ar
Feedback
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service

የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service

الذهاب إلى القناة على Telegram

.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
509
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ታላቅ የዲጂታይዜሽን ፕሮጀክት በይፋ አስጀመረ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር፣ የ«ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030» ስትራቴጂካዊ ግብ አካል የሆነውን ዘመናዊ የዲጂታይዜሽን ፕሮጀክት በይፋ አስጀምሯል። በምረቃ መርሐግብሩ ላይ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት ባስተላለፉት መልዕክት፤ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) ባለፉት 83 ዓመታት እጅግ ውድ የሆነውን የሀገሪቱን የጽሑፍ ሀብት በብሔራዊ ደረጃ ለመሰብሰብ፣ ለመጠበቅና ለትውልድ ለማሻገር ዕድል ያገኘ ቀዳሚ ተቋም መሆኑን ገልጸው ኢትዮጵያ የጽሑፍ ታሪኳ ጥንታዊና የስልጣኔ ምልክት የታየባት ቀዳሚ ሀገር ብትሆንም፣ የጽሑፍ ሀብቷን በሥርዓት የሚሰበስብ ዘመናዊ ስርዓት በማደራጀት በኩል ግን የታሪኳን ያህል ፈጣን እንዳልነበረች አንስተዋል። ይሁን እንጂ ይህንንም የታሪክ ምዕራፍ የሚቀይርና ያለንን ታሪካዊ ሀብት ወደ መላው ዓለም በዲጂታል መረብ የምታገናኝበትን የቴክኖሎጂ ሽግግር ዛሬ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ማብሰሯን ገልጸዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ በበኩላቸው፤ በሀገራችን ትናንት በርካታ ታሪካዊ ክንዋኔዎች መፈጸማቸውን፣ ብዙ እውቀቶች መመንጨታቸውንና ድርሳናት መጻፋቸውን አስታውሰዋል። እነዚህ ውድ ሀብቶችና እውቀቶች ዕድሜያቸው ሲገፋ ተበላሽተውና ወድቀው እንዳይቀሩ ወደ ነገ ማሻገር እንደሚገባ ጠቁመው፤ ቴክኖሎጂ የሰጠንን ትልቅ አቅም ተጠቅመን የትናንትን አድሰን ወደ ነገ ማሻገር መቻላችን ትልቅ ስኬት መሆኑን አብራርተዋል። ሚኒስትሩ አክለውም ዲጂታል ኢትዮጵያ ስንል ከዛሬና ከወደፊቱ ጉዟችን ባሻገር ወደኋላም ተመልሰን ታሪካችንን በዲጂታል ማዕቀፍ ውስጥ ማካተትን ይጨምራል። ትናንትን በማደስ፣ ዛሬን በማጎልበትና ነገ ደግሞ አዳዲስ እውቀቶችን በተግባር ላይ በማዋል የተሟላ የዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት የሚያስችል ትልቅ ፕሮጀክት ነው ብለዋል። በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ በበኩላቸው፤ ዛሬ የተበሰረው ፕሮጀክት በኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ተግባር የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ታላቅ ሀገራዊ ግብ እውን ለማድረግና ለትውልድ የምትተርፍ ሀገር ለመገንባት ትልቅ አበርክቶ ያለው በመሆኑ፣ ፕሮጀክቱ እስከሚጠናቀቅበት ጊዜ ድረስ በተሟላ ቁርጠኝነትና በትጋት እንዲሰራ በአደራ ጭምር አሳስበዋል። ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በርካታ የመንግሥትና የግል ተቋማት የቴክኖሎጂ ድጋፍ ጥያቄ አቅርበውለት የነበረ ቢሆንም የመረጃ ሀብቶቹን ወደ ዲጂታል የመቀየርን አስቸኳይነት በከፍተኛ ትኩረት በመገንዘብ ለቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ቅድሚያ በመስጠት እውን ያደረገው ፣  ዓለምአቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ እጅግ ዘመናዊ የዲጂታይዜሽን ቴክኖሎጂዎችን፣ ሶፍትዌሮችንና የሀርድዌር ሥርዓቶችን ያካተተ፣ ከእነዚህም መካከል ለጥንታዊ መጻሕፍት ልዩ ጥንቃቄ የሚያደርጉ ዘመናዊ የመጻሕፍት ስካነሮች፣ የሰነድና የካርታ መዛግብት ስካነሮች እንዲሁም የተደራጁ የኮምፒውተር አውታረ-መረብ መሰረተ-ልማቶች በአጠቃላይ 792,422 (ሰባት መቶ ዘጠና ሁለት ሺህ አራት መቶ ሀያ ሁለት) የአሜሪካ ዶላር ወይም በወቅታዊ ምንዛሬ 126,787,520 (መቶ ሀያ ስድስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሰማኒያ ሰባት ሺህ አምስት መቶ ሀያ) የኢትዮጵያ ብር ወጪ የተደረገበት ነው። ይህ የተዘረጋው ቴክኖሎጂ በተቋሙ ውስጥ ያሉትን የጽሑፍ ሀብቶች በሙሉ አቅም ወደ ዲጂታል ለመቀየር የሚያስችል ቋሚ መሰረተ-ልማት ሲሆን፤ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በተያዘው በዚህ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ላይ 20 ሚሊዮን ገጾችን ወደ ዲጂታል የመቀየር ሥራ በፓይለት ፕሮጀክትነት በተሳካ ሁኔታ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዟል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

በተቋሙ በሚገኙ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት የሜታዳታ አመዘጋገብ ዙሪያ በዘርፉ እየሰሩ ለሚገኙ ባለሙያዎች ሦሥተኛ ዙር የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሠጠ። ሰኔ 7/2018 ዓ.ም አዳማ ጥራት ያለው ሜታዳታ የተሻለ መዳረሻ፣የተሻለ ጥበቃ እና የተሻለ ዕውቀት ማጋራትን ያረጋግጣል ተባለ። የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት በተቋሙ የሚገኙ የሀገር መረጃዎችን ጥራት ያለው ሜታዳታ ውስጥ በማስገባት ሰዎች ወደ ተቋሙ መምጣት ሳይጠበቅባቸው መረጃ ማግኘት እንዲችሉ በዘርፉ ለሚሰሩ ባለሙያዎች አንድ ዓይነት አረዳድ እንዲኖራቸው የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል። በግንዛቤ ማስጨበጫው በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የተቋሙ ሥራ አመራር አቶ አብነት አበራ ይሄ ስልጠና ለሦሥተኛ ዙር እንዲሰጥ የተፈለገው በዘርፉ የሚሰሩ ባለሙያዎች የተለያየ እና የተዘበራረቀ የመረጃ አሞላል  እንዳላቸው በመገንዘብ የተዘጋጀ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና እንደሆነ ተናግረው  ይሄንን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ካገኙ በኃላ ስራውን የሚሰሩ ባለሙያዎች አንድ ዓይነት አረዳድ ኖሯቸው በዲጅታል 2030 ዓ.ም በመንግስት ደረጃ ለተያዘው ዲጂታል ኢትዮጵያ ትኩረት የተሰጠውን እንደ እኛ ተቋም የሚገኙ የሀገር መረጃዎች ሜታዳታ በትክክል መሙላት እንዲችሉ እና የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት እንደሚያስችላቸው ጠቁመዋል። ጥራቱን የጠበቀና ግልጽ የሆነ ሜታዳታ ካልያዝን እንደ ተቋም ከተመረጡ ተቋሞች ውስጥ ላንገባ ስለምንችል ይሄንን ስልጠና በማግኘታችሁ መረጃውን ወጥ በሆነ መልኩ መያዝ እንድንችልና ጥራት ያለው ሜታዳታ ተመዝግቦ መረጃው ለመረጃ ፈላጊዎች ግልጽ ሆኖ መቀመጥ እንዲቻል ለዘርፉ ባለሙያዎች እየተሰጠ የሚገኘው የግንዛቤ ማስጨበጫው ስልጠና ወቅቱን ያማከለ እንደሆነም ተናግረዋል። ይህንን ጊዜውን የዋጀ ስልጠና አዘጋጅቶ እየሰጠ የሚገኘው የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ግዛው ዋቅጅራ በግንዛቤ ማስጨበጫው የሜታዳታ ምንነት፣ በቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ መጻሕፍት፣ሰነዶች፣ ፎቶ ግራፎች፣ካርዶች፣ዲጅታል ፋይሎች እና ሌሎች ሀብቶች ለመግለጽ ለማደራጀት፣ ለሚፈልግ እና ለሚጠብቅ የሚያገለግል የተዋቀረ መረጃ መሆኑን ሲያስገነዝቡ የሜታዳታ አስፈላጊነትንም የመረጃ ፍለጋን እንደሚያሻሽል፣ የስብስብ አስተዳደርን እንደሚያቀላጥፍ፣ ዲጅታል ጥበቃንም እንደሚያጠናክር፣የመረጃ ልውውጥንም እንደሚያሳልጥ ጠቁመው የሚታዩ ተግዳሮቶችን በተመለከተ የባለሙያ እጥረት፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ውስንነት፣የሜታዳታ ቁጥጥር አለመዘርጋት፣መመዘኛ /መስፈርት/አለመኖር፣የመረጃ ጥራት ችግርም እንደሚገጥም ዳታ ጀምሮ የማቋረጥ ነገርም እንደሚኖር ተናግረዋል። ስራ አስፈጻሚው ባቀረቡት የግንዛቤ ማስጨበጫ ጽሑፋቸው በማጠቃለያነት ሜታዳታ በቤተ መዛግብትና ቤተመጻሕፍት ውስጥ የመረጃ አስተዳደር ፍለጋ፣ጥበቃ እና የመረጃ ልውውጥ መሠረታዊ መሣሪያ እንደሆነም ጠቁመው አክለውም ሜታዳታ በመረጃ አስተዳደር ተደራሽነት እና ጥበቃ መሠረት መሆኑንም ገልጸዋል። በመቀጠል በአብያተ መጻሕፍት መረጃ ሃብቶች መሪ ስራ አስፈጻሚ የማደራጃ ዴስክ ከፍተኛ ባለሙያ ወ/ሮ ሂሩት ካሳ ILARMs Essentials: Standard Cataloging Training እና የመዛግብት ማደራጃ ዴስክ ኃላፊ በአቶ አብይ ብሩክ ደግሞ በመዛግብት አደረጃጀት ከምዘና መረጣ ጅምሮ፣ አደረጃጀቱን፣ የመግለጫዎች አዘገጃጀቱን፣ ለመዛግብቱ እንክብካቤና ጥበቃ በማድረግ እንዴት አገልግሎት ላይ እንደሚውሉ እንዲሁም መዛግብት በ Integrated Library, Archives and Records Management System (ILARMS) Software እንዴት መዛግብቱ እንደሚደራጁ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል። በቀረቡት ሰነዶች ላይ ጥያቄ፣ሃሳብ አስተያየት ሲቀርብ ሰልጣኞቹ ስልጠናው ከበፊቱ በተሻለ እውቀት ኖሯቸው እንዲሰሩ በባለሙያዎች በታገዝ ዳታ እንዲያስገቡ ልምምድ ሲያደርጉ፤ከዚህ ቀደም በእቅድ ተለክቶ የተሰጣቸውን ዳታ የማስገባት ስራም በተቀመጠው እቅድ መሰረት አጠናክረው እንዲሰሩ ስራውን ከሚከታተሉ ሥራ አስፈጻሚዎች መልዕክት ሲተላለፍ በስልጠናው የዲጂታላይዝድ ባለሙያዎችም መሳተፍ እንደነበረባቸው ተመላክቷል። ስልጠናውን ለሰራተኞቹ ያመቻቸው የተቋሙ የሰው ሀብት አስተዳደር እና ብቃት  የሥራ ክፍልም ስልጠናዎች መዘጋጀት ያለባቸው ከባለሙያው የአቅም ክፍተት በመነሳት እንደሆነ ዛሬ ከነበረው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መረዳት እንደተቻለ ተጠቁሟል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

በሥነ ጥበብ ታሪክ ውስጥ ደማቅ አሻራ ላኖረው ታላቁ የጥበብ ሰው እውቅ ተሰጠ። የኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት በኢትዮጵያ ሥነ ጥበብ ታሪክ ውስጥ ደማቅ አሻራ ያኖረው፣ ብዕራዊ ለዛው ፍጹም አቻ ያልነበረው ባለቅኔ፣ ጸሐፌ ተውኔት እና የዘፈን ግጥም ደራሲ ሙሉጌታ ተስፋዬ ተወልዶ ባደገባት በወልዲያ ከተማ በስሙ የተሰየመ ቤተመጻሕፍት በቅርቡ ተመርቆ ለአንባቢያን ክፍት መደረጉ፥ ተቋማችን ትልቅ ዕውቅና የሚሠጠው በእጅጉ የሚመሰገን ተግባር ነው። ይህ በወልዲያ ከተማ አስተዳደር የባህል፣ ቱሪዝም እና ስፖርት መምሪያ አማካኝነት የተገነባው ዘመናዊው "የባለቅኔ ሙሉጌታ ተስፋዬ የሕዝብ ቤተመጻሕፍት"፤ ባለቅኔው ለኢትዮጵያ ሥነ ጥበብ ካለምንም ምንዳ ያበረከተውን ውድ የጥበብ ሥጦታ ለማሰብ የተቋቋመ የመጀመሪያው ታላቅ መታሰቢያ መኾኑን ተቋማችን ይገነዘባል። "ሰው የተፈጠረው ንጉሥም ቅዱስም ለመኾን ነው፤" በሚለው ጥልቅ ፍልስፍናው እና በዕውቀትም በመንፈስም በበሰለ ማንነቱ የሚታወቀው ሙሉጌታ ተስፋዬ፤ በኢትዮጵያ ሥነ ጥበብ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሠጠው ጠቢብ ነው። በተለይም በ1977 ዓ.ም. በወሎ የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ፣ "እውነት ከመንበርህ የለህማ!" በሚለው ግጥሙ የገለጸው ጥልቅ ሰብዓዊ ሩኅሩኅ ስሜት፣ እውነተኛውን የጠቢብነት ባሕርዩን የሚመሰክር ነው። ባለቅኔው በሙዚቃው ዘርፍም የነበረውን ታላቅ ቅኔያዊ ዐቅም፤ ለአበበ ተካ፣ ለጼዴንያ ገ/ማርቆስ፣ ለሐና ሸንቁጤ፣ ለብጽዓት ሥዩም፣ ለዣን ሥዩም ኄኖክ፣ ለፍቅረዐዲስ ነቅዓ ጥበብ፣ ለማርታ አሻጋሪ እና ለአበበ ብርሃኔ ባበረከታቸው የዘፈን ግጥሞች በተግባር አስመስክሯል። ተቋማችን ይህንን ታላቅ የጥበብ ሰው የሚዘክር ቤተመጻሕፍት በመገንባት ለባህል፣ ለጥበብ እና ለዕውቀት በሀገር ደረጃ የሚታወቅ ሥራ ላበረከቱ ኢትዮጵያውያን መታወሻ የማቆም ተግባርን በምሣሌነት ላሳየው ለወልዲያ ከተማ አስተዳደር አድናቆቱን እየገለጸ፤ ይህ ቤተመጻሕፍት የበርካታ አንባቢዎች የዕውቀት ማዕከል ኾኖ እንዲያገለግል ተቋማዊ ድጋፋችን እንደማይለያቸው በዚሁ አጋጣሚ ይገልጻል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

የሰኞ ንጋት «እንገናኝ እንሰናኝ» መድረክ፦ ትስስራችንን እናጠንክር፣ በርኅራኄ  እንተያይ ሰኔ 1/ 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ በ3ኛው ዙር «እንገናኝ እንሰናኝ» የሰኞ ንጋት መድረክ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት «ትስስራችንን እናጠንክር፣ በርኅራኄ እንተያይ» በሚል መሪ ሐሳብ ለተቋሙ ባልደረቦች ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በመድረኩ ላይ አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት እንደገለጹት፣ ሕዝቦች በተሳሰረ ማንነትና በትብብር አብረው አገርን እንደሚገነቡ እንጂ አንድ ወገን ብቻውን ቆሞ አገር ማቅናት እንደማይችል አስገንዝበዋል። ይህንን እውነት ወደ ተቋማዊ አሠራር ስናመጣውም፣ በተቋሙ ውስጥ ቀድሞ የነበረውም ሆነ ዘግይቶ የተቀላቀለው ሠራተኛ ሁሉ «ተቋም» በሚለው የጋራ ጥላ ሥር የየራሱን አሻራ እንደሚያሳርፍና ለጋራ ስኬት እንደሚሠራ አብራርተዋል። ዋና ዳይሬክተሩ በትብብርና አብሮነት ጉዞ ውስጥ ወሳኝ የሆኑትን Apathy (ግዴለሽነት)Sympathy (አዘኔታ) እና Empathy (የስሜት ተካፋይነት) የተሰኙ ሦስት ቁልፍ ፅንሰ-ሐሳቦችን በጥልቀት ዳስሰዋል። የቃላቱ ትርጉምና በተቋማዊ ግንባታ ላይ ያላቸው ሚናም በመድረኩ ላይ በሚከተለው መልኩ ተብራርቷል፦ Apathy (ግዴለሽነት)፦ የሌሎችን ሁኔታ፣ ችግርም ሆነ ደስታ ምንም ዓይነት ስሜት ሳይሰጡ በቸልተኝነት ማለፍ ሲሆን፣ ይህ ዓይነቱ አመለካከት የተቋምን ትስስር የሚጎዳ እንደሆነ ተገልጿል። Sympathy (አዘኔታ)፦ የሌላውን ሰው ችግር ወይም ስቃይ ከውጭ ሆኖ ማዘንና «አይዞህ» ማለት ሲሆን፣ ምንም እንኳ መልካም ቢሆንም ብቻውን ግን በቂ እንዳልሆነ ተብራርቷል። Empathy (የስሜት ተካፋይነት)፦ እራስን  በሌላው ሰው ቦታ ተክቶ፣ ያ ሰው ያጋጠመውን ችግር በእራስ ላይ እንደደረሰ አድርጎ የመረዳት ጥበብ ነው። አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት  አክለውም፣ «Empathy (የስሜት ተካፋይነት) ማለት የኛን ዕርዳታ ወደሚፈልግ ሰው አንድ እርምጃ ጠጋ ማለትን፣ በዚያ ሰው ጫማ ውስጥ ሆኖ የማሰብ ጥበብ ነው» ብለዋል። በመጨረሻም፣ የእያንዳንዱ ሠራተኛ አዎንታዊ አስተዋጽዖ በሌላው ላይ እየተጨመረ ለሚገነባው አገርና ተቋም፣ እርስ በርስ የመተሳሰር እና በርኅራኄ የመተያየት ክህሎትን ማዳበር እንደሚገባ አጽንዖት ተሰጥቶበታል። በተለይም በሕዝብ አገልግሎት (Public Service) ዘርፍ ላይ የተሰማሩ የተቋሙ ባልደረቦች፣ እርስ በርስ ክህሎትን የመጋራትና የመደጋገፍ (የመተናነጽ) ባህልን ይበልጥ ሊያጠነክሩ እንደሚገባ በማሳሰብ መድረኩ ተጠናቋል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

ግንቦት 29/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት "እንገናኝ እንሰናኝ!" የሠራተኞች የሠኞ ንጋት መድረክ በየኹለት ሳምንት የሚቀርበው ሦሥተኛ መድረካችን ሰኞ ሰኔ 1/2018 ዓ.ም ማለዳውን ይካሒዳል። በየኹለት ሳምንት የሚቀርበው ሦሥተኛው የሠራተኞች መወያያ መድረካችን በአጋጣሚ ሰኔና ሰኞ የገጠመበት ነው። ሰኔና ሰኞ በኢትዮጵያ ባህል ውስጥ ሁለት መጥፎ ወይም አስቸጋሪ ነገሮች በአንድ ጊዜ መገጣጠማቸውን የሚገልጽ ተወዳጅ ፈሊጣዊ አነጋገር ነው።  አነጋገሩ በዋናነት ሁለት ትርጉሞች አሉት። ቀጥተኛ ትርጉም፦ ሰኔ፦ በኢትዮጵያ የቀን አቆጣጠር የዓመቱ አስረኛ (10ኛ) ወር ሲሆን፣ የክረምቱ መግቢያና የዝናብ ወቅት ነው። ሰኞ፦ ከእሑድ እረፍት ቀጥሎ ሳምንት የሚጀመርበት የመጀመሪያው ቀን ነው። ዘይቤያዊ ትርጉም፦ አንድ ሰው ችግር ውስጥ እያለ ሌላ ተጨማሪ ፈተና ሲገጥመው «ነገሩ ሰኔና ሰኞ ሆነብኝ» ይባላል።  ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

‎ የድምጽ መስጫ ቀን ደረሰ ከ50 ሚሊዮን በላይ መራጮች የሀገራቸውን የነገ መጪውን ዕድል ለመወሰን ነገ ሰኞ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ቀጠሮ ይዘዋል። በምርጫ ሂደት የሚጸናው ሰላም፣ የተቋማት ጥንካ
የድምጽ መስጫ ቀን ደረሰ ከ50 ሚሊዮን በላይ መራጮች የሀገራቸውን የነገ መጪውን ዕድል ለመወሰን ነገ ሰኞ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ቀጠሮ ይዘዋል። በምርጫ ሂደት የሚጸናው ሰላም፣ የተቋማት ጥንካሬ እና የዜጎች ኃላፊነት በርካቶች የሚመኙትን የፖለቲካ መረጋጋትና የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማፋጠን ወሳኝ ሚና ይጫወታል። የዜጎች ንቁ ተሳትፎ፣የድምጽ ክብር እና የሕግ የበላይነት በተግባር የሚገለጽበት ታላቅ መድረክ ነውና ተስፋችን ብሩህ እንዲሆን የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል። ‎ ‎7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ውድድር ብቻ ሳይሆን፣ የዜጎች ድምጽ በሀገር ዕጣ ፈንታ ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ የሚያሳይ ወሳኝ ምዕራፍ ነው። ‎ ‎በዕለቱ ኢትዮጵያውያን የሀገራችንን ፖለቲካዊ እና ልማታዊ አቅጣጫ ለመወሰን በሚሊዮኖች ወደ ድምጽ መስጫ ጣቢያዎች የአንድ ድምጽ ዋጋዋን በመረዳት ይመራኛል፣ ያስተዳድረኛል፣ ይበጀኛል ለሚሉት ድምጻቸውን በመስጠት ይመርጣሉ። የተቋማችን ሰራተኞችም ለምርጫ የተሰጠንን የሥራ ቀን በተግባር የምንጠቀምበት እናድርግ እያልን መልካም ጊዜ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን። ‎ ‎ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

ሀገራችንን የጽሑፍ ቅርሶች በዓለም የትውስታ ማኀደር ለማስመዝገብ በቅርሶች አሰባሰብ ዙሪያ ሲካሄድ የነበረው መርሐ ግብር ተጠናቀቀ። ኢሊሌ ሆቴል ግንቦት 21/2018 ዓ.ም የጽሑፍ ቅርሶችን የማስመዝገብ ጉዳይ ሀገራዊ ፖሊሲ ሆኖ ሊቀርብ ይገባዋል ተባለ። የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከዩኔስኮ ጋር በመተባበር ለሁለት ቀናት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የሀገራችንን የጽሑፍ ቅርሶች በዓለም የትውስታ ማኀደር ለማስመዝገብ የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብር ተጠናቋል። በመርሐ ግብሩ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እና የብሔራዊ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የዓለም ትውስታ (ትዝታ) ማኅደር (MOW) ኮሚቴን ሥርዓት የማሲያዝ ዕቅድ ለውይይት አቅርበዋል። ኃላፊው ባቀረቡት የአሠራር ሥርዓት ማስያዣ ዕቅድ ላይ የአሠራር ሥርዓቱ በተቋሙ ሥርዓት ውስጥ መኾን ያስፈለገበት ምክንያቶች ሲገልጹ የኮሚቴው ተግባር በተቋሙ መዋቅር ውስጥ በብሔራዊ ደረጃ የትውስታ እና የጥንታዊ ጽሑፍ ቅርስ አስተዳደር መዋቅር ውስጥ ለማካተት፣የቴክኒክ አቅምን በማሳደግ እና የዩኔስኮን መመሪያዎች ተግባራዊ ለማድረግ፣ አገልግሎቱ ይህንን ውሕደት በመምራት ለኮሚቴው ዘላቂ መዋቅራዊ መሠረት እንደሚፈጥር ተናግረዋል። የተቋማዊነት ዕቅድ ስኬታማ እንዲኾን የሚከናወኑ የሕግ ማኀቀፍ ተግባራት በተመለከተ የዩኔስኮ መርኆዎች በሚያስቀምጡት መርኀ መሠረት፣ የኮሚቴውን መተዳደሪያ ደንብ ማርቀቅ እና ማፀደቅ ፤ከአዋጅ ቁጥር 179/91 ጋር ወይም፣ በቅርቡ ይወጣል ተብሎ ከሚጠበቀው አዲስ አዋጅ ጋር ማጣጣም እንዲሁም የመንግስት ድጋፍ እና ዕውቅና ማረጋገጥ እንደሚያስፈልግ ኃላፊው ባቀረቡት የአሠራር ሥርዓት ማስያዣ ዕቅድ ጽሑፋቸው ላይ አስፍረዋል። በብሔራዊ ኮሚቴው  አጠቃላይ ቅርሶችን በማስመዝገብ ሂደት ውስጥ እንዴት መሠራት እንዳለበት በዶ/ር አሉላ ፓንክረስ ጥቅል መረጃ ቀርቧል። ብሔራዊ ኮሚቴው  የአባ ገሪማ ወንጌላት እና የሐረር ጥንታዊ መዛግብት በዓለም የትውስታ ማኀደር ለማስመዝገብ የሚያስችል ስራ ሂደቱን በጠበቀ መልኩ መሰራቱን ዶ/ር አሉላ ተናግረዋል። ስራው እውቅና ተሰጥቶት እንዲሰራ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብት ቤተመጻሕፍት አገልግሎት፣የቅርስ ጥበቃ ባለሥልጣን እንዲሁም የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ብሔራዊ ኮሚቴው ጠቁሞ በተለይ ከወመዘክር የተቋሙ  ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ለማስመዝገብ በሂደት ላይ የሚገኙትን ቅርሶች ያሉበትን ሁኔታ ለመመልከት  ኮሚቴውን ቦታው ድረስ በመውሰድ ቅድመ ምልከታ የማድረግ ሥራ መሰራቱ ተገልጿል። ከዩኔስኮ አቶ ጌቱ አሰፋ ስራዎችን ለመስራት ስራ ማስኬጃ ፈንድ እንዴት ማግኘት እንደሚቻል አቅጣጫዎችን የሚጠቁሙ የግንዛቤ ማስጨበጫ ጽሑፍ ሲያቀርቡ ክልሎች በአካባቢያቸው ቢመዘገቡ ያሏቸውን ሁለት ሁለት ቅርሶች ካሏቸው ታሪካዊ አመጣጣቸውንና እድሜያቸው አንጻር ዝርዝረው አቅርበዋል። ብሔራዊ ኮሚቴው ሰርቶ ለዩኔስኮ እውቅና እንዲሰጣቸው የተላኩ የጽሑፍ ቅርሶች ይሁንታ የሚያገኙበት ጊዜን ውጤቱ በ2027 ሰኔ ወር ላይ እንደሚታወቅ ተጠቁሟል። በMOW የተመዘገቡ የመረጃ ሀብቶች ጠቅላላ ብዛት 570 ስብስቦች ከ72 አገሮች እና 4 ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የመጡ ዋና ዋና ርዕሰ  ጉዳዮች (key Topics) የሳይንስ አብዮት (scientific revolution) የሴቶች አስተዋጽኦ-በታሪክ (women's contribution to history) እንደሆነ ተገልጿል። በከሰዓቱ መርሐ ግብር በቀረበው የዕቅድ አሠራር ላይ ውይይት እና ብሔራዊ ኮሚቴው ስራውን በትኩረት ከመስራት አንጻር የወደፊት የትኩረት አቅጣጫ ላይ ትኩረት ማድረግ፤ከክልል አመራሮች ጋር የሚፈጠር የስራ ግንኙነት፤ ለወመዘክር ሪፖርት የማቅረብ ስርዓት መዘርጋትና ስራውን በዕቅድ ላይ በማካተት ቀጣይነት እንዲኖረው ማስቻል የሁሉንም ትብብር እንደሚጠይቅ በማመላከት ተጠናቋል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

በቅርሶች አሰባሰብ ዙሪያ ከዘጠኙ ክልሎችና ከሁለት የከተማ መሥተዳድሮች ለተውጣጡ የባህል፣ ቱሪዝምና ስፓርት ቢሮ ኃላፊዎችና  ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ አውደ ውይይት ተጀመረ። ኢሊሌ ሆቴል አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከዩኔስኮ ጋር በመተባበር ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ጥንታውያን የሀገራችንን  የጽሑፍ ቅርሶች በዓለም የትውስታ ማኀደር ለማስመዝገብ የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እያካሄደ ይገኛል። የሚሰራው ሥራ ኢትዮጵያ ካላት ሀብት ውስጥ የተመዘገበው ውስን በመሆኑ እኛም እንደ ሌሎች ሀገራት ሀብቶቻችንን በዓለም ለማስተዋወቅ በጋራ መሥራት እንዳለብን የሚያስችል መድረክ እንደሆነም ተጠቁሟል። በመድረኩ የዩኔስኮ በአዲስአበባ ዳይሬክተር ዶ/ር ሪታ ቢሶልት፣ፕሮፌሰር አሉላ ፓንክረስት፣ፕሮፌሰር አህመድ ዘካሪያከ፣ተቋሙ የጽ/ቤት ኃላፊው አቶ አባተ ካሳው እና የሚመለከታቸው የሥራ ክፍል አመራሮች እና ባለሙያዎች፣ የኢትዮጵያ የጽሑፍ ቅርሶች አስመዝጋቢ ብሔራዊ ኮሚቴ አባላት እንዲሁም የክልሎችና የከተማ መስተዳድሮች የባህልና ቱሪዝም ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተውበታል። የዩኔስኮ በአዲስ አበባ ዳይሬክተር ዶ/ር ሪታ ቢሶኖት በውይይት መድረኩ  ተገኝተው እንደተናገሩት ኮሚቴው በህዳር ወር 2025 ሁለት ጥንታዊያን የሀገራችንን ታላላቅ የጽሑፍ ቅርሶች በዓለም የትዝታ (የትውስታ) ማኅደር UNESCO ለማስመዝገብ አስፈላጊውን ሰነድ የማሟላት ስራ ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የበርካታ ቅርሶች ባለቤት ብትሆንም እስካሁን በወመዘክር ከዛሬ 20 ዓመት በፊት ከተመዘገቡት በዓለም አቀፍ የሰው ልጆች የአእምሮ ሀብትነት 12ቱን የጽሑፍ ቅርሶች የማስመዝገብ ስራ ብቻ መሰራቱን አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ ጥንታዊያን የጽሑፍ ቅርሶችን የማስመዝገብ ስራን ብሔራዊ ኮሚቴው በጥልቀት እየሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል። የአገሪቷን ሀብት ለተተኪው ትውልድ ለማሻገር ኮሚቴው እያከናወነ ያለውን እንቅስቃሴ አጠናክሮ በማስቀጠል ለማስመዝገብ በሂደት ላይ የሚገኙትን በተሻለ መልኩ አጠናክሮ መስራት እንዳለበት ተናግረዋል። በውይይት መድረኩ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት የመረጃ ሀብቶች አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈጻሚ በአቶ ስለሺ ሽፈራው የጽሑፍ ሀብቶች ጥበቃ እና እንክብካቤ የሚስተዋሉ ችግሮች እና የመፍትኤ ሃሳቦች ዙሪያ  የግንዛቤ ማስጨበጫ ጽሑፍ ለውይይት ቀርቦ ከተሳታፊው ጥያቄዎችና የመፍትኤ ሃሳቦች ተሰጥተዋል። በመቀጠልም በዩኔስኮ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ሴክተር ኃላፊ አቶ አደራው ገነቱ አጠቃላይ የአለም የትውስታ ማኀደር UNESCO -MOW  አወቃቀሩን፣ ቅርሶችን ለመመዝገብ መሟላት  ያለባቸው ነገሮች፣አሰራሩን ፣አደረጃጀቱንና እንዴት መሰራት እንዳለበት፣ ተግባርና ኃላፊነት አስመልክቶ በአፍሪካ፣ በአለምአቀፍ እና በብሔራዊ ደረጃ ያለውን ሂደት በዝርዝር አቅርበዋል። በከሰዓቱ መርሐ ግብር የክልሎችና የከተማ መስተዳድሮቹ ተወካዮች ያሏቸውን ቅርሶች ከማሰባሰብ አንጻር እያከናወኑ የሚገኙትን ተሞክሮ አቅርበዋል። በአሰራር ሂደቱ ላይ እቅዶችን ከወመዘክር ጋር አስተሳስሮ ከመስራት አንጻር ክፍተት እንዳለና ትኩረት የሚሻው ጉዳይ እንደሆነም ተሞክሮ ባቀረቡት ተወካዮች በስፋት የተነሳ ሃሳብ ነበር። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን!! ቴሌግራም https://t.me/wamezeker ድረገጽ፡ https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr

የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው ዓመተ ሒጅራ (የ2018 ዓ.ል) የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይ
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው ዓመተ ሒጅራ (የ2018 ዓ.ል) የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል።