cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

🇪🇹ኢትዮጵ🇪🇹

የዚህ ቻናል አላማ በተለያዩ በይነ መረብ የሚንሸራሸሩ መንፈሳዊ ይዘት ያላቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መረጃዎችን ማጋሪያ ነው። . . . . . . . . እንዲሁም  መንፈሳዊ የሆኑ አጫጭር ቪዲዮች ይለቀቁበታል። 🇪🇹ኢትዮጵ🇪🇹 @KIDUS017

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
Advertising posts
189مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

​​እንኳን ለታላቁ ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ #ልደት መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ ጸጋ ዘአብ ካህኑና እግዚእ ኃረያ ናቸው። እርሱ በክህነቱ እርሷ በደግነቷ በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል። በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው ቅዱስ ሚካኤል ጸጋ ዘአብን ከሞት እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል። በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል። ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24 ቀን በ1206 ዓ/ም ሲሆን የተወለዱት ደግሞ ታሕሳስ 24 ቀን በ1207 ዓ/ም ነው። በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል። ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል። #ዕድገት የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው "ፍሥሃ ጽዮን" ይሰኛል። ይሕንን ስም ይዘው አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል። በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል። በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል። ዲቁናም ከወቅቱ ዻዻስ አባ ጌርሎስ ተቀብለዋል። #መጠራት አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮስ ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ። የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ። "ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን። ከዚህ በሁዋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ። ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ። ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ ሰዓትን አላጠፉም። ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ። #አገልግሎት ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ። በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ። ያን ጊዜ ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት። 1ኛ. ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል። 2ኛው. ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር። ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ። ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን (ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል:: #ገዳማዊ ሕይወት ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል። እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል። እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት: በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26 ዓመታት አገልግለዋል። በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ (ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል። በተሰበረ እግራቸውም 6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል። #ስድስት_ክንፍ ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል። ጻድቁ ምድረ እሥራኤል የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር:: የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል። ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በሁዋላ ነው ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር። ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም። በገሃድ:- -በቤተ መቅደስ ብስራቱን -በቤተ ልሔም ልደቱን -በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን -በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን -በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር። የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ። በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን ወደ ሰማይ አሳረገቻቸው። #በዚያም :- -የብርሃን ዐይን ተቀብለው -6 ክንፍ አብቅለው -የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው -ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው -ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው -ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው -"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል። #ተአምራት የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው። ሙት አንስተዋል ድውያንን ፈውሰዋል አጋንንትን አሳደዋል እሳትን ጨብጠዋል በክንፍ በረዋል ደመናን ዙፋን አድርገዋል። ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል። በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል። በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና:: #ዕረፍት ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: እልፍ አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24 ቀን በ1306 ዓ/ም ዐርፈዋል። ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል። 10 ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል። 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...

ትግራይ ውስጥ ካህናትን የሚያከብር ሕዝብ ነው ያለው✝   ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ http://t.me/abagebrekidan http://t.me/abagebrekidan
نمایش همه...
🇪🇹ኢትዮጵ🇪🇹 @KIDUS017
نمایش همه...
✞አንቺ ነሽ ተስፋው✞ አንቺ ነሽ ተስፋው ለፍጥረት ኪዳነ ምሕረት የኛ እናት ዓለም ሁሉ በአንቺ ተፅናና ቃል ኪዳንሽ አስምሯልና (2x) ተስፋ ቆርጦ አዝኖ ለኖረ ልቡ በሀዘን ለተሰበረ መፅናናቱ ሆነሽለታል በኪዳንሽ ምሕረት አግኝቷል ስለዚህ ማርያም/ድንግል/ ሆይ እንወድሻለን(2x) ስምሽን ለልጅ ልጅ እንሳስባለን/እንናገራለን/(2x) አዝ====== በኪዳንሽ ለተማጸነ ሞት አለፈ ሕይወት ሆነለት የእርቃችን ሰነድ ነሽና ልጅስ ሰራን እንደገና ስለዚህ ማርያም/ድንግል/ ሆይ እንወድሻለን(2x) ስምሽን ለልጅ ልጅ እንሳስባለን/እንናገራለን/(2x) አዝ====== ትናንትና የደበዘዘው በኪዳንሽ ዛሬ ብሩህ ነው የታመነው የምሕረት ኪዳን ይፈውሳል ነፍስና ሥጋን ስለዚህ ማርያም/ድንግል/ ሆይ እንወድሻለን(2x) ስምሽን ለልጅ ልጅ እንሳስባለን/እንናገራለን/(2x) አዝ====== ለምርጦቹ መሐላ አድንኗል የማማለድ ፀጋን አድሏል እመቤቴ የአንቺስ ልዩ ነው የማለልሽ እርሱ ልጅሽ ነው ስለዚህ ማርያም/ድንግል/ ሆይ እንወድሻለን(2x) ስምሽን ለልጅ ልጅ እንሳስባለን/እንናገራለን/(2x) "አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት።" መዝ ፻፴፩፥፰ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇 •➢ ሼር // SHARE መዝሙር ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮ @ORTODOX_RINGTONES
نمایش همه...
እንኳን አደረሣችሁ፡፡ ዝም ብሎ በአፍ ኪዳነምሕረትን እወዳለሁ አይደለም፡፡ የጸጋ ስግዱ፡፡ ለዛሬም የኪዳነምሕረት የሚሆን የጸጋ የሚሰገድ ከታች በሚታየው ተዘጋጅቷል፡፡ የሰኔ ጎለጎታን አንብቡ በደንብ ዛሬ፡፡ #ጸባኦት_ይከተላችሁ @ORTODOX_RINGTONES
نمایش همه...
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞ ❖ ነሐሴ ፲፮ ❖ ✞✞✞ እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ የትንሳኤና የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞ +"+ ዕርገተ_ድንግል_ማርያም +"+ ➥ ይሕች ዕለት እጅጉን ታላቅና ክብርት ናት:: ምክንያቱም የድንግል ማርያም ሥጋዋ ተነስቶ ዐርጐባታልና:: ድንግል እመቤታችን ተነሳች: ዐረገች ስንል እንደ እንግዳ ደርሶ: እንደ ውሃ ፈሶ: ወይም በአጋጣሚ የተደረገ አይደለም:: ጥንቱን በአምላክ ልቡና ታስቦ: ሁዋላም ትንቢት ተነግሮለት ነው:: ታሪኩ: ነገሩ: ምሥጢሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ: ➟ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቅድመ ዓለም በአምላክ ልቡና ታስባ ትኖር ነበር:: ከነገር ሁሉ በፊት እግዚአብሔር እናቱን ያውቃት ነበር::ዓለም ተፈጥሮ አዳምና ሔዋን ስተው መርገመ ሥጋና መርገመ ነፍስ አግኝቷቸው በኃዘን ንስሃ ቢገቡ "እትወለድ እም ወለተ ወለትከ - ከ5 ቀን ተኩል (5500 ዘመናት) በሁዋላ ካንተ ባሕርይ ከምትገኝ ንጽሕት_ዘር ተወልጄ አድንሃለሁ" ብሎ ተስፋ ድኅነት ሰጠው:: ከአዳም አንስቶ ለ5500 ዓመታት አበው ነቢያትና ካህናት ስለ ድንግል ማርያም ብዙ ሐረገ ትንቢቶችን ተናገሩ:: መዳኛቸውን ሱባኤ ቆጠሩላት:: ምሳሌም መሰሉላት:: ከሩቅ ዘመን ሁነውም ሊያገኟት እየተመኙ እጅ ነሷት:: "እምርሑቅሰ ርእይዋ: ወተአምኅዋ" እንዲል:: +"+ የድንግል ማርያም ሐረገ ትውልድ +"+ *ከአዳም በሴት *ከያሬድ በሔኖክ *ከኖኅ በሴም *ከአብርሃም በይስሐቅ *ከያዕቆብ በይሁዳና በሌዊ *ከይሁዳ በእሴይ: በዳዊት: በሰሎሞንና በሕዝቅያስ ወርዳ ከኢያቄም ትደርሳለች:: ¤ከሌዊ ደግሞ *በአሮን: *አልዓዛር: *ፊንሐስ *ቴክታና በጥሪቃ አድርጋ ከሐና ትደርሳለች:: ➥ አባታችን አዳም ከገነት በወጣ በ5,485 ዓመት ወላዲተ_አምላክ ንጽሕና ሳይጐድልባት ኃጢአት ሳያገኛት ጥንተ አብሶ ሳይደርስባት ከደጋጉ ኢያቄም_ወሐና ትወለዳለች:: (ኢሳ. 1:9, መኃ. 4:7) "ወኢረኩሰት በምንትኒ እምዘፈጠራ" እንዳለ (ቅዱስ_ቴዎዶጦስ_ዘዕንቆራ) ➝ ከዚያም ከእናት ከአባቷ ቤት ለ3 ዓመታት ቆይታ ወደ ቤተ_መቅደስ ትገባለች:: በቤተ መቅደስም ለ12 ዓመታት ፈጣሪዋን እግዚአብሔርን እያመሰገነችና እያገለገለች እርሷን ደግሞ መላእክተ_ብርሃን እያገለገሏት ሕብስት ሰማያዊ ጽዋዕ ሰማያዊ እየመገቧት ኑራለች:: 15 ዓመት በሞላት ጊዜ ጻድቅ አረጋዊ_ዮሴፍ ያገለግላት ዘንድ ወደ ቤቱ ወሰዳት:: ➥ በዚያም መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ዜና*ድኅነትን ነግሯት አካላዊ ቃልን በማሕጸንዋ ጸነሰችው:: ነደ እሳትን ተሸከመችው*ቻለችው:: "ጾርኪ ዘኢይትጸወር: ወአግመርኪ ዘኢይትገመር" እንዳለ:: (ሊቁ_ቅዱስ_ኤፍሬም ለብሐዊ) ➟ ወልደ እግዚአብሔርን ለ9 ወራት ከ5 ቀናት ጸንሳ እንበለ ተፈትሆ (በድንግልና) ወለደችው:: (ኢሳ. 7:14) "#ኢየሱስ" ብላ ስም አውጥታለት በናዝሬት ገሊላ ለ2 ዓመታት ቆዩ:: ➥ አርዌ ሔሮድስ "እገድላለሁ" ብሎ በተሳበት ወቅትም ልጇን አዝላ በረሃብ እና በጥም በላበትና በድካም በዕንባና በኃዘን ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት ከገሊላ እስከ ኢትዮዽያ ተሰዳለች:: ልጇ ጌታችን 5 ዓመት ከ6 ወር ሲሆነው ለርሷ ለድንግል ደግሞ 21 ዓመት ከ3 ወር ሲሆናት ወደ ናዝሬት ተመለሱ:: ➝ በናዝሬትም ለ24 ዓመታት ከ6 ወራት ልጇን ክርስቶስን እያሳደገች ነዳያንን እያሰበ ኑራለች::እርሷ 45 ዓመትልጇ 30 ዓመት ሲሆናቸው ጌታችን ተጠምቆ በጉባኤ ትምሕርት ተአምራት ጀመረ::ለ3 ዓመታት ከ3 ወራትም ከዋለበት እየዋለች ካደረበትም እያደረች ትምሕርቱን ሰማች:: ➥ የማዳን ቀኑ ደርሶ ልጇ ክርስቶስ ሲሰቀልም የመጨረሻውን ፍጹም ሐዘን አስተናገደች:: አንጀቷ በኃዘን ተቃጠለ:: በነፍሷም ሰይፍ አለፈ:: (ሉቃ. 2:35) ጌታ በተነሳ ጊዜም ከፍጥረት ሁሉ ቀድማ ትንሳኤውን አየች:: ለ40 ቀናትም ሳትለይ ከልጇ ጋር ቆየች:: ➟ ከልጇ ዕርገት በሁዋላ በጽርሐ_ጽዮን ሐዋርያትን ሰብስባ ለጸጋ መንፈስ ቅዱስ አበቃች:: በጽርሐ ጽዮን ከአደራ ልጇ ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ለ15 ዓመታት ኖረች::በእነዚህ ዓመታት ሥራ ሳትፈታ ስለ ኃጥአን ስትማልድ: ቃል ኪዳንን ከልጇ ስትቀበል: ሐዋርያትን ስታጽናና ምሥጢርም ስትገልጽላቸው ኑራለች:: ➥ ዕድሜዋ 64 በደረሰ ጊዜ ጥር 21 ቀን መድኃኒታችን አእላፍ ቅዱሳንን አስከትሎ መጣ:: ኢየሩሳሌምን ጨነቃት:: አካባቢውም በፈውስ ተሞላ:: በዓለም ላይም በጐ መዓዛ ወረደ:: እመ ብርሃን ለፍጡር ከዚያ በፊት ባልተደረገ ለዘለዓለምም ለማንም በማይደረግ ሞገስ ክብርና ተአምራት ዐረፈች:: ሞቷ ብዙዎችን አስደንቁአል:: "ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ" እንዲል:: ➟ ከዚህ በሁዋላ መላእክት እየዘመሩ ሐዋርያቱም እያለቀሱ ወደ ጌቴሴማኒ በአጐበር ሥጋዋን ጋርደው ወሰዱ:: ይሕንን ሊቃውንት:-"ሐራ ሰማይ ብዙኃን እለ አልቦሙ ሐሳበ እንዘ ይዜምሩ ቅድሜኪ ወመንገለ ድኅሬኪ ካዕበ ማርያም ሞትኪ ይመስል ከብካበ" ሲሉ ይገልጡታል:: ➥ በወቅቱ ግን አይሁድ በክፋት ሥጋዋን እናቃጥል ስላሉ ቅዱስ_ገብርኤል (ጠባቂ መልአክ ነው) እነርሱን ቀጥቶ እርሷን ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ወስዶ በዕጸ ሕይወት ሥር አኑሯታል::በዚያም መላእክት እያመሰገኗት ለ205 ቀናት ቆይታለች:: ➟ ቅዱስ_ዮሐንስ መጥቶ ለሐዋርያቱ ክብረ ድንግልን ቢነግራቸው በጐ ቅንአት ቀንተው በነሐሴ 1 ሱባኤ ጀመሩ:: 2ኛው ሱባኤ ሲጠናቀቅም ጌታ የድንግል ማርያምን ንጹሕ_ሥጋ ሰጣቸው:: እየዘመሩም በጌሴማኒ ቀብረዋታል:: ➥ በ3ኛው ቀን (ነሐሴ 16) እንደ ልጇ ባለ ትንሳኤ ተነስታ ዐርጋለች:: ትንሳኤዋንና ዕርገቷንም ደጉ ሐዋርያ ቅዱስ_ቶማስ አይቶ: መግነዟን ተቀብሏል:: ሐዋርያቱም መግነዟን ለበረከት ተካፍለው: እንደ ገና በዓመቱ ነሐሴ 1 ቀን ሱባኤ ገቡ:: ➥ ለ2 ሳምንታት ቆይተው በዚህች ቀን ሁሉንም ወደ ሰማይ አወጣቸው:: በፍጡር አንደበት ተከናውኖ የማይነገር ተድላ ደስታና ምሥጢርንም አዩ:: ጌታ ራሱ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው:: የበዓሉን ቃል ኪዳን ሰምተው: ከድንግል ተባርከው ወደ ደብረ_ዘይት ተመልሰዋል:: ➣ ጽንዕት በድንግልናሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኚልን:: አእምሮውን ለብዎውን*ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን:: +"+ ቅዱስ_ጊጋር_ሶርያዊ +"+ ➝ ይሕ ቅዱስ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን የሶርያ መስፍን የነበረ ሲሆን ክርስቶስ በተወለደ ጊዜ ሰምቷል:: እመ ብርሃን ለስደት ስትወጣ በመጀመሪያ የሔደችው ወደ ሊባኖስ ተራሮች ነው::መስፍኑ_ጊጋር ነበርና እርሱም የአምላክ እናትነቷን አምኖ አክብሮ አስተናግዷታል:: ➥ ሔሮድስም ይሕንን ሲሰማ ጦር አስከትቶ ወደ ጊጋር ሔደ:: መስፍኑ ጊጋር ሔሮድስን እንደማይችለው ሲረዳ ድንግል ማርያምን ወደ ግብጽ ሸሽጐ አሸሻት::ሔሮድስንም ፊት ለፊት ተገናኘው:: ከአቅሙ በላይ ስለነበረም በወታደሮች ተማርኮ ወደ ሔሮድስ ቀረበ:: ➝ እመቤታችንንና ልጇን "አምጣ" ቢለው "አልናገርም" አለው:: በዚህ ምክንያት አካሉን ከብዙ ቆራርጦ ገድሎታል::በቤተ ክርስቲያን ታሪክም ስለ_እመ_አምላክ_ፍቅር የተሰዋ የመጀመሪያው ሰው ተብሎ ይታወቃል:: ጌታም ስለ ሃይማኖቱ ፍቅር ሰማዕትነቱ 3 አክሊላትን ሰጥቶታል::
نمایش همه...
አረሳውም ያንን እለት አልዘነጋው ያንን ደግነት እናቴ ሆይ ምልሽ ኪዳነምህረት እምዬ ሆይ ምልሽ ኪዳነምህረት ስላለኝ ነው ምክንያት 🙏🙏🙏🙏
نمایش همه...
ዝዋይ ኪዳነምህረት
نمایش همه...