cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

YeneTube

መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa

Ko'proq ko'rsatish
Advertising posts
131 800Obunachilar
+13324 soatlar
+8147 kunlar
+1 97230 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Обуначиларнинг ўсиш даражаси

Ma'lumot yuklanmoqda...

ኦሮሚያ ኢንሹራንስ ለ 122 ሺህ አርሶአደሮች 39 ሚሊዮን ብር የሰብል መድህን ካሳ ሊከፍል መሆኑ ተገለፀ! በግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ፣ በአለም ምግብ ፕሮግራም እና በፑላ አድቫይዘር ጥምረት ተጀምሯል የተባለውና በሀገሪቱ ትልቁ ነዉ የተባለው የሰብል መድህን ፕሮግራም የክፍ ስርአት መተግበር መጀመሩ ተነግሯል። በኢትዮጵያ የሰብል መድህን ታሪክ ዉስጥ ትልቁ መሆኑ በተነገረለት ፕሮግራም የኦሮሚያ ኢንሹራንስ ኩባንያ የመድህን ሰጪ እና የካሳ ከፋይ ተቋም በመሆን ለትግበራዉ 39 ሚሊዮን ብር መመደብ ካፒታል ሰምቷል። የመጀመሪያው ምዕራፍ እንደሆነ በተገለጸው ቢዚህ ስርዓት በአማራ ክልል የሚገኙ አነስተኛ አርሶአደሮች ተጠቃሚ መሆናቸው የተነገረ ሲሆን በቀጣይ በተለያዩ ክልሎች ለሚገኙ ለ 7.5 ሚሊዮን አርሶአደሮች ተደራሽ ይደረጋል ተብሏል። [Capital] @YeneTube @FikerAssefa
Hammasini ko'rsatish...
👍 23😁 3
አቶ ታዬ ደንደአ “የፀረሰላም ኃይሎችን በመደገፍ እና የጦር መሳሪያ ይዞ በመገኘት' ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸው! በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከኃላፊነታቸው መነሳታቸውን ተከትሎ በጸጥታ ሀይሎች ታህሳስ 2 ቀን በቁጥጥር ስር የዋሉት የቀድሞ የሰላም ሚኒስትር ዴዔታ አቶ ታዬ ደንደኣ “የፀረሰላም ኃይሎችን በመደገፍና ጦር መሳሪያ ይዞ በመገኘት” ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸው። በክሱ ላይ ፤ “ተከሳሹ የሰላም ሚኒስትር ዴዔታ ሆነው ሲሰሩ የሀገርን፣ የመንግስትንና የህዝብን ደህንነት ማረጋገጥ ሲገባቸው ይህን ወደጎን በመተው ፀረሰላም ኃይሎችን የሚደግፉ የፕሮፖጋንዳ መልዕክቶችን በማስተላለፍ በስማቸው በተከፈተ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ላይ ድጋፍ የሚገልጹ መልዕክቶችን ሲያስተላልፉ ነበር” የሚል ተካቷል፡፡ አቶ ታዬ ደንደኣ በቁጥጥር ስር ሲውሉ በራሳቸው እና በቤተሰባቸው ላይ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደደረሰባቸው ገልጸው አቤቱታ በቃል አቅርበዋል። ምርመራው ታሕሳስ 24 ማለቁንና ዘግይቶ ክስ መቅረቡንም ተቃውመዋል።ፍርድ ቤቱ ዋስትናውን በሚመለከት መርምሮ ብይን ለመስጠትም ለሚያዝያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። @YeneTube @FikerAssefa
Hammasini ko'rsatish...
😁 23👍 11👎 5 1👏 1👀 1
ተዋናይ አማኑኤል ሃብታሙ ዛሬ ጠዋት ከቤተሰብ እና ጠበቃው ጋር መገናኘቱ ተዘገበ ተዋናይ አማኑኤል ሃብታሙ "እብደት በሕብረት" የተሰኘ የአንድ ሰው ቴአትሩን ለማሳየት ወደ እስራኤል አገር ሊጓዝ ሲል ከአዲስ አበባ ኤርፖርት በፖሊሶች መያዙ ይታወሳል።በአዲስ አበባ ፖሊስ መምሪያ ውስጥ ታስሮ የሚገኘው ተዋናዩ የቅርብ ወዳጅ የሆነው ያሬድ ሹመቴ እንደገለጸው አማኑኤል ሃብታሙ "እጁ ከተያዘበት ሰዓት አንስቶ የተከሳሽነት ቃል ሳይሰጥ እንዲሁ በእስር ላይ" እንደሚገኝ ቤተሰቦቹን ዋቢ አድርጎ ጽፏል። ይኹን እንጂ የቤተሰብ ጠበቃ የማግኘት መብቱ ተጠብቆለት ከቤተሰብ እና ከጠበቃ ጋር ዛሬ ጠዋት ሊገናኝ መቻሉን እና "በመልካም" ሁኔታ ላይ መኾኑ ተመልካቷል። በሕጉ መሰረት ወደ ቀጣይ ሕጋዊ ሂደቶች ለማምራት እስከ ነገ የሚሆነውን ለማየትም ቤተሰቦቹ እየተጠባበቁ ነው ተብሏል።  እያዩ ፈንገስ የአንድ ሰው ቴያትር 'ቧለቲካ' የተሰኘው ምዕራፉ ለዕይታ ከቀረበ ከእጭር ጊዜ በኋላ ማለትም ከጥር 2 ቀን 2016 ጀምሮ የመንግስት የፀጥታ አካላት ለዓለም ሲኒማ የስራ ሀላፊዎች ባስተላለፉት ትእዛዝ  ለህዝብ እንዳይታይ መከልከሉ አይዘነጋም። Via Addis Maleda #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
የሰሊጥ ግብይት በሱዳንና በኢትዮጵያ የግጭት መነሻ እንደሆነ አንድ ጥናት አመለከተ! የሰሊጥ ምርት እና ግብይት፣ በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል፣ እንዲሁም በሁለቱም አገሮች የውስጥ አወዛጋቢ ጉዳዮች ዙሪያ የግጭት መንሥኤ እየሆነ እንደሚገኝ፣ አንድ ጥናታዊ ጽሑፍ አመለከተ፡፡ “The ‘conflict economy’ of sesame in Ethiopia and the Sudan” በሚል ርእስ የወጣውን ጥናት ከአዘጋጁት ሁለት ምሁራን አንዱ ዶ/ር አቤል አባተ ደምሴ፣ “የሰሊጥ ግብይት በሱዳንና በኢትዮጵያ የውስጥ እና የውጭ ጉዳዮች ላይ ተጽእኖ ፈጥሯል፤” ይላሉ፡፡ ዶ/ር አቤል፣ ላለፉት አራት ዓመታት፣ በለንደን በሚገኘው ዓለም አቀፍ የፖሊሲ ተቋም(ቻተም ሃውስ) የሮያል ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ተቋም የምርምር ባልደረባ ሆነው በመሥራት ላይ ናቸው፡፡ ምሁሩ በጥናታቸው ላይ እንዳመለከቱት፥ የመንግሥት ኀይሎች፣ የአካባቢ ልሂቃንና ሚሊሻዎች በሰሊጥ ምርት እና ንግድ ላይ ቁጥጥር ለማድረግ እየተፎካከሩ ናቸው፡፡ ፖሊሲ አውጪዎች፣ በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ያለውን ትስስር ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና የግብርና ለውጦችን በማስተካከል ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት፣ መሠረታዊ እና ተለዋዋጭ ፖሊሲዎችን መቅረጽ እንዳለባቸው መክረዋል፡፡ ፖሊሲ አውጭዎቹ መደበኛ ያልሆነ የንግድ ልውውጥን እንዲደግፉና ከታች ወደ ላይ ለአካባቢያዊ አብሮ መኖርና ትብብር ኹኔታዎችን እንዲያመቻቹ ጥናቱ ምክረ ሐሳብ ማቅረቡን ከአዘጋጆቹ አንዱ ዶ/ር አቤል አባተ ተናግረዋል፡፡ https://www.chathamhouse.org/2024/04/conflict-economy-sesame-ethiopia-and-sudan [VoA] @YeneTube @FikerAssefa
Hammasini ko'rsatish...
👍 11😁 3 1
ተዋናይ አማኑኤል ሃብታሙ ዛሬ ጠዋት ከቤተሰብ እና ጠበቃው ጋር መገናኘቱ ተገለጸ! ተዋናይ አማኑኤል ሃብታሙ "እብደት በሕብረት" የተሰኘ የአንድ ሰው ቴአትሩን ለማሳየት ወደ እስራኤል አገር ሊጓዝ ሲል ከአዲስ አበባ ኤርፖርት በፖሊሶች መያዙ ይታወሳል።በአዲስ አበባ ፖሊስ መምሪያ ውስጥ ታስሮ የሚገኘው ተዋናዩ የቅርብ ወዳጅ የሆነው ያሬድ ሹመቴ እንደገለጸው አማኑኤል ሃብታሙ "እጁ ከተያዘበት ሰዓት አንስቶ የተከሳሽነት ቃል ሳይሰጥ እንዲሁ በእስር ላይ" እንደሚገኝ ቤተሰቦቹን ዋቢ አድርጎ ጽፏል። ይኹን እንጂ የቤተሰብ ጠበቃ የማግኘት መብቱ ተጠብቆለት ከቤተሰብ እና ከጠበቃ ጋር ዛሬ ጠዋት ሊገናኝ መቻሉን እና "በመልካም" ሁኔታ ላይ መኾኑ ተመልካቷል። በሕጉ መሰረት ወደ ቀጣይ ሕጋዊ ሂደቶች ለማምራት እስከ ነገ የሚሆነውን ለማየትም ቤተሰቦቹ እየተጠባበቁ ነው ተብሏል። እያዩ ፈንገስ የአንድ ሰው ቴያትር 'ቧለቲካ' የተሰኘው ምዕራፉ ለዕይታ ከቀረበ ከእጭር ጊዜ በኋላ ማለትም ከጥር 2 ቀን 2016 ጀምሮ የመንግስት የፀጥታ አካላት ለዓለም ሲኒማ የስራ ሀላፊዎች ባስተላለፉት ትእዛዝ ለህዝብ እንዳይታይ መከልከሉ አይዘነጋም። [Addis Maleda] @YeneTube @FikerAssefa
Hammasini ko'rsatish...
👍 22😭 6 1
በ59 ሃገራት የሚገኙ ከ282 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለከፋ ረሃብ መጋለጣቸውን የመንግስታት ድርጅት ሪፖርት አመለከተ። የዓለማቀፉ ድርጅት ሪፖርት እንዳለው በአስከፊ ጦርነት ውስጥ የምትገኘው የጋዛ ሰርጥ በርካታ ቁጥር ያለው ተጋላጮችን በመያዝ ትመራለች። ከጎርጎርሳውያኑ 2022 ወዲህ 24 ሚሊዮን ተጨማሪ ሰዎች ለከፋ የምግብ እጥረት እና ለረሃብ መጋለጣቸውን ያመለከተው መረጃው ከጋዛ ጦርነት በተጨማሪ የሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት ሚሊዮኖች እርዳታ ጠባቂ አልያም በረሃብ አፋፍ ላይ ያሉ ናቸው ብሏል። በየዓለም የምግብ እርሻ ፕሮግራም ሪፖርት እንደሚያሳየው በአምስት ሃገራት ውስጥ የሚገኙ እና ቁጥራቸው ከ705 ሺ በላይ የሆኑ ሰዎች ደረጃ አምስት ወይም ለከፋ ረሃብ የተጋለጡ ናቸው። ከእነዚህ ውስጥ 80 በመቶውን ቁጥር የሚሸፍነው በጋዛው ጦርነት አስከፊውን ጊዜ በማሳለፍ ላይ የሚገኙት ፍልስጥኤማውያን ናቸው።ደቡብ ሱዳን ፣ ቡርኪና ፋሶ፣ ሶማሊያ እና ማሊ እያንዳንዳቸው በሺዎች የሚቆጠሩ ለረሃብ የተጋለጡ ዜጎች እና ስደተኞች በመያዝ ይከተላሉ።በሀገራቱ እና በአካባቢያቸው እየተደረጉ ያሉ ግጭቶች እና ጦርነቶች እስካልቆሙ ድረስ ችግሩ እየከፋ ሊሄድ እንደሚችል ዓለማቀፉ ድርጅት አሳስቧል። ከዚህ በተጨማሪ በያዝነው የጎርጎርሳውያኑ 2024 መጀመሪያ ላይ ኤል ኒኖ ያስከተለው የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ደረጃ የደረሰበት ወቅት እንደነበር ያስታወሰው ድርጅቱ የጎርፍ መጥለቅለቅን ጨምሮ በአንዳንድ የምስራቅ እና ደቡባዊ አፍሪካ ሀገራት የዝናብ እጥረትን በማስከተል ችግሩን ከድጡ ወደ ማጡ እንዳያደርገው ያሰጋኛል ብሏል።መንግስታት እና ለጋሾች በረሃብ ምክንያት «የጅምላ የሰውን ልጅ ውድቀት ለመታደግ» ርብርብ እንዲደረግ ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬሽ ጥሪ አቅርበዋል። [DW] @YeneTube @FikerAssefa
Hammasini ko'rsatish...
👍 20😭 7 3
ለድርጅትዎ የGOOGLE ማስታወቂያ ማሰራት ይፈልጋሉ? ማስታወቂያዎት ደንበኛ ሊሆንዎት ከፍተኛ እድል ወዳላቸው ሰዎች(Potential Customers) እንዲደርስስ? -ጉግል ሰርች ላይ ለሚመጡ ማስታወቂያዎች፤ -በዩቲውብና ጂሜይል ለሚታዩ ማስታወቂያዎች፤ -በተለያዩ አፕሊኬሽኖች ላይ የሚታዩ ማስታወቂያዎችን በማሰራት ምርትና አገልግሎትዎን ለማሳደግ ከፈለጉ ያናግሩን። ከዚህም በተጨማሪ ፌስቡክ፣ ኢንስታግራም እና ኤክስን በመሳሰሉ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ማስታወቂያ ማሰራትም ይችላሉ። ቴሌግራም፡ @adsommar ስልክ፡ 0954260423
Hammasini ko'rsatish...
👍 10👎 1
ኢትዮ ቴሌኮም የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን አስጀመረ! ኢትዮ ቴሌኮም በሀገር አቀፍ ደረጃ የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን በዛሬው ዕለት አስጀመረ፡፡በማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በወር በአማካይ 1 ሚሊየን ዜጎችን በመመዝገብ እስከ 2018 ዓ.ም ለ90 ሚሊየን ዜጎች አገልግሎቱን ለመስጠት መታቀዱ ተመላክቷል፡፡ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ፤ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ አስቻይ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ተዓማኒነት ያለው የማንነት መለያ ዲጂታል መታወቂያ ነው ብለዋል።ዲጂታል መታወቂያ አካታች ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባትና ዜጎች በኢኮኖሚው ዕኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዕድል ይፈጥራል ነው ያሉት፡፡ የብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ ምዝገባው አዲስ አበባን ጨምሮ በ29 ከተሞች ዛሬ በይፋ የተጀመረ ሲሆን፥ ዜጎች ባሉበት ቦታ ሆነው በቴሌብር ሱፐርአፕ መመዝገብ ይችላሉ መባሉን ፋና ዘግቧል፡፡ @YeneTube @FikerAssefa
Hammasini ko'rsatish...
👍 53👎 11 7
“በኢትዮጵያና ኤርትራ የሰብአዊ መብት አያያዙ እንደከፋ ነው” - ዩኤስ የዩናዩትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሀገራትን የሰብአዊ መብቶች አያያዝ በተመለከተ የሚያወጣውን ዓመታዊ ሪፖርት በትላንትናው ዕለት ይፋ አድርጓል።ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ትላንት ሚያዚያ 14/2016 ዓ.ም ባወጣው የሃገራትን የሰብአዊ መብቶች አያያዝ በሚተነትነው ሰፊ የአውሮፓያኑ የ2023 ዓመታዊ ሪፖርቱ፤ ፣የኢትዮጵያ መንግሥት ወይም የመንግሥት ወኪሎች፣ ከሕግ ውጪ የዘፈቀደ ግድያ መፈፀማቸውን፣ በርካታ የሃገር ውስጥና የውጪ ሃገራት የሰብአዊ መብት ቡድኖች ሪፖርት ጠቅሶ ይፋ አድርጓል።ግድያዎቹ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል እየተካሄዱ ባሉ ግጭቶች እንዲሁም ትግራይን ጨምሮ በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች የተፈጸሙ እንደሆነ አስታውቋል። የክልል ፖሊስ አባላትም ፣ ከመጠን ያለፈ እና ሕይወት የቀጠፈ ኃይል መጠቀማቸውን የጠቀሰው ሪፖርቱ፣ ለማሳያም፣ “በየካቲት ወር በወልቂጤ ከተማ የውሃ አገልግሎት እንዲመለስ በሰልፍ ለመጠየቅ በወጡ ነዋሪዎች ላይ በተወሰደው ርምጃ ሦስት ሰዎች ሲሞቱ 30 የሚሆኑት ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል” ብሏል። በሌሎችም አካባባዎች የተፈጸሙ ግድያዎችን ያካተተው ሪፖርት፣ የፌዴራሉ ፖሊስ ምርመራ ቢሮ በፖሊስ ኃይሎች የሚፈጸሙ ግድያዎችን በተመለከተ የሚያደርጋቸው ምርመራዎች ውስን መሆናቸውን እና የሚሰጠውን ቅጣት በተመለከተም በሚስጥር እንደሚይዝ ጠቁሟል።በግዳጅ መሰወርን አስመልክቶም፣ መንግሥትን የሚነቅፉ የፖለቲካ አስተያየት የሚሰጡ ግለሰቦች፣ የቀድሞ ጦር አባላት፣ የምርመራ ጋዜጠኞች፣ የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎች መሰወራቸውን አትቷል። ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ: https://amharic.voanews.com/a/7582081.html @YeneTube @FikerAssefa
Hammasini ko'rsatish...
👍 23😁 7 2
"የሚሊሻ አባላትን ትጥቅ ማስፈታት" አስመልክቶ በማህበራዊ ትስስር ገፆች እየተላለፈ ያለው መልዕክት ሀሰተኛ ነው" :- የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ጽ/ቤት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ጽ/ቤት አወጣ ተብሎ በተለያዩ ማህበራዊ ትስስር ገፆች ሲተላለፍ የነበረው "የሚሊሻ አባላትን ትጥቅ ማስፈታት" የተመለከተ ደብዳቤ በሐሰት የተቀናበረ መሆኑን የአማራ ክልል አስታውቋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳንኤል ደሳለኝ ከኢቢሲ ሳይበር ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ተጻፈ የተባለው ደብዳቤ ከመስሪያ ቤታቸው የወጣ አለመሆኑን እና የተቀነባበረ መሆኑን ገልጸዋል። ክልሉ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ የሚሊሻ ኃይሉን የማጠናከር ስራን እየሰራ ይገኛል ያሉት ሃላፊው፤ የርዕሰ መስተዳድሩን ጽ/ቤት የደብዳቤው ይዘትም ሆነ ቅርጽ ሀሰተኛ መሆኑን ጠቁመዋል። Via BBC @YeneTube @FikerAssefa
Hammasini ko'rsatish...
👍 27😁 14👎 3 3👏 1