በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን
ይህን አንድ የእስልምና እምነት ጥያቄ በሁለት ክፍል የቀረበውን መልስ ታነቡት ዘንድ ጋበዝኳችሁ።
ክፍል ፩
#የሙስሊም ጥያቄ፡-
«ኢየሱስ ክርስቶስ በመፅሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ መሰረት አምላክ እንዳለው ተናግሯል ወይስ አልተናገረም?» ከተናገረና ኢየሱስም አምላክ ነው ከተባለ ታዲያ፣ አምላክ እንዳለውም የተናገረው ከምን አንጻር ነው?
#የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መልስ፡-
አዎ፣ ተናግሯል (ማቴ 27:46፣ ዮሐ 20:17)፣ የተናገረውም ከምን አንፃር እንደሆነ ደግሞ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ ይህንንም ለመረዳት፣ ኢየሱስ ከመወለዱ በፊት አምላክ መሆኑን እና መለኮቱን ሳይለቅ እንዴት ሰውም መሆን እንደቻለ ማወቅ ያስፈልጋል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ በዮሐንስ ራእይ 19:13 ላይ ስለኢየሱስ ሲናገር፣ “ስሙም የእግዚአብሔር ቃል ተብሏል" ይላል፡፡ በዮሐንስ ወንጌል 1፡1 ላይ ደግሞ እንዲህ ተብሏል፣
«በመጀመሪያው ቃል ነበረ፣ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበር (ከእግዚአብሔር ጋር ነበረ)፣ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ፡፡ ስለዚህ በዮሐንስ ወንጌል 1፡1 ላይ "ቃል" ሲባል የሚያመለክተው የአብን ንግግር ሳይሆን በአካል ከአብ የተለየና ማንነት ያለው ሌላ አካልን (ወልድን) ለማመልከት ነው፡፡ እየተገለፀ ያለውም ስለ ሁለት አካላት (ስለአብ እና ስለ ወልድ) መሆኑን ለመረዳት እንዲህ ቢባልም ያስኬዳል፡-
በመጀመሪያው ወልድ ነበረ፣ ወልድም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበር (ከእግዚአብሔር ጋር ነበረ)፣ ወልድም እግዚአብሔር ነበረ።
"#እግዚአብሔር" ሲባል የአምላክን #ምንነት ነው የሚገልፀው እንጂ ልዩ #ማንነትን አይደለም፡፡ ለምሳሌ "ሰው" ሲባልም #ምንነትን እንጂ #ማንነትን አይገልፅም፡፡
ለምሳሌ፦ አበበ፣ ከበደ እና አየለ የሚባሉ ሶስት ሰዎች (ወይም አካላት) ቢኖሩ፣ አበበ ሰው ነው፣ ከበደም ሰው ነው፣ አየለም ሰው ነው:: 3ቱም በምንነታቸው (ሰው በመሆን) አንድ ናቸው፡፡ በማንነት ግን (ማለትም በአካልና በስም) 3 ናቸው-
1. አበበ - በማንነቱ ከበደ አይደለም፣ አየለም አይደለም፡፡
2. ከበደም በማንነቱ አየለ አይደለም፣ አበበም አይደለም
3. አየለ - በማንነቱ አበበ አይደለም፣ ከበደም አይደለም
ይህ ግልፅ ከሆነ፣ የአብ፣ ወልድ፣ እና መንፈስ ቅዱስም #አንድነትና ልዩ #ሦስትነት ግልፅ ይሆናል፡- አብ እግዚአብሔር ነው፣ ወልድም እግዚአብሔር ነው፣ መንፈስ ቅዱስም እግዚአብሔር ነው (የዮሐንስ ወንጌል በምንነታቸው (በመለኮት ወይም እግዚአብሔር በመሆን) አንድ ናቸው፡፡ በማንነት ግን (ማለትም በአካልና በስም) ሦስት (3) ናቸው:-
1. አብ - በማንነቱ ወልድ አይደለም፣ መንፈስ ቅዱስም አይደለም፡፡
2. ወልድም በማንነቱ መንፈስ ቅዱስ አይደለም፣ አብም አይደለም፡፡
3. መንፈስ ቅዱስ - በማንነቱ አብ አይደለም፣ ወልድም አይደለም፡፡
አንድነት ብዙ ትርጕም አለው፣ አንድ አካል ማለት ብቻ አይደለም፡፡
ለምሳሌ የሁሉም ሰው ምንነት አንድ ነው፣ ያውም "ሰው" የሚል መገለጫ አለው፡፡ ማንነታችን ግን በቁጥር የአለም ህዝብ ብዛት ያህል ነው፡፡ ስለዚህ #በምንነት የሰው ልጅ በሙሉ አንድ ነው፣ በማንነት (በአካል) ግን ከ7 ቢሊየን በላይ ነው፡፡ እኔን ጨምሮ የአለም ህዝብ ሁሉ አንድ የሰው ምንነት እንዳለን ሁሉ፣ አብ፣ ወልድ፣ እና መንፈስ ቅዱስም (3ቱም አካላት) በመለኮት ምንነት አንድ እግዚአብሔር ናቸው፡፡ ከሶስቱም በቀር መለኮት ያለው ወይም የአግዚአብሔር ምንነት ያለው ሌላ አካል የለም፣ ሙሉውን መጽሐፍ ቅዱስ (ከኦሪት ዘፍጥረት እስከ ዮሐንስ ራእይ) ብናነብ የምንረዳው ይህንኑ ነው፡፡
የዮሐንስ ወንጌል 1፡1ን ይበልጥ ለመረዳት በሰው ደረጃ እራሱ ስለሁለት ሰው ታሪክ ለመናገር ብንፈልግ፣ ለምሳሌ አበበ የሚባል ሰው ከሌላ ሰው ጋር እንደነበረ ለመግለጽ ታሪኩን እንዲህ ብለን በመጀመር መግለጽ እንችላለን፦
«በመጀመሪያው አበበ ነበረ፣ አበበም በሰው ዘንድ ነበረ (ማለትም ከሰው ጋር ነበረ)፣ አበበም ሰው ነበረ» ቢባል፣ ይህ አገላለፅ ስህተት የለውም፣ ስለሁለት ሰዎች እየተነገረ መሆኑም ግልፅ ነው፡፡
ይህን አገላለፅ ከተረዳን፣ እግዚአብሔር ወልድ አምላክነቱን ሳይለቅ እንዴት ሰውም መሆን እንደቻለ ወይም እንዴት ከሰው እንደተዋሃደ ወደ ሚያስረዳው ወደ ዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ አንዴ እንመለስ፦
«በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፡፡ ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም፡፡ … ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።» (ዮሐንስ 1:1-3:14)
በዛው ምዕራፍ ላይ ቁጥር 15ን ስንመለከት ደግሞ፣ ያ አለም ከመፈጠሩ በፊት በመጀመሪያው በእግዚአብሐር ዘንድ የነበረና "ቃል" የተባለው አካል ኢየሱስ መሆኑን እንረዳለን፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ እንዲህ በማለት መሰከረ፣ «ከእኔ በኋላ የሚመጣው እርሱ ከእኔ በፊት ነበረና ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል፤ ስለ እርሱ ያልሁት ይህ ነበረ» (ዮሐንስ 1:15)። እዚህ ጋ ልብ ማለት የሚያስፈልገው፣ በሉቃስ ወንጌል 1፡1-እስከ መጨረሻው እንደ ተገለጸውም፣ መጥምቁ ዮሐንስ በዕድሜ ኢየሱስን በ6 ወር የሚበልጥ ሆኖ ሳለ ነው "ከእኔ በፊት ነበረና ከእኔ ደልቅ የከበረ ሆኖአል” ብሎ ስለኢየሱስ የመሰከረው፡፡
እናም ከላይ የቀረቡት ማስረጃዎች የሚያመለክቱት እንግዲህ፣ መጀመሪያ "ቃል" ተብሎ የተገለጸው #አካል ያለወንድ ዘር ሥጋ ሆኖ ሲወለድ ኢየሱስ መሆኑን ነው የሚያመለክተው፡፡ ኢየሱስ ደግሞ የሕያው እግዚአብሔር (የአብ) ልጅ ነው (ዮሐ 6:69፣ ማቴ 16:13-19)። ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ሲባል ደግሞ በሥጋ ከተወለደ በኋላ ሳይሆን አለም ሳይፈጠርም በፊት የአብ የባህሪ ልጁ ሆኖ የኖረ ነው:: ይህንንም ለመረዳት ከብሉይ ኪዳን መጻህፍት አንዱ የሆነውንና ኢየሱስ በሥጋ ከመወለዱ 900 ዓመታትን አስቀድሞ የተጻፈውን መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ 30:3-4ን ብናነብ ይበለጥ ለመረዳት ይረዳል፡፡ ቃሉ እንዲ ህይላል፦
“ጥበብን አልተማርሁም፤ #ስለ_ቅዱሱም ዕውቀት የለኝም፡፡ ወደ ሰማደ የወጣ፣ የወረደስ ማነው? ነፋስን በእጁ ሰብስቦ የያዘ ማነው? ውኆችንስ በመጐናጸፊያው የጠቀለለ ማነው? የምድርን ዳርቻዎች ሁሉ የወሰነ ማነው? ስሙ ማን ነው? #የልጁስ ስም ማን ይባላል? የምታውቅ ከሆነ እስቲ ንገረኝ!" (መፅሐፈ ምሳሌ 30:3-4)::
በዚህ ጥቅስ ላይ “ቅዱሱ” ተብሎ እየተወራ ያለው እንግዲህ ማንነቱ ተመርምሮ ሊደረስበትና ሊታወቅ የማይቻል፣ ነፋስን በእጁ ሰብስቦ የያዘ፣ ውኆችንም በመጐናጸፊያው የጠቀለለና፣ የምድርን ዳርቻዎች ሁሉ የወሰነ አካል እየተወራ ሲሆን፣ ያ አካል ደግሞ (አንድ) ልጅም እንዳለው ሲያመለክት "#የልጁስ ስም ማን ይባላል?" ብሎ ያጠይቃል፡፡ በዮሐንስ ወንጌል 3፡16 ላይ የተባለውም እንዲህ ነው፣
«በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር (አብ) #አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።» (ዮሐ 3:16)
እና ስለዚህ፣ መፅሐፈ ምሳሌ 30:3-4 የሚናገረው ስለ አብና ስለአንድያ ልጁ (ኢየሱስ ክርስቶስ) መሆኑ ግልፅ ነው:: ኢየሱስም ከዚሁ አንቀፅ ጋር የሚገናኝን ነገር እንዲህ በማለት ተናግሯል፡-