cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

DW Amharic

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

نمایش بیشتر
Advertising posts
40 645مشترکین
+2324 ساعت
+2547 روز
+1 34330 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

በአዲስ አበባ “ኢፍጣራችን ለአንድነታችን” በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የጎዳና ላይ ኢፍጣር ስነ ስርዓት ባሁን ወቅት በታላቁ የረመዳን ፆም ላይ የሆኑት ህዝበ ሙስሊሙ አዲስ አበባ ውስጥ የጎዳና ላይ ኢፍጣር መርሃ ግብር በየዓመቱ ማካሄድ ከጀመሩ ይህ ዘንድሮ የተካሄደው ለአራተኛው ጊዜ መሆኑ ነው፡፡ ትናንት አዲስ አበባ መስቀል አደባባይ በተካሄደው በዚህ ሃይማኖታዊ ስርዓት ላይ በርካታ ህዝበ ሙስሊሙ የጸሎትና የኢፍጣር ስነስርዓቱን በታላቅ ድምቀትና በኅብረት አከናውነዋል፡፡ የመርሃግብሩ አስተባባሪ እና የእስልማ ሃይማኖት መመህር ዑስታዝ አቡበከር አህመድ የዚህ ፕሮግራም ዋና ዓለማ መተባበር እና አንድነትን ማሳየት ነው ይላሉ፡፡ “የረመዳን ወር አንዱ ዓላማ የተሳሳተ መንገድን የምናርምበት፤ በዚህን ወቅት የሚያሰባስቡንን ምክንያት የምናበዛበት” ነው ብለዋል፡፡ ዋና ዓላማው ሰዎችን በአንድነት ማሰባሰብ በጋራ በማስፈጠር የአንድነትና የመተባበር መንፈስ ማስፈንም ነው ተብሏል ። “ረመዳን የይቅርታ፣ የመተሳሰብና የመሰባሰብ ወቅት እንደመሆኑ በጎዳና ላይ ኢፍጣር አንድነታችንን የምናንጸባርቅበት እና ያለው ለሌለው የሚያካፍልበትም በመሆኑ በዚህን ወቅት ይቅር በመባባል ወደ ፈጣሪ ዱኣ የሚቀርብበትም ነው” የሚሉት ኡስታዝ አቡበከር እንደ አገርና ማኅበረሰብ መተባበር ይበጃል ሲሉም ጠይቀዋል ። በኢፍጣር ስነስርዓቱ የኢትዮጵያ እስልምና ምክር ቤት እና የአዲስ አበባ እስልምና ምክር ቤትን ጨምሮ የሃይማኖቱ መሪዎች እንዲሁም የተለያዩ ዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ እንግዶች መገኘታቸውም ተነግሯል። በመድረኩ ላይ ለተቸገሩ ወገኖች በተለይም በተለያዩ ሰው ሰራሽ እና በተፈጥሮ አደጋ በችግር ላይ የወደቁ ዜጎችን ማስታወስና መርዳት እንደሚገባውም በተላለፈው መልእክት ተስተጋብቷል። የቪዲዮ ዘገባ፦ |ሥዩም ጌቱ ዶይቸ ቬለ፤ ከአዲስ አበባ
نمایش همه...
نمایش همه...
የመጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ.ም. የዓለም ዜና

ዐርዕስተ ዜና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሂሳብቸው ከተቀመጠ ገንዘብ ውጭ በሕገወጥ መንገድ ገንዘብ ወሰደው በከፊል ተመላሽ አደረጉ ያላቸው ግለሰቦች ቀሪውን ገንዘብ እስከ ቅዳሜ መጋቢት 21 ቀን፣ 2016 ዓ.ም ካልመለሱ ማንነታቸውን በመገናኛ ብዙሀን ይፋ እንደሚያደርግ አስጠነቀቀ የባህር ዳር ከነማ የመሐል ሜዳ የእግር ኳስ ተጫዋች አለልኝ አዘነ የእግር ኳስ ቡድንኑ አስታወቋል። በዩናይትድ ስቴትሱ የሜሪላንድ ግዛት ዋና ከተማ ባልቲሞር የሚገኝ ድልድይ በመርከብ ተገጭቶ ከተደረመሰ በኋላ የደረሱበት አልታወቀም የተባለ ስድስት ሰዎች ፍለጋ ቆመ። የሕይወት አድን ሥራው ቆሞ ወደ አስከሬን ፍለጋ መገባቱን ባለስልጣናት ተናግረዋል።

نمایش همه...
አብዛኛዉ የኢትዮጵያዊ ደሐ ነዉ-ጥናት

አፍሮ ባሮ ሜትር የተባለዉ ተቋም ይፋ ባደረገዉ ጥናቱ መሠረት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እየተባባሰና የድህነት ደረጃም እየጨመረ ነዉ።በአፍሪካ ተሞክሮዎች እና ግምገማዎች በ39 ሀገሮች ላይ ገለልተኛ ሆኖ ይሰራል የሚባለው ይህ ተቋም በኢኮኖሚ፣ በግል ኑሮ ሁኔታ እና በድህነት ልኬት ላይ ያደረገው ጥናት እንዳመለከተዉ ኢትዮጵያ መልካም ሁኔታ ውስጥ አይደለችም

نمایش همه...
አማኑኤል ሆስፒታል ያጋጠመው የቦታ እጥረት

በአመት 130ሺ ማለት በቀን ከ 350 በላይ የአእምሮ ህመምተኞች ወደ ሆስፒታሉ ይመጣሉ። ሀኪሞቹም በሰአት በአማካይ 44 ህመምተኞችን ያክማሉ ማለት ነዉ።80% የሚሆኑት ወደ ሆስፒታሉ የሚመጡት ከባድ የአእምሮ ህክምና እና ክትትል የሚይስፈልጋቸው ናቸው

نمایش همه...
በምዕራብ አርሲ ዞን የዶዶላ የንጹሃን ግድያ

ለደህንነታቸው ስባል ስማቸው እንዳይጠቀስ ጠይቀው አስተያየታቸውን የሰጡን አንድ የአከባቢው ነዋሪ በአከባቢው በተከታታይ ይፈጸማል ያሉት መሰል ጥቃት በሰኞ እለትም የአገልጋዮችን ህይወት ከነቤተሰብ አጥፍቷል፡፡ “የተገደሉት ምዕመናን ናቸው፡፡

نمایش همه...
የአደባባይ ኢፍጣርና ርዳታ በድሬዳዋ

በከተማዋ በተለምዶ ለገሀር አደባባይ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ትናንት በተዘጋጀው የአፍጥር ዝግጅት ላይ ለዶይቼ ቬለ በሰጠው አስተያየት ከአደባባይ አፍጥሩ በተጨማሪ እገዛ ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች ድጋፍ የማሰባሰብ ስራ መስራታቸውን ገልጿል

نمایش همه...
የመካከለኛውን ዘመን የሰው ልጅ አመጣጥ የሚያሳይ አዲስ ግኝት በኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ ሉሲ ወይም ድንቅነሽን ጨምሮ በርካታ ቅሪተ አካላትና በዓለም ረጅም ዕድሜ ያስቆጠሩ የድንጋይ መሣሪያዎች መገኛ በመሆን፤በጥንታዊ የሰው ልጅ አመጣጥ ላይ በሚደረገው ምርምር ጉልህ ስፍራ አላት።በቅርቡ የወጣ አንድ የጥናት ግኝት ደግሞ የሰዉ ዘር መገኛ ብቻ ሳትሆን በመካከለኛው ዘመን የሰው ልጅ አመጣጥ ምርምርም ቀዳሚ መሆኗን የሚያሳይ ነው።

نمایش همه...
ኢትዮጵያ የዕዳ ክፍያ እፎይታዋን ለማዳን የአይኤምኤፍ ባለሙያዎችን የጉብኝት ውጤት ትጠብቃለች

የኢትዮጵያ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅትን ሥምምነት የሚጠባበቀው የዕዳ ክፍያ እፎይታ “ዋጋ ቢስ” የመሆን ሥጋት ተጋርጦበታል። እፎይታው ለመንግሥት 1.5 ቢሊዮን ዶላር በዓመት የሚያድን ነው። የአይኤምኤፍ ባለሙያዎች የአዲስ አበባ ጉብኝት ኢትዮጵያ ለሀገር በቀል የኤኮኖሚ ማሻሻያ በጠየቀችው 3.5 ቢሊዮን ዶላር ብድር ላይ ተጽዕኖ ይኖረዋል።

نمایش همه...
ድርቅ፣ረሃብ እና የምግብ ዋስት እጦት በኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ ያለው የድርቅ አዝማሚያ ከፍተኛ መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ኮነ፣ በተለይ በሰሜን እና ምዕራብ የሃገሪቱ ክፍሎች አስጊና ወደ ከፍተኛ ረሃብ ሊሸጋገር የሚችል የድርቅና ረሃብ አደጋ ማንዣበቡን አመልክተዋል

የድሬዳዋ ወጣቶች አፍጥርና ርዳታ ቪዲዮ፤ መሳይ ተክሉ
نمایش همه...
وارد شوید و به اطلاعات مفصل دسترسی پیدا کنید

ما این گنجینه ها را پس از تأیید هویت به شما نشان خواهیم داد. ما وعده می‌دهیم که سریع است!