ar
Feedback
Sinksar tube(ስንክሳር)

Sinksar tube(ስንክሳር)

الذهاب إلى القناة على Telegram

እኔ ቅዱስ ነኛና ቅዱሳን ሁኑ 1ጴጥ 1:15

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
2 511
المشتركون
-1024 ساعات
+1137 أيام
+42130 أيام
أرشيف المشاركات
🎯 ከዘማሪያን የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይፈልጋሉ? ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ 🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤 ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ 🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤 ዘማሪ አቤል መክብብ 🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤ዘማሪት ሲስተር ህይወት ተፈራ🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤ዘማሪ ዲያቆን ሙሉቀን ከበደ🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤 ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎚 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ 🎚 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ 🎤 የሁሉንም ዘማሪያን መዝሙር ለማግኘት 🔔 👇 🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን ሐምሌ 12-ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ንጉሥ ሕዝቅያስን ረድቶ በትዕቢት እግዚአብሔርን የሰደበውን ንጉሥ ሰናክሬምንና 185,000 ሠራዊቱን በአንዲት ሌሊት ጨርሶ በመግደል ታላቅ ተአምር ያደረገበት ዕለት ነው፡፡ + ዳግመኛም በዚኽች ዕለት አባ ሖር ሰማዕትነቱን በድል ፈጸመ፡፡ አማላጅነቱ ለሁላችን ለጥምቀት ልጆች ይደረግልንና ሊቀ መልአክት ቅዱስ ሚካኤል ያደረገው ተአምር ይህ ነው፡- መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን በዚህች ዕለት የመላእክት ሁሉ አለቃቸው የቅዱሳንም ረዳታቸው የሆነው ደጉ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ንጉሡን ሕዝቅያስን ግሩም በሆነ ተአምር ረድቶታል፡፡ ከጌታችን ልደት 700 ዓመታት በፊት ሕዝቅያስ የሚባል ንጉሥ በይሁዳ ላይ ነግሦ ነበር፡፡ ደጋጓቹ ነገሥታት ዳዊትና ሰሎሞን ካረፉ በኋላ የሕዝቅያስን ያህል ቅንና የእግዚአብሔር ሰው በእሥራኤል ላይ አልነገሠም፡፡ ንጉሡ ጣዖት አምልኮን ነቃቅሎ አጥፍቶ ሕዝቡ እግዚአብሔርን ብቻ እንዲያመልክ አድርጓል፡፡ ነገር ግን ቅዱስ ሕዝቅያስ በነገሠ በ14ኛው ዓመት የአሕዛብ (የአሦር) ንጉሥ ሰናክሬም በጠላትነት ተነሳበት፡፡ ወደ አካባቢውም መጥቶ ከቦ አስጨነቀው፡፡ ሰናክሬም በጦር እጅግ ኃይለኛ ነበር፡፡ የሠራዊቱም ብዛት ከ185,000 በላይ ነውና ንጉሥ ሕዝቅያስ እንደማይችለው ዐውቆ መልእክተኛ ላከበት፡፡ ‹‹ግብር እገብርልሃለሁ፣ የፈለግከውንም እሰጥሃለሁ፣ ነገር ግን ሀገሬን አታጥፋ፣ ኢየሩሳሌምን አታቃጥል፣ ሕዝቤንም አትግደል›› ብሎ ለመነው፡፡ እጅ መንሻ ግብሩንም ከከተማዋ የተገኘውን ወርቅና ብር ሁሉ ጭኖ ላከለት፡፡ ሰናክሬም ግን ሰይጣን ያደረበት ነውና የሕዝቅያስን ልመና በመናቅ አምላኩን እግዚአብሔርንም ተሳደበ፡፡ ‹‹ከእኔ እጅ የሚያድንህ ማነው? ሕዝቡንም እግዚአብሔር ያድናል ብለህ አታታልላቸው›› ሲል ላከበት፡፡ ሕዝቅያስም በዚህ ጊዜ የፈጣሪው ስም ሲሰደብ ሰምቷልና ፈጽሞ አዘነ፡፡ መልእክተኞችን ወደ ነቢዩ ቅዱስ ኢሳይያስ ልኮ እርሱ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ልብሱን ቀድዶ ማቅ ለበሰ፡፡ ስለ ኢየሩሳሌምና ሕዝቡም ፈጽሞ አለቀሰ፡፡ በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር የሰናክሬምን መገዳደርና የሕዝቅያስን ልመና ሰምቷልና ‹‹ስለ ባሪያዬ ስለ ዳዊት ከተማዋን አድናታለሁ›› ብሎ ለነቢዩ ኢሳይያስ ነገረው፡፡ ኢሳይያስም የእግዚአብሔርን መልእክት ለንጉሥ ሕዝቅያስ ነገረው፡፡ በዚያችም ሌሊት ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ከሰማያት በግርማ ወርዶ የሰናክሬምን 185 ሺውንም የጦር ሠራዊት በአንዲት ሌሊት በእሳት ሰይፉ ፈጅቷቸው አደረ፡፡ በለኪሶ የነበረው ሰናክሬምም በጧት ቢነሳ ሠራዊቱን ሁሉ የአስከሬን ክምር ሆኖ አገኘው፡፡ በታላቅ ድንጋጤ ሆኖ ወደ ነነዌ በመሄድ ወደ ጣዖት ቤቱ ሲገባ የራሱ ልጆች በሰይፍ ገደሉት፡፡ ትዕቢተኛው ሰናክሬምም ለአሕዛብ ሁሉ መዘባበቻ ሆነ፡፡ ቅዱስ ሕዝቅያስ ግን በፈጣሪው ታምኗልና ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልም ሞገስና ረዳት ሆኖታልና የዓለም ነገሥታት ሁሉ ፈሩት፣ እጅግ አከበሩትም፡፡ 1ኛ ነገ 18፡13፣ 19፡1፡፡ የሊቀ መልአክት ቅዱስ ሚካኤል አማላጅነቱ ለሁላችን ለጥምቀት ልጆች ይደረግልን! + + + ሰማዕቱ አባ ሖር፡- አባቱ ስርያቆስ በምትባል አገር ይኖር የነበረ አንጥረኛ ነው፡፡ ልጁን ሖርንም እግዚአብሔርን በመፍራት በሃይማኖት በምግባር አሳደገው፡፡ ጎልማሳ በሆነም ጊዜ ዘመነ ሰማዕታት ስለመጣ አባ ሖር በጌታችን ስም ሰማዕት ይሆን ዘንድ ፈርማ ወደምትባል አገር ሄደ፡፡ በዚያም በሃዲውን መኮንን ፊት ቀርቦ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ፡፡ መኮንኑም ይዞ በጽኑ አሠቃየው፡፡ ጌታችንም ከሥቃዩ ፈውሶት ተነሣ፡፡ ከሃዲ የነበረው መኮንንም ጌታችን ለአባ ሖር ያደረገለትን ታላቅ ተአምር አይቶ ከሚስቱና ከልጆቹ ጋር በጌታችን አመነ፡፡ እርሱም በማመኑ በሌላ መኮንን ዘንድ በተራው ብዙ ተሠቃይቶ ከነቤተሰቡ በሰማዕትነት ዐረፈና በመንግሥተ ሰማያት የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጀ፡፡ ይኽም ሌላኛው መኮንን አባ ሖርን ወደ እንዴና ላከው፡፡ በዚያም ከሃዲዎች በእጅጉ አሠቃዩት፡፡ በመንኮራኩር አበራዩት፣ ዘቅዝቀው ሰቅለው በእሳት በጋለ ብረት ደበደቡት፡፡ መኮንኑም አባ ሖርን ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ የከበረች ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ፡፡ ቅዱስ አባ ሖር አንገቱን ተሰይፎ የሰማዕትነትን አክሊል ተቀዳጀ፡፡ የእርሱም ማኅበርተኞቹ የሆኑ 127 ወንዶችና 20 ሴቶች አብረውት ተሰይፈው የድል አክሊልን ተቀዳጅተዋል፡፡ የአባ ሖር ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!

🎯 ከዘማሪያን የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይፈልጋሉ? ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ 🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤 ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ 🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤 ዘማሪ አቤል መክብብ 🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤ዘማሪት ሲስተር ህይወት ተፈራ🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤ዘማሪ ዲያቆን ሙሉቀን ከበደ🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤 ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎚 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ 🎚 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ 🎤 የሁሉንም ዘማሪያን መዝሙር ለማግኘት 🔔 👇 🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧

💠የንስሐ ◇የሽብሻቦ ◇ወረብ ◇የቅዱሳን እንዲሁም የመላእክት መዝሙር የምትፈልጉ ከሆነ አሁኑኑ JOIN በሉት ይሄ ቻናል ምርጥ ምርጥ መዝሙሮችን በጥራትና በፍጥነት ያሳያል። 𝐉𝐨𝐢𝐧👇👇👇
💠የንስሐ ◇የሽብሻቦ ◇ወረብ ◇የቅዱሳን  እንዲሁም የመላእክት መዝሙር የምትፈልጉ ከሆነ አሁኑኑ JOIN  በሉት  ይሄ ቻናል ምርጥ ምርጥ መዝሙሮችን በጥራትና በፍጥነት ያሳያል። 𝐉𝐨𝐢𝐧👇👇👇

††† ✝እንኳን ለቅዱሳን ጻድቃን ወከዋክብተ ገዳም አቡነ ኪሮስ: አባ ብሶይ እና አባ ሚሳኤል ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።✝ ††† ††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ††† ††† ✝አቡነ ኪሮስ ጻድቅ✝ ††† ††† የጻድቁን ስም የሚጠራ አፍ ንዑድ ነው: ክቡር ነው:: በእውነት የቅዱሱን አባት ክብር ለማግኘት መፋጠን ይበጃል:: #አቡነ_ኪሮስ የተወለዱት በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን ሲሆን ወላጆቻቸው ነገሥታት ናቸው:: ተወልደው ባደጉባት ሃገር #ቁስጥንጥንያ ገና በልጅነት ምቾት ሳያሳሳቸው መጻሕፍትንና ትሕርምትን ተምረዋል:: ወንድማቸው (ታላቁ #ቴዎዶስዮስ) በነገሠባቸው የመጀመሪያ ዓመታት በቤተ መንግስቱ ዙሪያ ግፍ በዝቶ ነበርና አቡነ ኪሮስ ከኃጢአት ለመራቅና ለጌታ ለመገዛት ከከተማው ጠፍተው: አሕጉር አቋርጠው ወደ ግብፅ ( #ገዳመ_አስቄጥስ) መጡ:: እርሳቸውን ለመፈለግ የተደረገው ሙከራ አልተሳካም:: ይባስ ብሎ የንጉሡ ልጅ #ገብረ_ክርስቶስ ሙሽርነቱን ጥሎ ወደ ሌላ ሃገር መነነ:: "የቅኖች ትውልድ ይባረካል" እንዳለ #ቅዱስ_ዳዊት:: አቡነ ኪሮስ ለሙሽራው ገብረ ክርስቶስ አጎቱ ናቸው:: አቡነ ኪሮስ በገዳም ውስጥ የታላቁ #አቡነ_በብኑዳ ደቀ መዝሙር ሆነው ለዘመናት ቆይተዋል:: ቅዱስ በብኑዳን አንበሳ በበላው ጊዜ በጣም አዝነው "ለምን ጌታ ሆይ?" በሚል መሬት ላይ ወድቀው አለቀሱ:: "ምክንያቱ ካልተነገረኝ አልነሳም" ብለው ከወደቁበት መሬት ላይ ሳይነሱ ለ40 ዓመታት አልቅሰዋል:: በዚህ ምክንያት ግማሹ አካላቸው አፈር ሆኖ ሣር በቅሎበታል:: ጌታችን ተገልጦ ምክንያቱን ነግሯቸዋል:: አካላቸውንም እንደነበረ መልሶላቸዋል:: አንድ ቀን ጻድቁ ለቅዱስ በብኑዳ ሞት ምክንያት የሆነው መነኮስ ታንቆ መሞቱን ሰምተው በጣም አዘኑ:: ሱባዔ ገብተው: ፍጹም አልቅሰው: ከጌታም አማልደው: የዛን ኃጥእ ነፍስ ከሲዖል አውጥተዋል:: በሌላ ጊዜ ደግሞ ኃጥአን የሞሉበት አንድ ገዳም በግብጽ ነበርና መቅሰፍት ወርዶ ሁሉንም ባንድ ቀን ሲያጠፋቸው አዩ:: ጻድቁ በዚህም ምክንያት ለ30 ዓመታት አልቅሰው: ሙታኑን አስነስተው: ንስሃ ሰጥተው: ገዳሙን የጻድቃን: ሕይወታቸውንም የፍቅር አድርገውታል:: ጻድቁ #እመቤታችንን ከመውደዳቸው የተነሳ በስዕሏ ፊት አብዝተው ይሰግዱና ያለቅሱ ነበር:: እመ አምላክም ተገልጣ ትባርካቸው ነበር:: ከዚህ በሁዋላ ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ሒደው ለ57 ዓመታት ማንንም ሳያዩ ተጋደሉ:: ጌታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ (ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና) በየቀኑ ይጐበኛቸው: ቁጭ ብሎም ያወራቸው ነበር:: በመጨረሻም በዚህች ቀን ጌታ አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን: ድንግል እመቤታችንና ቅዱስ ዳዊትን አስከትሎ ወረደ:: #ቅዱስ_ዳዊት ቀርቦ እያጫወታቸው: በበገናው እየደረደረላቸው: ከዝማሬው ጣዕም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው በፍቅር ተለየች:: ጌታችንም ታቅፎ: ስሞ ይዟቸው አረገ:: ሥጋቸውን #አባ_ባውማ ቀበሩት:: የአቡነ ኪሮስ ቁመታቸው ቀጥ ያለ: ጽሕማቸውም የተንዠረገገ ነበር:: እድሜአቸውን ግን መገመት የሚቻል አይመስለኝም:: †††✝ የበርሃው ኮከብ አባ ብሶይ✝ ††† ††† ታላቁ አባ ብሶይ (ቢሾይ):- ¤በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበሩ ¤በመላእክት መሪነት የመነኑ ¤የቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር ባልንጀራ ¤የአባ ባይሞይ ደቀ መዝሙር የነበሩ ¤በአጭር ጊዜ የብዙዎች አባት የሆኑ ሰው ናቸው:: ††† እንቅልፍን የማያውቁ ¤በ40 ቀን ብቻ እህል የሚቀምሱ ¤የጌታችንን እግር በየቀኑ እያጠቡ የሚመገቡ ¤ፈጣሪያቸውን በጀርባቸው ያዘሉ (ነዳይ መስሎ አግኝተውት) ¤በስብከተ ወንጌል አገልግሎት የተጉ ¤በርካታ ጻድቃንን የወለዱ ታላቅ የፍቅር ሰው ናቸው:: በዘመናቸው ብዙ ተአምራትን ሰርተው: #ቤተ_ክርሰቲያንን በንጽሕናቸው አስደስተው: ሐምሌ 8 ቀን ዐርፈዋል:: ግብፅ ውስጥ የሚገኘው ገዳማቸው ዛሬም ቤተ አበው: ተአምራት የማይለዩትና ተወዳጅ ነው:: ቦታው #መካነ_ሱባዔ_ወመንክራት ነውና:: ††† ✝አባ ሚሳኤል ነዳይ✝ ††† ††† መቼም ያ ዘመን (4ኛውና 5ኛው ክ/ዘመን) እጅግ የተባረከ ነው:: ቅዱሳኑ በብዛት የባለጸጐችና የነገሥታት ልጆች ናቸው:: አባ ሚሳኤልም የኬልቄዶን ንጉሥ ልጅ ሳሉ መንነው በበርሃ ለ65 ዓመታት ተጋድለዋል:: በመጨረሻ ግን በደዌ ምክንያት ወደቁ:: ለ5 ዓመታት መነኮሳቱ ሲጠይቁዋቸው ቆይተው ሰለቹ:: ከዛም ለ15 ዓመታት ላበታቸው በግንባራቸው እየተቀዳ: ያለ ምንም ምግብ እያቃሰቱ በበዓታቸው ወድቀው ኑረዋል:: ቸሩ አምላክ ግን 4ቱን ሊቃነ መላእክት ( #ሚካኤል: #ገብርኤል: #ሩፋኤልና #ሳቁኤልን) አዞላቸው ሲጠብቁዋቸው ኑረዋል:: በዚህች ቀንም #አቡነ_ኪሮስ መጥተው አጽናንተው: ጌታችንንም ጠርተው እንዲያርፉ አድርገዋል:: መላእክት እያጠኑና እየዘመሩ ጻድቁ ቀብረዋቸዋል:: በመቃብራቸውም ላይ ፈውስ የሆነ ጸበል ፈልቁዋል:: ††† እግዚአብሔር የእኛን ያይደለ የጻድቃኑን ቅድስና አስቦ ይራራልን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን:: ††† ሐምሌ 8 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.አቡነ ኪሮስ ጻድቅ (አረጋዊና ገዳማዊ) 2.አባ ብሶይ ጻድቅ (ኮከበ ገዳም) 3.አባ ሚሳኤል ነዳይ (ጻድቅ) 4.አባ ቢማ ሰማዕት 5.አባ በላኒ ሰማዕት 6.ቅዱሳን አቤሮንና አቶም (ሰማዕታት) ††† ወርሐዊ በዓላት 1.ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት 2.ኪሩቤል (አርባዕቱ እንስሳ) 3.አባ ሳሙኤል ዘደብረ ቀልሞን 4.ቅዱስ ማትያስ ሐዋርያ (ከ12ቱ ሐዋርያት) ††† "በረከት በጻድቅ ራስ ላይ ነው:: የኃጥአንን አፍ ግን ግፍ ይከድነዋል:: የጻድቅ መታሠቢያ ለበረከት ነው::" ††† (ምሳ. 10:7) ††† "እግዚአብሔር ፍርድን ይወድዳልና:: ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና:: ለዘለዓለምም ይጠብቃቸዋል. . . ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ:: በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ:: የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል:: አንደበቱም ፍርድን ይናገራል:: የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው:: በእርምጃውም አይሰናከልም::" ††† (መዝ. 36:28-31) ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††