cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)

የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
41 912
مشترکین
-1224 ساعت
-727 روز
-35130 روز
آرشیو پست ها
Photo unavailableShow in Telegram
ለጥናትና ምርምርዎ እገዛ ይፈልጋሉ?     አዎ ከሆነ መልስዎ! በመንግስትም ሆነ በግል ዩኒቨርሲቲ/ኮሌጅ በዲፕሎማ፣ዲግሪ እና በማስተርስ ፕሮግራም ለምትማሩ እና ትምህርታችሁን ጨርሳችሁ የምርቃት ጊዜያችሁን በጉጉት ለምትጠብቁ ሁሉ ስለ ጥናትና ምርምር በቂ እዉቀትን በመያዝ የመመረቂያ ፅሁፋችሁን ተመራጭ እና ተወዳጅ አድርጋችሁ በመስራት በጥሩ ዉጤት ትመረቁ  ዘንድ እናግዝዎታለን፡ If you need support related to:     1 Assignment / አሳይመንት 2 Research / ሪሰርች 3 Proposal / ፕሮፖዛል 4 Term Paper /  ተረም ፔፐር 5 Case study/ ኬዝ ስተዲ 6 Article Review 7  Mini research 8  Business plan 9  Environmental impact assessment [EIA] Any other Questions Contact us via @ResearcherETH @ResearcherETH @ResearcherETH
نمایش همه...
👍 11 1
Photo unavailableShow in Telegram
" የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ይሰጣል " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የ2016 ዓ.ም 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፤ " ፈተናው ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ለመስጠት ባይቻልም በክልሎች በተመረጡ ከተሞች ለመስጠት እየተሠራ ነው " ብለዋል። " በሁሉም ክልሎች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን ይወስዳሉ " ሲሉ አሳውቀዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ በተለመደው አግባብ ፈተናቸውን እንደሚወስዱ ገልጸዋል። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር እሸቱ ከበደ በበኩላቸው  ፤ " ፈተናው በኦንላይን ለመሥጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ ነው " ብለዋል። ተፈታኝ ተማሪዎች በሙከራ ፈተና እንዲለማመዱ እንደሚደረግ ገልጸዋል። የአሰልጣኞች ስልጠና በመስጠት ተማሪዎች ተደጋጋሚ ስልጠና እንደሚሰጣቸው አመልክተዋል። ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ይጀመራል ብለዋል። © ትምህርት ሚኒስቴር
نمایش همه...
👍 26😁 9 4
ተማሪ መመገብ ያልቻሉ ዩኒቨርስቲዎች እየበዙ ነው🤔 ዲላ ዩኒቨርስቲም የምግብ በጀት እጥረት እንደገጠመው ገልቷል፡፡ ቀደም ሲል የወላይታ ድቻ ዩኒቨርስቲ ተመሳሳይ እጣፈንታ እንደገጠመው መዘገባችን ይታወሳል፡፡ አብዛሃኛዎቹ ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸውን ለመመገብ ችግር እንደገጠማቸው በዚህ ዘገባችን ስር ከተሰጡት አስተያየቶች መረዳት ችለናል፡፡ ለማሳያነትም ድላ፣ ሀዋሳ እና አምቦ ዩኒቨርስቲ በበጀት እጥረትና በምግብ ግብኣት ችግር ተማሪዎቻቸውን መመገብ እንዳልቻሉ ከተሰጡት አስተያየቶች መረዳት ችለናል፡፡ ድላ ዩኒቨርስቲው በለጠፈው ማስታወቂያ እንደ ሀገር ባጋጠመን የምግብ በጀት እጥረትና የምግብ ዋጋ መጨመር ጋር በተያያዘ ተማሪዎች የምግብ በጀታቸው ሙሉ በሙሉ ካለቀ ወራት አስቆጥሯል ብሏል፡፡ ተማሪዎቼ ትምህርታቸውን አቋርጠው እንዳይወጡ አትክልት እንድመገቡ እያደረኩ ነው ብሏል፡፡ በአስቸኳይ የምግብ ጥሬ ዕቃ ግዥ አቅርቦ እንዲሟላልን ጠይቂያለሁ ያለው የድላ ዩኒቨርስቲ የአቅርቦት ሁኔታው እስከሚስተካከል በትዕግስት ጠብቁ ሲል አስታውቋል፡፡ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት @NATIONALEXAMSRESULT
نمایش همه...
👍 31😭 18🔥 3👎 1
ተማሪ መመገብ ያልቻሉ ዩኒቨርስቲዎች እየበዙ ነው🤔 ዲላ ዩኒቨርስቲም የምግብ በጀት እጥረት እንደገጠመው ገልቷል፡፡ ቀደም ሲል የወላይታ ድቻ ዩኒቨርስቲ ተመሳሳይ እጣፈንታ እንደገጠመው መዘገባችን ይታወሳል፡፡ አብዛሃኛዎቹ ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸውን ለመመገብ ችግር እንደገጠማቸው በዚህ ዘገባችን ስር ከተሰጡት አስተያየቶች መረዳት ችለናል፡፡ ለማሳያነትም ድላ፣ ሀዋሳ እና አምቦ ዩኒቨርስቲ በበጀት እጥረትና በምግብ ግብኣት ችግር ተማሪዎቻቸውን መመገብ እንዳልቻሉ ከተሰጡት አስተያየቶች መረዳት ችለናል፡፡ ድላ ዩኒቨርስቲው በለጠፈው ማስታወቂያ እንደ ሀገር ባጋጠመን የምግብ በጀት እጥረትና የምግብ ዋጋ መጨመር ጋር በተያያዘ ተማሪዎች የምግብ በጀታቸው ሙሉ በሙሉ ካለቀ ወራት አስቆጥሯል ብሏል፡፡ ተማሪዎቼ ትምህርታቸውን አቋርጠው እንዳይወጡ አትክልት እንድመገቡ እያደረኩ ነው ብሏል፡፡ በአስቸኳይ የምግብ ጥሬ ዕቃ ግዥ አቅርቦ እንዲሟላልን ጠይቂያለሁ ያለው የድላ ዩኒቨርስቲ የአቅርቦት ሁኔታው እስከሚስተካከል በትዕግስት ጠብቁ ሲል አስታውቋል፡፡
نمایش همه...
በመጪው ሰኔ የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች የአገልግሎት 500 ብር የመክፈል እና ደረሰኝ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው ሲል ትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በደብዳቤ ማሳወቁን ተመልክቻለሁ። አዩዘሀበሻ 👉ተጨማሪ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ የቴሌግራም ቻናሉን join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇 http://t.me/ayuzehabeshaofficial http://t.me/ayuzehabeshaofficial
نمایش همه...
👍 18👎 8 4🔥 2🤔 1
Photo unavailableShow in Telegram
#Update የመውጫ ፈተና መቼ ይሰጣል? ትምህርት ሚኒስቴር ሚያዝያ 9/2016 ዓ.ም ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፈው ደብዳቤ፤ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 14 እስከ 21/2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ የሚወስዱ የቅድመ ምረቃ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎችን መረጃ በማሰባሰብ በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በኩል አረጋግጠው ባሳለፍነው ሳምንት ለትምህርት ሚኒስቴር መላካቸውን ያገኘነው መረጃ ያሳያል። 👉https://t.me/hugadssachannel
نمایش همه...
👍 20😭 5 3
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ የፃፈው ደብዳቤ ፡ ጉዳዩ፦ ያለአግባብ ገንዘብ ከባንክ ወጭ ያደረጉ ተማሪዎችን ይመለከታል፤ እንደሚታወቀው ባንካችን መጋቢት 06/2016ዓ.ም የሲስተም ማዘመን ስራ እየተሰራ በተፈጠረው የሲስተም ችግር ምክንያት ደንበኞች ያለአግባብ ገንዘብ ሳይኖራቸው ከሂሳባቸው ወጭ ማድረጋቸው ይታወቃል፡፡ በዚህም መሠረት ባንካችን ከአ/ምንጭ ዩኒቨርስቲ ጋር በትብብር በተሰራው የማስመለስ ስራ አብዛኛው ደንበኞች ያለአግባብ የወሰዱትን ገንዘብ መመለስ ችለዋል፡፡ ነገር ግን ጥቂት የሚባሉ ደንበኞች ዕዳቸውን ከፍለው በሚፈለገው ፍጥነት ሊመልሱ አልቻሉም፡፤ በመሆኑም ዩኒቨርስቲው ይህንን የሀገር ሃብት ለማስመለስ እስካሁን ድረስ ለሠራው ሥራ ምስጋናችንን እያቀረብን፣ የቀረውን ገንዘብ ማስመለስ ይቻል ዘንድ ከዚህ ደብዳቤ ጋር ባያያዝነው ሠንጠረዥ ላይ በተመለከተው ዝርዝር መሠረት ልክ እንደዚህ ቀደሙ በተቋሙ ለሚገኙ ተማሪዎች ያለአግባብ የወሰዱትን ገንዘብ #በ48 ሰዓት ጊዜ ውስጥ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ተመላሽ እንዲደረግ ልዩ የሆነ መመሪያ እንዲሰጣቸው በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ [የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ] ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news
نمایش همه...
👍 32😁 19 6😭 3👏 1
Photo unavailableShow in Telegram
ዒድ ሙባረክ ! መጻህፍት ቤት ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1445 ዓ/ሂ የኢድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል። በዓሉ የሰላም፣የመተሳሰብ እና የፍቅር ይሆንላችሁ ዘንድ መልካም ምኞቱን ይገልጻል። ዒድ ሙባረክ
نمایش همه...
👍 21 4
نمایش همه...
7👌 4🥰 1👏 1
Photo unavailableShow in Telegram
የ8ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና የሚሰጥበት ቀን... የ2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ሰኔ 4 - 5/2016 እንዲሰጥ ተወስኗል። ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት @NATIONALEXAMSRESULT
نمایش همه...
👍 26 3🥰 2👎 1
Photo unavailableShow in Telegram
አዲስ ዓለም የልዩ-ፍላጎት አገልግሎት ዛሬ ማለትም ቅዳሜ ከምሽቱ2:30 ጀምሮ በtiktok አካውንቷ ብቅ ብላ ስለ ኦቲዝም ምንነት  ትተነትናለች። በፕሮግራሙ ዶ/ር ስመኝ ተስፋዬ ስለ ኦቲዝም ምንነት ያዘጋጀችውን ካጋራችን በኋላ የውይይት ጊዜ ይኖረናል። ዶ/ር ስመኝ በሐረማያ ዩኒቨርስቲ መምህርት ስትሆን፣ በማህበራዊ ገጿም ጤና ነክ ጉዳዮችን ለማህበረሰቡ በመልቀቅ ከሚመጡ ችግሮች ቀድመው ይጠነቀቁ ዘንድ ማህበራዊ ግዴታዋንም እየተወጣች ያለች እህታችን ናት። በዚህም በኦቲዝም ዙሪያ ትኩረት አድርጋ ለመስራት የምትሻ በመሆኗ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ከኦቲዝም ጋር በተያያዘ ተሳትፎ ታደርጋለች። ዛሬ ምሽት የአዲስ ዓለም የልዩ-ፍላጎት አገልግሎት ታድማ ስለ ኦቲዝም  ከቃረመችው ብሎም ለእናንተ የእውቀት ምንጭ የሚሆን መረጃ ይዛ ስለምትቀርብ በፕሮግራሙ በመታደም ብዙ ታተርፋላችሁ። ወንድምና እህቶቼ ምናልባት እርስዎ በማጋራትዎት አንድ ሰው ሊጠቅሙ ይችላሉና ሳይሰስቱ የሚመለከታቸው ሰዎች ላይ ይደርስ ዘንድ ያጋሩ ፕሮግራም ዛሬ ቅዳሜ ምሽት 2:30 ፕሮግራሙ የሚተላለፍባት ገጽ 👉http://tiktok.com/@belayzgetnet 👉http://tiktok.com/@simegn.tenachin
نمایش همه...
👍 11👌 2 1
በኢትዮጵያ ለተማሪዎች ዉጤት መቀነስ ምክንያቱ ‹‹ከፍተኛ የሙቀት መጠን ነዉ›› ሲል  የዓለም ባንክ ገለጸ🤔 የዓለም ባንክ አደረግኩት ባለዉ ጥናት በኢትዮጵያ ለተማሪዎች ዉጤት መቀነስ ምክንያቱ ከፍተኛ የሙቀት መጠን መጨመር ነዉ ብሏል፡፡ ከፈረንጆቹ 2003-2019 በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና የወሰዱ ወደ 2.5 ሚሊየን የሚጠጉ ተማሪዎችን ዳታ ሰብስቦ ያገኘዉ ዉጤት መሆኑን ነዉ ይፋ ያደረገዉ፡፡ በትምህርት ዓመቱ ለከፍተኛ ሙቀት የተዳረጉ በተለይ ደግሞ በፈተና ወቅት ከባድ ሙቀት የሚያገኛቸዉ ተማሪዎች ፤ቀዝቃዛ አየር ባለባቸዉ ስፍራዎች ከሚማሩ ተማሪዎች ጋር ሲወዳደር ዉጤታቸዉ በእጅጉ ቀንሶ ተገኝቷል ነዉ ያለዉ፡፡ እንደዚህ ዓይነት ተጽዕኖ በተለይ በሰብ-ሰሃራ አፍሪካ አገራት ላይ የበረታ ነዉ የተባለ ሲሆን፤ የአየር ንብረት ለዉጡን ለመቋቋም የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎች በስፋት አለመኖራቸዉ ሁኔታዉን እንደሚያባብሰዉም ነዉ የተገለጸዉ፡፡ የጥናቱ መሰረታዊ ግኝት የሆነዉ በትምህርት ዘመኑ ከፍተኛ ሙቀት የሚስተናገድባቸዉ ቀናት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸዉ እንዲቀሩ የሚያደርግ መሆኑን ነዉ፡፡ ይህም በኮሌጅ መግቢያ ፈተናዎች ላይ ወደ 2.28 በመቶ ዝቅ ያለ ዉጤት እንዲመዘገብ እንደሚያደርግ ነዉ፡፡ በጥናቱ ይፋ እንደሆነዉ ግልጽ የሆነ ምክንያት ባይቀመጥለትም ወንዶች ከሴቶች በበለጠ በሙቀት መጨመሩ ምክንያት የፈተና ዉጤታቸዉ ዝቅ ያለ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ከወንዶች ጋር ሲነጻጸሩም ሴቶች በተሻለ መልኩ በትምህርት ገበታቸዉ ላይ የሚገኙ እና ለትምህርታቸዉም ከፍተኛ ቦታ ያላቸዉ ሆነዉ ተገኝተዋል፡፡ አሁን ላይ በተለያዩ የአለማችን አገራት ለተማሪዎች ዉጤት መቀነስ የሙቀት መጨመር ምክንያት መሆኑን ማስረጃ አለን ሲሉ በዓለም ባንክ የሪሰርቸሮች ግሩፕ ዋና ተመራማሪ ፓትሪክ ቤህረር ተናግረዋል፡፡ ፓትሪክ ጨምረዉም ከፍተኛ ሙቀት ከተማሪዎቹ በተጨማሪ በመምህራን የስራ እንቅስቃሴ ላይም የራሱ ተጽዕኖ ይኖረዋል ነዉ ያሉት፡፡ ፖሊሲ አዉጪዎች ይህንን ጉዳይ በደንብ ትኩረት ሊሰጡት ይገባል ያሉት ተመራማሪዉ ፤በመማሪያ ክፍሎች ዉስጥ ያለዉን የሙቀት መጠን በማስተካከል ለተማሪዎች ምቹ የመማሪያ ስፍራን መፍጠር አለባቸዉ ብለዋል፡፡ የተሻለዉ አማራጭ እንደየአከባቢዉ የሚለያይ ቢሆንም ግን አንድ ነገር ግልጽ ነዉ ሲሉ የሚጨምሩት ተመራማሪዉ ፤ይህም ተማሪዎች ለከፍተኛ ሙቀት ያልተጋለጡ አከባቢዎች ላይ እጅግ በተሻለ ሁኔታ መማር እንደሚችሉ ነዉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በ2022 ዘ ጋርዲያን ይዞት በወጣዉ አንድ ጽሁፍ ከፍተኛ የሙቀት መጨመር በጥራት እንዳናስብ በማድረግ ፣ የማሰላሰል እና የማመዛዘን ችሎታችን ላይ ተጽዕኖ ስለሚኖረዉ ስህተት የመስራት ዕድላችንን ከፍ ያደርገዋል ሲል አስታዉቆ ነበር፡፡ @NATIONALEXAMSRESULT
نمایش همه...
😁 75👍 37🤣 17👎 4 4💯 2👏 1
Photo unavailableShow in Telegram
በቅርቡ መክፈል ይጀምራል ተብሎ በብዙዎች ዘንድ እየተጠበቀ ያለውና Bitcoin የተባለውን መገበያያ ይገዳደራል የተባለው notcoin የቴሌግራም bot ይህ ነው። ስንት Coin ሰራችሁ? እውን ይከፍላል ብላችሁ ታስባላችሁ? ቦቱ አሁን ላይ ታብ በማድረግ ብቻ ለተጠቃሚዎች coin እያጠራቀመ ይገኛል። ለመጠቀም 👇 https://t.me/notcoin_bot?start=r_573809_33060966 ከዚያም Start ማለትና የወርቅ ሳንቲሟን ታፕ ታፕ በማድረግ coin ማጠራቀም ይቻላል። ምንም እንኳ ብዙዎች በቅርቡ እንደ ቢትኮይን መገበያያ ይሆናል ቢሉም በዚያው ልክ ደግሞ ተቃራኒውን የሚያነሱ አልጠፉም። በተመሳሳይ ደግሞ ለማንኛውም በሚል ቦቱን አስጀምረው ከ1,000,000 በላይ coin ያጠራቀሙም ብቅ እያሉ ነው። ሩሲያውያን የቦቱ ባለቤቶችም በቅርቡ ጠብቁን ብለዋል። በቅርቡ እናያለን
نمایش همه...
👍 25 12🔥 7😁 1
https://t.me/notcoin_bot?start=r_573809_33060966 🎁 +2.5k Notcoin as a first-time gift 🎁🎁🎁 +50k Notcoin if you have Telegram Premium @PremiumBot
نمایش همه...
👍 2
የእርዳታ ተማጽኖ ዲያቆን ሱራፌል ገረመው መኮንን የ24 ዓመት ወጣት ሲሆን፤ የግራፊክስ ባለሙያ ነው። እንዲሁም በረጲ መካነ ጎልጎታ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በድቁና አገልጋይ ነው። ባለፉት ስድስት ወራት በገጠመው ከባድ የጉበት ህመም ምክንያት በተለያዩ ሆስፒታሎች የህክምና ክትትል ሲያደርግ ቢቆይም፤ ህመሙ ከፍተኛ ደረጃ ላይ በመድረሱ አስቸኳይ የጉበት ንቅለ ተከላ ማድረግ እንደሚገባው የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህክምና ቦርድ ወስኗል። የጉበት ንቅለ ተከላ ህክምናው በሀገር ውስጥ የማይሰጥ ሲሆን፤ በውጭ ሀገር ህክምናውን ለማግኘት እስከ ስድስት ሚሊየን ብር እንደሚያስፈልግ ተጠይቋል። ይህ ወጪ ከቤተሰብ አቅም በላይ በመሆኑ የወገኖቻችንን ድጋፍ መጠየቅ ግድ ብሎናል። በመሆኑም በወጣት ሱራፌል ገረመው የህክምና ድጋፍ አስተባባሪዎች፤ መሰረት ፀጋዬ፣ አለልኝ ዋለ እና ሎንያስ ገዛኸኝ ስም በጋራ በተከፈቱ አካውንቶች፤ 1000610015585 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 2957769765811 ዳሸን ባንክ 177682853 አቢሲኒያ ባንክ የተቻላችሁን ወገናዊ ድጋፍ እንድታደርጉልን እንጠይቃለን። ለተጨማሪ መረጃ +251947328673 ኤልሳቤጥ ገረመው +251946727171 ሎንያስ ገዛኸኝ
نمایش همه...
😢 32👍 22👏 3 2
Photo unavailableShow in Telegram
#Update የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች ምዝገባ ማድረጋቸውን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በቅርቡ መግለፃቸው ይታወሳል፡፡ የፀጥታ ችግር ካለባቸው አካባቢዎች በስተቀር በአብዛኛው የአገሪቱ አካባቢዎች የተማሪዎች ምዝገባ መጠናቀቁም ተገልጿል። የፈተናው ሕትመት በቀጣይ ቀናት እንደሚጀመር ለኢሳት የገለፁት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥም አረጋግጠዋል፡፡ ለ3ኛ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጠው ብሔራዊ ፈተናው፤ ዘንድሮ ለተፈጥሮ ሳይንስ እና ማኅበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስኮች ለእያንዳንዳቸው በስድስት የትምህርት አይነቶች እንዲሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር መወሰኑ አይዘነጋም፡፡ ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news
نمایش همه...
👍 20 5 2👏 2
👉ለመሆኑ የተማሪዎቹ ጉዳይ ከሕግ አንጻር እንዴት ይታያል❓ በጅማ ዩኒቨርሲቲ የሕግ መምህር የሆኑት ሃብታሙ ለገሰ የማይገባቸውን ገንዘብ ወጪ ያደረጉት ግለሰቦች በወንጀል እንደሚጠየቁ ይናገራሉ። የሕግ መምህሩ፤ “የሲስተም ችግሩን መሠረት በማድረግ ለራስ ወይም ለሌሎች የማይገባን ጥቅም ለማግኘት የተፈጸመው ተግባር የኮምፒዩር ወንጀልን ለመደንገግ በወጣ አዋጅ ሊታይ የሚችል የወንጀል ድርጊት ነው” ይላሉ። ንግድ ባንክ ካጋጠመው ክስተት ጋር በተያያዘ የተፈጸመው ተግባር በዚህ የኮምፒዩር ወንጀልን ለመደንገግ በወጣው አዋጅ ሊታይ አይችልም ቢባል እንኳ ጉዳዩ በመደበኛው የስርቆት ወንጀል ሊዳኝ እንደሚችል ሃብታሙ ይናገራሉ። የሕግ መምህሩ እንደሚሉት የራሳቸው ያልሆነን ገንዘብ ያወጡ ተማሪዎች በ3 ዓመት የቀላል እስራት እና ከ30ሺህ ብር ባልበለጠ የገንዘብ ቅጣት ሊቀጡ ይችላሉ ይላሉ። “ወንጀሉን የተፈጸመበትን ሁኔታ ከግምት በማስገባት ብዙ ርቀት ሄደው ብዙ ገንዘብ የወሰዱ ግለሰቦች ቅጣት ከዚህም በላይ ከባድ ቅጣት ሊጠብቃቸው ይችላል” ከእውቅናቸው ውጪ ገንዘብ ገቢ የተደረገላቸውም ግለሰቦች ቢሆኑ የራሳቸው ያልሆነን ገንዘብ ወይም የወንጀል ድርጊት ውጤት የሆነን ገንዘብ ይዞ በማቆየት በወንጀል ተጠያቂ እንደሚሆኑ ጨምረው አስረድተዋል። የንግድ ባንክ የሲስተም ችግርን እንደ መልካም አጋጣሚ ተጠቅመው ገንዘብ የወሰዱ ተማሪዎች የማይገባቸውን ገንዘብ በአስቸኳይ ተመላሽ እንዲያደርጉ አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ማስጠንቀቂያ አዘል ማስታወቂያዎችን ማውጣታቸው ይታወሳል። የሕግ መምህሩ ግን ዩኒቨርሲቲዎች ይህን የወንጀል ጉዳይ የመመልከት ሥልጣን የላቸውም ይላሉ። “ዩኒቨርሲቲዎች መመልከት የሚችሉት የባሕሪ ወይም የዲስፕሊን ግድፈቶችን እንጂ የወንጀል ጉዳዮችን ማየት አይቻላቸውም። ሊያደርጉ የሚችሉት ከሚመለከተው አካል ጋር ትብብር ማድረግ ነው” ይላሉ። ምንም እንኳ ጥሬ ገንዘብን በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ጊቢዎች ውስጥ ከሚገኙ ገንዘብ መክፈያ ማሽኖች (ኤቲኤም) ወጪ ቢያደርጉም ተማሪዎች ያለ አግባብ የተጠቀሙት የንግድ ባንክ ሥርዓትን እንጂ የኤቲኤም ማሽኑን አይደለም ይላሉ። [ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው] @NATIONALEXAMSRESULT
نمایش همه...
👍 22🤪 8 4😢 2
Photo unavailableShow in Telegram
ሁለት ብልት እና ሁለት ማህፀን ያላት ሴት የ25 ዓመቷ ብሪታናዊት አኒ ሻርሎት ከቢልየን ሰዎች መሀል እንኳን የመከሰት እድሉ ጠባብ በሆነው ዲዴልፊስ ተብሎ በሚጠራው ወጣ ያለ የመራቢያ አካል አቀማመጥ የተጠቃች ሲሆን በዚህም ምክንያት ሁለት ብልት እና ሁለት ማህፀን እንዳላት ተናግራለች። ሁለት የተለያያ የወር አበባ ሂደት በየወሩ እንደምታስታናግድ ገልፃ ብዙዎችን በጣም ያስገረመው ግን እራሴን እንደ ሁለት ስለምቆጥር ሁለት የወንድ ጓደኞች አሉኝ ማለቷ ነው ሲል ዘ ሰን ሰሞኑ አስነብቧል።
نمایش همه...
😁 56👍 26🤔 18 16😎 5😱 4🤨 3🥰 2👎 1
Photo unavailableShow in Telegram
በዘንድሮ ዓመት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ የተማሪዎች ምዝገባ ተካሂዷል በዘንድሮ ዓመት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ የተማሪዎች ምዝገባ መካሄዱን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገለጸ። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ለዘንድሮው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የተሳካ ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ ነው። ይህንንም ተከትሎ ተማሪዎች የሚፈተኗቸውን የትምህርት ዓይነቶች አውቀው ዝግጅት እንዲያደርጉ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር መከናወኑን አንስተዋል። ተማሪዎች በሥነ-ልቦና እራሳቸውን እንዲያዘጋጁ የተለያዩ ተግባራት መከናወናቸውንም ጠቅሰዋል። ለሀገር አቀፉ የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚቀመጡ የተፈታኝ ተማሪዎች ምዝገባ ከየካቲት 3 እስከ የካቲት 30/2016 ዓ.ም እንደሚያከናውን ተቋሙ መግለጹ ይታወሳል። ይህንንም ተከትሎ ተቋሙ የፀጥታ ችግር ካለባቸው አንዳንድ አካባቢዎች በስተቀር በአብዛኛው ሀገሪቱ አካባቢዎች የተማሪዎች ምዝገባ ተካሂዶ መጠናቀቁን ጠቁመዋል። በዚህም እስካሁን ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ መመዝገባቸውን ገልፀዋል። የተቀሩት የፀጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ተፈታኝ ተማሪዎች ምዝገባ ደግሞ በዚህ ሣምንት እንደሚከናወን ነው ያረጋገጡት። የፈተና ዝግጅት ሥራው የሀገሪቱን ሥርዓተ ትምህርት የተከተለና ተማሪዎቹን በአግባቡ መመዘን በሚያስችል መልኩ መዘጋጀቱን ጠቅሰዋል። የፈተናው ዝግጅት እየተገባደደ መሆኑን አንስተው በቀጣይ የፈተናው ሕትመት እንደሚጀመርም ገልፀዋል። የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የመስጫ ሰሌዳ ወደፊት ይፋ እንደሚሆንም ጠቁመዋል። @EthiopianEducationalTelevision
نمایش همه...
👍 29👎 5😁 3
🤣 60👍 24😁 19 7😢 5😐 3👏 1
Photo unavailableShow in Telegram
ማስጠንቀቂያው በተለያዩ ጊቢዎች ቀጥሏል 😁ትናንትና ማታ ከንግድ ባንክ የሌላችሁን ብር ለወሰዳችሁ ተማሪዎች በሙሉ😁 AASTU የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን @NATIONALEXAMSRESULT
نمایش همه...
😁 32👍 20 3🤨 2👎 1
Photo unavailableShow in Telegram
ትናንትና ማታ ከንግድ ባንክ የሌላችሁን ብር ለወሰዳችሁ ተማሪዎች በሙሉ😁 የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን @NATIONALEXAMSRESULT
نمایش همه...
😁 47👍 12 1
Photo unavailableShow in Telegram
👍 36 8👎 3🔥 2👏 1
#repost የመውጫ ፈተና ከረቡዕ ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል። በዚህ ፈተና ወቅት ከተማሪዎች እና ከፈታኞች ምን እጠበቃል ? [ ከተፈታኞች የሚጠበቅ ] - ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ክፍላቸው ሲመጡ ማንኛውም አይነት ስልክ፣ ስማርት ሰዓት ፣ ታብሌት ፣ ላፕቶፕና ... ወዘተ ተመሳሳይ ኤክትሮኒክ ቁሳቁስ መያዝ በፍፁም የተከለከለ ነው።  (ይዞ የተገኘ ፈተናው /ውጤቱ ተሰርዞበት በቀጣይ ጊዜ እንዲቀመጥ ይደርጋል) - ፈተና ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃ በፊት መፈተኛ ክፍል መገኘት አለባቸው። - ተፈታኞች ለፈተና ሲመጡ ID መያዝ ያለባቸው ሲሆን User Name እና Password lower-case and upper-case ፊደላትን ለይተው በጥንቃቄ መያዝ አለባቸው። - ተፈታኞች ፈተና ከተጀመረ በኃላ ከ30 ደቂቃ በፊት ከፈተናው ክፍል መውጣት የለባቸውም። - ተፈታኞች ፤ ፈተናውን የሚያስፈትኑ መምህራን በሚያሳዩት ቦታ ብቻ መቀመጥ አለባቸው። - ሁሉም ተፈታኝ እንዲቀመጥ የተመደበበት የራሱ ኮምፒውተር ላይ ብቻ ተቀምጦ መክፈትና መጠቀም አለበት። - በፈተና ክፍል ውስጥ መነጋገርም ሆነ ከቦታ ቦታ መዘዋወር በፍፁም የተከለከለ ነው። እንዲሁም ማንኛውም ተፈታኝ ከጎኑ ያለውን ተማሪ ኮምፒውተር በፍፁም ማየት የለበትም። - ምንም ዓይነት ወረቀት ወደ መፈተኛ ክፍል ይዞ መምጣት አይቻልም። - ተፈታኞች በምንም አይነት ሁኔታ መኮርጅም ሆነ ማስኮርጅ ተግባር ላይ ቢሳተፉ እርምጃ ይወሰድባቸዋል። - ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ለፈተናው ፈታኝ መምህራን እና ለአስተባባሪዎች መታዘዝ ያለባቸው ሲሆን የፈተናው ደንብና ስርዓት ተገዢ መሆን ይጠበቅባቸዋል። NB. ሁሉም ተፈታኞች ወደ ፈተና መፈተኛ ክፍል ተፈትሸው እንዲገቡ የሚደረግ ሲሆን ማንኛውም ተፈታኝ ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በፍተሻ ወቅት ይሁን ሥርዓት ለማስያዝ በሚደረግ እንቅስቃሴ እንቅፋት ሆኖ ከተገኘ ከመፈተኛ አከባቢ እንዲገለል ተደርጎ በቀጣዩ የመውጫ ፈተና መስጫ ወቅት እንዲቀመጥ ይፈቀድለታል። [ ከፈታኝ መምህራን የሚጠበቅ ] - የተፈታኝ ተማሪዎችን ID በአግባቡ በማረጋገጥ ወደ ክፍል እንዲገቡ ማደረግ ይጠበቅባቸዋል። - ተፈታኝ ተማሪዎችን በሥም ዝርዝራቸው መሠረት ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል። - ፈታኝ መምራህን የተፈታኝ ተማሪዎችን አቴንዳንሰ ይወስዳሉ ፤ ተማሪዎችን ፊርማ ያስፈርማሉ። - በፈተና ክፍል ውስጥ ደምጽ እንዳይሰማ፣ ተማሪዎች ከቦታ ቦታ እንዳይዘዋወሩ ተገቢውን ቁጥጥር ማድረግ አለባቸው። - የፈተናው አጠቃለይ ሂደት በትኩረት መከታተል አለባቸው። - በህመም ምክንያት ተማሪዎች ከመተኛ ክፍል መውጣት ቢፈልጉ ከሱፐርቨዘር ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን እርዳታ ያደርጋሉ። - ተማሪዎች በጎናቸው ያለውን ሌላ ኮምፒውተር እንዳይመለከቱ መቆጣጠር አለባቸው። - ተማሪዎች ፈተናው ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በፊት እንዳይወጡ መቆጣጠር ይጠበቅባቸዋል። - ሲኮርጅ ወይም ሲያስኮርጅ የተገኘ ማንኛውም ተማሪ ከመፈተኛ ክፍል እንዲወጣ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። - ፈተናው ከጀመረ ከ15 ደቂቃ በኃላ የሚመጣ ተማሪ እንዲገባ ማድረግ የላባቸውም። - የፈተና አፈጻጸም ሪፖርት ለሱፐርቨዘር ማቅረብ ይጠብቅባቸዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ነው የሰበሰበው። ለመላው ተፈታኞች መልካም ፈተና ይሆን ዘንድ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይመኛል ! (መልዕክቱ በባለፈው ዓመት የፈተና ወቅት የተዘጋጀ እና በቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ላይ የተለጠፈ ነው) የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን @NATIONALEXAMSRESULT Click here for advertisement @studentsnewsadv35bot
نمایش همه...
👍 47 13
#ExitExam የ2016 ዓ/ም የመውጫ ፈተና ከረቡዕ የካቲት 6 ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል። ቲክቫህ ፤ ከዩኒቨርሲቲዎች ያገኘው የተሻሻለ የፈተናው መርሀ ግብር ከላይ ባለው ፋይል አያይዞታል። መርሀ ግብሩ እንደሚያሳየው ከሆነ በመጀመሪያው የፈተና ቀን የጤና ተማሪዎች ፈታናቸውን ይወስዳሉ። @tikvahuniversity
نمایش همه...
👍 11 6👎 1
#repost የመውጫ ፈተና ከረቡዕ ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል። በዚህ ፈተና ወቅት ከተማሪዎች እና ከፈታኞች ምን እጠበቃል ? [ ከተፈታኞች የሚጠበቅ ] - ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ክፍላቸው ሲመጡ ማንኛውም አይነት ስልክ፣ ስማርት ሰዓት ፣ ታብሌት ፣ ላፕቶፕና ... ወዘተ ተመሳሳይ ኤክትሮኒክ ቁሳቁስ መያዝ በፍፁም የተከለከለ ነው።  (ይዞ የተገኘ ፈተናው /ውጤቱ ተሰርዞበት በቀጣይ ጊዜ እንዲቀመጥ ይደርጋል) - ፈተና ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃ በፊት መፈተኛ ክፍል መገኘት አለባቸው። - ተፈታኞች ለፈተና ሲመጡ ID መያዝ ያለባቸው ሲሆን User Name እና Password lower-case and upper-case ፊደላትን ለይተው በጥንቃቄ መያዝ አለባቸው። - ተፈታኞች ፈተና ከተጀመረ በኃላ ከ30 ደቂቃ በፊት ከፈተናው ክፍል መውጣት የለባቸውም። - ተፈታኞች ፤ ፈተናውን የሚያስፈትኑ መምህራን በሚያሳዩት ቦታ ብቻ መቀመጥ አለባቸው። - ሁሉም ተፈታኝ እንዲቀመጥ የተመደበበት የራሱ ኮምፒውተር ላይ ብቻ ተቀምጦ መክፈትና መጠቀም አለበት። - በፈተና ክፍል ውስጥ መነጋገርም ሆነ ከቦታ ቦታ መዘዋወር በፍፁም የተከለከለ ነው። እንዲሁም ማንኛውም ተፈታኝ ከጎኑ ያለውን ተማሪ ኮምፒውተር በፍፁም ማየት የለበትም። - ምንም ዓይነት ወረቀት ወደ መፈተኛ ክፍል ይዞ መምጣት አይቻልም። - ተፈታኞች በምንም አይነት ሁኔታ መኮርጅም ሆነ ማስኮርጅ ተግባር ላይ ቢሳተፉ እርምጃ ይወሰድባቸዋል። - ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ለፈተናው ፈታኝ መምህራን እና ለአስተባባሪዎች መታዘዝ ያለባቸው ሲሆን የፈተናው ደንብና ስርዓት ተገዢ መሆን ይጠበቅባቸዋል። NB. ሁሉም ተፈታኞች ወደ ፈተና መፈተኛ ክፍል ተፈትሸው እንዲገቡ የሚደረግ ሲሆን ማንኛውም ተፈታኝ ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በፍተሻ ወቅት ይሁን ሥርዓት ለማስያዝ በሚደረግ እንቅስቃሴ እንቅፋት ሆኖ ከተገኘ ከመፈተኛ አከባቢ እንዲገለል ተደርጎ በቀጣዩ የመውጫ ፈተና መስጫ ወቅት እንዲቀመጥ ይፈቀድለታል። [ ከፈታኝ መምህራን የሚጠበቅ ] - የተፈታኝ ተማሪዎችን ID በአግባቡ በማረጋገጥ ወደ ክፍል እንዲገቡ ማደረግ ይጠበቅባቸዋል። - ተፈታኝ ተማሪዎችን በሥም ዝርዝራቸው መሠረት ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል። - ፈታኝ መምራህን የተፈታኝ ተማሪዎችን አቴንዳንሰ ይወስዳሉ ፤ ተማሪዎችን ፊርማ ያስፈርማሉ። - በፈተና ክፍል ውስጥ ደምጽ እንዳይሰማ፣ ተማሪዎች ከቦታ ቦታ እንዳይዘዋወሩ ተገቢውን ቁጥጥር ማድረግ አለባቸው። - የፈተናው አጠቃለይ ሂደት በትኩረት መከታተል አለባቸው። - በህመም ምክንያት ተማሪዎች ከመተኛ ክፍል መውጣት ቢፈልጉ ከሱፐርቨዘር ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን እርዳታ ያደርጋሉ። - ተማሪዎች በጎናቸው ያለውን ሌላ ኮምፒውተር እንዳይመለከቱ መቆጣጠር አለባቸው። - ተማሪዎች ፈተናው ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በፊት እንዳይወጡ መቆጣጠር ይጠበቅባቸዋል። - ሲኮርጅ ወይም ሲያስኮርጅ የተገኘ ማንኛውም ተማሪ ከመፈተኛ ክፍል እንዲወጣ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። - ፈተናው ከጀመረ ከ15 ደቂቃ በኃላ የሚመጣ ተማሪ እንዲገባ ማድረግ የላባቸውም። - የፈተና አፈጻጸም ሪፖርት ለሱፐርቨዘር ማቅረብ ይጠብቅባቸዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ነው የሰበሰበው። ለመላው ተፈታኞች መልካም ፈተና ይሆን ዘንድ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይመኛል ! (መልዕክቱ በባለፈው ዓመት የፈተና ወቅት የተዘጋጀ እና በቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ላይ የተለጠፈ ነው) @tikvahuniversity
نمایش همه...
👍 4
የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 4/2016 ዓ.ም ይጀምራል፡፡ (ቀን ጥር 30/2016 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 4/2016 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን @NATIONALEXAMSRESULT Click here for advertisement @studentsnewsadv35bot
نمایش همه...
👍 23😢 6👎 5 4
Photo unavailableShow in Telegram
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምርቁ የሆኑት ዶ/ር መቅደስ ዳባ የጤና ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል። ዶ/ር መቅደስ ከነርሰሪ እስከ 12ኛ ክፍል በአዲስ አበባ ምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ትምህርት ቤት ተምረዋል። የመጀመሪያ ዲግሪ የህክምና ትምህርታቸውን በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተከታተሉ ሲሆን የማህጸንና ጽንስ ስፔሻሊቲ ትምህርታቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሰርተዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ረዳት ፕሮፌሰር ሆነው በማስተማር እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው የህክምና ትምህርት ክፍል ኃላፊ ሆነው አገልግለዋል፡፡ ዶ/ር መቅደስ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል በጽንስና ማህጸን ትምህርት ክፍል ውስጥ የሠሩ ሲሆን የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ፕሬዝዳንት ሆነውም ሠርተዋል፡፡ ዶ/ር መቅደስ ዳባ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ውስጥ በኃላፊነት ያገለገሉ ሲሆን ላለፉት 18 ወራት በዓለም ጤና ድርጅት ዋና መ/ቤት ከፍተኛ አማካሪ በመሆን አገልግለዋል።
نمایش همه...
👍 32👏 6 4
#Update የ2016 ዓ.ም አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ ተራዝሟል። የመውጫ ፈተናው ከጥር 27 እስከ የካቲት 01/2016 ዓ.ም ይሰጣል ተብሎ እንደነበር አይዘነጋም። ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ ይፋ ባደረገው መርሐግብር ፈተናው ከየካቲት 06 እስከ 09/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ታውቋል። ለአዲስ ተፈታኞች ሞዴል ፈተና ከጥር 27 እስከ 30/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ቲክቫህ ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘው መረጃ ያሳያል። የተፈታኞች ዝርዝር ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ በቀጣይ ቀናት እንደሚላክም ተገልጿል። HU_GC https://t.me/+vajm7ZnKWQk3OGFk
نمایش همه...
👍 45 10
Photo unavailableShow in Telegram
🎉Good News for Ethiopian Undergraduate Program Students ! Study in USA! 🇺🇸 ⭐️ከፍተኛ ትምህርቶን በአሜሪካ ሀገር እየተከታተሉ የሚሰሩበት ትልቅ ዕድል ! ✅ No Prepayment ! ✨ Bachelor Degree ✈️ ⭐Fast ProcessQuality Service High Visa Ratio Limited Spot ! Take your spot early live your dream ! 🟡🟡Contact us : 🔵 @Gossa07 ☎️ +251935343325 / +393444355194 ✅ ቴሌግራም ገፅዓችንን መቀላቀል እንዳይረሱ 👇👇👇: @Ethiogenuine1 @Ethiogenuine1 📍 Address : Addis Ababa, 22, Tsega Business Center, 7th Floor, Office No - H04 . 🌐 Www.Ethio-Genuine-Consultancy.com
نمایش همه...
👍 8
መቱ ዩኒቨርሲቲ ተወካይ ፕሬዝዳንት ተመድቦለታል። የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ፣ ምርምር፣ ቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት በድሉ ተካ (ዶ/ር) ከጥር 20 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከያዙት ኃላፊነት በተጨማሪ የመቱ ዩኒቨርሲቲ ተወካይ ፕሬዝዳንት ሆነው እንዲሠሩ በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) መመደባቸው ታውቋል። ዩኒቨርሲቲውን ላለፉት አምስት ዓመታት በፕሬዝዳንትነት ሲያገለግሉ የቆዩት እንደገና አበበ (ዶ/ር) በፌደራል ደረጃ ለአመራርነት መመረጣቸውን ከዩኒቨርሲቲው የተገኘ መረጃ ያሳያል። የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን @NATIONALEXAMSRESULT Click here for advertisement @studentsnewsadv35bot
نمایش همه...
👍 10 2👎 1