የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service
الذهاب إلى القناة على Telegram
.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡
إظهار المزيدلم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
514
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
+1
የኢትዩጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት በሮቤ ከተማ ለማካሔድ ይዟቸው ከመጣቸው ተግባራቶች መካከል ከሆኑት የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር እና የፓናል ውይይት መድረክ ነገ ጥር 26/2018 ዓ.ም ይከናወናሉ።
ማረሚያ ቤት መማሪያም መጻፊያም ቦታ ሊሆን ይችላል።(አቶ አባተ ካሳው)
ባሌ ዞን ማረሚያ ቤት
25/2018 ዓ.ም
"መጽሐፍትን በማንበብ እንታረም!" በሚል መሪቃል የንባብ ቀን በባሌ ዞን ማረሚይ ቤት መካሔድ ተጀመረ።
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት፣ ከኦሮሞ ባህል ማዕከል እና ከኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ጋር በመተባበር "የዳበረ ንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!" በሚል መሪ ቃል ከጥር 25/2018 ዓ.ም ጀምሮ በሮቤ ከተማ ለማካሄድ በተዘጋጀው የመጻሕፍት ሽያጭና አውደ ርዕይ፣ የንባብ ሳምንት እና የፓናል ውይይት መድረክ አንዱ የሆነው የማረሚያ ቤት የንባብ ሳምንት በባሌ ዞን ማረሚያ ቤት መካሔድ ጀምሯል።
በዝግጅቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሮቤ ዞን ማረሚያ ቤት ኃላፊ ኮማንደር ረቢራ ቃሲም በማረሚያ ቤቱ ያደረጋችሁት በጎ ተግባር የነበረብንን የመጽሐፍ እጥረት የሚሽፍን ሲሆን የተለገሱት መጽሐፍቶች ታራሚዎች ራሳቸውን እንዲያንጹበት ያደርጋልና በታራሚው ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው ሰለ ተቋሙ ተልዕኮ ንባብን በሀገሪቱ ለማስፋፋት እና የሀገሪቱን መረጃ በማሰባስብ እና በመሰነድ እየሰራ 83 ዓመታትን ያስቆጠረ ታላቅ ሀገራዊ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል።
ታራሚ በእርምት ጊዜው ያለውን የእርምት ጊዜ የሚያጣፍጥላችሁና የሚያፈጥንላችሁ ትምህርት ቤት አንዱ ንባብ ስለሆነ የእርምት ግዜያችሁን ለማጣፈጥ ንባብን ባህል አድርጉ በርካታ የሀገራችን ታላላቅ ደራስያንና ጸሐፍት ታላላቅ ስራዎችን ሰርተው ለንባብ ያበቁት የእርምት ጊዜያቸውን ተጠቅመው ነው ብለዋል።
የእያንዳንዱ ግለሰብ ታሪክ ያስተምራል በቆይታችሁ ልትጽፉ ይገባል።
ማረሚያ ቤት መማሪያም መጽሐፊያም ቦታ ሊሆን ይችላል።
በዝግጅቱ በታራሚዎች የሥነ-ጽሑፍ ስራዎች ቀርበዋል።
ንባብና የማረሚያ ቤት ህይወት በደራሲ ኢሳያስ ወርዶፋ፣የመዝጊያ ስንቅ በደራሲ ይታገሱ ሲቀርብ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህሩ በዶክተር ኑረዲን አማን የማረሚያ ቤት ቆይታ ታራሚው በንባብ ራሱን ሊያጎለብት እንደሚገባ ግንዛቤ ተሰጥቷል።
በመጨረሻም ሥነ-ጽሑፍ ላቀረቡ ታራሚዎችና ከአገልግሎቱ ለሮቤ ማረሚያ ቤት የተለገሱ በበጀት ከአንድ መቶ ሰባ ዘጠኝ ሺህ ብር በላይ የፈጁ በቁጥር አራት መቶ አምስት መጽሐፍት የአገልሎቱ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው ለሮቤ ማረሚያ ቤት ኃላፊ ኮማንደር ረቢራ ቃሲም አስረክበዋል።
በዝግጅቱ የአገልግሎቱ የጽ/ቤት ኃላፊ እና የዋና ዳይሬክተሩ ተወካይ አቶ አባተ ካሳው፣የሮቤ ዞን ማረሚያ ቤት ኃላፊ ኮማንደር ረቢራ ቃሲም፣ደራሲ ኢሳያስ ኦርዶፋ እና ደራሲ ይታገሱ ጌትነት የማረሚያ ቤቱ የተለያየ ስራ ክፍል ኃላፊዎች፣የሚድያ አካላት ተገኝተውበታል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
ደማቅ አቀባበል የባሌ ዞን መግቢያ በሆነችው ዲንሾ ወረዳ ዲንሾ ብሔራዊ ፓርክ
ዲንሾ ወረዳ
24/2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት፣ ከኦሮሞ ባህል ማዕከል እና ከኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ጋር በመተባበር "የዳበረ ባህል ለትምህርት ጥራት!" በሚል መሪ ቃል ከጥር 25/2018 ዓ.ም ጀምሮ በሮቤ ከተማ ለማካሄድ ባዘጋጀው የመጻሕፍት ሽያጭና አውደ ርዕይ፣ የንባብ ሳምንት እና የፓናል ውይይት መድረክ የአቀባበል መርሐ ግብር በዲንሾ ብሔራዊ ፓርክ የአቀባበል ዝግጅቱን በድምቀት አካሂዷል።
በመርሐ ግብሩ የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው እና የሚመለከታቸው የስራ ክፍል ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣የዲንሾ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ኢድሪስ፣የባሌ ዞን ም/አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም ኃይሌና የሚመለከታቸው የስራ ኃላፊዎች እና አባ ገዳዎች እና ሀዳሲንቄዎች ተገኝተውበታል።
በቦታው በርካታ አመራሮች መልዕክት ሲያስተላልፉ የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ኢድሪስ ወደ ሰላም እና የልማት አምባሳደር ወደሆነችው ዲንሾ ወረዳ በሰላም መጣችሁ ብለዋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
ጥር 23/2018 ዓ.ም
በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት
አዲስ አበባ
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግበትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ዛሬ ጥር 23/2018 ዓ.ም ለታላቁ ደራሲ (አጋዝ) ገብረየሱስ ኃይለማርያም በተለያዩ ቋንቋዎች በሥነ ጽሑፍ ዘርፉ ላበረከቱት ታላቅ አሻራ የላቀ ምስጋና የምስክር ወረቀተ አበረከተ።
በዝግጀቱ የደራሲው ታሪክ በዕዝራ እጀጉ በስፋት ሲቀርብ፣በደራሲ ብርሃነ አለሙ ገሳ ስለ አጋዝ ገብረየሱስ ግለሰባዊ ጥረትና ችሎታ እንዲሁም በገጣሚ ክፍሌ ተመስገን ከ'ጫሙት ሽካ' መጽሐፍ ስራ ላይ በአጭሩ ለታዳሚው ቀርቧል።
በምስክር ወረቀቱ አበርክቶ ላይ የተቋሙ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው በመገኘት ለሰሩት በርካታ የሥነ ጽሑፍ ስራዎች ምሥጋና ሰጥተዋቸዋል።
ደራሲው በተለያዩ ቋንቋዎች 15 መጻሕፍትን በማሳተም ለአንባቢ እንዳበረከቱ በፈረንጆቹ ሚሊኒየም መባቻም ሱሉልታ ተራራ ላይ በማደር የሚሊኒየም የመጀመሪያዋን ቀን የንጋት ጀምበር ፎቶ ግራፍ መሰነዳቸውንም ኃላፊው ተናግራዋል።
ከደራሲው ታሪካዊ ፎቶ ከመሰነድ በተጨማሪ በጉራጊኛ ቋንቋ ያሳተሟቸውና ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፉላቸው "የጫሙት ሽካ" እና "ተኬትነት አጂነት" የተሰኙትን መጻሕፍቶቻቸውን የመጀመሪያ ቅጂ ለተቋሙ ማስረከባቸውንም በዝግጀቱ በመግለጽ ምስጋናና ክብር ተሰጥቷቸዋል።
በመጫረሻም የደራሲውን ሰነዶች እንዲሁም ተወዳጅ ሚድያና ኮሙኒኬሽን የመዝገበ አዕምሮ መጽሐፍ ቅጽ 3 በስጦታ ለተቋሙ ያበረከተውን ለተቋሙ የሰነድና መዛግብት አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ለአቶ ሰለሞን ጠና በክብር አስረክበዋል።
በዝግጅቱ ላይ የአገልግሎቱ የጽ/ቤት ኃለፊው አቶ አባተ ካሳው፣የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ መሰረት አመርጋ እና ጥሪ የተደረገላቸው የደራሲው አድናቂዎች ተገኝተዋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት፣ከኦሮሞ ባህል ማዕከል እና ከኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ጋር በመተባበር ከጥር 25/2018 ዓ.ም ጀምሮ "የዳበረ ንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!" እንዲሁም "መጻሕፍትን በማንበብ እንታረም!" በሚል መሪ ቃል በሮቤ ከተማ እና በባሌ ዞን ማረሚያ ቤት የመጻሕፍት ሽያጭ እና አውደ ርዕይ፣የንባብ ሳምንት፣የፓናል ውይይት፣ መድረክ ለማካሔድ ዝግጀቱን አጠናቋል።
👉 ተቋሙ በቆይታው የመጽሐፍ አወድ ርዕይ ያካሒዳል።
👉የባሌ እና አካባቢው መዛግብት በተቋሙ የሚገኙትን ያስጎበኛል።
👉የንባብ ክበባት ምሥረታ እና በተጋበዙ ታላላቅ ደራሲያን ለተማሪዎች አነቃቂ ንግግር ይደረጋል፡፡
👉 የሥነ-ጥበብ ምሽት እና የተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር ይደረጋል፡፡
👉 ለትምህርት ቤቶች የመጻሕፍት ስጦታ ይደረጋል፡፡
👉 በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዩች ላይ የሚያጠነጥኑ ጽሑፎችን በማቅረብ ከሚመለከታቸው ጋር ውይይት ይደረጋል።
👉በባሌ ዞን ማረሚያ ቤት የንባብ ቀን ያካሒዳል፡፡
👉የታራሚዎች የሥነ ጽሑፍ ውድድር ያካሒዳል።
👉የመሰረተ ልማቶችና ቱሪስት መዳረሻዎችንና ትምህርት ቤቶች ጉብኝት በማካሔድ የሮቤ ቆይታውን ያጠናቅቃል
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻኅፍት አገልግሎት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች
እንኳን ለከተራና ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል።
በዓሉ የፍቅር፣ የመተሳሰብ፣ የሰላምና የደስታ እንዲሆንላችሁ ጭምር ይመኛል።
መልካም ዐውድ ዓመት!!
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
