ESAT (ኢሳት🇪🇹)®
ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot 🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹
نمایش بیشتر247 437مشترکین
+3724 ساعت
-647 روز
-76430 روز
- مشترکین
- پوشش پست
- ER - نسبت تعامل
در حال بارگیری داده...
معدل نمو المشتركين
در حال بارگیری داده...
نمایش همه...
ሼር/share
የኤሌክትሪክ ኃይል በመላ ሀገሪቱ መቋረጡን የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ‼️
ዛሬ ከቀኑ 09:46 ጀምሮ ከባህርዳርና አካባቢው በስተቀር የኤሌክትሪክ ኃይል በመላው አገሪቱ መቋረጡን ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል።
ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል በማህበራዊ ትስስር ገፁ በሲስተም ላይ በገጠመ ችግር ኃይል መቋረጡን እና ለጊዜው የችግሩን ምክንያት ለማወቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስታውቋል።
የተቋረጠውን ኤሌክትሪክ መልሶ የማገናኘት ሥራ የተጀመረ ሲሆን ችግሩን በመቅረፍ ዳግም ሲስተሙን መልሶ እስከሚገናኝ ድረስ ሕብረተሰቡ በትዕግስት እንዲጠብቅም ተቋሙ ጠይቋል።
@Esat_tv1
@Esat_tv1
ሼር/share
የአማራ ክልል የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ለአገሪቱ ቋሚ የቀውስ ምንጭ ከሚያደርጉት ተግባራት እንዲታቀብ ሲል አስጠነቀቀ‼️
የአማራ ክልል የትግራይ ክልል ግዜያዊ አሥተዳደር ለሀገሪቱ ቋሚ ቀውስ ምንጭ ከሚያደርጉት ተግባራት እንዲታቀብ ሲል ያስጠነቀቀው ዛሬ መጋቢት 19 ቀን 2016 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ነው፡፡
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የአማራ ክልል ተማሪዎች መፃህፍትን ምክንያት በማድርገ ጠብ አጫሪ የሆነ መግለጫ ያስታወሰው የአማራ ክልል፣ጊዜያዊ አስተዳደሩ አውጥቶት የነበረው መግለጫ ‹‹አሳሳችና ጠብ አጫሪ ፍላጎት የተሸከመ ነው›› ብሏል፡፡
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር መግለጫውን ከወጣ ከሦስት ቀናት በኋላ ማለትም መጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ.ም ከነበረበት አካባቢ በመንቀሳቀስ የራያ አላማጣ ወረዳ ቀበሌዎችን በመያዝ ነዋሪዎችን በመግደልና በማሰቃየት ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡
በመማሪያ መፃህፍቶቹ ተካተዋል የተባሉ አካባቢዎች ካለፉት 30 አመታት በፊት ጀምሮ የማንነትና ራስን በራስ የማሥተዳደር ጥያቄዎች ሲቀርቡባቸው የነበሩ መሆናቸውንም አክሏል፡፡ የአማራ ክልል መንግሥት በእነዚህ አካባቢዎች የተማሪዎች የመማር መብት እንዲከበር ግዴታውን መወጣቱን ሰበብ አድርጎ የወጣ ነው ያለው የጊዜያዊ አስተዳደሩን መግለጫ፣ ድርጊቱ የሚያሳየው ከድርብርብ ውድቀቶቹ ትምህርት አለመውሰዱን ነው ሲል አጣጥሎታል፡፡
በአገሪቱ እነዲሁም በሁለቱ ክልሎች መካከል ቀውስ ከሚፈጥሩ ተግባራት በመቆጠብ ‹‹ከለመደው አጓጉል የካርታ ፖለቲካ ጨዋታ እንዲወጣ›› አሳስቦ፣ ለዘላቂ ሠላምና ለሕዝቦች አንድነት መጽናት በሚበጅ ሐሳብና ተግባር ላይ እንዲያተኩር አሳስቧል፡፡
@Esat_tv1
@Esat_tv1
ሼር/share
ዜጎች የብሔራዊ መታወቂያ ካርድ በኦንላይን ተመዝግበው ባሉበት እንዲመጣላቸው የሚያስችል አገልግሎት ተጀመረ‼️
ብሔራዊ መታወቂያ ካርድን በኦንላይን ተመዝግቦ በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት በኩል ካርዱን ካሉበት ሆነው በማዘዝ ባሉበት የማድረስ ሥራ መጀመሩን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታወቀ።
የብሔራዊ መታወቂያ ካርድ የሕትመት ሥራ በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ሲከናወን የቆየ ሲሆን የብሔራዊ መታወቂያ ካርዱን ማግኘት የሚፈልጉ ዜጎችም አገልግሎቱን ለማግኘት በአካል መገኘት ይኖርባቸው ነበር። አሁን ግን ዜጎች አገልግሎቱን በቀላሉ ማግኘት እንዲችሉ የኦንላይን ምዝገባ የተጀመረ ሲሆን የክፍያ ሥርዓቱም በቴሌ ብር እና በባንክ መክፈል እንደሚቻል ተጠቁሟል።
የብሔራዊ መታወቂያ ካርድ ማግኘት የሚፈልጉ ዜጎች card-order.fayda.et ድረ ገጽ ላይ በኦንላይን መመዝገብ እንደሚችሉ ሲገለፅ ፥ በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት በኩል ካርዱን ባሉበት ቦታ እንዲመጣላቸው ማዘዝ ይችላሉ ተብሏል። ዜጎች ምዝገባ ከማድረጋቸው በፊት የፋይዳ ቁጥራቸውን የሚገልጽ የጽሑፍ መልዕክት በስልካቸው ስለመላኩ ማረጋገጥ እንደሚኖርባቸውም ነው የተገለፀው።
@Esat_tv1
@Esat_tv1
ሼር/share
መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ
ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ።
https://t.me/Poppycarmarket
☎️ 0911248768 👈 ይደውሉልን
Rechargeable hearing Aid 🦻
ባለቻርጅ የማዳመጫ መርጃ
👉🦻🏻መስማት አልቻሉም?
🦻 ለሁልም እድሜ ክልል የተሰራ አለመስማትን እንዲሰማ የሚያረግ
🦻የእሩቁን ድምፅ በማቅረብ ያጎላል: የቅርቡንም በጥራት በማስማት ይረዳል :
🦻እንዲሁም በጩኸት የሚፈጠር ህመምን ይከላከላ የጆሮ የመስማት አቅም ማነስ ድምፅን ከሩቅ ለመስማት እንድነቸገር ያደርጋል
🦻በእድሜ ለገፉ እንዲሁም
በተለያያ ምክንያት በአደጋም በተፈጥሮ ለሚከሰት የመስማት ችግር ላጋጠማቸው
ይዘዙ ልጆች እስከ አዋቂ መጠቀም ይችላሉ ክፍለ ሀገር አንልካለን
አዲስ አበባ መገናኛ በነፃ እናደርሳለን
ዋጋ፦ 4999 ብር
☎️ 0910647273 / 0936115487
🚚ያለተጨማሪ ክፍያ ያሉበት ድረስ እናመጣለን
Telegram👉🏼 https://t.me/trutruekawoch
4ኛው ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው‼️
"ኢፍጣራችን ለአንድነታችን" በሚል መሪ ሐሳብ እየተካሄደ በሚገኘው የኢፍጣር ሥነ-ሥርዓት ላይም የቁርዓን ንባብን ጨምሮ የተለያዩ ሐይማኖታዊ ክንውኖች እየተካሄዱ ነው፡፡
ከአዲስ አበባ እና አጎራባች ከተሞች የተውጣጡ በርካታ የሐይማኖቱ ተከታዮች፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳይ ምክር ቤት አመራሮች፣ ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች፣ በኢትዮጵያ የተለያዩ ሀገራትን አምባሳደሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
@Esat_tv1
@Esat_tv1
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የራሳቸውን ያለሆነ ገንዘብ በህገወጥ መንገድ ወስደው በከፊል የመለሱ ወይም ሙሉ በሙሉ ተመላሽ ያላደረጉትን 5,166 ግለሰቦች ስም ዝርዝር ዛሬ ይፋ አደረገ‼️
ግለሰቦቹ ቀሪ የወሰዱትን ገንዘብ እስከ ቅዳሜ መጋቢት 21 ከቀኑ 11 ሰዓት ድረስ እንዲመልሱ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።
ይህንን የማያደርጉ ከሆነ ወደ ህጋዊ እርምጃዎች እንደሚገባ ገልጿል።
ስማቸውን ከፎቷቸው ጋር በማድረግ ህገወጥ ገንዘብ በመውሰድ ወንጀል መጠርጠራቸውን ለህግ አካላትና ለህዝብ እንደሚያሳውቅ ገልጿል።
@Esat_tv1
@Esat_tv1
ሼር/share
ኢትዮጵያ ኮከብ ተጨዋቿን አጣች‼️
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የባህርዳር ከነማው ድንቅ የአማካይ ተጨዋች አለልኝ አዘነ በድንገት ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል።
በቅርቡ የጋብቻ ስነ ስርዓቱን በቤተክርስቲያን የፈፀመው አዲሱ ሙሽራ ድንገት ዛሬ ለሊት ህይወቱ ማለፉ ተረጋግጧል ።
ለአርባምንጭ ታዳጊ ቡድን እስከ ዋናው፤ ለሀዋሳ ከተማና አሁን ለባህርዳር ከተማ በሊጉ የሚጫወተው አለልኝ አዘነ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንም ጥሪ ተደርጎለት አገልግሎት ሰጥቷል።
አመለ ሸጋው ተጨዋች አለልኝ አዘነ ላለፉት ሁለት አመታት በጣና ሞገዶቹ ቤት አስደናቂ ብቃቱን በማሳየት ክለቡንና ሀገሩን እያገለገለ የሚገኝ ወጣት ተጨዋች ነበር።
@Esat_tv1
@Esat_tv1
Rechargeable hearing Aid 🦻
ባለቻርጅ የማዳመጫ መርጃ
👉🦻🏻መስማት አልቻሉም?
🦻 ለሁልም እድሜ ክልል የተሰራ አለመስማትን እንዲሰማ የሚያረግ
🦻የእሩቁን ድምፅ በማቅረብ ያጎላል: የቅርቡንም በጥራት በማስማት ይረዳል :
🦻እንዲሁም በጩኸት የሚፈጠር ህመምን ይከላከላ የጆሮ የመስማት አቅም ማነስ ድምፅን ከሩቅ ለመስማት እንድነቸገር ያደርጋል
🦻በእድሜ ለገፉ እንዲሁም
በተለያያ ምክንያት በአደጋም በተፈጥሮ ለሚከሰት የመስማት ችግር ላጋጠማቸው
ይዘዙ ልጆች እስከ አዋቂ መጠቀም ይችላሉ ክፍለ ሀገር አንልካለን
አዲስ አበባ መገናኛ በነፃ እናደርሳለን
ዋጋ፦ 4999 ብር
☎️ 0910647273 / 0936115487
🚚ያለተጨማሪ ክፍያ ያሉበት ድረስ እናመጣለን
Telegram👉🏼 https://t.me/trutruekawoch
وارد شوید و به اطلاعات مفصل دسترسی پیدا کنید
ما این گنجینه ها را پس از تأیید هویت به شما نشان خواهیم داد. ما وعده میدهیم که سریع است!