cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Wuchale 17 General Secondary and Preparatory School

ቻናላችን ላይ: 👉 የተማሪዎች ዜና 👉 የመምህራን መልእክት 👉 ትኩስ የፈተና መረጃዎች 👉 አዳድስ ማስታወቂያዎች 👉 አጋዥ እና መማሪያ መፅሃፍት Creator & Admin @bura_rb Join group t.me/wuchale_17 Channel t.me/wuchale17

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
Advertising posts
185مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

#Update የዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ ሆኗል። ትምህርት ሚኒስቴር የ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ አድርጓል። የ2013 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ መንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ ላመጡ ተማሪዎች ምደባ ተደርጓል። ከዚህ በፊት በተገለጸዉ የመቁረጫ ነጥብ እና ከኦሮሚያ፣ አማራ፣ አፋርና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ተጨማሪ ተማሪዎች ምደባ የሚያስገኝላቸው ውሳኔ መተላለፉ ይታወሳል፡፡ በዚህም መሰረት ተማሪዎች ከዛሬ ጀምሮ የተመደቡበትን ዩኒቨርስቲ ለማየት በድህረገፅ፡-https://result.ethernet.edu.et ፣ በSMS፡- 9444 እንዲሁም በቴሌግራም፡- @moestudentbot መጠቀም ይችላሉ። ተማሪዎች ከምደባ ጋር ተያይዞ ላላችው ማንኛውም ጥያቄ በድህረገፅ https://complaint.ethernet.edu.et በማመልከት ጥያቄዎቻቸውን ማቅረብ ይችላሉ፡፡ ዩኒቨርሲቲዎች እስከ ሚያዝያ 24/2014 ዓ.ም ድረስ ተገቢዉን ዝግጅት አድርገው የመጀመሪያ ዓመት አዲስ ገቢ ተማሪዎችን የቅበላ መርሃ ግብር የሚያሳዉቁ በመሆኑ ተማሪዎች አስፈላጊዉን ዝግጅት እንዲያደርጉም ሚኒስቴሩ ጥሪ አቅርቧል። ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር @tikvahethiopia
نمایش همه...
Bio G12 TG👆👆👆 📚ዘንድሮ Entrance ለምትፈተኑ 💡Biology TG Grade 12 ላይ በየ Unitu ያለውን በደምብ ቅጥቅጥ አርጉ አንብቡና ጥያቄዎችን ስሩ በጣም ይጠቅማቸዋል ✅አስበኀዋል Entrance እኮ ማለት 12 እና ከዛ በላይ አመታት ጊዜያችንን የፈጀንበት ነው!መቼም መዘጋጀታችንን አናቆምም። ለተጨማሪ PDF መረጃ ይሄን ቻናል JOIN ማድረግ ትችላላችሁ👇👇 https://t.me/+5UtUmeE0OYAwOGU8 https://t.me/+5UtUmeE0OYAwOGU8 💥💥💥💥💥💥
نمایش همه...
​​GRAPHENE: THE CARBON-BASED WONDER MATERIAL Since its discovery in 2003, graphene has been a hot topic in chemistry and materials science research. It's been linked with water purification, electronics, and biomedical applications. This post focuses on the properties of Graphene.WHAT IS GRAPHENE❓ ✏ Graphene is a single layer of graphite, the carbon-based material found in pencil leads. Graphite has been known for centuries, but graphene was only isolated in 2003, by shearing layers off of graphite using sellotape. It's a single atom-thick layer of carbon atoms, that are arranged in a flat, hexagonal lattice structure.THE PROPERTIES OF GRAPHENE 💎 Graphene's 'wonder material' reputation stems from its superlative properties. It is a million times thinner than a piece of paper, yet stronger than diamond, and 200 times stronger than steel, due to the strong carbon-carbon bonds. It's also a flexible material, and conducts heat and electricity better than copper. Being only one atom thick, almost 98% of visible light passes through graphene, making it transparent. ━━━━━━━━━━━ 🧪 @universeofknowledge0
نمایش همه...

📌 የ2014 ዓ.ም የዘንድሮ የ12ተኛ ክፍል ብሄራዊን ፈተና ከመስከረም 2015 ዓ.ም በፊት እንደማይሰጥ ተገለፀ ! 📌ፈተናው ከ9ኛ ክፍል እስከ 12ተኛ ክፍል የሚያካትትና የኢኮኖሚክስ ሳብጀክትን እንደማያካትት መገለፁ የሚታወስ ነው ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ! https://t.me/temhert_bebete https://t.me/temhert_bebete
نمایش همه...
ትምህርት ሚኒስቴር ከክልልና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች ጋር በመወያየት በ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና እርማት እና ውጤት ላይ ያስተላለፈውን ውሳኔ አጠቃላይ መግለጫ። @atc_news @atc_news @atc_news @atc_news
نمایش همه...
የዩኒቨርሲቲ ምደባ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ይፋ ይሆናል ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቆናል። መቼ ? በየትኛው ቀን ? ስለሚለው ጉዳይ አንድ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ኃላፊ ቁርጥ ያለውን ቀን ለማሳወቅ እየተሰራ ነው ፤ ቀኑንን እናሳውቃለን ሲሉ ለቲክቫህ መልዕክት ልከዋል። @tikvahethiopia
نمایش همه...
የጥናት እቅድ አወጣጥ (ለተማሪዎች ሼር) 1. ለነገ ዝግጁ ሁኑ ሁሌም ዛሬ ለምነሰራው ብቻ ሳይሆን ነገ ለምንሰራው ስራ እቅድ በማውጣት ዝግጁ ልንሆን ይገባል! ለነገ ዝግጁ ሰትሆኑ ሰአታችሁን በአግባቡ ተጠቅማችሁ የቤት ስራችሁን በብቃት ወይንም በጊዜው ለማጠናቀቅ ይረዳችኃል! 2. የጥናት ቡድን ፍጠሩ ይህ የድሮ ዘዴ ሊመሰል ይችል ይሆናል! ነገር ግን አሁንም ቢሆን የጥናት ቡድን መፍጠር እጅግ በጣም ጠቃሚ ነው! እድሜ ለቴክኖሎጂ መሻሻል በሁላችንም ለማለት በሚያስደፍር መልኩ በምንጠቀምባቸው ስልኮች የሚገኙት እንደ ጎግል ፕላስ የመሰሉ ማህበራዊ ድረገፆች ከአስር በላይ ለሆኑ የጥናት ቡድኖች በቀጥታ የምስል እና የድምፅ ውይይት ለማድረገ ያስችላሉ! ስለሆነም በተለያዩ ቦታዎች ላይ ከሚገኙ የትምህርት አቻ ጓደኞች ጋር በአካልም ሆነ በተለያዩ የቴክኖሎጂ መገልገያዎች የጥናት ቡድኖች በመፍጠር እውቀትን እና ልምዶችን ልንጋራ ይገባል! 3. አንድ ነገር ለመስራት መደበኛ ልምድ ይኑራችሁ! – ከትምህርት ጋር የተገናኙ ስራዎችን ለመስራት እለታዊ የሆነ መደበኛ ጊዜ ስትመድቡ ሁሌም ቢሆን የሚሰጣችሁን የትምህርት ሀላፊነቶች እና የቤትስራዎች በአግባቡ እና በጊዜው ሰርቶ ለመጨረስ ይረዳችኃል! በአካባቢያችሁ ያሉ ሰዎችም ይህን ተረድተው ከአላማችሁ እንዳያሰናክሏችሁ አድርጉ! 4. ለጥናት ምቹ የሆነ ቦታ ያመቻቹ ! – ሁሌም ቢሆን የምታጠኑበት ስፍራ ምቾት ሊሰጣችሁና ትኩረት ለማድረግ የሚረዳችሁ ሊሆን ይገባል! 5. ሁሌም ቢሆን ተጠባባቂ እቅድ ይኑራችሁ – ብዙ ጊዜ ለትምህርት እና ለጥናት የምንገለገልባቸው እንደ ኮምፒውተር የመሳሰሉ መሳሪያዎች በማንጠብቃቸው ሰአቶች ሊበላሹ ብሎም ሊጠፉና ሊሰረቁ ይችላሉ! ስለዚህም አስፈላጊ የምንላቸውን ፋይሎች በተለያየ መልኩ በተጠባባቂነት ልንይዛቸው ይገባል! 6. የቀን መቁጠርያ አዘጋጁና ተጠቀሙ – በሁሉም የትምህርት ተቋማትና ደረጃዎች የአጭርና የረጅም ጊዜ የጥናት ስራዎች ይሰጣሉ! ታዲያ እንደ ርዝመታቸው እና እጥረታቸው ተማሪዎች በመዘናጋት ስራቸውን በአግባቡ ሳይወጡ ሲቀሩ ይስተዋላል! ይህን አስወግዶ ሀላፊነትን በአግባቡ ለመወጣት ከእለት ተእለት የትምህርት እና የጥናት እንቅስቀሴ ጀምሮ የረጅምና የአጭር ጊዜ ሀላፊነቶቻችንን በቀን መቁጠርያ አማካይነት እቅድ ልናወጣላቸው እና ልንተገብራቸው ይገባል! 7. የተደራጃችሁ ሁኑ በትምህርት ቆይታችሁ የምትገለገሉባቸውን መሳሪያዎች የትምህርት ሰአት የጥናት ሰአታችሁን የመዝናኛ ሰአታችሁን የገንዘብ አጠቃቀም እቅዳችሁን በመለየት ሁሉንም በስርአት በቦታውና በሰአቱ በመጠቀም የተደራጃችሁ ሁኑ! 8. አዎንታዊ አስተሳሰብን ያጎልብቱ ! የትምህርት ቤት ሕይወት ጠንካራ ስራን የሚፈልግና በጭንቀት ብሎም በመሰናክሎች የተመላ ነው! እነዚህን የሚገጥሙንን ጭንቀቶችና መሰናክሎች ተቋቁመን ስኬታማ ለመሆን ከምንመኛው የምረቃ በዓላችንም ለመድረስ አዎንታዊ አስተሳሰብን ልናጎለብት ይገባል! እንዴት አዎንታዊ አስተሳሰብን ማጎልበት እንደምንችል ኩሉ ኔትወርክ በቀጣይ ጠቃሚ ምክሮች ይዞላችሁ የሚመጣ ይሆናል! 9. እረፍት ውሰዱ ጥናት ከመጀመራችሁ በፊት ሆነ በጥናት መሀል አጭር የእረፍት ጊዜ መውሰድ ችግር እንደሌለው ልንረዳ ይገባል! ምክንያቱም የእረፍት ጊዜያቶች መንፈሳችሁን እንድታድሱ እና ወደጥናት ስትመለሱ ትኩረት አድርጋችሁ እንድትሰሩ ይረዳችኃል! 10. ዝርዝር የስራ እቅድ ወይንም check list ይኑራችሁ! – ብዙን ጊዜ የምንማራችሁ ትምህርቶች እለታዊ የሙከራ ስራ እና የቤት ስራዎች ይኖራቸዋል! በመሆኑም የሁሉንም የምንማራቸውን የትምህርት አይነቶች ሀላፊነቶች በአግባቡ ለመወጣት የስራ ዝርዝር በማዘጋጀት እቅድ ልናዘጋጅላቸው ይገባል! ይህም የስራ ሀላፊነታችንን በአግባቡ ለመወጣት ይረዳናል! 📌 Join and share 👇👇👇 @Aconcise @Aconcise
نمایش همه...
"የትምህርት ሚኒስቴር በአጭር ጊዜ ውጤቱን ይገልጻል።" የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የተላከው አጣሪ ኮሚቴ በፈተና አስተራረም ዙሪያ የደረሰበትን ሂደት ይፋ አድርጓል። የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ይፋ ከተደረገ በኋላ በተማሪዎች፣ በመምህራን፣ በወላጆች እና በተቋማት ቅሬታ መፈጠሩ ይታወቃል። የፈተና ውጤቱ የአስተራረም ስህተት አለበት እንዲሁም በጦርነቱ ውስጥ የነበሩ አካባቢዎችን ግምት ውስጥ ያስገባ አይደለም የሚሉ ቅሬታዎች ተነስተውበታል። በአማራ ክልል በ12ኛ ክፍል የፈተና አስተራረም ዙሪያ የተነሳውን ቅሬታ ለማጣራት የክልሉ ትምህርት ቢሮ አጣሪ ኮሚቴ መላኩ ይታወሳል። አጣሪ ኮሚቴው የደረሰበትን ሂደት በተመለከተ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል። መግለጫውን የሰጡት የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የኮሚቴው ሰብሳቢ ሙላው አበበ ፈተናው በአማራ ክልል ያለምንም ችግር ተጠናቅቆ እንደነበር አስታውሰዋል። ፈተናው ታርሞ ውጤት ሲታይ ችግር ስለነበር ሳይስተካከል መለቀቅ የለበትም የሚል ቅሬታ ትምህርት ቢሮው ማቅረቡንም አንስተዋል። የተነሱ ችግሮች ሳይጣሩ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ መቆረጥ እንደሌለበት መግለጻቸውንም ተናግረዋል። የውጤት መቀያቀር እና የፈተና አስተራረም ስህተት ስለነበር አጣሪ ኮሚቴ ወደ አዲስ አበባ መላኩንም አስታውቀዋል። "በትምህርት ቤታቸው ጎበዝ የነበሩ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ውጤት ያላመጡበት ምክንያት፣ አንዳንድ ተማሪዎች በአንድ ትምህርት ከፍ ያለ ውጤት በአንደኛው ደግሞ የወረደ ያመጡበት ምክንያት፣ ምንም አይነት ተማሪዎች ያላስገቡ ትምህርት ቤቶችንና የውጤት መቀያየር ለምን ኖረ? የሚለውን ይዘው መሄዳቸውንም" ገልጸዋል። የዩኒቨርሲቲ መግቢያ በጦርነት ለተጎዱ አካባቢዎች ታሳቢ ያደረገ አይደለም የሚለው ጥያቄም ሌላው ጉዳይ እንደሆነ ተናግረዋል። ማሽኑን አናምንም ብለን በእጃችን ሁሉ አርመን አረጋግጠናል፣ የውጤት አገላለፁ ምን ያክል ትክክል ነው የሚለውንም አይተናል ብለዋው። የፈተና ቡክሌት መቀያየር ችግር እንደተመለከቱም ገልጸዋል። ምንም ያላሳለፉ ትምህርት ቤቶችን ርእሰ መምህሩን በመውሰድ ጎበዝ ተማሪዎችን በእጃችን ሁሉ የማረም ሥራ ሠርተናል ነው ያሉት። በአማራ ክልል ተማሪዎች ውጤት መቀነሱ በጦርነት ምክንያት የሥነ ልቦና ችግር ስለነበረባቸው ነውም ብለዋል። እነዚህን ተማሪዎች ከሌሎች ተማሪዎች ጋር እኩል መመዘን ፍትሐዊ አለመሆኑን ቢሮው መጠየቁንም ጠቁመዋል። ከሲቪክስ ውጤት በተጨማሪ በሌሎች ላይም ጥርጣሬ አለን መታየት አለበት የሚል ጉዳይ ማቅረባቸውንም ገልጸዋል። ፈተናዎች ወጥተዋል የሚል ወሬ በመናፈሱ ተማሪዎች ሳይረጋጉ መፈተናቸው በውጤታቸው ተፅዕኖ መፍጠሩንም ተናግረዋል። የትምህርት ቢሮው ኃላፊ ማተብ ታፈረ (ዶ/ር) እየተነሱ ያሉ ጉዳዮችን ያለ እረፍት እየተከታተሉ መሆናቸውን አስታውቀዋል። የክልሉ ተማሪዎች ያላቸው አቅም ይታወቃል ያሉት ኃላፊው ነገር ግን በተማሪዎች ውጤት ላይ የታየው የውጤት ማሽቆልቆል የተጠበቀ እንዳልነበር ተናግረዋል። ለውጤት ማሽቆልቆል ምክንያት የፈተና አስተራረም ችግር፣ በሌሎች አካባቢዎች አብላጫ እድል ተወስዶባቸው ይሆናል የሚልና ጦርነቱ ያመጣው ችገር ይሆናል የሚል ጉዳዮችን ይዘው መሥራታቸውንም ተናግረዋል። የተቋቋመው ኮሚቴ ያገባኛል ከሚሉ አካላት የተውጣጣ መሆኑንም ገልፀዋል። በቴክኖሎጂ ችግር እንዳይፈጠር የሶፍት ዌር ባላሙያ ጭምር በኮሚቴው መካተቱን ተናግረዋል። ቢሮው በትኩረት እየሠራበት መሆኑን የተናገሩት ዶክተር ማተብ ዝም ብሎ የራስን ሃሳብ ብቻ ማቅረብ የሕዝብ ጥያቄም አልመለሰም፣ ሕዝብም አላዳነም ነው ያሉት። ትምህርት ሚኒስቴርም ኮሚቴው ማጣራት የሚገባውን ጉዳይ እንዲያጠራ ትብብር ማድረጉንም አስታውቀዋል። እንደሲቪክስ በጣም የወጣ ባይሆንም በሌሎች የትምህርት አይነቶችም ጥርጣሬ መነሳቱንም ተናግረዋል። በተነሱ ችግሮች በተደረገ ውይይት በትምህርት ስርዓቱ ላይ ያለው የእምነት መላላት እንዲስተካከል መስማማታቸውን ገልፀዋል። የፈተናዎች ስርቆት መኖሩንም በተደረገው ውይይት መገለፁን እና ከዚህ አዙሪት ለመውጣት የሚያስችል ሥርዓት መዘርጋት እንደሚያስፈልግ መግባባታቸውንም ተናግረዋል። የአማራ ክልልን ከማንም ክልል ጋር ሳናወዳድር በራሱ ክብረ ወሰን ነው ያወዳደርነው ያሉት ዶክተር ማተብ በአንድ ዓመት እንደዚህ አይነት የውጤት ማሽቆልቆል ሊፈጠር እንደማይችል ዝርዝር ጉዳይ ማቅረባቸውን ገልፀዋል። በተደረገው ውይይት ጦርነቱ በተማሪዎች ውጤት ላይ ተፅዕኖ ማሳረፉን መስማማታቸውንም አስታውቀዋል። ውሳኔው ደግሞ ከፍ ባሉ አካለት እንዲሰጥ መግባታቸውንም አንስተዋል። እኛ ጥያቄ ያቀረብነው ተማሪዎች አማራ ስለሆኑ ሳይሆን ችግር ውስጥ ስለነበሩና ችግሩን በግልጽ ስለምናውቀውና ስለነበርንበት መታየት ስላለበት ነው ብለዋል። ለሚነሱ ችግሮች እንደሚታገሉም አረጋግጠዋል። በሕልውና አደጋ ውስጥ የነበሩ ተማሪዎች ለፈተና ሲዘጋጁ ነበር ብሎ መከራከር እንዳማይቻልም ገልፀዋል። የአማራ ክልል ወጣቶች በጦርነቱ ምክንያት ከሌሎች አካባቢዎች በተለየ መልኩ በሕልውና ዘመቻው ተሳትፈዋል። በርካታ መምህራን በጦርነቱ ተሳትፈው ተሰውተዋል። በዚህ ሁኔታ ውስጥ የነበረ ተማሪ ተረጋግቶ ተፈትኗል ማለት አይቻልም፤ ይህን ሰው የሆነ ሁሉ እንዲረዳው እንፈልጋለን፣ ኢትዮጵያውያን በዚህ ልክ እንዲረዱን እንፈልጋለንም ብለዋል። ጦርነቱ ከፍተኛ የሆነ ችግር አድርሷል ይህ ሊታመን ይገባልም ነው ያሉት። በአስከፊ ጦርነት ውስጥ ቆይተው ያለ በቂ ዝግጅት የተፈተኑ ተማሪዎች የተለየ ፍትሐዊ ውሳኔ ይፈልጋሉ ብለዋል። በሀገር በተቃጣ ጦርነት የአማራ ክልል ተማሪዎች ተለይው ሰላባ መሆን የለባቸውምም ብለዋል። እንዲህ አይነት ችግር በየትኛውም አካባቢ ይፈጠር ለፍትሐዊነት እንታገላለን ነው ያሉት። ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ ዓይናችን ከጉዳዩ ላይ አናነሳም፣ የተወከልነው የሕዝብ ጥያቄ ለመመለስ ነው፣ ሌላ ጉዳይ የለንም፣ መተማመን ሊኖረን ይገባል፣ እኛ የሕዝባችን ልጆች ነንም ብለዋል። በትምህርት ሚኒስቴር በኩልም በአጭር ጊዜ ውጤቱን ይገልጻል ብለዋል። አሁን የተፈጠረው እንዲፈታ ጥሩ ሂደቶች መኖራቸውን ያነሱት ኃላፊው፤ ቀጣይ ተፈታኞች ተገቢ ዝግጅት እንዲያደርጉ የሞራልም የሙያም ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል። #አሚኮ @wuchale17 @wuchale17
نمایش همه...
📚 Grade 12 Chemistry. Entrance Questions @universeofknowledge0 @universeofknowledge0
نمایش همه...