cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ማህበረ ተዋህዶ

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን። ይህ ቻናል #መንፈሳዊ_መዝሙሮች #መንፈሳዊ_ጽሑፍ #ቅዱሳንን_እንወቅ #የታላላቅ_መንፈሳዊ_ጉባኤ_ማስታወቂያ #የመንፈሳዊ_ጉዞ_ማስታወቂያ ስለሚቀርብበት ተቀላቀሉን የጉዞ ማስታወቂያ በቻናሉ እንዲተዋወቅላቹ የምትፈልጉ ከታች ባለው አካውንት ይላኩልን #ሐሳብ_አስተያየት_ካላቹ ☞ @Mahletay11

نمایش بیشتر
Advertising posts
286مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
+230 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Repost from N/a
ታላቅ የንግስ በአል ጥሪ በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ካቴድራል የዛሬ 32 ዓመት በ1983ዓ.ም ግንቦት 27 በዘመኑ በነበረው የመንግስት ለውጥ ምክንያት በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ/ክ አካባቢ የነበረው የጥይት ማምረቻ ካምፕ ፈንድቶ ጥይቶቹ ወደ ተለያየ አቅጣጫ መዝነብ ጀመሩ ሆኖም የአካባቢው ምዕመንም፣ ኢ አማንያንም ወደ ቅዱስ ያሬድ ቤ/ክ በመግባት ይህንን መከራ ምንም ሰው ሳይጎዳ አንድ ሰው እንኳን ሳይሞት ሕንጻ ቤተክርስቲያኑን ምንም ሳይሆን ይህንን አሰቃቂ እና ከባድ መከራ ሌላ ቦታ እየተፈናጠረ የሰው ነብስ ቢያጠፋም አቅራቢያው ባለው በቅዱስ ያሬድ ካቴድራል ገብተው የተጠለሉት ሕዝቦች ምንም ሳይጎዱ ተርፈዋል ስለሆነም ይህንን ያደረገው << እምቶነ እሳት ዘይነድድ አንገፈነ>> ከሚነደው እሳት ያወጣን አምላከ ቅዱስ ያሬድ መድኃኔአለም በታላቁና በታሪካዊው ብርቅዬ በሆነው በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ካቴድራል የፊታችን ግንቦት 27 በእለተ እሁድ የዛሬ 32 አመት የተፈጸመውን በማሰብ ታቦተ ሕጉ ከመንበረ ክብሩ ወጥቶ መድኃኔአለም አምላካችን መድኃኔአለም አባታችን እኛ ልጆቹን ይባርከናል በእለቱም ብፁአን አበው ሊቃነ ጳጳሳት መምህነ ወንጌል መዘምራን ይገኛሉ አድራሻ፦ ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል ፍላወር በሚወስደው መንገድ
نمایش همه...
መጋቢት ፳፮ [ 27 ] መድኃኔዓለም (ጥንተ_ስቅለቱ) መጋቢት ሃያ ሰባት በዚችም ቀን የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዓለም ድኅነት በሥጋ ተሰቀለ። ፈጣሪዋ በዕንጨት መስቀል ላይ ተዘርግቶ ተሰቅሎ በአየችው ጊዜ ፀሐይ ጨለመች እርሱም ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም የነሣትን ለባዊት ነባቢት የሆነች ነፍሱን ከሥጋው ለያት ሐዋርያ ጴጥሮስ በሥጋ ምውት ሲሆን በመለኮት ሕያው ነው እንዳለ ነፍሱ ከመለኮት ሳትለይ ከሥጋ ተለየች በዚያ ጊዜ ሥጋ ከመለኮት ሳትለይ በዕንጨት መስቀል ላይ ተሰቅሎ ነበር። እንዲሁም ነፍስ ከመለኮት ጋራ አንድ ሁና እሥረኞች ነፍሳትን ትፈታቸው ዘንድ ወደሲኦል ወረደች። መድኃኔዓለም ክርስቶስ ስለ ዓለም ሁሉ ድኅነት በሥጋ ተሰቅሏልና ሞቱን በአንክሮ እናዘክር ዘንድ የልቡናችን ዐይን ወደ ቀራንዮ እናንሳ! እነሆ ክፉዎች አይሁድ ሰይጣን ልባቸውን አስቶታልና እንደ ወረንጦና እንደ ወስፌ እንደመርፌም ያለ 300 እሾህ ያለው ስረወጽ አድርገው አክሊል ሠርተው ከፍላት አግብተው በጉጠት አንስተው ‹ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሥ ነህ ዘውድ ይገባሃል› ብለው በራሱ ላይ ደፉበት፡፡ ለአክሊለ ሦኩም 73 ስቁረት ነበረው፡፡ እራሳቸው እንደ መሮ፣ ወርዳቸው እንደ ሞረድ 4 ማዕዘን አሠርተው ቁመታቸውን ክንድ ከስንዝር፣ ስለታቸውን እንደ ወስፌ አድርገው 73 ችንካር ሠርተው በ73ቱ ስቁረት አግብተው በጌታችን በራሱ ላይ ቢመቱበት ሥጋ ለሥጋ ገብቶ መሐል ልቡን ወጋው፡፡ አክሊለ ሦኩን በራሱ ላይ አድርገው ሲያበቁ ከቤት ወደ አደባባይ እያመላለሱ ‹‹ንጉሥ ሆይ!...›› እያሉ ምራቃቸውን እየተፉበት ተዘባበቱበት፡፡ መስቀል አሸክመው ከሊቶስጥራ እስከ ቀራኒዮ ድረስ እያዳፉ ሲወስዱት 136 ጊዜ በምድር ላይ ጣሉት፡፡ ከኋላ ያሉት ‹‹ፍጠን›› እያሉ ገፍትረው ይጥሉታል፣ ከፊት ያሉት ደግሞ ‹‹ምን ያስቸኩልሃል?›› እያሉ መልሰው ገፍትረው ይጥሉታል፡፡ ከዚህ በኋላ ክፉዎች አይሁድ ቁመታቸውን ክንድ ከስንዝር ስለታቸው ደግሞ እንደ ወስፌ የሆኑ 5 ችንካሮችን ሠርተው ሳዶር በሚባለው ችንካር ቀኝ እጁን፣ በአላዶር ግራ እጁን፣ በዳናት ሁለት እግሮቹን፣ በአዴራ መሐል ልቡንና በሮዳስ ደረቱን ቸንክረው የአዳም ራስ ቅል ባለበት ቀራኒዮ አደባባይ ላይ ሰቅለውታል፡፡ ክፉዎች አይሁድ መድኃኔዓለም ክርስቶስን እንደያዙት የኋሊት አስረው አፍንጫውን 25 ጊዜ ቢመቱት ደሙ በመሬት ላይ እንደ ውኃ ፈሰሰ፡፡ ከጌቴሴማኒ እስከ ሐና ቤት ድረስ አስረው የፊተኞቹ ሲጎትቱት የኋለኞቹ እየለቀቁት የኋለኞቹም በተራቸው ሲጎትቱት የፊተኞቹ ይለቁታል፡፤ እንዲህ እያደረጉ 65 ጊዜ ከመሬት ጋር አጋጭተውታል፡፡ ሳውል በእግሩ ሲረግጠው ጌታችን ‹‹መመለስህ ላይቀር ለምን ትረግጠኛለህ?›› ቢለው ስለዚህ ንግግርህ ብሎ ሳውል 440 ጊዜ አስገረፈው፡፡ ክፉዎች አይሁድ መድኃኒታችንን በሁለት ግንዶች መካከል አድርገው 65 ጊዜ ከግንዱ ጋር አጋጩት፡፡ ቀያፋ በሚመረምረው ጊዜ ጌታችን ‹‹አምላነቴን አንተው ራስህ ተናገርኽ›› ቢለው አይሁድ በእጃቸው ሲመቱት እጃቸውን ቢያማቸው ድንጋይ ጨብጠው 120 ጊዜ ፊቱን ጸፉት፡፡ አይሁድ ወደ ጲላጦስ ዘንድ ሲወስዱት ‹‹ምናልባት ጲላጦስ ባይፈርድበት እንኳ እንዳይቆጨን›› ብለው 305 ጊዜ በሽመል ደብድበውታል፡፡ በአምላክነቱ ቻለው እንጂ የአንዱ ምት ብቻ በገደለው ነበር፡፡ በርባን የይሁዳ የሚስቱ ወንድም (አማቹ) ስለነበር እርሱ እንደፊታለትም ከዋጋው ከ30ው ብር ጋር አብሮ ተደራድሮበት ነበር፡፡ ሰይጣን ልባቸውን ለክፋት ያስጨከናቸው ክፉዎች አይሁድ በጲላጦስ አደባባይ የጌታችንን ፂሙን 80 ጊዜ ነጭተውታል፡፡ ጲላጦስ እንደ ሕጋቸው 41 ብቻ ገርፈው እንዲለቁት ቢያዝም ክፉዎች አይሁድ ግን ጌታችንን ሲገርፉት ‹‹አሠቃቂ ግርፋቱን አይተን ልባችን እንዳይራራ›› ብለው ሰንጠረዥ ገበጣ ሰርተው ሲጫወቱ አንዱ ተነስቶ እስከ 60 እና 70 ድረስ ይገርፍና ሲደክመው ‹‹ቆጠራችሁን?›› ብሎ ይጠይቃል፡፡ ‹‹አልቆጠርንም›› ሲሉት ከድካሙ የተነሣ ‹‹እኔው ልግረፍ እንደገና እኔው ልቁጠር›› ብሎ ትቶት ሲቀመጥ ሌላኛው ይነሣና እንደዛኛው ሁሉ በተራው 60 እና 70 ይገርፈዋል፡፡ ሁሉም እንዲህ እያሳሳቱ የራሳቸውን ሕግ እየተላለፉ አይሁድ ጌታችንን ሥጋው አልቆ አጥንቱ እንደበረዶ ነጭ ሆኖ እስኪታይ ድረስ 6666 ጊዜ ጽኑ ግርፋትን ገረፉት፡፡ በእነዚህ ሁሉ ግርፋቱ ወቅት 366 ጊዜ ሥጋው ተቆርሶ መሬት ላይ ወድቋል፡፡ ክፍል 2 ይቀጥላል....
نمایش همه...
ብፁዕ ዶ/ር አቡነ አረጋዊ ዐረፉ ሐምሌ 9 ቀን 2009 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አንብሮተ ዕድ የሾሙት ጳጳሳት 14 ኤጲስ ቆጶሳት መካከል አንዱ የሆኑት በቀድሞ ስማቸው አባ ኃይለማርያም መለሰ ዶ/ር በጵጵስና ስማቸው ብፁዕ አቡነ አረጋዊ ዶ/ር የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት እና የውጪ ግንኙነት መምሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋና የጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። ብፁዕነታቸው ለረጅም ጊዜ ከሀገር ውጪና በሀገር ውስጥ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሊሻላቸው ሳይችል ቀርቶ ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ተለይተዋል። በረከታቸው ይደርብን።
نمایش همه...
የስልጣነ ክህነት ቅብብሎሽ(Apostolic Succession) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከጌታ ደቀመዝሙር ወንጌላዊው ማርቆስ ጀምሮ ያልተቋረጠ የስልጣነ ክህነት ቅብብሎሽ አላት። ያልተቋረጠው የእስክንድርያው መንበረ ማርቆስ ስልጣነ ክህነት ቅብብሎሽ እንደሚከተለው ነው: 1. ማርቆስ 2. አንያኖስ 3. ሜልያስ 4. ክርዳኑ 5. አምብርዮስ 6. ዮስጦስ 7. አውማንዮስ 8. መርክያኖስ 9. ክላውያኖስ 10. አክርጵያኖስ 11. ዮልዮስ 12. ድሜጥሮስ 13. ያሮክላ (ሔራክልስ) 14. ዲዮናስዮስ 15. መክሲሞስ 16. ቴዎናስ 17. ጴጥሮስ (ተፍጻሜተ ሰማዕት) 18. አኪላስ 19. እለእስክንድሮስ 20. አትናቴዎስ 21. ጴጥሮስ 2ኛ 22. ጢሞቴዎስ 23. ቴዎፍሎስ 24. ቄርሎስ 25. ዲዮስቆሮስ 26. ጢሞቴዎስ 2ኛ 27. ጴጥሮስ 3ኛ 28. አትናቴዎስ 2ኛ 29. ዮሐንስ 30. ዮሐንስ 2ኛ 31. ዲዮስቆሮስ 2ኛ 32. ጢሞቴዎስ 3ኛ 33. ቴዎዶስዮስ (ቴውዳስስ) 34. ጴጥሮስ 4ኛ 35. ድምያኖስ 36. አንስጣስዮስ 37. አንድራኒቆስ 38. ብንያሚን 39. ያቃቱ (አጋቶን) 40. ዮሐንስ 3ኛ 41. ይስሐቅ 42. ስምዖን 43. እለእስክንድሮስ 2ኛ 44. ቆዝሞስ 45. ቴዎድሮስ 46. ካኤል (ሚካኤል) 47. ሚናስ 48. ዮሐንስ 4ኛ 49. ማርቆስ 2ኛ 50. ያዕቆብ 1ኛ 51. ስምዖን 2ኛ 52. ዮሳብ 1ኛ (ዮሴፍ) 53. ካኤል (ሚካኤል) 2ኛ 54. ቆዝሞስ 2ኛ 55. ስንትዮ 1ኛ 56. ሚካኤል 1ኛ 57. ገብርኤል 1ኛ 58. ቆዝሞስ 3ኛ 59. መቃርዮስ 1ኛ 60. ታውፋኔዎስ 61. ሚናስ 2ኛ 62. አብርሃም 63. ፊላታዎስ 64. ዘካርያስ 65. ስንትዩ 2ኛ 66. ክርስቶዶሉ (ገብረ ክርስቶስ) 67. ቄርሎስ 2ኛ (ጌርሎስ) 68. ሚካኤል 2ኛ 69. መቃርዮስ 2ኛ (መቃርስ) 70. ገብርኤል 2ኛ 71. ሚካኤል 3ኛ 72. ዮሐንስ 5ኛ 73. ማርቆስ 3ኛ 74. ዮሐንስ 6ኛ 75. ቄርሎስ 3ኛ 76. አትናቴዎስ 3ኛ 77. ገብርኤል 3ኛ 78. ዮሐንስ 7ኛ 79. ታውዳስዮስ 2ኛ 80. ዮሐንስ 8ኛ 81. ዮሐንስ 9ኛ 82. ብንያሚን 2ኛ 83. ጴጥሮስ 5ኛ 84. ማርቆስ 4ኛ 85. ዮሐንስ 86. ገብርኤል 4ኛ 87. ማቴዎስ 1ኛ 88. ዮሐንስ 5ኛ 89. ዮሐንስ 11ኛ 90. ማቴዎስ 2ኛ 91. ገብርኤል 6ኛ 92. ሚካኤል 4ኛ 93. ዮሐንስ 12ኛ 94. ዮሐንስ 13ኛ 95. ገብርኤል 7ኛ 96. ዮሐንስ 14ኛ 97. ገብርኤል 8ኛ 98. ማርቆስ 5ኛ 99. ዮሐንስ 15ኛ 100. ማቴዎስ 3ኛ 101. ማርቆስ 6ኛ 102. ማቴዎስ 4ኛ 103. ዮሐንስ 16ኛ 104. ጴጥሮስ 6ኛ 105. ዮሐንስ 17ኛ 106. ማርቆስ 7ኛ 107. ዮሐንስ 18ኛ 108. ማርቆስ 8ኛ 109. ጴጥሮስ 7ኛ 110. ቄርሎስ 4ኛ 111. ጴጥሮስ 8ኛ 112. ቄርሎስ 5ኛ 113. ዮሐንስ 19ኛ 114. መቃርዮስ 3ኝእ 115. ዮሳብ (ዮሴፍ) 2ኛ 116. ቄርሎስ 6ኛ 117. ባሲልዮስ 118. ቴዎፍሎስ 119. ተክለሃይማኖት 120. መርቆሬዎስ 121. ጳውሎስ 122. ማትያስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሐዋርያዊት ናት! ዮሐንስ 10 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ወደ በጎች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚወጣ እርሱ ሌባ ወንበዴም ነው፤ ² በበሩ የሚገባ ግን የበጎች እረኛ ነው። አንዲት ቤተክርስቲያን አንድ ሲኖዶስ አንድ መንበር አንድ ፓትርያርክ
نمایش همه...
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ደብረ ዘይት (የዐቢይ ጾም አምስተኛ እሑድ) የዕለተ ሰንበት መዝሙር፣ እንዘ ይነብር እግዚዕነ ..................... ምስባክ፡ መዝ ፵፱፥፫ እግዚአብሔርሰ ገሃደ ይመጽእ ወአምላክነሂ ኢያረምም እሳት ይነድድ ቅድሜሁ ትርጒም፦ እግዚአብሔር በግልጥ ይመጣል አምላካችን ዝም አይልም እሳት በፊቱ ይነዳል ………………….. መልእክታት 👉 1ኛ ተሰ 4፡13-ፍፃሜው 👉 2ጴጥ 3፡7-15 👉 ግብ ሐዋ 24፡1-22 ወንጌል 👉 ማቴ ፳፬፥፩ -፴፮ …………………. የሚቀደሰው ቅዳሴ 👉ቅዳሴ ዘአትናቴዎስ (አሰም ለክሙ) ጾሙን ጾመ በረከት ያድርግልን!
نمایش همه...
ጊዮርጊስ ሆይ ከእኛ ወገን ነህን? ወደ አድዋ ከዘመተው ሕዝብ አብዛኛው ባዶ እግሩን ነበር:: ዳዊት ጎልያድን ሊዋጋ ሲወጣ ከያዛት በትር በቀር አብዛኛው ሰው መሣሪያ አልታጠቀም:: አብዛኛው ዘማች ባዶ እጁን የዘመተው ሁለት ነገር አስቦ ነው:: መሣሪያ ባይኖረውም በውጊያው መካከል ከጠላት ጦር መሣሪያ ነጥቄ እዋጋለሁ አለዚያም ከሚወድቁት ላይ መሣሪያ አንሥቼ እዋጋለሁ ብሎ ነበር:: በውጊያው ታንክ በጎራዴ እስከመማረክ ያደረሳቸውም ይህ ቆራጥነታቸው ነበር:: ለመንፈሳዊ ጥንካሬያቸው ደግሞ ምሥጢሩ አብራ የዘመተችው የቤተ ክርስቲያን ጸሎት እና ንጉሡ በድንግል ማርያም ስም ምለው የሠጡት አደራ ነበር:: ለተገፉ የሚቆመው ሰማዕቱ ጊዮርጊስም በግፍ ባሕር አቁዋርጠው በደሃ ሕዝብ ላይ እሳት ከሚያዘንቡት ከአባቱ ዘመዶች ከሮማዊያን ጋር ሳይሆን እንደ ዳዊት በትር ይዘው በእግዚአብሔር ስም ከወጡት ባለማተቦች ጋር በምልጃው ተሰልፎ ዋለ:: በዚያች ዕለት አንድ ጣሊያናዊ ቅዱስ ጊዮርጊስን አግኝቶ ኢያሱ ቅዱስ ሚካኤልን እንደጠየቀው "ከእኛ ወገን ነህ ወይንስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህ? " ብሎ ቢጠይቀው ኖሮ "እኔ አሁን ከእግዚአብሔር ተልኬ መጥቻለሁ ይልቅስ የቆምክባት መሬት ኢትዮጵያ የተቀደሰች ናትና ጫማህን ከእግርህ አውልቅ" ባለው ነበር:: የዐድዋ ዘማቾች ጾመኞች ነበሩ:: እንግሊዝም ጣሊያንም ሰይጣን ይመስል ኢትዮጵያን የተዋጉአት በዐቢይ ጾም ነበር:: "ወድቀህ ብትሰግድልኝ መንገድና ፎቅ እሰራልሃለሁ" ያለንን ጣሊያን አባቶቻችን "ሒድ አንተ ጣሊያን የራስህን እንጂ የእኔን አታስብምና" ብለው ድል ነሡት:: ዘማቾቹ የምግብ እጥረት ቢኖርም እንኩዋን ጾሙን ትተን ካልበላን አላሉም:: ድንገት መሞቴ አይቀር ብበላ ይሻለኛል ሳይሉ ተዋግተው ድል ተቀዳጁ:: እኛ በሰላም ጊዜ የምንተወውን ጾም እነርሱ በጦርነት ላይም ሆነው አልተዉትም:: በዚያ ድል  ሀገሪቱ ለዐርባ ዓመት ከጦርነት ስታርፍ ለዕድሜ ዘመንዋ ደግሞ ከቅኝ ግዛት ዐረፈች:: ቅኝ ግዛት ብንገዛ ኖሮ ደሃ አንሆንም ነበር የሚል ሰው አይጠፋም:: ይህንን አሳብ የብዙ አፍሪካውያን ሀገራት ጆሮ አይስማው:: ዛሬ ነጻ ከወጡም በኁዋላ በባርነት ሕሊና የሚሰቃዩ ብዙ ናቸው:: ብዙ በፈረንሳይ የተገዙ የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት ዛሬም ድረስ በአደራ አስተዳደር በፈረንሳይ በእጅ አዙር ይተዳደራሉ:: በተባበሩት መንግሥታት ሳይቀር ቅኝ ገዢዎቻቸውን ተወካይ ሁነኝ ብለው የሚልኩ ሀገራት አሉ:: ዛሬም ድረስ በአንዳንድ አፍሪካ ሀገራት ጥቁሮች ሊስተናገዱ በተሰለፉበት ሱፐር ማርኬት አንድ ነጭ ከመጣ ሰልፍ ሳይይዝ ቅድሚያ ይስተናገዳል:: (በዓይኔ ያየሁት ነው) ዛሬም ድረስ ብዙ አፍሪካዊያን ጥቁር በአስተሳሰብ ከነጭ በታች ነው ብለው ያምናሉ:: በዜኖ ፎቢያ የገዛ ወንድሞቻቸው አፍሪካውያንን የሚያሰቃዩ ደቡብ አፍሪካውያን ነጭ ሰፈር ግን ዝር አይሉም:: ሂሳብ ስታሰላ ሲያዩህ እንኩዋን አንተ ጥቁር ሆነህ እንዴት ያለ ካልኩሌተር መደመር ቻልክ የሚሉ ሰዎች ተፈጥረዋል:: በአውሮፓ በአሜሪካ ተወልደው አድገው ስኬታማ የሆኑት ጥቁሮች እንኩዋን የቤተሰብ ስማቸው ላይ አያቶቻቸውን በባርነት የገዛው ነጭ ገዥ ስም አብሮ ስለሚለጠፍ የዕድሜ ልክ የበታችነት ይሰማቸዋል:: አባቶቻችን ከብዙ ጣጣ አድነውናል አሁን ራሳችን የምንፈጥረውን ችግር ቢያዩ ለማመን የሚቸገሩ የሚሆኑትም ዘር ሳይለዩ አብረው የተዋደቁት ጀግኖች ናቸው:: ቅዱስ ጊዮርጊስ ዛሬም ቤሩታዊት ኢትዮጵያን ከዘረኝነትና ጥላቻ ደራጎን ይታደጋት ዘንድ የምንማጸንበት ጊዜ ነው:: ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
نمایش همه...
ይህንን ያውቃሉ? ብጹዕ አቡነ ዼጥሮስ (ዶክተር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ በአውሮፓና አሜሪካ ከሚገኙ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በኢኮኖሚክስ፣ በሳይኮሎጂ እና ሶሾሎጂ የትምህርት መስኮች ሶስት የማስተርስ ዲግሪ (ሁለተኛ ዲግሪ) በቲዎሎጂ Phd (ዶክትሬት ዲግሪ) ያላቸው እጅግ ሊቅ (ሙሁር) ናቸው። በአሜሪካ ቺካጎ ዩኒቨርሲቲ የቲዎሎጂ መምህር በመሆን ሰርተዋል። ቅድስት ቤተክርስትያናችን በቤተክህነት ትምህርት ብቻ ሳይሆን በሳይንሳዊውም የትምህርት ዘርፍ እጅግ በላቁ ሊቃውንት የምትመራ፣ የምትተዳደር እና የምትጠበቅ መሆኗን ልብ ይሏል።
نمایش همه...
​​​​ዐቢይ ጾም ጾም ማለት ሰውን ከምግብ መከልከል ነው፡፡ (ፍትሃ ነገስት አንቀፅ.15) “ጾምሰ ተከልኦተ ብዕሊ ዕምመብልዕ በጊዜ እውቅ” ጾም ማለት በታወቀው ዕለት በታወቀው ሰዓት ሰው ከምግብ የሚከለከለው መከልከል ነው፡፡ መብል መጠጥ የኀጢአት መሠረት ነው በመብል ምክንያት ሞት በሰው ልጆች ላይ መጣ “ይችን ዕፀ በለስ ብትበሉ ሞትን ትሞታላችሁ” ዘፍ.2፥17 ጾም ማለት ሰውነት ከሚፈልጋቸው ነገሮች ሁሉ መከልከል ለሰውነት የሚያምረውን የሚያስጐመዥውን ነገር መተው ማለት ነው። መብል መጠጥ ከልክ ሲያልፍ ከተዘወተረም ከእግዚአብሔር ይለያል፤ “ያዕቆብ በላ ጠገበ ወፈረ ገዘፈ ደነደነ ፈጣሪው እግዚአብሔርን ተወ ሕይወቱ ከእግዚአብሔር ተለየ” ዘዳ.32፥15-17 “የእግዚአብሔር መንግሥት መብልና መጠጥን አትሰብክም” ሮሜ.14፥16፣ 1ቆሮ.8፥8-13 “ዛሬ የሚራቡ የሚጠሙ ብፁአን ናቸው ይጠግባሉና ማቴ.5፥6 ጾም የሥጋ መቅጫ ነው፤ “ነፍሴን /ሰውነቴን/ በጾም ቀጣኋት መዝ.68፥10 ጾም በነቢያት የተመሠረተ በክርስቶስ የጸና በሐዋርያትም የተሰበከና የተረጋገጠ ለክርስቲያኖች ዲያብሎስን ድል የምንነሣበት መንፈሳዊ የጦር ዕቃ ነው፡፡ ስለዚህ ሐዋርያዊትና ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እንደምታስተምረን ይህን ጾም ከምግብ ለመከልከል ጋር ጸሎትን፥ ስግደትን፥ ምጽዋትንና የንስሐ ዕንባን ጨምረን እንጹመው፡፡ ጌታችንና ነቢያት፣ ሐዋርያት የተውልን መንፈሳዊ መሣሪያ ነውና፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ጾም የጾመው ለአብነት፣ ለማስተማር፣ ለአርዓያ ነው፡፡ በዚህ ታላቅ ጾም ጥንተ ጠላታችን ዲያብሎስ፣ ከሰው የሥጋ ጠባይ የሚመጣ ስስትና ፍቅረ ንዋይ ድል የተነሱበት ነው፡፡ እኛም ይህን እያሰብን በተለያየ መንገድ የሚመጣብንን ፈተና ለማራቅ ከዚህ ታላቅ ጾም በረከት እንድናገኝ እንጾማለን፡፡ ጸልዮ ጸልዩ፣ ጾሞ ጹሙ ብሎናል፡፡ ማቴ.6-16፡፡ ስለዚህም ትእዛዙን ለማክበር እንጾማለን፡፡ የዚህ ታላቅ ጾም ስያሜዎች የሚከተሉት ናቻው ፡- ዐቢይ ጾም ባሕርይ አምላክ በሆነዉ በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተመሠረተ በመሆኑ ዐቢይ ወይም ታላቅ ጾም ይባላል፡፡ ጾመ ሁዳዴ በጥንት ጊዜ ገባሮች ለባለ ርስት የሚያርሱት መሬት ሁዳዴ ተብሎ ይጠራ ነበር፡፡ እኛም ባለቤቱ ኢየሱስ ክርስቶስን እያሰብን የምንጾመው በመሆኑ ጾመ ሁዳዴ ተብሏል፡፡ የካሳ ጾም አዳምና ሔዋን ከገነት የተባረሩት ለውርደት ሞት ለሲዖል ባርነት የበቁት በመብል ምክንያት ነው፡፡ በመብል ምክንያት የሞተውን የሰው ልጅ ጌታችን በፈቃዱ በፈጸመው ጾም ካሰው፤ መንፈሳዊ ረሃብን በረሃቡ ካሰለት፡፡ ስለዚህም የካሳ ጾም ተባለ፡፡ የድል ጾም አርዕስተ ኃጣውእ /ማቴ. 4/ ድል የተነሱበት በመሆኑ የድል ጾም ተብሏል፡፡ የመሸጋገሪያ ጾም ጌታችን ከሕገ ኦሪት ወደ ሕገ ወንጌል ሊያሸጋግረን የጾመው ጾም በመሆኑ የመሸጋገሪያ ጾም ተብሏል፡፡ ጾመ አስተምህሮ ጌታችን የጾመው ለትምህርት ነው፡፡ እርሱ መጾም ያለበት ሆኖ አይደለም፡፡ ስለዚህም ይህ ጾም ጾመ አስተምህሮ ይባላል፡፡ አርባ መአልትና አርባ ሌሊት ጾመ ማቴ.4፥2 የቀድሶተ ገዳም ጾም ጌታችን ከከተማ ርቆ ከሰው ተለይቶ /በገዳመ ቆሮንጦስ/ በመጾም ከከተማ ርቆ ከሰው ተለይቶ በብሕትውና መኖርን ቀድሶ የሰጠበት፣ የመጥምቁ ዮሐንስና የነቢዩ ኤልያስን ገዳማዊነት የባረከበት በመሆኑ የቀድሶተ ገዳም ጾም ተብሏል፡፡ የመዘጋጃ ጾም ሕዝበ እሥራኤል የፋሲካውን በግ ከመመገባቸው በፊት ዝግጅት ያደርጉ ነበር፡፡ እኛም ትንሣኤን ከማክበራችን፣ ሥጋና ደሙን ከመቀበላችን በፊት በጾምና በጸሎት ዝግጅት የምናደርግበት በመሆኑ የመዘጋጃ ጾም ተብሏል፡፡ የሥራ መጀመሪያ ጾም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ሥጋ ለብሶ በምድር ሳለ ስብከት፣ ተዓምራት ከመጀመሩ በፊት የጾመው ጾም ነውና የሥራ መጀመሪያ ጾም ይባላል። ሼር
نمایش همه...
የነነዌ 3ኛ ቀን ጸሎተ ምሕላ በተለያዩ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት
نمایش همه...