉት ራሳቸው የዛሬ ሦስት ዓመት ISIS (Al Nusera) ነበሩ።