cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

@Mehanaym pp 2

👋ሰላም ይብዛላችሁ ❤️ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች 👉ይህ @Mehanaym888 ነው በዚህ ቻናል 🖼 የፕሮፋይል ፒክቸሮች 🎶 መዝሙሮችን ግጥሞችን እንዲሁም ትምህርቶችን ታገኛላችሁ

Больше
Страна не указанаЯзык не указанКатегория не указана
Рекламные посты
193
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней
Архив постов
. "ሚስቴን ቆንጆ ብያት አላውቅም" ብዙዎች ከአጋንንት እስራት እየተፈቱ ነው 🕑-21:22Min💾-.19.5MB @marsilchannel @marsilchannel △Join Us△
Показать все...
. ደም ያስተፋኛል የመልካም ወጣት ምስክርነት 🕑-14:52Min💾-.20.9MB @marsilchannel @marsilchannel △Join Us△
Показать все...
. ጨቅጭቃኝ ነው የመጣሁት የመልካም ወጣት ምስክርነት 🕑-11:45Min💾-.7.4MB @marsilchannel @marsilchannel △Join Us△
Показать все...
. ደም ያስተፋኛል የመልካም ወጣት ምስክርነት 🕑-14:52Min💾-.36.7MB @marsilchannel @marsilchannel △Join Us△
Показать все...
. ጨቅጭቃኝ ነው የመጣሁት የመልካም ወጣት ምስክርነት 🕑-11:45Min💾-.40.8MB @marsilchannel @marsilchannel △Join Us△
Показать все...
. "ሚስቴን ቆንጆ ብያት አላውቅም" ብዙዎች ከአጋንንት እስራት እየተፈቱ ነው 🕑-21:22Min💾-.50.1MB @marsilchannel @marsilchannel △Join Us△
Показать все...
📚ልጅነት 🌟ልጅነት የለሰለሰ መሬት ፣ ወጣትነት የአዝመራ ዘመን ፣ ሽምግልና ደግሞ የአጨዳ ዘመን መሆኑን አስተውል። በሽምግልናህ የምታጭደው የወጣትነትህን አዝመራ ነውና ዛሬ ለምትዘራው ተጠንቀቅ። 🌟 ሁልጊዜ የበላዮችህን አትመልከት ፤ የበታቾችህንም ተመልከት። ለድምፅ አልባዎች ጩህላቸው ፣ ለተጠቁት ተሟገትላቸው። እውነት እውነት በማለትህ የምታጣው ሀሰተኛ ወዳጅህን ብቻ ነው። እውነት እውነት በማለትህ የምታተርፈው ግን እውነተኛ ወዳጅን ነው። 🌟እወድሃለሁ ብለህ የምትናገረውን ቃል ውለታ አታድርገው ፣ መውደድህን የምትናገረው እንወድሃለን እንዲሉህ አይሁን ፣ ሠላም ያለው አፍቃሪ የራሱን ፍቅር ያለ ምክንያት መፈፀም የሚችል ብቻ እንደሆነ እወቅ። መወደድህን ለመስማት አትጠብቅ። ✝ @Excellent_youth ✝ ✝ @Excellent_youth
Показать все...
📚አትጨነቅ ከአንተ ጀርባ ሆነው ስለሚያወሩ ሰዎች አትጨነቅ፥ አትዘን ምክንያቱም እነሱ የራሳቸውን የህይወት መንገድ መስመር መምራት ተስኗቸው እንዲሁም የአንተን ስህተት በመፈለግ የተጠመዱ ናቸው። ስለ እነሱ አትጨነቅ ምክንያቱም አንተ ሰዎች ምን ይሉኛል ብለህ የምትጨነቅ ከሆነ የሰዎች እስረኛ ነህና! ስራህ ከበረዶ 10ሺህ እጥፍ የነጣ ቢሆንም ከሰው ትችት አታመልጥምና ለሰው ወሬ ጆሮ አትስጥ! አንተ እንደገባህ እንጂ ሰዎች እንደ ተረዱክ አትኑር! ✝ @Excellent_youth ✝ ✝ @Excellent_youth
Показать все...
📚መጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቅዱስ የተሰጠን መጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ቡድኖች እንዲኖሩን ሳይሆን በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተመሰረተ ህይወት እንዲኖረን ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ለጥናትና ለምርምር የተሰጠን የቀለም ትምህርት አይደለምና። በመጽሐፍ ቅዱስ ፕሮግራሞች ላይ በጣም ፈጣን በኑሮ ወይም በሰልፍ ሜዳ ላይ ግን ቀርፋፋ የሆነው ከመጽሐፍ ቅዱስ ዓላማ ጋር #ስለተላለፍን ነው። መጽሐፍ ቅዱስ የተሰጠን በዋናነት #እንድናጠናው ሳይሆን #እንድንኖረው ነውና። ✝ @Excellent_youth ✝ ✝ @Excellent_youth
Показать все...
(ኦሪት ዘዳግም 31፥6) ======= 6፤ ጽኑ፥ አይዞአችሁ፥ አትፍሩ፥ ከፊታቸውም አትደንግጡ፤ አምላክህ እግዚአብሔር እርሱ ከአንተ ጋር ይሄዳል፤ አይጥልህም፥ አይተውህም። 👉 @Mehanaym888
Показать все...
እግዚአብሔር ያዘጋጃል              አንተ ከመኖሪያህ ተነስተህ ወደ አንድ ከተማ በመኪና ስትጓዝ ለዓይን ያማረህን ለምላስ የጣመህን ምግብ ቋጥረህ ትጓዣለህ። እስራኤላውያን ከግብፅ ባርነት ወጥተው የሲና ምድረ በዳን ሲያልፉ የቋጠሩት ምሳና እራት አልነበረም። በማያርሱበት በማይዘሩበት በማያጭዱበት ሁኔታ ውስጥ ሆነው፣ ጎራ ብለው የሚበሉበት ሬስቶራንት በሌለበት፣ የታሸገ ምግብ የሚገዙበት ሱፐርማርኬት ባልኖረበት ምድረ በዳ ላይ እግዚአብሔር መናና ድርጭት እየመገበ መራቸው። ከመሀላቸው አንዳች የተራበ አልነበረም። እግዚአብሔር መሪ የሆነበት ህይወትና ጉዞ በጉድለት ሳይሆን በበረከትና በጠል የተመላ ነው። ወዳጄ አምላክህ እስራኤልን በምድረ በዳ የመገበ፣ እውር አሞራን የሚቀልብ፣ ድንጋይ የተጫነውን ትል የማይረሳ፣ ትንሿን ትንኝ ሳይዘነጋ የሚመግባት ጌታ ነው።  አንተንማ ሞቶልህ እንዴት ይረሳሀል? ርቦህ እንዴት ይጨክንብሀል በፍፁም!        ምድረ በዳ በሆነ የህይወት ቀጠና ብታልፍ፣ ዘርተህ የማታጭድበት ሰርተህ የማታተርፍበት፣ ቀድተህ የማትጎነጭበት ሁኔታ ላይ ብትሆን እንኳ በሚያስፈልግህ ሁሉ መለኮታዊ እጁን ይገልጥልሀል።            ምድረ በዳ ነው ብሎ ሰው ሲጨነቅ በምድረ በዳ አንተን ለመርዳት የማይከለክለው ጌታ የበረከቱን ጠል ያዘንምልሀል። በሲና ምድር እስራኤላውያን ብቻ ሳይሆኑ ብዙ ሰዎች ለጉብኝት አልፈዋል፣ ሀገር አቋርጠው ሄደዋል ያቋርጡ እንጂ መና አልበሉም ከአለት ውኃ አልጠጡም የጠጡት በእግዚአብሔር ያመኑት እስራኤላውያን ብቻ ናቸው። አንተ ግን ሰው በሚራብበት ዘመን ትጠግባለህ፣ ሰው በሚጠማው ዘመን ትረካለህ፣ በሚሞትበት ዘመን በህይወት ትኖራለህ። ምክንያቱም እግዚአብሔር ያዘጋጃል! " እናት ከእንቅልፍ ቀስቅሳ ታበላለች እግዚአብሔር ግን ከሞትም ቀስቅሶ ይመግብሀል።" በነገር ሁሉ አትጨነቅ እግዚአብሔር ያዘጋጃል። ✍አዶኒ @adonigospel @adonigospel
Показать все...
♦️💕የጌታ ልጆች💕♦️ https://t.me/ye_geta_lijoch
Показать все...
በእኔ ሳላችሁ ሰላም እንዲሆንላችሁ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ። የዮሐንስ ወንጌል 16:33
Показать все...
. መዘመር አይደክመኝ ህፃን ክርስቲያን ▷ @yedestaye_elilta ◁ ▷ @yedestaye_elilta ◁ △Join Us△
Показать все...
የምስጋና ና ተሐድሶ ኮንፍረስ በአዳማ ቦሰት ፌሎ 26-28 ከዕሮብ- አርብ ከሰዓት ፦09:00 አገልጋይ አቦጊዳ ዘማሪ ቤኪ ወ/ዊ ፊሊ ዘማሪ አቢያታ አገልጋይ ወንዴ ዘማሪ ናቲ አድራሻ፦ ፒኮክ አዲሱ መናኸሪያ ፒኮክ ሙሉ ወንጌል ቤተ ክርስቲያን
Показать все...
"ድንቅ ነው" ዘማሪት ቤቲ ወልዴ Amazing Gospel Song sʜᴀʀᴇ ◈JOIN◈ sʜᴀʀᴇ @Mehanaym888
Показать все...
የእለቱ ቃል 🗞 ዘጸአት 20 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵ አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም፤ በሚጠሉኝ እስከ ሦስተኛና እስከ አራተኛ ትውልድ ድረስ የአባቶችን ኃጢአት በልጆች ላይ የማመጣ፤ ⁶ ለሚወድዱኝ፥ ትእዛዜንም ለሚጠብቁ እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ ምሕረትን የማደርግ እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝና።
Показать все...
በፈጣሪህ ተደገፍ! ህይወትህን የሚቀይረው ከሰው ጠብቀህ የምታገኘው ነገር አይደለም፤ ፀጋው፣ ስጦታው፣ ቸርነቱ ከማያልቀው ከፈጣሪህ ከምታገኘው በረከት ነው ህይወትህ የሚቀየረው። ወዳጄ በጭራሽ ከሰው እንዳጠብቅ፤ ሰው ማለት ሸንበቆ ነው የሆነ ቀን መቀንጠሱ አይቀርም! ከፈጣሪ ቀጥሎ ራስህን እመነው! ©inspire in Ethiopia @marsilchannel ❇️
Показать все...
አትፍሩ፥ ዛሬ የምታዩአቸውን ግብፃውያንን ለዘላለም አታዩአቸውምና ቁሙ፥ ዛሬ ለእናንተ የሚያደርጋትን የእግዚአብሔርን ማዳን እዩ። እግዚአብሔር ስለ እናንተ ይዋጋል፥ እናንተም ዝም ትላላችሁ አላቸው። ኦሪት ዘጸአት 14:13,14
Показать все...
እስኪ አንድ ትልቅ ትርጉም ያለው ግጥም ልጋብዛችሁ አቅጣጫ ቢስ ሆኜ በአለም ውሰጥ ስቀመጥ፤ በጎውን ከክፉ አስተውዬ ሳልመርጥ፤ ውሸትን ከእውነት ጋር በርዤ ስቀይጥ፤ የሃጥያትን ፅዋ ብርሌ ስጨብጥ፤ የሞት ውሃ ጥሞኝ ገልብጬ ስጨልጥ፤ እውነት ውገጅልኝ ብዬ ስሸመጥጥ፤ በጥፋት ባህር ውሰጥ ተዘፍቄ ስሰምጥ፤ የዘላለም ቤቴን ትቼው ስፈረጥጥ፤ ወደ ፊት እያየሁ ወደኋላ ስሮጥ ፤ ከፋ አወዳደቄ ቦታዬን ስለውጥ። ፈተናው በዝቶብኝ ሰውነቴ ደቆ፤ ገላዬ ሰልስሎኝ አንጀቴ ተጣብቆ፤ ማገልገል አቅቶኝ ሃይል እንደ ገል ደርቆ፤ መቅረዜ ባዶ ነው ዘይቴ ፈሶ አልቆ። የማበራ መስሎኝ ሳለውቅ ጨልሜአለው፤ እንደ ሻማ ስቀልጥ ለካስ ሰምብቻለው። ኩራዜ ብቻ አለ ላምባው ፈሶ አለቀ፤ ያበራ እንደነበር በሽታው ታወቀ፤ ንፍስ ነካውና ኩራዜም ጨለመ ፤ ተክዬ አላቆምኩት ድንኳኔም ዘመመ። ቤት መስራት ጀምሬ ሳንቃ ሳይገባበት፤ የሚያጠናክረው ማገር ሳያርፍበት፤ በቆመው አጣና ጭቃ ለጠፍኩበት፤ ከውጭ ብቻ እንዲታይ በቀለም አስዋብኩት። ጣራውን ሳልከድን ማገሩን ሳልጨርስ፤ ጭቃ ለደብኩበት ግድግዳው እንዲለብስ። በአለቱ ላይ ቆሞ አልተመሠረተም፤ በጣራው ትክክል ምሰሶ አልቆመም፤ የማዘኑ ድንጋይ ቦታውን አልያዘም፤ ቤቱ ተሰራ እንጂ ደጋፊ አላገኘም፤ የኃላ የኃላ ማዘንበሉ አይቀርም ። ደጄን በሳር ሳይሆን በገለባ አጠርኩት፤ ሌባ ረግጦት ገባ ሃብቴን አስወሰድኩት። የጠበቁት መስሎኝ ቤቴን አዘረፍኩት። ለሞት የሚጣደፍ ፍቅር ተላላፊ ፤ የሠላም ውል አፍራሽ አጥር ሰብሮ ጠፊ፤ ስምን አስደልዞ ከህይወት መፅሐፍ ወቶ፤ ለጠላት ተማርኮ ለአለም እጅ ሰቶ፤ መሸሽ ምን ያዋጣል ከአምላክ ተለይቶ። ቃልኪዳን አፋርሼ ኮብልዬ ልጠፋ ፤ እንደገና ለአለም ልደክም ልለፋ፤ ባቢሎን ትዝ ብላኝ ድንበሬን ሳሰፋ፤ የቀረበልኝን ማዕድ ስደፋ፤ አንጋጥጬ እያየሁ ያለ አቅሜ ስጋፋ፤ የነበረኝ ሁሉ ከእጄ ላይ ተደፋ። ሰንሰል ጎመን መስሎን አላምጠን ስንበላ፤ ሆዳችን ሳይጠግብ በምሬት ተሞላ። ሀጥያትን እንደ እህል አላምጠን ስንበላ፤ ከመንጋው ተለየን ቀረን ወደኃላ። አልተሰበሰብኩም በቃሉ አልታመንኩም፤ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ አልተመላለስኩም። በእምነት የቆምኩ መስሎኝ መውደቄን ሳላውቀው፤ እግሬ በእግዚአብሔር ቤት ልቤ ግን በአለም ነው። በአለም ፍርፋሪ እየተደለለ፤ ጠንካራ አቋም አጣሁ ልቤ ተከፈለ። ልቤ ልፋስፍስ ነው መቁረጥ ያቅተኛል ፤ አሁንም ከአለም ጋር ጨዋታ ያምረኛል። ከነአንን አላይም አልወርስም በተስፋ፤ እንደ ሎጥ ድንኳኔን ወደ ሰዶም ላስፋ፤ ከፍናፍንቶች ጋር በሀጥያት ልፋፋ፤ የጨው አመድ ልሁን ነፍሴም በዚያ ትጥፋ። እያለ ሲዝናና የዚች አለም ኗሪ፤ ከተፍ ይልበታል የመከራው ጥሪ ። ሞገደኛ ሆኖ ከአምላክ ጋር መጣላት፤ ማገዶ መሆን ነው ለሚፋጀው እሳት፤ አይጠቅምም በኃላ እያወቁ ማጥፋት። @Christinalageta @Christinalageta ♦join and share❤️
Показать все...
ልጆች ሆይ፥ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ አሸንፋችኋቸውማል፥ በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና። 1 የዮሐንስ ወንጌል 4:4
Показать все...
እነሆ በ Audio ተለቀቀ ዘመን የማይሽራቸው ከ1997 አንስቶ እስከ 2008 የተዘመሩ ዝማሬዎች ማስታወሻ። መዝሙሩን ለዘመሩ ዘማርያን ፣ግጥም እና ዜማ ለሰሩ አገልጋዬች ሁሉ እግዚአብሔር ፀጋውን ያብዛላቸው። ክራር ዘማሪ አብዲሳ ያደታ ድምፅ ቀረፃ እና ቅንብር ዲያቆን ሐዋዝ ተገኝ
Показать все...
. በጩቤ ሊወጋኝ የመልካም ወጣት ምስክርነት 🕑-6:34Min💾-.8.2MB @marsilchannel @marsilchannel △Join Us△
Показать все...
. በጩቤ ሊወጋኝ የመልካም ወጣት ምስክርነት 🕑-6:34Min💾-.13.1MB @marsilchannel @marsilchannel △Join Us△
Показать все...
የእለቱ ቃል 😌😌❤️❤️ኤፌሶን 5 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እንግዲህ እንደ ተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ፥ ² ክርስቶስም ደግሞ እንደ ወደዳችሁ ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ በፍቅር ተመላለሱ። ³ ለቅዱሳን እንደሚገባ ግን ዝሙትና ርኵሰት ሁሉ ወይም መመኘት በእናንተ ዘንድ ከቶ አይሰማ፤ ⁴ የሚያሳፍር ነገርም የስንፍና ንግግርም ወይም ዋዛ የማይገቡ ናቸውና አይሁኑ፥ ይልቁን ምስጋና እንጂ። ⁵ ይህን እወቁ፤ አመንዝራም ቢሆን ወይም ርኵስ ወይም የሚመኝ እርሱም ጣዖትን የሚያመልክ በክርስቶስና በእግዚአብሔር መንግሥት ርስት የለውም። ⁶ ከዚህ የተነሣ በማይታዘዙት ልጆች ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ይመጣልና ማንም በከንቱ ንግግር አያታልላችሁ። ⁷ እንግዲህ ከእነርሱ ጋር ተካፋዮች አትሁኑ፤ ⁸ ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁና፥ አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ፤ ⁹-¹⁰ የብርሃኑ ፍሬ በበጎነትና በጽድቅ በእውነትም ሁሉ ነውና ለጌታ ደስ የሚያሰኘውን እየመረመራችሁ፥ እንደ ብርሃን ልጆች ተመላለሱ፤ ¹¹ ፍሬም ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፥ ይልቁን ግለጡት እንጂ፥ ¹² እነርሱ በስውር ስለሚያደርጉት መናገር እንኳ ነውር ነውና፤ ¹³ ሁሉ ግን በብርሃን ሲገለጥ ይታያል፤ የሚታየው ሁሉ ብርሃን ነውና። ¹⁴ ስለዚህ፦ አንተ የምትተኛ ንቃ ከሙታንም ተነሣ ክርስቶስም ያበራልሃል ይላል። ¹⁵ እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንድትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ፤ ¹⁶ ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ። ¹⁷ ስለዚህ የጌታ ፈቃድ ምን እንደ ሆነ አስተውሉ እንጂ ሞኞች አትሁኑ። ¹⁸ መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና፤ ¹⁹ በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ፤ ²⁰ ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ። ²¹ ለእያንዳንዳችሁ በክርስቶስ ፍርሃት የተገዛችሁ ሁኑ። ²² ሚስቶች ሆይ፥ ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ፤ ²³ ክርስቶስ ደግሞ የቤተ ክርስቲያን ራስ እንደ ሆነ እርሱም አካሉን የሚያድን እንደ ሆነ ባል የሚስት ራስ ነውና። ²⁴ ዳሩ ግን ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ እንዲሁ ሚስቶች ደግሞ በሁሉ ለባሎቻቸው ይገዙ። ²⁵-²⁶ ባሎች ሆይ፥ ክርስቶስ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳት ሚስቶቻችሁን ውደዱ፤ በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤ ²⁷ እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ። ²⁸ እንዲሁም ባሎች ደግሞ እንደ ገዛ ሥጋቸው አድርገው የገዛ ሚስቶቻቸውን ሊወዱአቸው ይገባቸዋል። የገዛ ሚስቱን የሚወድ ራሱን ይወዳል፤ ²⁹-³⁰ ማንም የገዛ ሥጋውን የሚጠላ ከቶ የለምና፥ ነገር ግን የአካሉ ብልቶች ስለሆንን፥ ክርስቶስ ደግሞ ለቤተ ክርስቲያን እንዳደረገላት፥ ይመግበዋል ይከባከበውማል።
Показать все...
የሐዋርያት ሥራ 2፥15-24 15 ለእናንተ እንደ መሰላችሁ እነዚህ የሰከሩ አይደሉም፥ ከቀኑ ሦስተኛ ሰዓት ነውና፤ 16 ነገር ግን ይህ በነቢዩ በኢዩኤል የተባለው ነው፡— 17 እግዚአብሔር ይላል፡— በመጨረሻው ቀን እንዲህ ይሆናል፤ ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፥ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፥ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ፤ 18 ደግሞም በዚያች ወራት በወንዶችና በሴቶች ባሪያዎቼ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ትንቢትም ይናገራሉ። 19 ድንቆችን በላይ በሰማይ፥ ምልክቶችንም በታች በምድር እሰጣለሁ፤ ደምም እሳትም የጢስ ጭጋግም ይሆናል፤ 20 ታላቅ የሆነ የተሰማም የጌታ ቀን ሳይመጣ ፀሐይ ወደ ጨለማ ጨረቃም ወደ ደም ይለወጣሉ። 21 የጌታን ስም የሚጠራም ሁሉ ይድናል። 22 የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ ይህን ቃል ስሙ፤ ራሳችሁ እንደምታውቁ፥ የናዝሬቱ ኢየሱስ እግዚአብሔር በመካከላችሁ በእርሱ በኩል ባደረገው ተአምራትና በድንቆች በምልክቶችም ከእግዚአብሔር ዘንድ ለእናንተ የተገለጠ ሰው ነበረ፤ 23 እርሱንም በእግዚአብሔር በተወሰነው አሳቡና በቀደመው እውቀቱ ተሰጥቶ በዓመፀኞች እጅ ሰቅላችሁ ገደላችሁት። 24 እግዚአብሔር ግን የሞትን ጣር አጥፍቶ አስነሣው፥ ሞት ይይዘው ዘንድ አልቻለምና። 'የሐዋርያት ሥራ 2:15-24'
Показать все...
👉 ይቅርታን መቀበያ መንገዱ በደልን አለመቁጠርና ይቅር ብሎ ማለፍ ነው:: 👉ለማልማት ብለን ባጠፋነው 👉ለማከም አስበን ባሳመምነው 👉ለማስደሰት ብለን ባሳዘነው 👉ለማፅናናት ብለን ባቆሰልነው 👉 ለማብራት ብለን ባጨለምነው 👉 ለማብላት ብለን ባስራብነው 👉 ለማጠጣት ብለን ባስጠማነው 👉 ለመሰብሰብ ብለን በበተነው 👉 ለመገንባት ብለን ባፈረስነው 👉 በማወቅ ይሁን ባለማወቅ 👉 ላጠፋነው ይቅር እንባባል:: ይቅርታ ሠላም ነው፤ እረፍት ፤ የ አብሮ መኖር ሚዛን የ ስብዕና ዕድገት መገለጫ፡፡፡፡፡፡ ተባረኩ ♦መልካም ቅደሜ♦ @Christinalageta @Christinalageta
Показать все...
❤️#ሳልወድህ_የወደድከኝ❤️ =================== ሳልወድህ የወደድከኝ ሳልመርጥህ የመረጥከኝ በከበረው ደም ገዝተህ እንዲያው ልጅህ ያረከኝ አበሳዬን አራከው ቀንበሬን ሰባበርከው (ፍቅርህ ለእኔ ልዩ ነው ስምህን ላሞጋግሰው) (፪x) ኃጢአተኛ ሳለሁ ጽድቅ የማይገባኝ መርገሜን ወሰደው ኢየሱስ በደሙ አነጻኝ የከሰሰኝ ጠላት እግሬ ስር ወደቀ በረሃው ሕይወቴ ደረቁ ምንጭን አፈለቀ ሳልወድህ የወደድከኝ ሳልመርጥህ የመረጥከኝ በከበረው ደም ገዝተህ እንዲያው ልጅህ ያረከኝ አበሳዬን አራከው ቀንበሬን ሰባበርከው (ፍቅርህ ለእኔ ልዩ ነው ስምህን a ላሞጋግሰው) (፪x) ለዚህ የሚያበቃ ጽድቅ እንኳን ሳይኖረኝ በሰማዩ ስፍራ በቀኙ እንዲሁ አከበረኝ ምህረቱ ብዙ ይሄ ታላቅ ጌታ ከእኔ ጋር ሆናችሁ በዜማ አክብሩት በልልታ ሳልወድህ የወደድከኝ ሳልመርጥህ የመረጥከኝ በከበረው ደም ገዝተህ እንዲያው ልጅህ ያረከኝ አበሳዬን አራከው ቀንበሬን ሰባበርከው (ፍቅርህ ለእኔ ልዩ ነው ስምህን ላሞጋግሰው) (፪x) የዕዳ ጽህፈቴን በደሙ ደምስሶ ጠላቴን በእጄ እረግጦ ሰጠኝ አሳልፎ ጽኑ ስልጣን አለኝ የአምላክ ልጅ ሆኛለሁ የፈታኝን ጌታ ተፈትቸ አከብረዋለሁ ሳልወድህ የወደድከኝ ሳልመርጥህ የመረጥከኝ በከበረው ደም ገዝተህ እንዲያው ልጅህ ያረከኝ አበሳዬን አራከው ቀንበሬን ሰባበርከው (ፍቅርህ ለእኔ ልዩ ነው ስምህን ላሞጋግሰው) (፪x) ዘማሪ ተስፋዬ ጫላ ✝ @Excellent_youth ✝ ✝ @Excellent_youth
Показать все...
. ከልጅ ጋር መሆን ከፈለክ የመልካም ወጣት ምስክርነት 🕑-11:51Min💾-.34.1MB @marsilchannel @marsilchannel △Join Us△
Показать все...
. ሥራዬ ሰዎችን መነቀስ ነበር የመልካም ወጣት ምስክርነት 🕑-4:02Min💾-.2.9MB @marsilchannel @marsilchannel △Join Us△
Показать все...
. ከልጅ ጋር መሆን ከፈለክ የመልካም ወጣት ምስክርነት 🕑-11:51Min💾-.9.5MB @marsilchannel @marsilchannel △Join Us△
Показать все...
. ሥራዬ ሰዎችን መነቀስ ነበር የመልካም ወጣት ምስክርነት 🕑-4:02Min💾-.17.5MB @marsilchannel @marsilchannel △Join Us△
Показать все...
የእለቱ ጥቅስ ⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 (የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 18) ---------- 1፤ ሳይታክቱም ዘወትር ሊጸልዩ እንዲገባቸው የሚል ምሳሌን ነገራቸው፥ 2፤ እንዲህ ሲል። በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ። 3፤ በዚያችም ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፥ ወደ እርሱም እየመጣች። ከባላጋራዬ ፍረድልኝ ትለው ነበር። 4፤ አያሌ ቀንም አልወደደም፤ ከዚህ በኋላ ግን በልቡ። ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ ሰውንም ባላፍር፥ 5፤ ይህች መበለት ስለምታደክመኝ ሁልጊዜም እየመጣች እንዳታውከኝ እፈርድላታለሁ አለ። 6፤ ጌታም አለ። ዓመፀኛው ዳኛ ያለውን ስሙ። 7፤ እግዚአብሔር እንኪያስ ቀንና ሌሊት ወደ እርሱ ለሚጮኹ ለሚታገሣቸውም ምርጦቹ አይፈርድላቸውምን? 8፤ እላችኋለሁ፥ ፈጥኖ ይፈርድላቸዋል። ነገር ግን የሰው ልጅ በመጣ ጊዜ በምድር እምነትን ያገኝ ይሆንን? 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 ⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️ @Mehanaym888 @Mehanaym888 🥰🥰 መልካም እሁድ 🥰🥰
Показать все...
የእለቱ ጥቅስ ⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 (ወደ ኤፌሶን ሰዎች ምዕራፍ 6) ---------- 6፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ እንደሚያደርጉ እንደ ክርስቶስ ባሪያዎች እንጂ ለሰው ደስ እንደምታሰኙ ለታይታ የምትገዙ አትሁኑ። 7፤ ለሰው ሳይሆን ለጌታ እንደምትገዙ በትጋትና በበጎ ፈቃድ ተገዙ፤ 8፤ ባሪያ ቢሆን ወይም ጨዋ ሰው፥ እያንዳንዱ የሚያደርገውን መልካም ነገር ሁሉ ከጌታ በብድራት እንዲቀበለው ታውቃላችሁና። 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 ⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️⛅️ @Mehanaym888 @Mehanaym888
Показать все...
---------------- (2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕ. 1) ---------- 4፤ እርሱ በመከራችን ሁሉ ያጽናናናል፥ ስለዚህም እኛ ራሳችን በእግዚአብሔር በምንጽናናበት መጽናናት በመከራ ሁሉ ያሉትን ማጽናናት እንችላለን። 5፤ የክርስቶስ ሥቃይ በእኛ ላይ እንደ በዛ፥ እንዲሁ መጽናናታችን ደግሞ በክርስቶስ በኩል ይበዛልናልና። 6፤ ዳሩ ግን መከራ ብንቀበል፥ ስለ መጽናናታችሁና ስለ መዳናችሁ ነው፤ ብንጽናናም፥ እኛ ደግሞ የምንሣቀይበት በዚያ ሥቃይ በመጽናት ስለሚደረግ ስለ መጽናናታችሁ ነው። 7፤ ተስፋችንም ስለ እናንተ ጽኑ ነው፤ ሥቃያችንን እንደ ተካፈላችሁ እንዲሁም መጽናናታችንን ደግሞ እንድትካፈሉ እናውቃለንና። --------------- 🌹🌹 melkam ken🌹🌹 ፀጋ እና ሰላም ለሁላችሁ ይሁን!!
Показать все...
" ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ ላደርግ ይገባኛል፤ ማንም ሊሠራ የማይችልባት ሌሊት ትመጣለች።" (የዮሐንስ ወንጌል 9:4)
Показать все...