Chillax Betting
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
5 327
المشتركون
+624 ساعات
+477 أيام
+4730 أيام
أرشيف المشاركات
5 326
#ጥቆማ
#ECSU
በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ የሚሰጡ የትምህርት ፕሮግራሞች፦
College of Management, Leadership & Governance
➫ Public Service Leadership
➫ Public Policy Studies
➫ Management
➫ Tourism & Hotel Management
➫ Public Governance & Administration
College of Finance & Economics
➫ Economics
➫ Accounting & Finance
➫ Public Financial Management
➫ Tax & Customs Administration
➫ Procurement & Asset Management
➫ Logistic & Supply Chain Management
➫ Marketing Management
College of Social Science & Development Studies
➫ Sociology
➫ Psychology
➫ Political Science & International Relations
➫ Journalism & Communication
➫ Development Management
➫ Environmental Science
College of Urban Studies
➫ Urban Planning & Design
➫ Urban Land Management Information Systems
➫ Real Property Valuation
➫ Surveying Engineering
➫ Urban Engineering
College of Innovation & Digitalization
➫ Software Engineering
➫ Computer Science
➫ Data Science
➫ Information Systems
➫ Information Technology
School of Law
➫ Law
5 326
+1
በሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ በክልሉ በ2017 የትምህርት ዘመን በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎችና ሌሎች ባለድርሻዎች እውቅናና ሽልማት አበርክቷል።
በመርሀ-ግብሩ ላይ የተገኙት ትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በሀረሪ ክልል በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የተመዘገበው 22 በመቶ ውጤት አበረታች መሆኑን ጠቁመው ክልሉ ለትምህርቱ ዘርፍ የሰጠውን ትኩረት ማሳያ ነው ብለዋል።
እንደ ሀገር በትምህርት ዘርፉ የሰራና የለፋ ብቻ ውጤት የሚያገኝበት ሥርዓት እየተዘረጋ መጥቷል ያሉት ሚኒስትሩ ዛሬ የተሸለማችሁ በአቋራጭ ሳይሆን በስራና በድካም ያገኛችሁት ውጤት በመሆኑ ልትኮሩ ይገባችኋል ብለዋል።
በቀጣዩ የ2018 የትምህርት ዘመንም የ12 ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና በክልሉ ሙሉ በመሉ ከወረቀት ነፃ በሆነ መልኩ በኦላይን ለመስጠት ከክልሉ አመራር ጋር መግባባት መደረሱንም ሚኒስትሩ ገልፀዋል።
በመሆኑም በክልሉ አሁን በተገኘው ውጤት መዘናጋት ሳይኖር የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።
ሚኒስትሩ አክለውም ይሄ ትውልድ የሥራ ትውልድ፣ በራሱ የሚኮራ ትውልድ እንዲሆን እንደ ሀገር የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል።
በዕውቅናና ሽልማት መርሀ-ግብሩ ላይ የትምህርት ሚኒስቴርና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ሌሎችም ክልሎች ተሞክሮዉን ይወስዳሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን።
5 326
+1
#AdigratUniversity
ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሁሉም የቅድመ ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ ነባር መደበኛ ተማሪዎች መግቢያ ቀናት መስከረም 19 እና 20/2018 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡
በ2017 ዓ.ም በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርታቹን ስትከታተሉ ቆይታችሁ ማለፊያ ውጤት ያመጣቹ ተማሪዎቸ ወደ ዩኒቨርሲቲ የምትገቡት በ2018 ዓ.ም አዲስ ከሚመደቡ ተማሪዎች ጋር መሆኑ ተገልጿል፡፡
5 326
+2
#KUE
#ScholarshipOpportunity
ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት ላመጡና በትምህርት ዘርፍ መሰማራት ለሚፈልጉ አመልካቾች ለ2018 የትምህርት ዘመን ልዩ የስኮላርሽፕ ዕድል አመቻችቷል፡፡
የዚህ ልዩ የስኮላርሺፕ ተጠቃሚ መሆን የሚፈልጉ ተወዳዳሪዎች የትምህርት ሚኒስቴርን መመዘኛ መስፈርት ያሟሉ እና በቀጣይም ውል ገብተው በትምህርት ዘርፍ ለመሰማራት ፈቃደኛ የሆነ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
የነጻ ትምህርት ዕድሉ ተጠቃሚ ተማሪዎች የሚያገኟቸው ጥቅሞች፦
➫ የምግብ፣ የመኝታ እና ሙሉ የትምህርት ወጪያቸው በዩኒቨርሲቲው ይሸፈናል፣
➫ የኪስ ገንዘብ በየወሩ ይሰጣቸዋል፣
➫ የትምህርት ቁሶች ወጪ ይሸፈንላቸዋል።
የማመልከቻ አማራጮች፦
በአካል በመቅረብ ወይም በኦንላይን
በኦንላይን ለማመልከት 👇
ከላይ በምስሉ ላይ የተያያዘውን QR Code ስካን ያድርጉ
(አመልካቾች ማመልከት የሚችሉባቸው የትምህርት አይነቶች ከላይ ከተያያዘው ምስል ይመልከቱ።)
5 326
+1
ቅሬታዎን ያስገቡ!
በ12ኛ ክፍል ውጤትዎ ላይ ያለዎትን ቅሬታ በኦንላይን በቀጥታ ያስገቡ!
➫ https://result.eaes.et ላይ ይግቡ፣
➫ የአድሚሽን ቁጥርዎን ያስገቡ፣
➫ የመጀመሪያ ስምዎን ያስገቡ፣
➫ ውጤትዎን ይመልከቱ፣
➫ እዛው ገፅ ላይ ወደታች ስክሮል ያድርጉ፣
➫ 'Submit Complaint' የሚለውን ይጫኑ፣
➫ 'My Complaints' የሚለውን ይጫኑ፣
➫ ቅሬታዎን ከማስገባትዎ በፊት ከዚህ በፊት ቅሬታ አስገብተው ከነበረና ምላሽ ከተሰጠዎ ይመልከቱ፣
➫ የተሰጠዎን ምላሽ ይመልከቱ። #EAES
5 326
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስቲም ማዕከል በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ያስፈተናቸው ሁሉም ተማሪዎች ማለፋቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡
63.4% የሚሆኑ ተፈታኞች ከ500 በላይ ውጤት አስመዝግበዋል።
በዩኒቨርሲቲው ስቴም ማዕከል ከፍተኛው ውጤት በተማሪ ኤፍራታ ዓለማየሁ የተመዘገበው 558 ሲሆን፤ ዝቅተኛው ነጥብ 429 መሆኑ ተገልጿል።
5 326
የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ሼርድ ትምህርት ቤት በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ካስፈተናቸውን ስምንት ተማሪዎች ሰባቱ ማለፋቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡
5 326
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በአዊ ዞን እና በምዕራብ ጎጃም ዞኖች በጸጥታ ችግር ምክንያት ትምህርታቸውን አቋርጠው ቆይተው በዩኒቨርሲቲው የማጠናከሪያትምህርት ተከታትለው የ12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ 162 ተማሪዎች መካከል 128 ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ውጤት ማስመዝገባቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡
ከአጠቃላይ ተፈታኞቹ 78.4% የማለፊያ ውጤት ያመጡ ሲሆን፤ 27 ተማሪዎች ከ400 በላይ ነጥብ ማስመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡
በተማሪ አላልኝ አበበ የተመዘገበው 530 ነጥብ ከፍተኛው ውጤት ሆኖ መመዝገቡም ተገልጿል፡፡
5 326
የፋርማ ኮሌጅ ሰራተኞች የታላቁ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ሀገራዊ ፕሮጀክት ማጠናቀቂያ በዓልን ምክንያት በማድረግ በደማቅ ሁኔታ አከበሩ።
በዝግጅቱ ወቅት የፋርማ ኮሌጅ ሰራተኞች፣ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ፣ የትውልድ፣ የአንድነት፣ የተስፋ እና የእድገት ምልክት መሆኑን በመግለጽ ይሄንን በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ትልቅ ስኬት በማየታቸው ከፍተኛ ደስታና ኩራት እንደተሰማቸው ተናግረዋል።
በሥነ ሥርዓቱ ላይ የኮሌጁ ፕሬዝዳንት አቶ ስዩም ከበደ ባደረጉት ንግግር የታላቁ ህዳሴ ግድብ በአንድነት፣ በፅናት እና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ትብብር የተገነባ፣ ለአሁኑ እና ለመጪው ትውልድ ትሩፋት እና የኢትዮጵያ የጋራ መንፈስ አንፀባራቂ ምልክት መሆኑን የተናገሩ ሲሆን፣ ፋርማ ኮሌጅ ለአገሪቱ የትምህርት፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማበርከት ያለውን ቁርጠኝነት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
