cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

TIKVAH-ETHIOPIA

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

Больше
Рекламные сообщения
1 341 952Подписчики
+76924 часа
+3 0427 дней
+25 15330 дней
Архив постов
#ኢራቅ የኢራቅ ፓርላማ ፫ግብረሰዶም / የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን ከ10 እስከ 15 ዓመት በሚደርስ እስር የሚቀጣ አዲስ ሕግ ማርቀቋን ቢቢሲ ዘግቧል። በአዲሱ ሕግ መሠረት ጾታቸውን የቀየሩ ሰዎች ከ1 እስከ 3 ዓመት ሊታሰሩ ይችላሉ። በአዲሱ ሕግ ፦ ➡️ የግብረሰዶም / የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን የሚያበረታቱ፣ የሚያስተዋውቁ፤ ➡️ ሴተኛ አዳሪነትን የሚያራምዱ፤ ➡️ ጾታ ለመቀየር ቀዶ ህክምና የሚያደርጉ ዶክተሮችን፤ ➡️ " ሆን ብለው " እንደ #ሴት የሚሆኑ ወንዶች እና " በሚስት መለዋወጥ " ላይ የተሠማሩ ሰዎች እስራት ይጠብቃቸዋል ፤ ዘብጥያም ይወርዳሉ። የሕጉ ዓለማ ፥ " የኢራቅን ማህበረሰብ ከሞራል ዝቅጠትና ግብረ ሰዶማዊነት ከሚያደርሰው አደጋ ለመጠበቅ ነው " ተብሏል። እንደ ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘገባ ፥ መጀመሪያ ላይ ረቂቁ ግብረሰዶማውያን #በሞት_እንዲቀጡ የሚል የነበረው ቢሆንም በአሜሪካ እና በአውሮፓ ሀገራት ከፍተኛ ተቃውሞ ነው የተሻሻለው። የኢራቅ ፓርላማ አባል የሆኑት አሚር አል-ማሙሪ ፥ " አዲሱ ሕግ #ኢስላማዊ እና ማህበረሰባዊ እሴቶችን የሚቃረኑ ልዩ ጉዳዮችን ለመዋጋት ትልቅ እርምጃ ነው " ብለዋል። #አሜሪካ በውጭ ጉዳይ መ/ ቤቷ በኩል የሕጉን መፅደቅ ተቃውማለች " ለሰብአዊ መብትና ነፃነት ጠንቅ ነው " በማለት ተቃውማለች። " ሕጉ የኢራቅን ኢኮኖሚ የሚያቀዛቅዝ እና የውጭ ኢንቨስትመንትን የመሳብ አቅምን ያዳክማል" ብላለች። የምዕራቡ ዓለም ሀገራት ሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችም ሕጉን ተቃውመዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመረጃው ምንጮች ቢቢሲ እና ሮይተርስ መሆናቸውን ይገልጸል። @tikvahethiopia
Показать все...
#FakeNews🚨 አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ምንም አይነት የተለየ ወታደራዊ እንቅስቃሴ የለም። ከወራት በፊት መሰል የፈጠራና ሀሰተኛ መረጃ ሲያሰራጩ የነበሩ የ #የሶማሊያ አክቲቪስቶችና የማህበራዊ ትስስር ገጾች ከሰሞኑን ዳግም የፈጠራ ወሬዎችን ፅፈው ማሰራጨትን ይዘዋል። እያሰራጩ ካሉት ሀሰተኛ እና የፈጠራ ወሬ አንዱ " በአዲስ አበባ የተለየ ሁኔታ እንዳለ ፣ ወታደራዊ እንቅስቃሴ እንደጨመረ፣ በየቦታው ወታደሮች እንደተበተኑ " የሚገልጽ ነው። ይህ ሀሰተኛ እና የፈጠራ ወሬ ሲሆን በከተማዋ ውስጥ አንዳችም የተለየ የወታደራዊ እንቅስቃሴ የለም። ምንም እንኳን ጉዳዩ ውሸት ቢሆንም በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ይህ ሀሰተኛ መረጃ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች እየተመለከቱት ፣ እያጋሩት እንደሆነ መመልከት ተችሏል ስለሆነም ጥንቃቄ አድርጉ። #AddisAbaba #Ethiopia @tikvahethiopia
Показать все...
#DStvEthiopia #ሁሉምያለውእኛጋርነው በቀን በ12 ብር በወር በ350 ብር ብቻ ! ተወዳጁን ሀገርኛ ድራማዎችን እና መዝናኛዎችን የምናገኝበት አቦል ቲቪ ከሜዳ ወደ ጎጆ ፓኬጅ መጣ! ምን ይሄ ብቻ ኒክ ጁኒየር በአማርኛ፥ ዚ-ዓለም የተከታታይ ድራማ ቻናል እና ሌሎችም የዲኤስቲቪ ቻናሎችን በጎጆ ፓኬጅ ያገኛሉ። አሁን ጎጇችን ሞላ፤ በወር 350... በቀን 12ብር ብቻ #DStvEthiopia #AbolTV #NickJrAmh #TraceMuzika #Zeeዓለም
Показать все...
🥰 1
" ሆሣዕና '' (የዐብይ ጾም 8ኛ ሳምንት) ሆሣዕና ከስምንቱ የዐቢይ ጾም እሁዶች አንዱና የመጨረሻው ሳምንት ተብሎ የሚጠራው ከትንሣዔ ቀድሞ የሚገኝ የሕማማት መግቢያ ዋዜማ ነው። ሆሣዕና ማለት የቃሉ ትርጉም  " እባክህ አሁን አድን " ማለት ነው። ዕለቱ ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ውርንጭላ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙትና የሚከተሉት ሕዝብ በተለይም ሽማግሌዎች እና ሕፃናት '' ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ ፣ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው ፤ ሆሣዕና በአርያም '' በማለት በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት ነው፡፡  ይህ ዕለት በቤተክርስቲያን ውስጥ ዘንባባ ተይዞ፣ እየተዘመረ እጅግ ልዩ በሆነ ሁኔታ ይታሰባል። በዐብይ ጾም ከሰርክ ሆሣዕና ጀምሮ እስከ ትንሣዔ ሌሊት ያሉት ዕለታት የሚገኙበት ሳምንታት ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡ ዕለታቱም የዓመተ ፍዳ ፣ የዓመተ ኩነኔ መታሰቢያ ናቸው፡፡ በዚህ ጊዜ በተለይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስርዓት ካህናት መስቀል በእጃቸው አይዙም፣ አያሳልሙም ፣ ይፍቱኝ ተብሎ ወደካህን አይቀረብም፤ ይህ ሳምንት የጌታን የመጨረሻው ስቃይ የሚታሰብበት ነው። #TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba @tikvahethiopia
Показать все...
426🙏 30🥰 25🕊 12👏 8😡 5😢 3🤔 2😱 2
#ሆሣዕና ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ2016 ዓ/ም ሆሣዕና በዓል አስመልክተው በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተገኝተው ትምህርት፣ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጥተዋል። ቅዱስነታቸው ፤ የዛሬው የሆሣዕና በዓል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙት እና የሚከተሉት ህዝብ በተለይ አእሩግ እና ሕጻናት " ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም ሚመጣ የተባረከ ነው ፤ ሆሣዕና በአርያም " በማለት ጌታችንን መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል መሆኑን አስረድተዋል። ቅዱስ ፓትርያርኩ ሰሙነ ህማማትንም  አስመልክተው ለመላው ምዕመናን አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ቅዱስነታቸው ፦ " ሰሙነ ሕማማትን እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አስጀምሮ እንዲያስፈጽመን ለብርሃነ ትንሳዔው እንዲያበቃን እግዚአብሔር አምላካችንን እንለምነዋለን። ሰሙነ ሕማማትን ሁላችንም በየአካባቢያችን ባለው ቤተክርስቲያን ተገኝተን ሰሞነ ሕማማትን ፣ ስግደቱን ፣ ጸሎቱን፣ ልመናውን በሕብረት ወደ እግዚአብሔር አምላካችን እንጸልያለን። በጸሎታችን ደግሞ ያለውን ችግር ሁሉ እንዲያስወግድልን ፦ - #ሰላሙን፣ - #ፍቅሩን፣ - #አንድነቱን እንዲሰጠን የሁላችንም ጸሎትና ምኞት ነውና እግዚአብሔር አምላካችን ከዚያ ያድርሰን ሰሙነ ሕማማቱን በሰላም ያስፈጽመን። " #TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba @tikvahethiopia
Показать все...
116🙏 13🕊 4🤔 1😭 1
#SamiTech አዳዲስ ላፕቶፕች  ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!! @samcomptech በአገልግሎት አሰጣጣችን ላይ እና  በዕቃዎቻችን ጥራት ላይ  ደንበኞቻችን ምስክሮቻችን ናቸው። ዛሬም ብዛትንም ጥራትንም ሳንቀንስ እያስተናገድን እንገኛለን። ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች ፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች ፣ ለጌመሮች ወ.ዘ.ተ አቅምን ካገናዘቡ እስከ ቅንጡ ላፕቶፖች ይህ ቀረ ሳይሉ የሚያገኙበትን ሱቃችንን ይጎብኙ። የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ ባሉበት ሆነው ይዘዙን እናደርሳለን። የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት ይሄን 👉 @samcomptech ተጭነው በቴሌግራምው ማየት ይችላሉ። @sww2844 0928442662 / 0940141114 https://maps.app.goo.gl/H3PM1NrTcQ4SWkK17
Показать все...
12🕊 3🤔 2😭 1
#RoseWood ለተለያዩ አገልግሎት የሚዉሉ ሼልፎችን ከሮዝዉድ ፈርኒቸር  ይዘዙ 👌 ለ ወዳጅ ዘመዶ ሼር ያድርጉልን  🙌 ሮዝዉድ ፈርኒቸር  📲 0905848586 ኣድራሻ  :  📍4ኪሎ ኣምባሳደር ሞል 2ኛ ፎቅ                   📍 እንቁላል ፋብሪካ ሩፋኤል Showroom Location 👇 https://goo.gl/maps/X6Q2exa7dfvjBPvWA ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ  👇 https://t.me/R0seWood https://t.me/R0seWood
Показать все...
#ጥንቃቄ🚨 " ማህበረሰቡ ያለበትን #የቤት_እጦት እና ፍላጎት በመገንዘብ ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ከኢትዮ - ቴሌኮም ጋር በመተባበር 100 ሚሊዮን ብር መድቦ እየሰራ ነው " እየተባለ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚሰራጨው መረጃ ፍጹም #ሀሰተኛ ነው። በማህበራዊ ሚዲያው የሚዘዋወረው መልዕክት አጭበርባሪዎች ህብረተሰቡን #ለማጭበርበር የፈጠሩት ነው። " ሼር ብቻ እያደረጋችሁ የቤት ባለዕድለኛ ሆኑ ፣ ተሸለሙ " የሚሉት መልዕክቶች በሁለቱም ተቋማት እውቅና የሌላቸው የአጭበርባሪዎች ስራ ናቸው። " ቤት ታገኛላችሁ ሼር አድርጉ " እንዲህ የሚባል ነገር የለም። ውድ የቲክቫህ ቤተሰቦቻችን ፤ መሰል #በውሸት የተሞሉ የማጭበርበሪያ ስልቶችን እንድትጠነቀቁ ከዚህ ቀደም በዛ ያሉ መልዕክቶች ተለዋውጠናል ፤ በቂ እውቀትም አላችሁ። ምናልባት እንዲህ ያለን ሀሰተኛ መልዕክት አምኖ የሚጭበረበር ወዳጅ ዘመንድ እንዳይኖራችሁ አስገንዝቧቸው። #TikvahFamily @tikvahethiopia
Показать все...
" የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ይሰጣል " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የ2016 ዓ.ም 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፤ " ፈተናው ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ለመስጠት ባይቻልም በክልሎች በተመረጡ ከተሞች ለመስጠት እየተሠራ ነው " ብለዋል። በሁሉም ክልሎች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን ይወስዳሉ ሲሉም አሳውቀዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ በተለመደው አግባብ ፈተናቸውን እንደሚወስዱ ገልጸዋል። የሀገር አቀፍ ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎትም ፈተና በኦንላይን ለመሥጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ ነው ብሏል። ተማሪዎች በሙከራ ፈተና እንዲለማመዱ እንደሚደረግ ገልጿል። የአሰልጣኞች ስልጠና በመሥጠት ተማሪዎች ተደጋጋሚ ስልጠና እንደሚሠጣቸው ተገልጿል። ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ይጀመራል ተብሏል። #MoE @tikvahethiopia
Показать все...
" ኑሮ ውድነቱ መፍትሄ ይሻል። መፍትሄ እንሻለን " - የኢሰማኮ ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ  የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሰማኮ) ከኑሮ ውድነት ጋር ተያይዞ የስራ ግብር እንዲቀነስ ፤ የዝቅተኛ ደመወዝ ወለል የሚወስን የደመወዝ ቦርድ እንዲቋቋም እየሰራ መሆኑ ይታወቃል። የኢሰማኮ ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ ከኑሮ ውድነቱ አንፃር የዘገየው የሰራተኞች ዝቅተኛ የደሞዝ ወለል እና የግብር ቅነሳ ምላሽ ማግኘት እንዳለበት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል። " አሁንም #በቀን_አንድ_ጊዜ ብቻ በልቶ ለመዋል የሚቸገር ሰራተኛ ነው ያለው " ያሉት አቶ ካሳሁን ሰራተኛው ካለው ገቢ አንፃር ችግሩ የሰፋ እንደሆነ አስረድተዋል። እነዚህ ጥያቄዎች #በአዎንታዊ_መልኩ መታየት እንዳለባቸው ጠቁመዋል። አቶ ካሳሁን " ዝቅተኛ የደሞዝ ወለል በሚመለከት ስራና ክህሎት ሚኒስቴር የዝቅተኛ የደሞዝ ወለል የሚወስን ቦርድ የሚቋቋምበት ደምብ ላይ ጥናት ማድረጋቸውን በቅርቡ አሳውቀውናል " ሲሉ ተናግረዋል። የኑሮ ውድነት በጣም አሳሳቢ እየሆነ በመምጣቱ ሰራተኛው ችግር ውስጥ መግባቱን የጠቆሙት ፕሬዝዳንቱ " ትክክለኛ ግብር ከፋይ ሰራተኛው ነው። ለመንግስት ቀኝ እጁ በሚከፍለው ግብር ሰራተኛው ነው። የግብር ቅነሳው አንድ እና ሁለት የለውም ዘግይቷል " ሲሉ ጠቁመዋል። አቶ ካሳሁን ፤ ሚያዚያ 23 ቀን በኢትዮጵያ ለ49ኛ ጊዜ በሚከበረው ዓለም አቀፉ የሠራተኞች ቀን (ሜይዴይ) አዳራሽ ውስጥ እንደሚከበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቀዋል። " አሁንም ቢሆን ባልተመለሱልን ጉዳዮች ላይ ነው የምንወያየው። የቀኑ መሪ ቃል ' ለሰላም እና ለኑሮ ውድነት መፍትሄ እንሻለን ' የሚል ነው  ብለዋል። " የሰላም ችግር አለ። ሰራተኞች በአንዳንድ ቦታዎች ይታገታሉ ፣ ይሞታሉ " ያሉት አቶ ካሳሁን ፎሎ ፤ " ይሄ እስከ መቼ ይቀጥላል ? ማንኛውም ማህበረሰብ ላይ እንደሚደርሰው ጉዳት ሁሉ ሰራተኛውም ላይ እየደረሰ ነው ፤ ስለዚህ ለሰላም መፍትሄ መምጣት አለበት " ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። #TikvahEthiopiaFamilyAA @tikvahethiopia
Показать все...
#ICS የሕዝብ ተ/ም/ቤት የሕግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ፤ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎትን የ9 ወር አፈጻጸም ትላንት ገምግሟል። ኮሚቴው ከዚህ ግምገማ በፊት ማለትም ሚያዚያ 3/2016 ላይ #ድንገተኛ ምልከታ አድርጎ ነበር። ቋሚ ኮሚቴው ምን አለ ? - ምንም እንኳ የተጀመሩ ሥራዎች ጥሩና ተስፋ ሰጪ ቢሆኑም በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታዩ ችግሮችን እና የተገልጋይን ቅሬታ መፍታት አልተቻለም። - ተገልጋዮች አገልግሎት ለማግኘት ብለው በሚደርስባቸው እንግልትና ስቃይ ምክንያት በተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከፍተኛ ቅሬታ እንደሚያቀርቡ በድንገተኛ ምልከታ መመልከት ተችሏል። - በዋና መ/ ቤቱ ተገልጋይ በተቋሙ ሠራተኞች ፦ ➡️ #መሰደብ፣ ➡️ #መመናጨቅ ➡️ #መገፍተር_ጭምር የሚደርስበት በመሆኑ ተገልጋይ በሥነ ምግባር መስተናገድ አለበት። - በአዲስ አበባ " ካሳንቺስ አካባቢ " የሚገኘዉ የውጪ ዜጎች አገልግሎት ተቋም የሚሰጠው አገልግሎት ኢትዮጵያን የማይመጥን፣ ምቹ ያልሆነ እና የንጽህና ጉድለት ያለው ነው። ይህ መታረም አለበት። - ዋናው መስሪያ ቤት ለአገልግሎት ምቹ ያልሆነ፣ ሕንፃው የቆየ እና አስፈላጊዉን የማሻሻያ ጥገና ያላገኘ ነው። ሕንፃው ከተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ ባህሪ ጋር የማይጣጣም ስሪት ያለው ነው። - በዋና መስሪያ ቤት ያለው መጨናነቅ እንዲቀንስ በአዲስ አበባ ከተማ ከአምስት ያላነሱ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች እንዲከፈቱ የመፍትሔ ሃሳብ ቢሰጥም አልተፈጸመም። በተለይ በአዲስ አበባ ቅርንጫፍ የማስፋፋት ሥራዎች መሠራት አለበት። - የደላላ ሰንሰለት በመለየት ማቋረጥ ያስፈልጋል። - አሁንም ከደላሎች ጋር የሚመሳጠሩ የተቋሙ #ሠራተኞች በመኖራቸው ትኩረት ሰጥቶ መሥራት አለበት። - የሠራተኛ ባጅ አለመኖሩም ሊታሰብበት ይገባል። በምክር ቤቱ የተገኙት የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት ለተነሱት ጉዳዮች ምላሽ ሰጥተዋል። ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/EPA-04-27-2 #EPA @tikvahethiopia
Показать все...