ዜማና ቅኔ 4 𝔾𝕠𝕤𝕡𝕖𝕝
5c560cdb5 የቻናሉ ራዕይ 👇👇 "በዜማና በቅኔ ወንጌልን ላልሰሙ ማሰማት ነው።" በውስጡም ሳምንታዊ የመፅሐፍ ቅዱስ ተከታታይ ትምህርታዊ ጥናት በድምፅና በፅሁፍ ይቀርባል፣የቆዩና አዳዲስ ዝማሬዎች ፣ እንዲሁም መንፈሳዊ ይዘት ያላቸው መልዕክቶች ይቀርባሉ ይቀላቀሉት ይወዱታል። ለአስተያየ️ት 👉 Henok Hatiya 👉 @hevensong
Більше15 339
Підписники
Немає даних24 години
+267 днів
+14030 днів
Архів дописів
4. Yoseph Ayalew ስጋት እንዳይገባኝ Sigat Aygebagnim
🕠 05:38 💾 5.7 MB
Join us 👇👇👇
👉👉 @zemaenaqine 👈👈
👉👉 @zemaenaqine 👈👈
share to your friends
👨👩👦👦👨👩👧
❤ 10👍 4
4. Yoseph Ayalew ስጋት እንዳይገባኝ Sigat Aygebagnim
🕠 05:38 💾 5.7 MB
Join us 👇👇👇
👉👉 @zemaenaqine 👈👈
👉👉 @zemaenaqine 👈👈
share to your friends
👨👩👦👦👨👩👧
Singer Mentesnot Manaye ማለዳ ስነሳ
🕠 10:1217 💾 18.1 MB
Join us 👇👇👇
👉👉 @zemaenaqine 👈👈
👉👉 @zemaenaqine 👈👈
share to your friends
👨👩👦👦👨👩👧
"ባለ ዘጠኝ ዜማ መዝሙር"
--የዜማ ያለህ--!
መዝሙር/መዘመር በአጭሩ ሲተረጎም መልዕክተ ቃላትን በዜማ ማቀንቀን ማለት ነው።
አንድ መዝሙር ከመልዕክቱ አንጻር አንድ ማዕከላዊ ጉዳይ የሚያትት ሲሆን በተለያየ አገላለጽ እና ቃላት ብዙ ጊዜ አዝማቹን ያብራራል። የመዝሙሩ ዋና መልዕክት አዝማቹ ላይ ይጫናል፣ ከዚያ እሱ በቁጥሮች እና በማዳመቂያዎች ይብራራል ማለት ነው።
ዜማውም እንደዚሁ ነው። Theme and variation ይባላል። የዜማው ውቅር የራሱን አንድ ዘውግ ይይዝና እዚያ ውስጥ ዋና ሀሳብ (Melodic theme) ይይዛል፣ ከዚያ በቫሪዬሽን ይራባል።
ስለዚህ መልዕክቱም በቃላት ይራባል ዜማውም በድምጾች አደረጃጀት እና ልዩ ልዩነት (Variations) ይራባል።
ይህ ዜማዊው እርባታ ባለንበት ዘመን በጣም ፈር የለቀቀ እና አሰልቺ እየሆነ ነው። ለምን? መሠረታዊ የዜማ ህግጋትን መከተል አሻፈረኝ የሚሉ ባለማወቅ እንዲሁ ሰውን የሚከተሉ ዘማሪያን እየበዙ በመምጣታቸው ይመስለኛል።
ለምሳሌ: የዜማ ቅርጾች *ABA* country form የሚባሉ አሉ (ቁጥሮች በአንድ ዜማ፣ አዝማች በሌላ ዜማ) ሁለት ዜማ ብቻ ያዘሉ ናቸው።
*ABCA* የሚባሉ ደግሞ አዝማች፣ ቁጥር እና ሌላ ማድመቂያ አዝማች።
*ABCDA* ሌላው ሁሉ አለ ማድመቂዎቹ ሁለት ሲሆኑ ነው።
A ሁል ጊዜ አዝማች ነው።
ከዚህ በላይ ዜማ በአንድ መዝሙር ላይ ማጨቅ ሙዚቃዊ ወንጀል ነው። ለሙዚቃ አቀናባሪ ራሱ ፈተና ነው። ስንት ኮርድ ስንት ላይን አሬንጅ ያድርግ? ወይ ዋጋውን መጨመር ነው...ውይ ትዝ አለኝ 1999 የሆነ ባለ 8 ዜማ መዝሙር ቅኔ ስቱዲዮ ውስጥ ስሠራ የተቸገርኩት።
ዜማ መብዛት ብቻ ሳይሆን አሁን ፋሽን የሆነው መዝሙሩ ሊያልቅ ሲል መጨረሻ ላይ ያልተሰማ አዲስ ዜማ ይጀመርና ፌድ እያደረገ ያልቃል።
ይህ ማለት አንድ መጽሐፍ ደራሲ መግቢያ ሀተታ እና መደምደሚያ አድርጎ ስለ አንድ ጉዳይ ጽፎ መጨረስ ሲገባው መደምደሚያ (ማጠቃለያ) ላይ ፈጽሞ በመጽሐፉ ውስጥ ያላነሳውን ሀሳብ መጀመርና በዚያ ማቆም እንደ ማለት ነው።
ለምሳሌ: ስለ ጋብቻ ጽፎ ሙሉውን መጽሐፍ መደምደሚያ ላይ ስለ ቡሩንዲ ፕሬዚዳንት የህወት ታሪክ ቢጀምር አያስቅም?
የመጽሐፍ ድርሰት እና የመዝሙር ድርሰት መርሁ ያው አንድ ነው። ዜማም ልክ እንደ መጽሐፍ መግቢያ፣ ሀተታ፣ መደምደሚያ አለው።
ለጠቅላላ እውቀት ዜማ ስትሰሩ 3 ነገሮችን ተረዱ።
1. Chorus /አዝማች/አንድ አይነት ግጥም አንድ አይነት ዜማ---አዝማች ከዘመናችን መዝሙር እየጠፋ መሆኑን ልብ ይሏል። ይህ ፈጽሞ ትክክል አይደለም!
2.Verse /ቁጥር/ አንድ አይነት ዜማ የተለያየ ግጥም።
3.Bridge /ማዳመቂያ /ልበለው፥ ሁለት አይነት ቢበዛ።
በዚህ መርህ ውስጥ ሆናችሁ በነጻነት ዜማዎችን መሥራት እንጂ ከእውቀት ነጻ የሆነ አካሄድ አያስፈልግም። Freedom in the principle. ህግ መጣስ ከተፈለገም ህጉን ካወቁ በኋላ!!!
የድሮ መዝሙሮች (ከ25 አመት በፊት) በጣም ተወዳጅ የመሆናቸው ምሥጢር ጠንካራ አዝማች ስላላቸው ቅቡል እና ቀላል በመሆናቸው ይመስለኛል። ጉባኤ ላይ ሲዘመሩ ህዝቡ ቢያንስ ተደጋግሞ የሚመጣውን አዝማች እየጠበቀ በጉጉት አብሮ ይዘምራል።
ዘንድሮ በዘጠኝ ዜማ ስታጣድፈው ትዕይንትህን ቁጭ ብሎ ያያል። አንተም ምን አይነት ደንዛዛ ህዝብ ነው? የሜልኮል መንፈስ ነው እያልክ እነሆ ትጨናነቃለህ።
የውጭ ሀገራት መዝሙሮችን ስናይ ውበታቸው ቅለታቸው ነው። Chorus, verse, bridge በቃ። ከዚያ መደጋገም አለቀ።
የእኛ ነገር ሁሉ ውስብስብ ይሆናል ባህላችን መሠለኝ፥
ለማንኛውም እናስብ እንወቅ እንበርታ ለማለት ነው።
መልካም ቀን
ረታ ጳውሎስ 2015
ምሳሌ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ልጄ ሆይ፥ ሕጌን አትርሳ፥ ልብህም ትእዛዛቴን ይጠብቅ።
² ብዙ ዘመናትና ረጅም ዕድሜ ሰላምም ይጨምሩልሃልና።
³ ምሕረትና እውነት ከአንተ አይራቁ፤ በአንገትህ እሰራቸው፤ በልብህ ጽላት ጻፋቸው።
⁴ በእግዚአብሔርና በሰው ፊትም ሞገስንና መልካም ዝናን ታገኛለህ።
⁵ በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤
⁶ በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል።
#ይወደኛል
የእግዚአብሔር በግ ይወደኛል (3X)
በእኔ ቦታ ታርዶልኛል ይወደኛል (2X)
ከፍ ከፍ ከፍ ያለ ነው (3X)
ከፍ ከፍ ልሸከመው ከፍ ከፍ የማልችለው
ከፍ ከፍ ከፍ ያለ ነው
ፍቅርህ በላዬ (2X)
ኢየሱስ ጌታዬ
ከፍ...
ፍቅር...
የእግዚአብሔር በግ...
እንዴት ወደደኝ ከእሱ የራኩትን
በክፉ በደል ተዘፈኩትን
ምኔ ደስ አለው የሚወደኝ ጌታ
እሱ ሞተልኝ የመሞቴ ለታ
ከራሱ ይልቅ እኔን ያፈቅረኛል
ይወደኛል
አይሏል ጨምሯል በላዬ (3X)
መልካም ሰርቼ የማላሻሽለው
ጥሩ ሰርቼ ከፍ የማላደርገው
መልካም ሰርቼ የማላሻሽለው
ጥሩ ሰርቼ ከፍ የማላደርገው
የኢየሱስ ፍቅር ከፍ ከፍ ያለነዉ
ከኔ በጎነት ያልተጀመረ ነዉ
የጌታ ፍቅር ከፍ ከፍ ያለነዉ
ከኔ በጎነት ያልተጀመረ ነዉ
ይወደኛል (4X)
ከፍ...
ፍቅርህ...
ከፍ...
ፍቅርህ...
Join us 👇👇👇
👉👉 @Zemaenaqine 👈👈
👉👉 @Zemaenaqine 👈👈
share to your friends
👨👩👧👦👨👩👧👨👩👦👦
#ለመልካም_ሆነልኝ
ለካ ይታለፋል ማይታለፈው
ከልኩ አያልፍም የሰው ፈተናው
ምጠፋ መስሎኝ ፈራች እንጂ ነፍሴ
ለካ ያስጨነከኝ ለጥቅሜ ለራሴ
በእሳት እያለፍኩ ስፈተን
ወርቅ አደረገው ህይወቴን
ጌታ ሆይ አሁን ተማርኩ ተስተካከልኩ
አመፃን ጥዬ ፅድቅንም ያዝኩ
ያ ልፍስፍሱ ጠነከረ እንጂ ልቤ
አላጠፋኝም የጋለው ከአጠገቤ
ተስማምቶ የኖረ ከአፈር እና ከጭቃ
እሳት ሲያገኘው ሆነ የክብር ዕቃ
ጠንክሬ በርትቼ እንድመላለስ
ልቤን አጀገነው ቅዱሱ መንፈስ
ቀዝቃዛ ሂወቴ በፈተናው ሞቀ
እሳቱ ሲነካው ነጠረ ደመቀ
ዘመኔ እንዲደምቅ እንዲያበራ
መቼ መሰለኝ የምሰራ
ልክ እንደ ድንጋይ ተራ የነበረ
እሳት ሲያገኘው ሆነ የከበረ
ለመልካም ሆነልኝ ሆነልኝ (2X)
ለበጎ ሆነልኝ ሆነልኝ (2X)
ለመልካም ሆነልኝ ሆነልኝ
ለመልካም ሆነልኝ ያስጨነከኝ
ለበጎ ሆነልኝ ሆነልኝ
ለበጎ ሆነልኝ ያስጨነከኝ
በመከራ ውስጥ መታዘዝን ተማረ
በስጋው ወራት አንተን አከበረ
እኛ ዳንን እንጂ በእርሱ መከራ
ህይወታችን ጣፍጧል በጠጣው መራራ
እሱ ኃያል ሳለ ምስኪን መሰለ
ከአመፀኞች ጋር ተሰቀለ
በጌታ መከራ ስንቶች ዳኑ
አቀረባቸው ወደ ዙፋኑ
ጌታ ሆይ...
Join us 👇👇👇
👉👉 @Zemaenaqine 👈👈
👉👉 @Zemaenaqine 👈👈
share to your friends
👨👩👧👦👨👩👧👨👩👦👦
አባ ወድሀለዉ
አባ ወድሃለው (8X)
የፀሎቶቼን ርዕሶቼን ይዤ ጥያቄ
በርከክ ስል ለምን እንደመጣሁ እርስት አድርጌ
የምለው ጠፋኝ ታዲያ ምን ልበል
ከናፍርቶቼ አወጡ ይሄን ቃል
አባ ወድሃለው (8X)
መገኘትህ ህልውናህ መልስ ይሆነኛል
የያዝኳቸው ቃላቶቼ ይሰወሩብኛል
ግን አንደበቴ ሚደጋግመው ማይዘነጋው
እንዲህ ነው ሚለው አባ ወድሃለው
ኦሆ ወድሃለው ወድሃለው አባ ወድሃለው (2X)
አባ ወድሃለው (6X)
አባ ወድሃለው (8X)
የቅርቤ
ከሲዖል መውጣቴ ይበቃኝ ነበረ
በዚያ አላበቃም ፍቅሩ ጨመረ
ቀረበኝ አልሆንኩም ብቸኛ
አምላኬ ልክ እንደ ጓደኛ
ሳይዘው ሳይገድበው ትልቅነቱ
አብሮኝ ነው ኢየሱስ ትሁቱ
የቅርቤ ልበልህ የቅርቤ (2X)
ከእስትንፋሴ ይልቅ የቅርቤ
የቅርቤ ልበልህ የቅርቤ
ከእስትንፋሴ ይልቅ ይልቅ የቅርቤ ነህ
ፊትህን ተርቤ መቼ መቼ አጣሁህ
የሆድ የውስጤን ታውቀው የለም ወይ ሳልተነፍስ
ውዴ ኢየሱስ
ሰው ሚያውቀው ጉብዝናዬን
መቼ አየ ገመናዬን
ሸፍነኸው ጉድለቴን
ሚታየው ግን ሙላቴ
የቅርቤ...
ዞር ብዬ ወደ ኋላ መንገዴን ሳይ
የአንተ እንጂ የእኔ ኮቴ አይታይ
አባጣ ጎርባጣውን እኔ መውጣቴ
ይዘኸኝ ልክ እንደ እናቴ
ምንም ባሳዝንህ በድካሜ
ታግሰኽ አቆምከኝ መድህኔ
ሰው ሚያውቀው...
በሰዎች መሐል ወይም ለብቻዬ
ድምፁን ያሰማኛል አብሮኝ ነው ጌታዬ
በዚህ ሂድ በዚያ ሂድ እያለኝ
ጠላት የማሰውን አለፍኩኝ
አምላኬ የመከረኝን
ሰምቼው አለፍኩኝ ስንቱን
የቅርቤ...
ሰው ሚያውቀው...
የቅርቤ...
7. Bereket Tesfaye ክብር አለ Kiber Ale በረከት ተስፋዬ
ሃሌሉያ እያሉ መላዕክት በሙሉ
ኢየሱስ ለሚል ስም ይንበረከካሉ
አይነፃፀርም ከተዋረዱቱ
ስሙ ከፍ ያለ ነው በሰማይ ካሉቱ
ለቆ ከፍ ያለ የተከበረ
በሰማያት ላይ አንድ ስም አለ
ስሙን ሊያከብር ጰራቅሊጦስ
ከሰማይ መጥቷል መንፈስ ቅዱስ
በስሙ ላይ ክብር አለ (3X)
ማዳን አለ ክብር አለ
ፍቅር አለ ክብር አለ
እዚህ ስም ላይ ክብር አለ
ዘይት አለ ክብር አለ
ማዳን አለ ክብር አለ
ቅባት አለ ክብር
የትኛው ተራራ ነው
ስሙ ሲጠራ የሚቆመው
የትኛው ሸለቆ ነው
ይሄ ስም የማይሞላው
የትኛው በሽታ ነው
በዚህ ስም ፊት የሚቆመው
የትኛው ሰይጣን ነው
ስሙ ሲጠራ የሚቆመው
በስሙ ላይ ክብር አለ (3X)
ቅባት አለ ክብር አለ
ማዳን አለ ክብር አለ
ኢየሱስ ስም ላይ ክብር አለ (7X)
ቅዱስ ስሙን አመልካለሁ ለሌለው እኩያ
አሁንም ክብር ይሁን ለኢየሱስ ስም ሃሌሉያ
ዕውር ሚያበራ ሽባ ሚተረትር
ከአብ የተሰጠን የክርስቲያን በትር
ፃድቅ ሰው ጠርቶት መች ተሸነፈ
ክፉ የት አገኘዉ እንዳሰፈሰፈ
እዚህ ስም ላይ ክብር አለ
ፈውስ አለ ክብር አለ
ታምራት አለ ክብር አለ
ሂወት አለ ክብር አለ
ድነት አለ ክብር አለ
ከፍታ አለ ክብር አለ
ክብር አለ (4X)
የኢየሱስ ስም ከስሞች
ሁሉ በላይ ነው በላይ ነው (4X)
እንኳን በምድር መንግስተ ሰማይ
ሁሉ አሻቅቦ ሚያየው ወደላይ
የኢየሱስ ስም የስሞች ማማ
ፃድቅ ጀግኗል ስሙን ሲሰማ
ክብር አለ (16X)
Join us 👇👇👇
👉👉 @Zemaenaqine 👈👈
👉👉 @Zemaenaqine 👈👈
share to your friends
👨👩👧👦👨👩👧👨👩👦👦
#Abet_Mihretih #አቤት_ምህረትህ
አቤት ምህረትህ እንዴት ታላቅ ነው
መለኪያ የለው መስፈሪያ የለው እንዴት ታላቅ ነው እንደምን ታላቅ ነው
ያንት ምህረት ከማን ጋር ይስተያይ
ከፈጠርከው ፍጥረት ከምድር ወይ ሰማይ
የሚስተካከልህ ማን አለ በውኑ
አባቴ ምህረትህ ያክላል አንተኑ
መለኪያ የለው መስፈሪያ የለው እንዴት ታላቅ (2X)
ሳይታዘዝ ጠላት እጅ ገብቶ
ሳምሶን ወደቀ ከመስመር ወጥቶ
ግን ምህረት ለምኖ መቼ አፈረ
የራሱ ፀጉር ማደግ ጀመረ
በህይወት ከሰራው በሞቱ ባሰ
ለዛ ኪዳን ሰው ምህረት ደረሰ
አንድ ዕድል ብቻ ባይለምንህ
ይኖር ነበረ በቸርነትህ
እንዴት እንዴት እንዴት ታላቅ ነው (2X) እንዴት ኧረ እንዴት
እንዴት እንዴት እንዴት ታላቅ ነው (2X) እንዴት ያንተ ምህረት
አቤት ምህረትህ...
ብትጨምርለት አስራ አምስት ዓመት
ተዝቆ በማያልቅ ከሰፊ ምህረት
ከኖረበት ዕድሜ ከምህረትህ ወስዶ
አንተን ሳያከብር ጨረሰው በባዶ
እኔንም ገብቶኛል የቃልህ ዕውነት
ለካ ምዘምረው ባንተ ምህረት
መሃሪነትህን እዘምረዋለሁ
በጉልበቴ ሳይሆን በምህረት እኖራለሁ
እንዴት...
መለኪያ የለው...
#Abet_Mihretih #አቤት_ምህረትህ
🕠 07:07 💾 12.0 MB
Join us 👇👇👇
👉👉 @Zemaenaqine 👈👈
👉👉 @Zemaenaqine 👈👈
share to your friends
👨👩👧👦👨👩👧👨👩👦👦
አሜን አሜን
አሜን አሜን (16X)
ወንጌል ሲነገረኝ አትንገሩኝ ባይ
ጠንካራ ነበረ ልቤ እንደ ድንጋይ
ግን አንድ ቀን ጭንቀት ወደ ህይወቴ መጣ
ዕውቀት የመሰለኝ ምንም አላመጣ
ቢጨንቀኝ ቢጠበኝ ልሞክረው ብዬ
በስብከት ሞኝነት አሄ ይሁን አሜን ብዬ
አይቼ ማላውቀው የደስታ ካባ
ህይወቴ ለበሰ ኢየሱስ ሲገባ
ዛሬማ እሞትለታለሁ
ሂድ ቢለኝ ወዴት እሄዳለሁ
እሱ ነው የመጨረሻዬ
አሜን ያልኩት ኢየሱስ ጌታዬ
አስገባሁት አሜን ልቤን ከፍቼ አሜን
ይኸው አለሁ አሜን ድኜ ቀርቼ አሜን
ያስገባሁት አሜን አሜን ብዬ አሜን
መድኃኒት ሆነኝ አሜን ኢየሱስዬ አሜን
ኢየሱስዬ ውድዬ (4X)
አሜን አሜን...
እንኳንስ ሊያቀርበኝ ሊገባ ከቤቴ
መጥራት ማይገባኝ ስሙን በአንደበቴ
ጌታ ግን ደግ ነው ምህረት የለበሰ
ለጠፋሁት ልጁ ፍቅርን ደገሰ
ፍርድ ነበረብኝ በሞት የሚያስቀጣ
የገዛ በደሌ ያመጣብኝ ጣጣ
ጌታ ግን ከፈለ የኃጢያቴን ዕዳ
አሜን በማለቴ ነውሬን አፀዳ
በኢየሱስ ህይወት አጊንቻለሁ
ልለየው እንዴት እችላለሁ
እስካይችል ይሄ ትከሻዬ
አይሏል ፍቅሩ በላዬ
አስገባሁት....
ኢየሱስዬ...
አሜን አሜን...
ከሰማይ ወረደ አሜን አሜን ደግሞ
ለእኔ ሞተ አሜን አሜን
ከሙታን ተነሳ አሜን አሜን
በክብር አረገ አሜን አሜን
ልክ እንደ መብረቅ አሜን አሜን
ከላይ እያበራ አሜን አሜን
ዳግም ይመለሳል አሜን አሜን
ከቅዱሳን ጋራ አሜን አሜን
ስምን ያተረፉ በየዘመናቸው
ተከታዮቻቸው ሲሞቱ ረሷቸው
ሁለት ሺ ዓመት ታሪክ ያልሸፈነው
ሰንጥቆ የመጣ የኢየሱሴ ስም ነው
ይኼን ስሰማ አሜን በማለቴ
ሰመረ ብርሃን በራ ቤቴ
አሜን በማለቴ (3X)
ሰመረ ሂወቴ
አሜን ያልኩት ጌታ (3X)
እስራቴን ፈታ
#አማላጄ
የኢየሱስ ደም ዛሬም ትኩስ ነው (2X) አማላጄ ነው
የጌታዬ ደም ዛሬም ትኩስ ነው (2X) አማላጄ ነው
የሰው ዘር ሁሉ ያዳም ስህተት
ይዞት ወደቀ ወደ ጥፋት (2X)
ማንም እንዳይድን ይሄን ቢረዳ
ሊከፍለው መጣ ለኃጢያት ዕዳ አወይ ለእኔ ዕዳ
የኃጢያት ደሞዝ ነውና ሞት
ሞቴን ሞተልኝ ሰጠኝ ሂወት (2X)
ኃጢያት ተሻረ ከእኔ ላይ
በፈሰሰልኝ ጎልጎታ ላይ ቀራኒዮ ላይ
በገዛ ደሙ እርቅ አወረደ
የጠፋሁትን ስለወደደ
ኃጥዕ ተብዬ ስም ለወጣልኝ
በደሙ አንፅቶ ፃድቅ አስባለኝ
ከደጉ አባቴ አሁን ታረኩ
በቅዱስ ደሙ ስለታጠብኩ
ሌላ አማላጅ ሳያስፈልገኝ
በቀኙ ሆንኩ ደሙ አቀረበኝ
የኢየሱስ ደም.....
የኢየሱስ ደም ሳያስታርቀኝ
የማን ፀሎት ነው የሚያስታርቀኝ
የኢየሱስ ደም ያላነፃኝ
የማን ፀሎት ነው የሚያነፃኝ
የኢየሱስ ደም ሳያስታርቀኝ
የማን ምልጃ ነው የሚያስታርቀኝ
የኢየሱስ ደም ያላጠበኝ
የማን ምልጃ ነው የሚያጥበኝ
ያስታረቀኝ ከአባቱ አማላጅ የሆነልኝ
ስለ ኃጢያቴ ጥብቅና በአብ ፊት የቆመልኝ
የኢየሱስ ደም.....
ለሆንኩት ለኔ ለሞት ፍርደኛ
በአብ ቀኛ ያለው አንዱ ብቸኛ
ስለበደሌ እሱ ነው ዋሴ
የሚቆምልኝ ልክ እንደ ራሴ
መሰላል ያየው ያዕቆብ በህልሙ
መካከለኛ ነው ክቡር ደሙ
ሰማይ ከእኔ ጋር ዕርቅ ያደረገው
በማንም አይደል በኢየሱስ ደም ነው
ያስታረቀኝ ከአባቱ....
Join us 👇👇👇
👉👉 @Zemaenaqine 👈👈
👉👉 @Zemaenaqine 👈👈
share to your friends
👨👩👧👦👨👩👧👨👩👦👦
አለዉ
አለሁ በምህረቱ አለሁ በይቅርታው (እየማረኝ) አለሁ
አለሁ ምህረት አጊንቻለሁ እኔ ምን እሆናለሁ
አለሁ ሞቴ ተሽሯል አለሁ ምህረቱ ገኗል አለሁ
አለሁ ህመሜን ወስዷል አለሁ እኔ ምን እሆናለሁ
እነ ሚካኤል እነ ገብርኤል
እነ ሱራፌል እነ ኪሩቤል
በክንፎቻቸው ተከልለውት
ፊቱ ሚቆሙለት አምላክ የሚሉት
በገራፊዎች ፊት ቆመልኝ እሱ ግን ስለ እኔ
ፍቅር ግድ ቢለው ሊያወጣኝ ከኃጢያት ከኩነኔ
ዙፋን የነበረው ከሰማይ ዳዊትን የረዳ
ተንከራተተልኝ ኢየሱስ ከናዝሬት ይሁዳ
ፍቅሩ ፈሰሰ ከምህረት ደጅ
እግዚአብሔር ከሰማይ ሰጠኝ አንድ ልጅ
ኑሮዬን ኑር አለኝ የእኔን ልብሰ ለበሰ
ቆሻሻ ሂወቴን በደሙ ቀደሰ
አለሁ ሞቴ ተሽሯል...
ይሁን በምትል ቃል ፍጥረትን የሰራ
ጥበብ የሻተውን ጥበብን ያስወራ
አባቶች ሲጠሩት በእሳት የመለሰ
እረኛው ዳዊትን ተናግሮ ያነገሰ
እንደሚታረድ በግ ዝም አለ ስለ እኔ ኢየሱስ
ፍቅርን የኖረ በተግባር የፍቅር ንጉስ
ምድርን ያቆመ በቃሉ ያላንዳች ምሶሶ
እሱ ግን ዝም አለ ሞተልኝ የእኔን ውርደት ለብሶ
ፍቅሩ ፈሰሰ...
አለሁ ሞቴ ተሽሯል...
አለሁ በምህረቱ አለሁ...
አብ ከላይ ሆኖ ለኔ ራራልኝ አዘነ
ሊያድነኝ ሽቶ አንድ ልጁ ላይ ጨከነ
ፍቅር ልሂድ አለ ታዘዘ ለአባቱ
ክብሩን ትቶ ወርዶ አዳነኝ በሞቱ
ፍቅር እንደ ኢየሱስ የለም (8X)
#የዉሃ_በረሃ
ብዙ ፍጥረት ያለው ባህር ውቅያኖሱ
ለየብስ ሩብ ሰጥቶ ቀሪውን መልበሱ
ላጥፋ ካለ አጥፊ ጡንቻ አለው ፈርጣማ
ካንዱ ጌታ በቀር ማንንም አይሰማ
ጥም አርኪ ይመስላል ግን ለጠማው ደሃ
ውስጡ ስለሌለው ለመጠጥ የሚሆን አንድ ብርጭቆ ውሃ
ሰነፍ መርከበኛ ውቅያኖሱ ዳር
ሚጠጣውን ሰይዝ መጓዝ ቢጀምር
ውሃ መሃል ደርሶ ውሃ ይጠማዋል
ውሃ በረሃ ላይ በውሃ ጥም ይሞታል
አንድ ጉድጓድ አለች በጣም ትንሽዬ
ህፃን ነህ አዋቂ ጨዋ ነህ ዱርዬ
ሳትል ሳታዳላ ሁሉን ታጠጣለች
ይህን ንፁህ ውሃ ታመነጨዋለች
ጠቢቡ ገበሬ እሷ ዳር ይዘራል
ዘሩም ምንጯን ነክቶ ማን ደርቆ ይቀራል
ጌታ ኢየሱስን በዕምነቱ የነካ
ከህይወት ውሃ ምንጭ ጠጥቶ እረካ
ስንት ምስኪነ አለ ሳይተኛ ሚያነጋ
ነፍሱ ምትገረፍ በጥማት አለንጋ
እግዚአብሔር ነፍሱን ነይ ላርካሽ ቢላት
የእግዚአብሔርን ሳይሆን ለነፍሱ ሆዱን ሰማላት
ጌታ በሌለበት በዚያ ባዶ ቦታ
ምኑንም ቢከቱ አይሰጥም እርካታ
ሰማይ እና ምድር ባንዴ ተጠቅልሎ
የኢየሱስን ቦታ አይሞላውም ችሎ
የተከበበ በማይጠጣ
በዓለም ያለ ሰው ኢየሱስን ያጣ
በጀልባ እንደጠፋ ውቅያኖስ ላይ
ኢየሱስ የሌለው ሰው እሱ አይደል ወይ
ተበልቶ ተጠጥቶ የለም እርካታ
ኑሮ ማለት ሃሩር ከሌለው ጌታ
ዳግመኛ አልጠማኝም አንዴ ጠጥቼው
ጎዶሎ የለኝም ውስጤ ሙሉ ነው
Join us 👇👇👇
👉👉 @Zemaenaqine 👈👈
👉👉 @Zemaenaqine 👈👈
share to your friends
👨👩👧👦👨👩👧👨👩👦👦
የዉሀ በረሀ
ብዙ ፍጥረት ያለው ባህር ውቅያኖሱ
ለየብስ ሩብ ሰጥቶ ቀሪውን መልበሱ
ላጥፋ ካለ አጥፊ ጡንቻ አለው ፈርጣማ
ካንዱ ጌታ በቀር ማንንም አይሰማ
ጥም አርኪ ይመስላል ግን ለጠማው ደሃ
ውስጡ ስለሌለው ለመጠጥ የሚሆን አንድ ብርጭቆ ውሃ
ሰነፍ መርከበኛ ውቅያኖሱ ዳር
ሚጠጣውን ሰይዝ መጓዝ ቢጀምር
ውሃ መሃል ደርሶ ውሃ ይጠማዋል
ውሃ በረሃ ላይ በውሃ ጥም ይሞታል
አንድ ጉድጓድ አለች በጣም ትንሽዬ
ህፃን ነህ አዋቂ ጨዋ ነህ ዱርዬ
ሳትል ሳታዳላ ሁሉን ታጠጣለች
ይህን ንፁህ ውሃ ታመነጨዋለች
ጠቢቡ ገበሬ እሷ ዳር ይዘራል
ዘሩም ምንጯን ነክቶ ማን ደርቆ ይቀራል
ጌታ ኢየሱስን በዕምነቱ የነካ
ከህይወት ውሃ ምንጭ ጠጥቶ እረካ
ስንት ምስኪነ አለ ሳይተኛ ሚያነጋ
ነፍሱ ምትገረፍ በጥማት አለንጋ
እግዚአብሔር ነፍሱን ነይ ላርካሽ ቢላት
የእግዚአብሔርን ሳይሆን ለነፍሱ ሆዱን ሰማላት
ጌታ በሌለበት በዚያ ባዶ ቦታ
ምኑንም ቢከቱ አይሰጥም እርካታ
ሰማይ እና ምድር ባንዴ ተጠቅልሎ
የኢየሱስን ቦታ አይሞላውም ችሎ
የተከበበ በማይጠጣ
በዓለም ያለ ሰው ኢየሱስን ያጣ
በጀልባ እንደጠፋ ውቅያኖስ ላይ
ኢየሱስ የሌለው ሰው እሱ አይደል ወይ
ተበልቶ ተጠጥቶ የለም እርካታ
ኑሮ ማለት ሃሩር ከሌለው ጌታ
ዳግመኛ አልጠማኝም አንዴ ጠጥቼው
ጎዶሎ የለኝም ውስጤ ሙሉ ነው
Join us 👇👇👇
👉👉 @Zemaenaqine 👈👈
👉👉 @Zemaenaqine 👈👈
share to your friends
👨👩👧👦👨👩👧👨👩👦👦
አማላጄ
የኢየሱስ ደም ዛሬም ትኩስ ነው (2X) አማላጄ ነው
የጌታዬ ደም ዛሬም ትኩስ ነው (2X) አማላጄ ነው
የሰው ዘር ሁሉ ያዳም ስህተት
ይዞት ወደቀ ወደ ጥፋት (2X)
ማንም እንዳይድን ይሄን ቢረዳ
ሊከፍለው መጣ ለኃጢያት ዕዳ አወይ ለእኔ ዕዳ
የኃጢያት ደሞዝ ነውና ሞት
ሞቴን ሞተልኝ ሰጠኝ ሂወት (2X)
ኃጢያት ተሻረ ከእኔ ላይ
በፈሰሰልኝ ጎልጎታ ላይ ቀራኒዮ ላይ
በገዛ ደሙ እርቅ አወረደ
የጠፋሁትን ስለወደደ
ኃጥዕ ተብዬ ስም ለወጣልኝ
በደሙ አንፅቶ ፃድቅ አስባለኝ
ከደጉ አባቴ አሁን ታረኩ
በቅዱስ ደሙ ስለታጠብኩ
ሌላ አማላጅ ሳያስፈልገኝ
በቀኙ ሆንኩ ደሙ አቀረበኝ
የኢየሱስ ደም.....
የኢየሱስ ደም ሳያስታርቀኝ
የማን ፀሎት ነው የሚያስታርቀኝ
የኢየሱስ ደም ያላነፃኝ
የማን ፀሎት ነው የሚያነፃኝ
የኢየሱስ ደም ሳያስታርቀኝ
የማን ምልጃ ነው የሚያስታርቀኝ
የኢየሱስ ደም ያላጠበኝ
የማን ምልጃ ነው የሚያጥበኝ
ያስታረቀኝ ከአባቱ አማላጅ የሆነልኝ
ስለ ኃጢያቴ ጥብቅና በአብ ፊት የቆመልኝ
የኢየሱስ ደም.....
ለሆንኩት ለኔ ለሞት ፍርደኛ
በአብ ቀኛ ያለው አንዱ ብቸኛ
ስለበደሌ እሱ ነው ዋሴ
የሚቆምልኝ ልክ እንደ ራሴ
መሰላል ያየው ያዕቆብ በህልሙ
መካከለኛ ነው ክቡር ደሙ
ሰማይ ከእኔ ጋር ዕርቅ ያደረገው
በማንም አይደል በኢየሱስ ደም ነው
ያስታረቀኝ ከአባቱ....
#እሱ_ሰዉ_ከበረ
በለሷን ፍሬዋን የጠበቀ
ይበላል ትግስቱ ያላለቀ
ጌታውን የጠበቀ ሰው
ስፍራዬን አለቅም ያለው
እሱ ሰው ከበረ አሄሄ ጌታን ያከበረ (2X)
ስምዖን ትጉህ እና ፃድቅ ሰው ነበረ
አያለው ቅዱሱን እያለ የኖረ
ሲጠብቅ ቆይቶ ህፃኑን ሲያየው
እጆቹን አንስቶ እንደዚህ አለዉ
ለህዝቦች ሁሉ መድኃኒት (2X)
የሆነውን እሱን ስላየሁት (2X)
መኖር አልሻም ውሰደኝ በቃ (2X)
በፅድቄ የኖርኩት እሱን ጥበቃ ልጁን ጥበቃ
ለኔ ስኬት (3X) ጌታን ማየት
ለኔ ከፍታ (3X) ፊትህ ነው ጌታ
ያርስ የለ ወይ በበጋ ልቡን ጥሎ
ገበሬው አምኖ ይዘንባል ብሎ
በደረቅ መሬት አምኖ ያረሰ
በክረምት እርሻው እረሰረሰ
እኔም እጠብቅሃለው
መውደዴን በዚ አሳይሃለው
አንድ ቀን ዓለም እያየህ
ልትወስደኝ ትመጣልኛለህ
ለኔ ስኬት...
ለኔ ከፍታ....
በለሷን.....
ፍፃሜው ክብር ነው አንተን መጠበቄ
መብራቴን አብርቼ ወገቤን ታጥቄ
እጠብቅሃለሁ እስክትመለስ
ሙሽራው አዳኜ ጌታዬ ኢሱስ
ፊትህን እንዳይ ተርቤ የለ ወይ እርቦኝ የለ ወይ
ለጥቂቶች ማዳን ብትዘገይ (2X)
ጨመረብኝ ፍቅርህ በየለቱ (2X)
ተናፍቀኃል ኢየሱስ የናዝሬቱ (2X)
እስክትመጣ እስክትመለስ
ጠብቅሃለው ውዴ ኢየሱስ
ጠነከተብኝ ፍቅርህ በረታ
በቶሎ ናልኝ የህይወቴ ጌታ
መምህሩ
የሞተን በቃሉ የሚያነሳ
ደግሞም የሚፈውስ......
ሳይታይ ጠባሳ
ምስክር ለሚሻ እኔ አለሁ
በስሙ አምኜ ተፈውሻለሁ
እንኳን ፊቱ ያለሁቱ (እንኳን ስሙን ያመንኩቱ)
ዳኑ ከጀርባ የነኩቱ
ኢየሱስ ብሉ የተጣራ
በልቷል ፈውስን እንደ እንጀራ
ፈውስን እንደ እንጀራ እንደ እንጀራ (2X)
ሀገር የሚያውቃት ከቤተ መቅደስ ስትመላለስ
ለፈውሷ ሳይሆን አምላኳን ወዳ ቀድማ የምትደርስ
ያሸማቀቃት ያስጎበጣትን ጀርባዋ ላይ
ይዛ ስትገባ ለካ ቀደሟታል ቅኖች የሚያይ
ቢዳስሳት ጌታዋ
ተፈወሰ ጀርባዋ
ወደቀላት ቀንበሩ
ስለመጣ መምህሩ
አዳኝ መጥቷል መምህሩ
ፍቅር መጥቷል መምህሩ
ንጉስ መጥቷል መምህሩ
ፈዋሽ መጥቷል መምህሩ
ደከመኝ ሳትል ተመላለሰች
ህመሟን ይዛ እቤቱ መጣች
ልክ እንደ ልማዷ ከምኩራብ ስትደርስ
የዛን ዕለት ሰባኪው መምህሩ ኢየሱስ
ቢዳስሳት ጌታዋ
ተፈወሰ ጀርባዋ
ወደቀላት ቀንበሩ
ስለመጣ መምህሩ
አዳኝ መጥቷል መምህሩ
ፈዋሽ መጥቷል መምህሩ
......... መጥቷል መምህሩ
ፍቅር መጥቷል መምህሩ (5X)
ልጅቷ ሞታለች አታድክም መምህሩን
ለወላጅ አባቷ ብለው አረዱት መርዶን
አትፍራ ብቻ እመን ሰምቶ አለው ጌታ
እቤታቸው ሄደ ባዛ ለቅሶ ጫጫታ
ተኛች እንጂ መች ሞተች
ቢላት ሳቁ ለቀስተኞች
ጌታ ወደ ውስጥ ገባና
ተነሽ አንቺ ብላቴና
በድኗ ልጅ ተነሳች
የጌታን ድምፅ ሰማች
ሙታን አቤት ሚሉት
ኢየሱስ የዓለም መድሃኒት
እንኳን ፊቱን የጀርባውን ቀሚስ
አይተው የለ ወይ የነካው ሲፈወስ
አልዳነችም ወይ ያቺ ምስኪን
በዕምነት ብትነካው ቀሚሱን
እንኳንስ ፊቱን ጀርባው መድኃኒት
አምኖ ለነካው የሚሰጥ ሂወት
የሚያገፋፋው አላማኝ መች ታጣ
በዕምነት ለነካች ከጀርባው ኃይል ወጣ
ፈውስ እንደ እንጀራ.....
እንኳን ፊቱ ያለሁቱ......
ይህን ወንጌል ያልሰማ እንዲሰማ
አውጃለሁ ከገጠር ከተማ
እንደሚያድን እንደሚታደግ
እሰብካለሁ ስለ እግዚአብሔር በግ
ያድናል የምለው እኔ
አድኖኝ ስላየሁ ባይኔ
ያድናል እኔ ያልኩት
አድኖኝ ስላየሁት
ያድናል (8X)
🕠 04:31 💾 4.3 MB
Join us 👇👇👇
👉👉 @Zemaenaqine 👈👈
👉👉 @Zemaenaqine 👈👈
share to your friends
👨👩👧👦👨👩👧👨👩👦👦
ረሃቤ(Rehabe) ዘማሪ ሙሉቀን ባልቻ Gospel Singer Muluken Balcha #Ethiopia_Protestant_Mezmur_መዝሙር_2023
ምን ልበል ምን ልናገር ቃላትም አጠረኝ
የሞትን አዋጅ ሽሮ በሕይወት ኑር ሲለኝ
ምህረቱ እንደፀና የሚያውቀኝ ያውቀው የለ
ያ ክፉ እንዳይጎዳኝ ቁጣውን ከለከለ
እኔማ ሳሰላስለው እኔማ የትናንቱን (፪x)
እኔማ ምክንያት ሆነኝ እኔማ ለማመስገን (፪x)
እኔማ እንደሌላ ሰው እኔማ ዝም አያሰኘኝ (፪x)
እኔማ ሀገር ያውቅ አይደል እኔማ እንደረዳኸኝ (፪x)
የተጠበቁ ጉድጓዶች ምንጫቸው ነጠፈ (፬x)
ያም ሄደ እያለፈ ይሄም ሄደ እያለፈ (፬x)
ብቻውን ህዝቡን የመራ በደረቁ ምድር (፬x)
ምንኛ ታማኝ ነው ታማኙ እግዚአብሔር (፬x)
አለኝታዬ (፬x) መከታዬ (፬x)
ቁምነገር ተገኘበት አይጠቅምም የተባለው
የሰማይ የምድር ጌታ ከሱ ጋር አብሮ ዋለ
በንጉስ ገበታ ላይ ተገኘ በክብር
ምስኪኑን የሚያነሳ ማነው እንደ እግዚአብሔር
እኔማ ሳሰላስለው እኔማ የትናንቱን (፪x) ያለፍኩትን (፪x)
እኔማ ምክንያት ሆነኝ እኔማ ለማመስገን (፪x)
እኔማ እንደሌላ ሰው እኔማ ዝም አያሰኘኝ (፪x)
እኔማ ሀገር ያውቅ የለ/እኔማ እንደረዳኸኝ (፪x)
ሁሉም ያውቅ የለ (፪x)
ያሰብኩት እንዳይሞላ እንቅፋት ሲገጥመኝ
ከፊቴ እየቀደመ ገለል አረገልኝ
ማዕበሉ እንዳያሰጥመኝ ንፋሱን ሲገስፀው
አይኔ አይቷል በዘመኔ ፍጥረታት ሲታዘዘው
እኔማ ሳሰላስለው እኔማ የትናንቱን (፬x) ያለፍኩትን (፪x)
እኔማ ምክንያት ሆነኝ እኔማ ለማመስገን (፬x)
እኔማ እንደሌላ ሰው እኔማ ዝም አያሰኘኝ (፬x)
እኔማ ሀገር ያውቅ የለ እኔማ እንደረዳኸኝ
#ማራናታ Bereket Tesfaye
የመምጣትህ ነገር የመጨረሻው
የነገርከን ትንቢት እየሆነ ነው
ናፍቆቱ አስባለኝ አሜን ማራናታ
ላይህ ጓጉቻለው እየሱስ የኔ ጌታ
ጌታ እየሱስ አትመጣም ወይ
የደማልኝን ጎንህን ልይ
አንተን ለማየት አይኖቼ ሻቱ
ቶሎ ናልኝ የሱሴ የናዝሬቱ
ካንተ ጋር ልዋል ካንተ ጋር ልደር
እንደ ዩሃንስ በደረትህ ስር
ደስታዬ የምለው ትልቁ እርካታዬ
አንተ ያለህበት ስኖር ነዉ ጌታዬ
በሌለህበት ከማገኝ ድሎት
ምድረ በዳ ላይ ካንተ ጋር ልሰንብት
አንተን የማየት ናፍቆት ገባብኝ
እንደ ጓጓሁኝ መች ቀራለሁኝ
ከአመፃ ብዛት ፍቅር ቀዘቀዘ
ሰው ወንድሙን ገሎ መቼ ተወቀሰ
አመፀኞች በዙ ክፍቱ ጨምሮ
ተላልፈው ተሰጡ ለማይረባ ኑሮ
የድሆች ዳኛ የሁሉ አለቃ
ናና ከልክለዉ ለቅሶአችን ይብቃ
የእናቶች እንባ ይላል ዋይ ዋይ
ሩሩህ ጌታ አትመጣም ወይ
ቤተክርስቲያን ተነሽና አብሪ
ፍቅርን ለጣሉት እንዳትዘምሪ
የገሀነም ደጅ ለካ ጥላቻ ነው
ማይቋቋምሽ ሰይፍሽ ፍቅር ሲሆን ነው
ጦር መሳርያውን ፍቅር ያደረገ
ጠላቱን ረቶ ወንድም አደረገ
የሰው ጠባብ አፍ የሚጎርስ እህል
ክፉ አንደበት አክሏል ሲኦል
አትመጣም ወይ ማራናታ
አናርፍም ወይ ማራናታ
ናናናና ማራናታ 4x
ሀሳዊ መምህራን ነብያቶች በዙ
ተናገረኝ ባዮች ለገንዘብ የተገዙ
ለታመመዉ ምስኪን እንግዳ ማረፊያ
በሽታው ሳያንሰዉ በፀሎት ሰበብ ዝርፊያ
ደምህ ተረግጦ ገንዘብ ገነነ
አንተን ያወቀ ሰው ክፉ ሆነ
ነዋይ ሚያፈቅር ትውልድ ተነሳ
ያረክለትን ምህረት የረሳ
ፈዉሱ ለታይታ ለንግድ ቀረበ
በአዳኙ ስም ገንዘብ ተሰበሰበ
ገብያው ደርቶ በወንጌል ሰበብ
ስንቱን ታዘብነው አወይ ጉድ አጀብ
በሰጠዉ ፀጋ የሆነ ነጋዴ
በፍርድ ቀን የሚል ነው ወይኔ ጉዴ
መምጣቱ አይቀርም የእረኞች አለቃ
ስለ በጎቹ የሚራራ ጠንቃቃ
አትመጣም ወይ ማራናታ
አናርፍም ወይ ማራናታ
ናናናና ማራናታ 4x
ወደ አለም ሂድ ወንጌልን ስበኩ
ነበር የተባልነው መስክሩ ታደጉ
ሰው ግን ካስማ ሰርቶ ወንበሯን ወደደ
መምህርና ጌታ መባልን ለመደ
ወንጌል እንስራ አንቱታው ቀርቶ
ይሸለም የለ ወይ የሰራ ተግቶ
ከታበይንበት ዙፋናችን
እስኪ እንውረድ ለጌታችን
አላወጣንም አጋንንቶችን
አልፈወስንም ወይ በሽተኞችን
ጌታ በስምህ ብዙ አድርገን
አላዉቃችሁም ስለምን አልከን
ከሚሉት ወገን እንዳይሆን ህይወቴ
መብራቴን ላብራ ሳይጎድል ዘይቴ
እስክትመጣልኝ ወይ እስክትወስደኝ
እየጠበኩክ እፀናለሁኝ
ናናናና ማራናታ3x
"ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን በመነሣቱ ለሕያው ተስፋና ለማይጠፋ፥ እድፈትም ለሌለበት፥ ለማያልፍም ርስት እንደ ምሕረቱ ብዛት ሁለተኛ የወለደን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ፤ ይህም ርስት በመጨረሻው ዘመን ይገለጥ ዘንድ ለተዘጋጀ መዳን በእምነት በእግዚአብሔር ኃይል ለተጠበቃችሁ ለእናንተ በሰማይ ቀርቶላችኋል።"
1ኛ ጴጥሮስ 1፥3-5
ታድለናል ተመርጠናል እንኳን የጌታ ሆናችሁ መልካም በዓል 🙏