ኢትዮ በረዳ
365 ቀናቶች በሳቅ እናሳልፍ * እንኳን ደህና መጡ ኢትዮ በረዳ ለይ ያሎትን ሀሳብ አስተያየት በዚ ማሳወቅ ይችላሉ 👇👇 @Ethiopian_Family_bot ሽንት አስጨራሽ ቀልዶቻችን ፍርፍርብሎ ለመገልፈጥ ከፈለጉ ይቀላቀሉን join፤ - #ኡፍ_አለቀ
Ko'proq ko'rsatish4 415
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar
- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Obunachilar o'sish tezligi
Ma'lumot yuklanmoqda...
በሀገራችን በአብዛኛው የምንኖረው የሌሎች ሰዎችን ሕይወት በማጥናትና በመጠየቅ ነው። ሰዎች የራሳቸው የሆነ ሕይወት አላቸው። እያንዳንዱ ሰው የራሱ የሆነ አኗኗር፣ አካሄድ፣ አመለካከትና ባህርይ አለው። ብዙውን ጊዜ ግን የራሳችንን ሕይወት ከመኖር ይልቅ የሌላው ኑሮ ያሳስበናል። የምናወራው ስለ ሰው ነው፣ የምንጠይቀው ስለ ሰው ነው፣ የሚያሳስበን የሰው ትዳር ነው፣ የሚያሳስበን የሰው ልጅ ነው፣ የሚያሳስበን የሰው ሥራ ነው፣ የሚያሳስበን የሰው አለባበስ ነው፣ የሚያሳስበን የሰው የሆነ ነገር ነው።
#ልዑል
34900
እኔ ይገርመኛል በዚህ አእምሮዋችን መኖር ስለቻልን ከ 100% የምናውቀው እኮ ወይም እውቀታችን ቢለካ -100 ነው ጠዋት እንነሳለን ቁርስ ካለ እንደነገሩ ይሆናል ምሳም እንደዛው እራትም እንደዛው ሁሉም አይደለም ትንሽ መስራት የሚችለው ነው ይሄን የሚበላው እጅግ ሲበዛ ጥቁር ድንጋይ ነን ማንፈለጥ ማይገባን ተመሳሳይ ኑሮ ለ 70 እና ለ 80 አመት የምንኖር ደግሞ ሚገርመኝ ድህነታችን መሀይምነታችን ድንቁርናችን ሳይቀነስ ሳይጎድል ለልጅ ልጆቻችን እናስተላልፋለን አዲስ ነገር ሲመጣ ይሄማ ጠንቋይ ነው ይሄማ ሞርተኛ ነው ይሄማ ይቀጥላል ከሰማህኝ ልንገርህ ለራስህ ንገረው እኔ ምን ያህል አቃለው ለመኖር አሁን ያለኝ አእምሮ በቂ ነው ብለህ አስብ አዲስ ነገር ፈልግ ቆፍር ውጣ ውረድ
አእምሮህን አትገድበው ሁሉንም መርምር
ጠቢብ ሁን ።
#ልዑልሰገድ
49810
🌞🌅አንዳንድ ጠዋቶች አሉ። እኛ ሳንሆን እነሱ የሆነ ዓይነት ትርጉም ሚሰጡን። የጠፋ ራሳችንን ወይም፣ የቆየ ና የዘነጋነው ትዝታችንን ከተደበቀበት ያወጡታል። አመድ ና አፈሩን አራግፈውለት፣ ወደ መቅደስ ህሊናችንን ና ቤቱ ወደ ሆነው መኔፈሳችን ይመልሱታል። ከአልጋ ወርደን መሬቱን የረገጥንበት ሁኔታ፣ ኤርፎን እደሰካን መጀመሪያ የምንሰማው ዘፈን፣ ማለዳ ምትወጣ ፀሀይ ያየንበት መንገድ፣ ምናውቀውን ግን የራቀ ወይም የሸሸን ሚመስል ሰው ስናይ.......ብቻ የሞተ ደጉ ትዝታችንን ዳግም ለመውለድ አጋጣሚውን ይጠቀማል።🌅🌞
፨፨፨፨፨፨መልካም ምሽት፨፨፨፨፨፨
38200
"ሁሉን ነገር መፈለግ፣ ሁሉን መሻት፣ ያለገደብ ለመኖር ማሰብ የዚህ ዓለም ጣጣ፣ የድካም ምንጭ ነው። የምትጠቀምበትን ያክል ብቻ እወቅ፤ የሚያጠግብህን ያክል ብቻ ብላ፤ የሚያረካህን ያክል ብቻ ጠጣ፤ ሁሉን ነገር ማጣት ሰቀቀን ቢሆንም ሁሉን ነገር ማግኘትም ዕዳ ይሆናል፡፡ ምንም አለማወቅ ባዶነት ቢሆንም ሁሉን ማወቅ ደግሞ ሸክምም ይሆናል።"
39920
የተረጋጋ ህይወት እንዲኖርህ መፅሀፍትን አንብብ ብዙ አታውራ ማውራት ሲኖርብህ ግን ዝም አትበል ምክርና አስተያየት ለመቀበል አትፍራ ለተደረገልህ ጥሩ ነገር አመስግን ፤ በቂ እንቅልፍ ተኛ የማታውቀውን ጠይቅ ፤ በየወሩ ካለህ ገቢ ላይ ትኝሽም ቢሆን ቆጥብ ዛሬ መስራት የምትችለውን ዛሬውኑ ስራ።
የሠው ልጅ ሲቸግረው ልብሱን የቤቱን ዕቃ፤ ኩላሊቱንም ሳይቀር ሊሽጥ ይችላል ህሊናውን ከሸጠ ግን በጠና ቸግርታል ማለት ነው።
41520
በዚህ ዓለም ላይ ሞትን ያክል ሰባኪ ያለ አይመስለኝም። አያዳላም። አይራራም። ቀጠሮ ያከብራል - አይዘገይም።
ችግሩ ወደ ጉባኤ ገብተን ከሰባኬ ወንጌሉ የሚወጣውን ቃለ እግዚአብሔር እንደማንሰማው ሁሉ የሞተን ለመቅበር ታድመንም የሞትን ስብከት አናዳምጥም። ለሞተ እናለቅሳለን እኛን ግን እንረሳለን።
አቤቱ አንተው አውጣን አውጣን!
#ልዑል ሰገድ
53210
የአማራ መታረድ ይብቃ ብሎ የሚታገልን ጀግና ሽማግሌ ታቦት አሲዞ አስለምኖ በእርቅ አሳቦ ማሰር ውርደት ነው።
59210