cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

muaz jemal

@Muazjemal

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat ko'rsatilmaganTil ko'rsatilmaganKategoriya ko'rsatilmagan
Advertising posts
498Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Обуначиларнинг ўсиш даражаси

Ma'lumot yuklanmoqda...

የጠፉ ተማሪዎች ጉዳይ አነጋጋሪነቱ ቀጥሏል፡፡ ልጆቹ የት ናቸው?
Hammasini ko'rsatish...
የጠፉት ተማሪዎች ጉዳይ (ሙአዝ ጀማል) 1 "እነ ኧከሌ ጩሁ እንጂ" ሳንል ድምፃችንን ማሰማት እንችላለን፡፡ በተፈጠሩ ጉዳዮች ሁሉ የሆነን ጎራ ማጥቃት ማንንም አይጠቅምም፡፡ ፌሚኒስቶችን መዝለፍ ልጆቹን አይመልሳቸውም፡፡ 2 የልጆቹ ጉዳይ (ሴቶችም ወንዶችም አሉበት ስለተባለ) የት እንዳሉ ማወቅ አልተቻለም፡፡ መንግስት አስመልሻለሁ ያላቸውን ሰዎች ሳይረከብ መግለጫ ሰጥቶ ከሆነ (በርግጠኝነት ወደዛ ድምዳሜ እየመጣን ነው) ተዓማኒነቱን ያሳጣዋል፡፡ እዚህ አስቀያሚ ጨዋታ ውስጥ ግን እነማን ሊኖሩ ይችላሉ? : ➊ የጃልመሮ ሰራዊት(?) በአከባቢው ያሉ አማፂያን እነሱ ስለሆኑ.... ሰውዬው የፖለቲካ ብስለቱ እምብዛም ስለሆነ መደራደሪያ ሊያደርጋቸው አስቦ ሊሆን ይችላል፡፡ ➋ መንግስት ፦ የጃል መሮን ሰራዊት ለማስመታት ልጆቹን ራሱ ጋር አድርጎ (አግቶ) ውግያ ለመግጠም፡፡ (ይሄ ብዙ አያሳምንም፡፡ ቢያንስ አስፈትቻለሁ ካለ በኋላ ሊለቃቸው ፡፡ ይችል ነበር፡፡) ➌ ይሄ በጣም የደከመ ጥርጣሬ ነው፡፡ ቢሆንም አለመገመት ከባድ ነው፡፡ ከአጋቾች በኩል ምንም መግለጫ ሳይሰጥ ፤ ምንም አይነት ቪድዮና ፎቶ ሳይወጣ (እኔ በበኩሌ ያየሁት የለም) እንዴት ስማቸው ታወቀ ፣ ቤተሰባቸው ተገኘ ፣ ፎቷቸው ተለቀቀ? አመለጠች የተባለችው ልጅ ለBBC ቃሏን ሰጥታለች፡፡ እንዴት አገኟት? እንዴት አገኘቻቸው? የተናገረችው ዲፓርትመንት ግቢ ውስጥ የማይሰጥ መሆኑ ይሄንን ጨዋታ ሌላ ግሩፕ በማይገመት መልኩ እየተጫወቱት ነው ያስብላል፡፡ ------------ የሆነው ሆኖ ልጆቹ መለቀቅ አለባቸው፡፡ ከዚህ ጉዳይ ለማትረፍ እየተሯሯጡ ያሉ ወገኖችም ከዚህ ርካሽ ጉዳያቸው ቢታቀቡ ጥሩ ነው፡፡ በሚዲያ የደረሰንን መረጃ አንለቅም ሀገር ያፈርሳል ብሎ ለቤተሰብና ይሄንን ጉዳይ ለሚከታተል ሰው እያለቀሱ ማርዳት (ያላቸው መረጃ ምን እንደሆነ ሳይታወቅ) ሀገር አያድንም፡፡መንግስትም ጥርት ያለ መግለጫ (ከይቅርታ ጋር ጨምሮ) መስጠት አለበት፡፡ ----- #ልጆቹ_የትናቸው? #Bring_back_our_student
Hammasini ko'rsatish...
አዲስ ማለዳ ጋዜጣ ዛሬ ቅዳሜ 16/2012 ይህንን መስላ ወጥታለች፡፡
Hammasini ko'rsatish...
ፍትህ ነገ ቅዳሜ ጥር 16/2012 ይህንን መስላ ትመጣለች፡፡
Hammasini ko'rsatish...
ይሄንን ፋራ ህዝብ ምን አድርጌ ላሰልጥነው ቆይ?😪 - ገና የኖቬል ሽልማት ሲታወጅና አብያችን መመረጡን ስሰማ እንዲህ ብዬ ነበር፡፡ትራምፕ ሲነግርህ ባረቀብህ እንጂ🤷‍♂️ "ከዓለም አንፃር ስትታይ ከጥፍር ቆሻሻ በላይ ተፅዕኖ ማትፈጥረው ሀገር መሪ የኖቬል ሽልማትን መቀበሉ እንዲሁ ይከነክነኛል" ሙሉውን ኮሜንት ላይ ሊንኩ አለ፡፡ ፡ በደንብ ላብራራልህ? : - እኛ እንደ ሀገር የምንኖረው አሜሪካና ሌሎች ሀያሎች ስለፈቀዱልን ነው፡፡ - ፖለቲካችንን እኛ አንመራውም ፤ መሪዎቹም ለመምራት አስበው አያውቁም፡፡ በነጮቹ እጅ ነው፡፡ - ምርጫውን ከፈለጉት ይከናወናል ፤ ካልፈለጉት ያራዝሙታል፡፡ አብጠህ ብትፈነዳ ምንም አታመጣም፡፡ - ዲሞክራሲህን አፈርፍረህ ብላው፡፡ ቅድሚያ ጥቅማቸውን ነው ሚያሰሉት፡፡ አንተ የኔ ፉዞ መጠቀሚያ ነህ፡፡ የሚተነፍስ ሮቦታቸው ነህ፡፡ ህይወቴን ለብሔሬ ገብራለሁ በል፡፡ ካልፈለጉት ራስህን እንኳን ማጥፋት እንዳትችል ያደረጉሀል፡፡ መጥፋትህ ካማራቸው ፤ ሊቢያን ተመልከታት፡፡ - ከሶሪያ በላይ ታሪክ አለን አትለኝም መቼስ፡፡ - በማታውቀው ፖለቲካ ጦስ ከምትሆን ፤ ጦሴን ጥንቡሳሴን ብለህ ስራህን ወጥር፡፡ - ስራ ፍጠር ፤ ተማር ፤ አንብብ ፤ ነቃ በል፡፡ ጃዋር እንጀራ አይገዛልህም፡፡ አብን ግራ እንደገባት አይተሀል መቼስ፡፡ ህውሀትዬ አመዷ ቡን ብሏል፡፡ ብሔርህ እከካም ነው፡፡ ሀገሪቷ ራሱ እከክ ነች፡፡ ችጋራም ሀገር ላይ ወጥሮ መስራት እንጂ ከረቫት እያነቁ በየመድረኩ የተሰለቸ ዲስኩር ማቅረብ ለታዬ ቦጋለ መፅሀፍ ማተሚያ ብቻ ነው የተረፈው፡፡ ፡ አሪፍ አርብ አመሻሽ♥
Hammasini ko'rsatish...
Re እኔ ፣ እኔ የምወደው ሰው ና የማይመቸኝ ባህሪ ------ አራዳ ሲባል ትዝ የሚለኝ ፈገግታዬ ነው፡፡ ዘናጭ ፈገግታ ነው ያለኝ፡፡ (እንደዛ ይመስለኛል) አራዳ ነኝ፡፡ ተንኮል አላሳብብህም፡፡ ከተጋጨኸኝ ግን አልሰማህም...ጥፋትህ እስኪገባህ ድረስ ፍዳህን አበላሀለው፡፡ ሼም ከያዘህ በይቅርታ እፋታለሁ፡፡ ፀዴ ከሆንክ አንጋጭም፡፡ ካነበብክ አለቃዬ ነህ...ፊልም ትወደዳለህ...ሻለቃ ብዬሀለው...ግጥም ከፃፍክ ነግሰሀል,..ይሄ ሁሉ ባይሆንም ቀልድ ከገባህ ጀለስ ነን፡፡ ይመችህ ካካበድክ እፋታሀለው፡፡ ሾካካ ነህ?...ትቀፈኛለህ፡፡ በኔ ፊት ማንንም እንዳታማ,,,ሰንፍ ከሆንክ አለቀልህ...ታዛቢ ከሆንክ ከነትዝብትህ ገደል ግባ...ፈሪ አይመቸኝም...አጉል ደፋር ያስጠላኛል...ጉረኛ ሳቄን ነው ሚያመጣው...አንተ ራስህን ስትሆን ደስ ትለኛለህ፡፡ ያኔ እልልል ያልን ወዳጆች እንሆናለን፡፡ እኔ ደስ የሚለኝ እንዲህ አይነቱ ሰው ነው፡፡ እናንተስ እንዴት ያለ ሰው ይደብራቹሀል? እንዴት ያለ ሰው ይመቻቹሀል? አውሩኝ እስኪ...
Hammasini ko'rsatish...
Muaz: welcome 👍 የታባህ ጠፍተህ መጣህ?😡 ማን ልበል?😂 👍😂😡
Hammasini ko'rsatish...
👍 9
😂 10
😡 10
ሀሳብን የመግለፅ ነፃነት እስከ ዝምታ (እኔ ሙአዝ ነኝ!) ፡ ይሄ ዘመን እውነት የመባል አንድ ነገር የለም ብሎ ያምናል፡፡ እውነትህን አንተ ነው ምትሰራው፡፡ ስለሌሎች ግድ የለም፡፡ ብቻ እኔ ያመንኩት ነው ሀቅ፡፡ የናንተው የበሬ ወለደ ታሪክ ነው የማለት መብትን ያጎናፅፋል፡፡ ምክንያቱስ? ሁላችንም የየግላችን ሚዲያ አለን፡፡ ፡ ታዲያ በዚህ ጊዜ ፤ የትኛው እውነት እንደሆነ በማይታወቅበት ዘመን አንድ ርዕስ ላይ የሙጥኝ ብለን ፤ ጅማታችን እስኪበጠስ የምንከራከርለት ጉዳይ ይኑር አይኑር ፤ ይፈፀም አይፈጸም ፤ ልክ ይሁን ስህተት ማረጋገጥ አንችልም፡፡ ምክንያቱም አንድ እውነት የለም! : መረጃ ማዛባትና የሀሰት ዜናዎች ለዚህ እውነታ ጥሩ ግብአቶች ሲሆኑ ፤ የጥላቻ ንግግርና አግላይ ገለፃዎች ደግሞ እሳቱ ላይ ቤንዚን አርከፍካፊዎች ናቸው፡፡ ለዚህ መፍትሄው ምንድነ ነው የሚለው ላይ እናንተ አዋቂዎች ናችሁና የምትሉትን በሉ፡፡ እኔ ግን ጊዜያዊ መፍትሄ አለኝ፡፡ ፡ የዝምታ መብት! ፡ ይሄ በብዙዎቻችን የተዘነጋ ፤ "በበላዮቻችን" የተነጠቅነው መብት ነው፡፡ ያለመናገር መብት እንዳለን የረሳን ብዙ ሰዎች አለን፡፡ በተለይ የኛ ዝምታ እየተንበለበለ ያለውን እሳት ፤ የሚንቀለቀለውን ጥፋት የማብረድ ሀይል እንዳለው ሲገባን፡ከመብቶቻችን ሁሉ ትሉቁን መብት እንደተነጠቅን ይገባናል፡፡ (ያው አነጣጠቃቸው systematic ነዋ ፤ መቼስ "ዝም አትበል ብሎ የከለከለኝ የለም" የሚል ተሟጋች አይጠፋምና) ፡ ሁላችንም ሀሳብ የመግለፅ ነፃነት አለን፡፡ ይሄ ሰብአዊ መብት ላይ የሰፈረ የመብት አካል ነው፡፡ እንደው መብት ተገኘ ተብሎ ግን ያንንም ይሄንንም ማንቦራጨቅ ምንጩን ማደፍረስ ነው፡፡ ነገ ጠዋት ሁላችንም ውሀ የምናገኝባትን ምንጭ አንቦራጭቀን ካደፈረስናት ተጠምተን በድርቅ ማለቃችን ነው፡፡ ለአንዳንዶች መፍትሄው መጮህ ነው፡፡ ለእኔ ደግሞ መፍትሄው ዝምታ ነው፡፡ እንግዲህ በዚህ ዘመን የትኛው ነው እውነት ብሎ መልስ የሚያገኝ አካል የለም፡፡ ሀሳብን የመግለፅ ነፃነት እስከ ዝምታ!!!
Hammasini ko'rsatish...
ደግሞ መጥተናል😜
Hammasini ko'rsatish...
Kirish va batafsil ma'lumotga kirish

Biz sizga kirlanganingizdan so'ng bu kunodaliklarni ochamiz. Biz va'da qilamiz, bu tez!