ar
Feedback
ㅤ♰ ማሕተቤ ✟

ㅤ♰ ማሕተቤ ✟

الذهاب إلى القناة على Telegram

“ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።” — መዝሙር 122፥1 💬 ለማንኛውም ጥያቄና አስተያየት @Ortho_29 🙏 ♡ እንኳን ደኅና መጡ። ♡

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
291
المشتركون
+124 ساعات
+77 أيام
+730 أيام
أرشيف المشاركات
​«አማኑኤል አምላኬ ሆይ! ከዓለም ጩኸትና ግርግር ሸሽቼ ወደ አንተ ዝምታ እጠጋለሁ። ማንም በሌለበት፣ ማንም በማይሰማኝ የብቸኝነት ሰዓት የነፍሴ ቅርብ አንተ ነህ። ቃልህን ሰምቼ የማልጠነቅቅ፣ በእምነት ጎዳና ላይ የምንገጫገጭ ደካማ ነኝ፤ ነገር ግን ፍቅርህ አይጥለኝም። እንባዬ በፊጥህ ሲፈስ የልቤን ስብራት የምትጠግንልኝ አንተ ብቻ ነህ። ከአንተ ጋር ስሆን ብቸኝነት አይሰማኝም።»

​«አማኑኤል ሆይ! ቃልህን እሰማለሁ፣ ነገር ግን ለመፈጸም አቅም ያጣሁ ደካማ ፍጡር ነኝ። ዛሬ በፊትህ ቆሜ የምምለውን ቃል፣ ነገ የምዘነጋ ምስኪን ነኝ። ነገር ግን እኔ በደካማነቴ ስወድቅ፣ አንተ በ
​«አማኑኤል ሆይ! ቃልህን እሰማለሁ፣ ነገር ግን ለመፈጸም አቅም ያጣሁ ደካማ ፍጡር ነኝ። ዛሬ በፊትህ ቆሜ የምምለውን ቃል፣ ነገ የምዘነጋ ምስኪን ነኝ። ነገር ግን እኔ በደካማነቴ ስወድቅ፣ አንተ በሁሉን ቻይነትህ ትደግፈኛለህ። የእኔ ክዳት የአንተን ታማኝነት አይለውጠውም። ጌታ ሆይ! ወደ ራሴ ስመለከት ተስፋ እቆርጣለሁ፣ ወደ አንተ ስመለከት ግን በይቅርታህ ብዛት ነፍሴ ትለመልማለች። ውስጤ ያንተን ቸርነት ተጠምቷል፤ ከእኔ ድካም ይልቅ የአንተ ምሕረት ይበልጣልና በደረትህ አስጠጋኝ።» ♡ ㅤ  ❍ㅤ     ⎙ㅤ  ⌲ ˡᶦᵏᵉ   ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

“የሚለምን ሁሉ ይቀበላልና፥ የሚፈልግም ያገኛል፥ መዝጊያውንም ለሚያንኳኳው ይከፈትለታል።”
  — ሉቃስ 11፥10

✅“ከደስታም ጋር በሁሉ ለመጽናትና ለመታገሥ እንደ ክብሩ ጉልበት መጠን በኃይል ሁሉ እየበረታችሁ፥ በቅዱሳንም ርስት በብርሃን እንድንካፈል ያበቃንን አብን እያመሰገናችሁ፥ በነገር ሁሉ ደስ ልታሰኙ ለጌታ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እንለምናለን።”💟
— ቆላስይስ 1፥12

“ጥበብን የሚያገኝ ነፍሱን ይወድዳል፥ ማስተዋልንም የሚጠብቅ መልካም ነገርን ያገኛል።”
  ምሳሌ 19፥8

ምድር በጨለማ ስትዋጥ ነገ በህይወት እንደምቆይ በአንተ ተስፋ ነበረኝ እነሆ አንድ ቀን ጨመርክልኝ  የቸርነት ባለቤት ልዑል እግዚአብሔር ስለሰጠኸን ቀን እናመሰግንሃለን
ሎቱ ስብሐት እግዚእነ🙏

“በሰላም እተኛለሁ አንቀላፋለሁም፤ አቤቱ፥ አንተ ብቻህን በእምነት አሳድረኸኛልና።”
  — መዝሙር 4፥8

​"የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።"
— (መዝሙረ ዳዊት 33፥7)

የማይነጋ የመሰላቹን ሌሊት ማያልፍ የመሰላቹን ቀናት ሳምንታት ወራት አመታትን ወደ ኋላ መለስ ብላቹ አስቡ አልፈዋል አሁንም እግዚአብሔር ይዘን እንሻገራለን። ♡ ㅤ  ⎙ㅤ  ⌲        ✉️          ˡᶦᵏᵉ    ˢᵃᵛᵉ    ˢʰᵃʳᵉ   ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ʟɪᴋᴇ ɪᴛ ᴅᴏᴇsɴ'ᴛ ᴄᴏᴜɴᴛ ᴘʀᴇss ɪᴛ ♡                ✨#sʜᴀʀᴇ@orho_28 & #ʟɪᴋᴇ@ortho_28

​"አትበል 'ባለፈው ብዙ ኃጢአት ሠርቻለሁ፤ ወደ እግዚአብሔር መመለስ አልችልም' ብለህ። ንስሐ የባለፈው የሕይወትህ ማብቂያ፣ የአዲሱ የሕይወትህ ደግሞ መጀመሪያ ናት። እግዚአብሔር ያለፈውን ታሪክህን አይመለከትም፤ ይልቁንም ዛሬ ባለው የልብህ ቆራጥነት ላይ በመመስረት አዲስ መንገድን ይከፍትልሃል።" ​+ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ +

​"አንድን ሰው በወደቅክበት ኃጢአት ስታየው፣ በእርሱ ላይ አትፍረድ፤ ይልቁንም እግዚአብሔር እስከ አሁን እንደማይጥልህ በማሰብ አመስግነው። ምናልባት አንተ ልትወድቅ የነበርክበትን አደጋ እግዚአብሔር በቸርነቱ ስላቆመው ነው። የሰው ኃጢአት የራስህን ድካም የምታስታውስበት መስተዋት ይሁን።" ​+ አባ ይስሐቅ ሶርያዊ +

እንዲ:መኖር☺️ ፍቅር:ማለት: ክርስቶስ:በሰውም:ሲገለጥ:በመለኮቱም(በኃይሉ):ሲገለጥ:መቀበል:ማለት:ነው። ፍቅርም:ማለት:የምንወደው:ሰው:በሰውም(ሲደክም፤ሲደህይ):በኃይልም:(በሀብትም፣በጤናም):መቀበል:
እንዲ:መኖር☺️ ፍቅር:ማለት: ክርስቶስ:በሰውም:ሲገለጥ:በመለኮቱም(በኃይሉ):ሲገለጥ:መቀበል:ማለት:ነው። ፍቅርም:ማለት:የምንወደው:ሰው:በሰውም(ሲደክም፤ሲደህይ):በኃይልም:(በሀብትም፣በጤናም):መቀበል:መቻልነው።

“እግዚአብሔር ግን እውነተኛ አምላክ ነው፤ እርሱም ሕያው አምላክና የዘላለም ንጉሥ ነው፤ ከቍጣው የተነሣ ምድር ትንቀጠቀጣለች፥ አሕዛብም መዓቱን አይችሉም።”
  — ኤርምያስ 10፥10

😇ነገር ግን ቃሉን የሚማር ከሚያስተምረው ጋር መልካምን ነገር ሁሉ ይከፋፈል። አትሳቱ፤ እግዚአብሔር አይዘበትበትም። ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና፤📕 በገዛ ሥጋው የሚዘራ ከሥጋ መበስበስን ያጭዳልና፥ በመንፈስ ግን የሚዘራው ከመንፈስ የዘላለምን ሕይወት ያጭዳል።
ገላትያ 6፥6:7:8 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯

"ነፍስህን በዓለማዊ ወሬዎችና በሃሜት አትቀልባት፤ ልብህን ከባድና እረፍት ቢስ ያደርጉታልና። ሁልጊዜ ወደ ውጭ ብቻ የሚያይ አእምሮ በሮቹ እንደተከፈቱ ቤት ነው፤ ማንኛውም ሌባ በቀላሉ ሊገባበት ይችላል። ሐሳቦችህን ከእግዚአብሔር ጋር በውስጥህ ጠብቃቸው።" + ቅዱስ ሰራፊም ዘሳሮቭ +

አቤቱ ጌታ ሆይ፥ አንተ ከእኔ ውጪ አይደለህም፤ አንተ በውስጤ ነህ እንጂ። አንተን በማስብበት (በማስታውስህ) ጊዜ፥ ዓይኖቼን ወደ ላይ ብቻ አላነሳም፤ አንተ በላይ በሰማያት ብቻ ያለህ አይደለህምና፤ አንተ በውስጤ ነህ እንጂ፥ ከውጭም አልፈልግህም... 'ዓይኖቼን እጨፍናለሁ፥ ሆኖም ግን አየሃለሁ' ብሎ የጻፈው ጸሐፊ እውነት ነበረው።" ​— ፓትርያርክ አባ ሺኖዳ —