cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Addis Post

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استاخبار و رسانه‌ها19 766
Advertising posts
4 199مشترکین
-324 ساعت
-437 روز
-7330 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

እንደምን አደራችሁ!! መልካም የስራ ቀን! መልካም ሰኞ @adissposts ነን፡
نمایش همه...
👍 4 4
ትምህርቱን አቋርጦ ትልቅ ህልም ሰንቆ፣ አስደናቂ ሄሊኮፕተር በመስራት የራሱን ህይወት የቀጠፈው ወጣት...... ይህ ወጣት ከ3 አመታት በፊት የ7ኛ ተማሪ ነበር። ት/ቤት ገብቶ ብዙም ደስተኛ ስላልነበር በአነስተኛ ብረታ ብረቶች ስራ ይሰራ ነበር። ብዙም ሳይቆይ ወዲያው በፈጠራ ስራ ተጠመደ። በአነስተኛ ጉልበት ረጅም ርቀት ምትሄድ ባለ 1 መቀመጫ ሄሊክፕተር መስራት ጀመረ። ወደ 1600 ሰዓታትም በፈጀው ሙከራ እና ስራ የሚደንቅ ውጤት ሲያይ ነበር። ለ3-4 አመታት በዚህ ሙከራ ተሰማርቶ፣ በአከባቢው እንደ እብድ ሲታይ፣ ግን ደሞ ማይታመን ውጤት በቅጽበት እያሳየ ነበር። ለመጨረሻ ሙከራ ያደረገበትን ምሽት እየቀረጸውም ነበር፣ ድንገት ግን ፊልም ሚመስል አሳዛኝ ክስተት ሆነ። የሄሊኮፕተሩ ተሽከርካሪ ብረት ወልቆ ወደ ውስጥ በመሹለክ ጭንቅላቱን አገኘው። ሼይክህ እስማኤል ወዲያው ሆስፒታል ቢወሰድም፣ ህይወቱን ማትረፍ አልተቻለም። በወቅቱ አለም መነጋገሪያ አድርጎትም ነበር። ብሩክ ቀን እየተጠነቀቃችሁ! እኛ @addisposts ነን። ሼር ያድርጉ!
نمایش همه...
👍 5
ኢራን በባለፈው በሶሪያ በሚገኘው ቢሮዬ እስራኤል ለከፈተችብኝ ጥቃት ምላሽ ሰጥቻለሁ ስትል አስታወቀች። 300 ድሮኖችን በእስራኤል ሰማይ ላይ አዝንባለች። እስራኤል በበኩሏ 99% የሚሆነውን መክቻለው አክሽፌያለሁ ብላለች። "የቃል ኦፕሬሽን" ብላ ኢራን የሰየመችው አዲሱ ጥቃት፣ ወደ ጎረቤት ሀገራት ግጭት እንዳይስፋፋ የተሰጋ ሲሆን፣ የባይደን መንግስት ኦፕሬሽኑን "የሽብር ጥቃት" ብሎ ጠርቶታል። የባይደን መንግስት በዚህ ጉዳይ ከእስራኤል ጎን መቆሙን ቢያሳውቅም፣ የእስራኤልን የስለላ ድርጅት ሞሳድን የሚገዳደር እንቅስቃሴ አሁንም ቀጥሏል። ኢራን አሁንም ቢሆን እስራኤልን ማስፈራራቷ አይሏል። "አሁንም በድጋሜ" ጥቃት ከከፈተችብኝ ቅጣቴንም ከበድ አረገዋለሁ ብላለች። አሜሪካንም በግልጽ "አይመለከትሽም" የሚል ብላሽ ሰታታለች። አለም የእስራኤልን የበቀል ጥቃት ምን ሊሆን እንደሚችል እየጠበቀ ነው። @addisposts ነን የትም ሽፋን ያላገኙ ምርጥ መረጃዎችን ያግኙ
نمایش همه...
👍 4
ኢራን ምሽቱን እስራኤል ላይ የድሮን ዝናብ ስታዘንብ ማምሸቷን ተገለጸ። ይህን ተከትሎ እስራኤል በግዛቷ ድንገተኛ ደውል ደውላለች። እስራኤል በዘመኗ እንደዚህ አይነት ውርጅብኝ እና ጥቃት ወርዶባት እንደማያቅ አሳውቃለች። አሁን ላይ ቀጥታ በምሽት የእስራኤል ሰማይ ላይ የኢራን ድሮኖች እንደ እሳት ሲወነጨፉ ታይቷል። ኢራን ከድሮን በተጨማሪ ሮኬቶችን ቀላቅላ ተኩሳለች። የእስራኤል እና ኢራን ፍጥቻ ወዴት ያመራ ይሆን? ከራሺያ ጋር ትግል የቀጠለው የዩክሬኑ ዘነለስኪ፣ አሜሪካ እሱን ረስታ ትኩረቷ ሁሉ እስራኤል ላይ ሆኗል። @addisposts ነን አዳዲስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ።
نمایش همه...
👍 3 1
የገንዘብ የመግዛት አቅም አሁን ካለበት የባሰ ከቀነሰ ኑሯችን ወዴት ያመራ ይሆን? ኢትዮጵያ ጫና ላይ ነች፣ በዚህ ውጥንቅጥ ውስጥ ሌላ ራስ ምታት እና ትኩሳት ወደ ህዝባችን እየመጣ ነው። ኢትዮጵያ ምን አይነት አጣብቂኝ ውስጥ ነች? ኢትዮጵያ እምቢ ወይም እሺ ብትል፣ በሁለቱም አማራጭ መጥፎ ውጤቶች አሉበት። ብድር ልውሰድ ብትል ዛሬ ሱቅ ገብተን በ100 ብር ምንገዛው እቃ 180-250 ብር ይንራል። አይ ብድር አንፈልግም ካልንም ደሞ የአጠቃላይ ብድራችን 28 ቢሊዮን ዶላር ሽግሽግ ሳይኖረው፣ ብድር መክፈል እንደማንችል ተቆጥሮ፣ አለም አቀፍ ኢንቨስተሮች የቢዝነስ ሰዎች ሁሉ መንገዳቸውን ዘግተው፣ ኢኮኖሚውን ዜሮ ያረጉታል። አሁን አሁን ከእስር በእስር ግጭት በተጨማሪ በአለም መድረክ የታወቅንበት ጉዳይ፣ የኢኮኒሚያችን መቆርቆዝ ነው።
نمایش همه...
👍 4 1
ኢራን የእስራኤልን ግዙፍ ጀልባ በቁጥጥር ስር አውላ ወሰደች። የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጠባቂ ሄሊኮፕተር የእስራኤል ንብረትነት ያለውን ግዙፍ ጀልባ ሲቆጣጠር የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል ተለቋል። እስራኤል ምን አለች? የእስራሌል ባለ ስልጣናት ኢራን ዋጋ ትከፍልበታለች በማለት መልዕክት ልከዋል። ጀልባው እንዴት ሊወሰድ ቻለ? ጀልባው ከአረብ ኢሜሬትስ ተነስቶ በህንድ ውቂያኖስ በኩል በማለፍ በንግድ ስራ ላይ ያተኮረ ቢሆንም፣ ኢራን ግን እስራኤልን ማመን ማቆሟን ተገልጿል። የኢራን መንግስት ለእገታው እውቅና የሰጠ ሲሆን፣ እስራኤል በበኩሏ ይህ የለየለት የውንብድና ስራ በመሆኑ በአለም አቀፍ ህግ ያስከስስሳል ብላለች። ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ታጣቂዎችን እንደምትደግፍ እንዲሁም እስራኤልን ለማጥፋት ከፍተኛ ፖለቲካዊ ፍላጎት ያላቸውን ሀይሎች ተገን አድርጋ ልትወጋት ደፋ ቀና እያለች መሆኑን ባለ ስልጣናቱ ጨምረው ገልጸዋል። ኢራን በባለፈው እስራኤል በሶርያ ዲፕሎማቲክ ቢሮ በወሰደችው የአየር ጥቃት በተፈጠረው ጥፋት እና የንጽሁሃን እልቂት፣ እስራኤል ከኢራን ከባድ አጸፋ ይወሰድብኛል ብላ እየፈራች መሆኑን ተናግራለች። እስራኤል ከኢራን መልሶ ጥቃት እንደሚደርስባትም በማወቅ ከአሜሪካ እና መሰል ሀገሮች ብዙ ድጋፍን እየተቀበለች ዝግጅቷን ቀጥላለች። @addisposts ነን
نمایش همه...
👍 6 2
አሜሪካ እና ቻይና ሰማዩን ለመያዝ የገቡበት ትንቅንቅ። አስተውለን ከሆነ ወፎች፥ አሳዎች እንዲሁም በርካታ ህይወት ያላቸው ፍጥረታት ተሰብስበው ይንቀሳቀሳሉ፡ ይህም ሊያጠቃቸው የሚፈልግን ግራ ያጋባል። አሜሪካ ከ10 አመታት በፊት ያበለጸገችው ቴክኖሎጂ እንደ አንዳንድ ተመራማሪዎች ከሆነ ከኑውክለር የባሰ አደገኛ ነው። በመቶ እና በሺህ የሚቆጠሩ ጥቃቅን ድሮኖች እንደ ንብ ሲጓዙ፡ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ወይም AI ታግዘው እንደፈለጉ ቦታ ሲቀይሩ፡ የጠላትህ ድሮን መጥለፊያ ግራ አጋብቶ እንዲጠቃ ያረገዋል። ከሰሞኑ ስለዚህ ቴክኖሎጂ ምን አዲስ ነገር አለ? ቻይና ይህንን ዘርፍ ተቀላቅላ ከፍተኛ የምርምር ውጤት እያገኘች ሲሆን፡ አሜሪካ በበኩሏ ላለመቀደም ብዙ እየሰራችበት ነው። ይህ ቴንክኖሎጂ ከክላስተር ቦምብ ጋር ቢመሳሰልም፡ ግን በሰው ሰራሽ አስተውሎቱ እና ውስብስብ ቀመሩ ድንቅ አድርጎታል። ለመጀመሪያ ጊዜ ይህንን ስራ ላይ አውላ አመርቂ ውጤት ያሳየችው ያስመሰከረችው እስራኤል ነች። ንቦች በብዛት ሆነው ሲሄዱ ሚያሰሙትን አስፈሪ ድምጽ፡ ይህ የድሮን ውጤት ምድር ላይ የከተመ ጠላ በማስፈራራት ስነ ልቦና የማዳከም ብቃት አለው። @addisposts ነን 🙏🙏🙏
نمایش همه...
👍 7
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው በቁጥጥር ስር ዋለ። ከጥቂት ወራት በፊት ታስሮ ከእስር የተፈታው የቀድሞ የአውሎ ሚዲያ ባልደረባ አሁን ላይ " አልፋ ቲቪ " የተሰኘ የማህበራዊ ሚዲያ መስራች እና አዘጋጅ ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው በፀጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር መዋሉን ጠበቃ ታደለ ገብረመድህንን ዋቢ አድርጎ አዲስ ስታንዳር አስነብቧል። የጋዜጠኛውን መታሰር ባለቤቱ ሄለን አባተ አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ፤ ትላንት የፊንፊኔ ኢንተግሬትድ ብሮድካስቲንግ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋዜጠኛ ሰቦንቱ አህመድ በአዲስ አበባ ፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለች ሲሆን (በለቡ ፖሊስ ጣቢያ ነበረች) ዛሬ ወደ ቢሾፍቱ መወሰዷን የጣቢያው ዋና ዳይሬክተር ለሚ ታዬ መናገራቸውን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገፅ አስነብቧል። ሰቦንቱ ትላንት በፖሊስ የተያዘችው አመሻሽ ላይ ከስራ ቦታዋ ስትወጣ ሲሆን በቁጥጥር ስር ያዋሏት ፖሊሶች የፍርድ ቤት ትዕዛዝ አለመያዛቸውንም ዋና ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። አክለውም፤ ትላንት ለቡ ፖሊስ ጣቢያ እያለች አነጋግረዋት እንደነባርና የተያዘችበት ምክንያት ምን እንደሆነ እንዳልተገለጸላት ፍርድ ቤትም እንዳልቀረበች ለ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገፅ " አስታውቀዋል። ጋዜጠኛዋ ዛሬ ወደ ቢሾፍቱ ከተማ እንድትወሰድ ተደርጓል። @tikvahethiopia
نمایش همه...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" Galatoomaa Tour " የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ እና የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሀመድ ወደ በሰኔ እና ሃምሌ ወር 2022 ወደ #ሰሜን_አሜሪካ እና #አውሮፓ እንደሚጓዙ ታውቋል። አመራሮቹ ጉዟቸውን " Galatoomaa Tour " በሚል የሚያደርጉ ሲሆን በተለያዩ ከተሞች ከደጋፊዎቻቸው ጋር ይገናኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። ጉዞውን በተመለከተ እስካሁን በሁለቱ ወራት የሚያዳርሷቸውን ከተሞች እና ቀናት ይፋ ከመሆን በዘለለ ለጊዜው በዝርዝር ይፋ የተደረገ መረጃ የለም። @tikvahethiopia
نمایش همه...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የ " ፍትህ መጽሔት " ማኔጂግ ዳሪክተር ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ " የሀገር መከላከያ ሰራዊትን በህዝብ ዘንድ አመኔታ ለማሳጣትና ሁከትና ብጥብጥ በማስነሳት ወንጀል " መጠርጠሩን መርማሪ ፖሊስ ዛሬ ለፍ/ቤት ገልጿል። ፖሊስ ጋዜጠኛ ተመስገን በተጠረጠረበት ሁከትና አመጽ ማስነሳት ወንጀል በምስክር ለማስመረጥና የምስክር ቃል ለመቀበል ተጨማሪ ማስረጃ ለመሰብሰብ እና የምርመራ ስራውን አጠናክሮ ለመቅረብ 14 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት እንዲሰጠው ችሎቱን ጠይቋል። የጋዜጠኛ ተመስገን ጠበቃ ሄኖክ አክሊሉ መከላከያን መተቸት እምነት ማሳጣት አለመሆኑን ጠቅሶ ተከራክሯል። በምስክር ማስመረጥ ለተባለውም ቢሆን ተመስገን አገር የሚያውቀው በመሆኑ ማስመረጥ ጥያቄው ተገቢ እንዳልሆነ ገልጿል። ጠበቃው አክሎም ጋዜጠኛ ተመስገን የሚሰራበት ሚዲያ ፍቃድ ያለው ህጋዊ ተቋም እንደመሆኑ ወንጀል ሰራ እንኳ ቢባል በመገናኛ ብዙሃን አዋጅ እንጂ በጊዜ ቀጠሮ ሊጠየቅ እንደማይገባ ተከራክሯል። ፖሊስ በዩቱዩብ ቃለመጠይቅ እያደረገ ከሌሎች አካላት ጋር ሁከትና አመጽ የማነሳሳት ስራ እየሰሩ ነው ሲል ባቀረበው የመነሻ ምርመራ ሪፖርትን በተመለከተ ጋዜጠኛ ተመስገን ከ4 አመት ወዲህ ምንም አይነት ከማንም ጋር ቃለመጠየቅ እንዳላደረገ ጠበቃ ሄኖክ አብራርቷል።  በሚሰሩበት ሚዲያ የሀገር መከላከያ ተቋምም ቢሆን ተተችቻለው በህዝብ ዘንድ እምነት አጣሁ ብሎ አለመቅረቡን  ጠቅሰው ቢቀርብ በመገናኛ ብዙሀን አዋጅ መሰረት በሚሰራበት ሚዲያ ማስተካከያ ከማድረግ እንደማይታለፍ መከራከሪያ ነጥቡ ጠቅሷል። ያንብቡ ⬇️ https://telegra.ph/Tarik-Adugna-05-27 ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ @tikvahethiopia
نمایش همه...