cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

የ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መፅሃፍ ቅዱስ

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፈራጅ እንጂ አማላጅ አይደለም፡- ዘፍ 3:22 1ኛ ሳሙ 16:1 ኢሳ 9:6 ዳን 7:14 ሆሴ 13:4 ዘካ 9:9-10 ሚክ 5:2 ሉቃ 1:32-33 ዮሐ 10:30 ሉቃ 2:12 ዮሐ 14:7 ሮሜ 9:5 ቆላ 2:9-10 ቲቶ 2:11-13 ዕብ 1:3-4 ዕብ 1:10-11 1ኛ ጴጥ 3:23 1ኛ ዮሐ 2:23 ራእ 3:22 ራእ 22:12-13 ማኔኔት ተቄል ፋሬስ አሜን

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
507
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ዝማሬ መላእክት ያሰማን
نمایش همه...
እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሰን። የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ለምንድን ነው ለመስቀል ክብር የምትሰጠው? መስቀል "መስቀል ኃይላችን ነው ኃይላችን መስቀል ነው የሚያፀናን መስቀል ነው መስቀል ቤዛችን ነው መስቀል የነፍሳችን መዳኛ ነው አይሁድ ይክዱታል እኛ ግን እናምነዋለን ያመነው እኛም በመስቀሉ እንድናለን ድነናልም።" /የዘወትር ጸሎት/ በብሉይ ኪዳን መስቀል የእርግማን ምልክት ና የወንጀለኞች መቀጫ ነበር::(ዘዳ 21:23) ክርስቶስ በደሙ ስለቀደሰው ግን ቅዱስ መስቀል ተብሏል። በመስቀል ድህነትን አግኝተናል።(1ኛ. ጴጥ 2: 24-25) ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለሙን ከኃጢአትና ከሞት ለማዳን በቀራኒዮ የተሰቀለበት ቤዛችን ነው። መስቀል የነጻነታችን ግርማ: የድህነታችን መገኛ: ጠላትን ድል የምንነሣበት መሳሪያችን ነው። ሰውን በመስቀል ላይ መቅጣት የተጀመረው በጥንቱ ፋርስ በዛሬዋ ኢራን /ከክርስቶስ ልደት በፊት/339-33/ ዓመት ነው። ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ለምንድን ነው ለመስቀል ክብርን የምትሰጠው? 1. ክርስቶስ መስዋዕት ሆኖ ራሱን የሠዋበት እውነተኛ መንበር በመሆኑ፤ 2. የክርስቶስ ደም የፈሰሰበት: እኛ የዳንበት የነጻነት አርማችን ስለሆነ፤ 3. የአምላካችን መለኮታዊ ፍቅር የተገለጠበት መሳሪያ በመሆኑ፤ የመስቀል ዓይነቶች ___ 1. የመጾር መስቀል:- ±±±±±±±±±±±±± በቅዳሴ እና በማዕጠንት ጊዜ ሠራዒው ዲያቆን የሚይዘው ነው። 2. የእጅ መስቀል:- ±±±±±±±±±±±±±±± ካህናት ምእመናንን የሚባርኩበት በእጅ የምትያዝ የመስቀል ዓይነት ናት። 3. የአንገት መስቀል:- ±±±±±±±±±±±±±±±± ምእመናን ለአምላካቸው ያላቸውን ፍቅር ለመግለጽ ከማዕተባቸው ጋር በአንገታቸው የሚያደርጉት ነው። 4. እርፈ መስቀል:- ±±±±±±±±±±±±±± በማንኪያ ቅርጽ ተሠርቶ በእጅታው ላይ የመስቀል ምልክት ያለበት ነው። ሠራዒው ዲያቆን በቅዳሴ ጊዜ የአምላካችንን ክቡር ደሙን ለምእመናን የሚያቀብልበት ነው። እንዲሁም ጌታችን በእለተ አርብ የተወጋበት ጦር ምሳሌ ነው። መስቀል ከተለያዩ ማዕድናት ይሰራል መስቀል ከተለያዩ ማዕድናት ሊሰራ ይችላል: መስቀሉ የሚሰራባቸው ማዕድናት የራሳቸውን ባህርያት እንዳላቸው ሁሉ ምሳሌውን ለመግለጽ ብቁ ናቸው ብለው አባቶች ያስቀመጡትን እንደሚከተለው እንመለከታለን፦ 1. የእንጨት መስቀል:- ---------------------------- ጌታችን የተሰቀለው በዕጽ በእንጨት ላይ መሆኑን ለማመልከት ነው። + ለምን ኢየሱስ ክርስቶስ በእንጨት ተሰቀለ? አዳም ዕጽ/ እንጨትን በልቶ ሞትን በማምጣቱ ክርስቶስም በእንጨት ተሰቀሎ ህይወትን ሊሰጠን በእንጨት መስቀል ተሰቀለ። 2. የብረት መስቀል:- -------------------------'-' ጌታችን በአምስቱ ቅንዋተ ለመቸንከሩ ምሳሌ ነው። 3. የብር መስቀል:- --------------------------- ይሁዳ በሠላሳ ብር አሳልፎ ስለመስጠቱ። በተጨማሪም ከብር ቢሰራ ተስፋን: ዕድልን ያመለክታል። ይኸውም እርሱ ለሰው ልጆች ሁሉ ቤዛ ሊሆን በደሙ ዋጋ ከፍሏልና ከእርሱ ተስፋ እንድናደርግ ያመለክተናል። 4. የወርቅ መስቀል፦ --------------------------- ከወርቅ ቢሰራ ወርቅ ንጹህ እንደሆነ ንጹሀ ባህርይ እድፈት የሌለው ጽኑ አንተ ነህ ብሎ ለመመስከር ነው። 5. የመዳብ መስቀል:- ------------------------------ መዳብ ቀለሙ ቀይ ይመስላል: ጌታችን ለእኛ ብሎ ያፈሰሰው ደም ምሳሌ ነው። ብዙዎች የመስቀል ጣላት ሆነው መስቀልን ጣኦት ነው ይላሉ ጣኦት ማለት ግን የሠይጣን ስም የሚጠራበት ፣የሚመለክበት ነው። መስቀል ደግሞ የመድኃኒዓለም ስም የሚጠራበት ህማሙን የሚድኑበት አርማችን፣ ኃይላችን ነው እንጂ መስቀል አምላክ አይደለም። በመስቀል የተሠቀለው ግን አምላክ ነው። ምሳሌ: ሰው አልጋ ላይ ሲተኛ አልጋ ላይ ተኛ ይባላል እንጂ እንጨቱ ላይ ተኛ አይባልም: ሰው የቤቱን በር ሲዘጋ እጨቴን ልዝጋ አይልም በሩን ልዝጋ ይላል እንጂ: አልጋ አልጋ ይባላል የተሰራው ከእንጨት ሊሆን ይችላል ነገር ግን እንጨት ተብሎ አይጠራም: በርም በር ይባላል እንጂ እንጨት ተብሎ አይጠራም። እንዲሁም ጌታ የተሰቀለበትን መስቀል መስቀል ይባላል ፤እንጂ እንጨት አይባልም። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ብሏል: "ብዙዎች ለክርስቶስ መስቀል ጠላቶቹ ሆነው ይመላለሳሉና፤ ብዙ ጊዜ ስለ እነርሱ አልኋችሁ፥ አሁንም እንኳ እያለቀስሁ እላለሁ። መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው። (ፊልጵ 3÷18-19) " ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።" ( ገላ 6:14) የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና። የጥበበኞችን ጥበብ አጠፋለሁ የአስተዋዮችንም ማስተዋል እጥላለሁ ተብሎ ተጽፎአልና። (1ኛ ቆሮ 1÷18-19) 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://telegram.me/tewahdomserete 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
نمایش همه...
የ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መፅሃፍ ቅዱስ

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፈራጅ እንጂ አማላጅ አይደለም፡- ዘፍ 3:22 1ኛ ሳሙ 16:1 ኢሳ 9:6 ዳን 7:14 ሆሴ 13:4 ዘካ 9:9-10 ሚክ 5:2 ሉቃ 1:32-33 ዮሐ 10:30 ሉቃ 2:12 ዮሐ 14:7 ሮሜ 9:5 ቆላ 2:9-10 ቲቶ 2:11-13 ዕብ 1:3-4 ዕብ 1:10-11 1ኛ ጴጥ 3:23 1ኛ ዮሐ 2:23 ራእ 3:22 ራእ 22:12-13 ማኔኔት ተቄል ፋሬስ አሜን

​#መስቀሉ_አበራ እዮሐ አበባዬ መስከረም ጠባዬ(፪) መስከረም ሲጠባ ተተክሎ ደመራ ህዝበ ኢትዮጵያን እዩት ችቦውን ሲያበራ በታላቁ ብርሃን በመስቀል ደመራ(፪) በኃጢአት ጨለማ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ተውጠን ሳለን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ የክርስቶስ መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ብርሃን ሆነልን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ትምህርተ መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ሆኖን ላመንነው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ በቃሉ ለምንድን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ የእግዚአብሔር ኃይል ነው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ✞ መስቀል ባንዲራችን የነጻነት አርማችን(፪) በኢየሩሳሌም አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ አይሁድ አብረው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ያዳናቸውን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ አናውቅም ብለው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ የድሉን መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ከመሬት ቀብረው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ መስሏቸው ነበር አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ውጦ የሚያስቀረው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ በቀራንዮ ጎልጎታ ጠላታችን ድል ተመታ(፪) ንግሥቲቷ እሌኒ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ በጣም የታደለች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ደመራን አቁማ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ፍለጋ ጀመረች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ መስቀለ ክርስቶስ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ወዴት ነው እያለች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ በጣን ጢስ ተመርታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ መስቀሉን አገኘች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ በመስቀል መከታ ቆስጠንጢኖስ ድል ተመታ(፪) ነገር ግን መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ተቀብሮ አልቀረም አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ተራራ አፍርሶ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ጠላት አሳፈረ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ መስቀል ሲወጣ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ታላቅ ሁካታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ድውይ ሲፈወስ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ አንካሳው ዳነ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ሙታን ተነሱ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ይመስገን ጌታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ብርሃን ወጣ ከመስቀሉ ክርስቲያኖች እልል በሉ (፪) መስቀል መከታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ይሁን ጋሻችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ እንዳይደፈር አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ዳር ድንበራችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ኢትዮጵያ ኑሪ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ በእምነት ፀንተሽ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ጌታ በመስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ የባረከሽ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ መስቀሉ አበራ እንደ ፀሀይ ጮራ (፪) መስቀሉን አምነን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ተሳልመነዋል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ከክብሩ ዙፋን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ በእርሱ ባርኮናል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ እንሰግድለታለን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ የፀጋ ስግደት አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ በእርሱ ላይ ስላለ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ኃይለ መለኮት አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ መስቀል የእኛ ጋሻ የዲያብሎስ ድል መንሻ (፪) የኢትዮጵያን መኩሪያ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ኑ ተመልከቱልን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ የመስቀሉን ብርሃን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ነፀብራቁን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ እፀ መስቀሉ ነው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ የእኛ መከታችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ የተሰጠን ለእኛ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ምልክታችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ በመስቀል እንመካለን እንድንበታለን(፪) የዳዊት ልጅ ያዕቆብ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ የሀገራችን ኩራት አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ የኢትዮጵያ ንጉሥ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ጌታን የሚፈራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ መስቀል ተሸክሞ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ሀገሪቱን ሲዞር አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ድካሙን ሳይፈራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ መስቀል ተሸክሞ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ብርሐን እያበራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ የመስቀሉ ፍቅር በእኛ ላይ ይደር(፪) መናገሻ እንጦጦ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ የረር አምባ አመራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ሲፈለግ ሰንብቶ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ የመስቀል ተራራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ጊሸን ላይ አገኘ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ የአምባሰል ተራራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ግማደ መስቀሉ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ አርፏል ከዚያ ስፍራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ መስቀል መስቀላችን የክርስቲያን ኃይላችን(፪) የመስቀል ለታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ የደመራው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ኢትዮጵያውያን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ተደስተው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ በሀገር ልብሳቸው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ አምረው ደምቀው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ በአደባባዩ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ተሰብስበው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ ይዘምራሉ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ መስቀል ብለው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ የመስቀሉ ደመራ በኢትዮጵያ ሲያበራ(፪) መዝሙር በማኅበረ ፊሊጶስ Join https://telegram.me/tewahdomserete https://telegram.me/tewahdomserete
نمایش همه...
የ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መፅሃፍ ቅዱስ

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፈራጅ እንጂ አማላጅ አይደለም፡- ዘፍ 3:22 1ኛ ሳሙ 16:1 ኢሳ 9:6 ዳን 7:14 ሆሴ 13:4 ዘካ 9:9-10 ሚክ 5:2 ሉቃ 1:32-33 ዮሐ 10:30 ሉቃ 2:12 ዮሐ 14:7 ሮሜ 9:5 ቆላ 2:9-10 ቲቶ 2:11-13 ዕብ 1:3-4 ዕብ 1:10-11 1ኛ ጴጥ 3:23 1ኛ ዮሐ 2:23 ራእ 3:22 ራእ 22:12-13 ማኔኔት ተቄል ፋሬስ አሜን

#መስቀሉ_አበራ 👉 በማህበረ ፊሊጶስ
نمایش همه...
መሃረኒ ድንግል Please join 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://telegram.me/tewahdomserete https://telegram.me/tewahdomserete
نمایش همه...
Please join for more መዝሙር 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://telegram.me/tewahdomserete https://telegram.me/tewahdomserete
نمایش همه...