DW Amharic
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።
نمایش بیشتر- مشترکین
- پوشش پست
- ER - نسبت تعامل
در حال بارگیری داده...
در حال بارگیری داده...
ዐርዕስተ ዜና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሂሳብቸው ከተቀመጠ ገንዘብ ውጭ በሕገወጥ መንገድ ገንዘብ ወሰደው በከፊል ተመላሽ አደረጉ ያላቸው ግለሰቦች ቀሪውን ገንዘብ እስከ ቅዳሜ መጋቢት 21 ቀን፣ 2016 ዓ.ም ካልመለሱ ማንነታቸውን በመገናኛ ብዙሀን ይፋ እንደሚያደርግ አስጠነቀቀ የባህር ዳር ከነማ የመሐል ሜዳ የእግር ኳስ ተጫዋች አለልኝ አዘነ የእግር ኳስ ቡድንኑ አስታወቋል። በዩናይትድ ስቴትሱ የሜሪላንድ ግዛት ዋና ከተማ ባልቲሞር የሚገኝ ድልድይ በመርከብ ተገጭቶ ከተደረመሰ በኋላ የደረሱበት አልታወቀም የተባለ ስድስት ሰዎች ፍለጋ ቆመ። የሕይወት አድን ሥራው ቆሞ ወደ አስከሬን ፍለጋ መገባቱን ባለስልጣናት ተናግረዋል።
አፍሮ ባሮ ሜትር የተባለዉ ተቋም ይፋ ባደረገዉ ጥናቱ መሠረት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እየተባባሰና የድህነት ደረጃም እየጨመረ ነዉ።በአፍሪካ ተሞክሮዎች እና ግምገማዎች በ39 ሀገሮች ላይ ገለልተኛ ሆኖ ይሰራል የሚባለው ይህ ተቋም በኢኮኖሚ፣ በግል ኑሮ ሁኔታ እና በድህነት ልኬት ላይ ያደረገው ጥናት እንዳመለከተዉ ኢትዮጵያ መልካም ሁኔታ ውስጥ አይደለችም
በአመት 130ሺ ማለት በቀን ከ 350 በላይ የአእምሮ ህመምተኞች ወደ ሆስፒታሉ ይመጣሉ። ሀኪሞቹም በሰአት በአማካይ 44 ህመምተኞችን ያክማሉ ማለት ነዉ።80% የሚሆኑት ወደ ሆስፒታሉ የሚመጡት ከባድ የአእምሮ ህክምና እና ክትትል የሚይስፈልጋቸው ናቸው
ለደህንነታቸው ስባል ስማቸው እንዳይጠቀስ ጠይቀው አስተያየታቸውን የሰጡን አንድ የአከባቢው ነዋሪ በአከባቢው በተከታታይ ይፈጸማል ያሉት መሰል ጥቃት በሰኞ እለትም የአገልጋዮችን ህይወት ከነቤተሰብ አጥፍቷል፡፡ “የተገደሉት ምዕመናን ናቸው፡፡
በከተማዋ በተለምዶ ለገሀር አደባባይ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ትናንት በተዘጋጀው የአፍጥር ዝግጅት ላይ ለዶይቼ ቬለ በሰጠው አስተያየት ከአደባባይ አፍጥሩ በተጨማሪ እገዛ ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች ድጋፍ የማሰባሰብ ስራ መስራታቸውን ገልጿል
ኢትዮጵያ ሉሲ ወይም ድንቅነሽን ጨምሮ በርካታ ቅሪተ አካላትና በዓለም ረጅም ዕድሜ ያስቆጠሩ የድንጋይ መሣሪያዎች መገኛ በመሆን፤በጥንታዊ የሰው ልጅ አመጣጥ ላይ በሚደረገው ምርምር ጉልህ ስፍራ አላት።በቅርቡ የወጣ አንድ የጥናት ግኝት ደግሞ የሰዉ ዘር መገኛ ብቻ ሳትሆን በመካከለኛው ዘመን የሰው ልጅ አመጣጥ ምርምርም ቀዳሚ መሆኗን የሚያሳይ ነው።
የኢትዮጵያ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅትን ሥምምነት የሚጠባበቀው የዕዳ ክፍያ እፎይታ “ዋጋ ቢስ” የመሆን ሥጋት ተጋርጦበታል። እፎይታው ለመንግሥት 1.5 ቢሊዮን ዶላር በዓመት የሚያድን ነው። የአይኤምኤፍ ባለሙያዎች የአዲስ አበባ ጉብኝት ኢትዮጵያ ለሀገር በቀል የኤኮኖሚ ማሻሻያ በጠየቀችው 3.5 ቢሊዮን ዶላር ብድር ላይ ተጽዕኖ ይኖረዋል።
በኢትዮጵያ ያለው የድርቅ አዝማሚያ ከፍተኛ መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ኮነ፣ በተለይ በሰሜን እና ምዕራብ የሃገሪቱ ክፍሎች አስጊና ወደ ከፍተኛ ረሃብ ሊሸጋገር የሚችል የድርቅና ረሃብ አደጋ ማንዣበቡን አመልክተዋል
ما این گنجینه ها را پس از تأیید هویت به شما نشان خواهیم داد. ما وعده میدهیم که سریع است!