cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

TIKVAH-ETHIOPIA

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

نمایش بیشتر
Advertising posts
1 338 023مشترکین
+41624 ساعت
+4 1147 روز
+31 27530 روز
توزیع زمان ارسال

در حال بارگیری داده...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
تجزیه و تحلیل انتشار
پست هابازدید هابه اشتراک گذاشته شدهديناميک بازديد ها
01
#Update የ " ቲክቶክ " እገዳ በኪርጊስታን ተግባራዊ ሆነ። ኪርጊስታን " ቲክቶክ " በመላ ሀገሪቱ  እንዲታገድ ውሳኔ ማስለፏ ይታወሳል በዚሁ ውሳኔ መሰረት የቴሌኮም አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶች ትዕዛዙን ወደ መፈጸም #እርምጃ ገብተዋል። በሀገሪቱ " ቲክቶክ " መስራት እንዳቆመም ተነግሯል። ሰዎች መተግበሪያውን ሲከፍቱን የሚያገኙት መልዕክት " Unable to load, please try again." የሚል ነው። ውሳኔው በሀገሪቱ ብሔራዊ ደህንነት መ/ቤት የተላለፈ ነው። የኪርጊስታን ዲጂታል ሚኒስቴር ቲክቶክን የሚያስተዳድረው ' ባይት ዳንስ ' ኩባንያ ፥ " #የልጆችን ፦ - አእምሯዊ፣ - አካላዊ፣ - መንፈሳዊ እና #ሥነምግባራዊ እድገትን ለመጠበቅ በህግ የተዘረዘሩ ህጋዊ መስፈርቶችን ማክበር አልቻለም " ብሏል። በዚህም ምክንያት " ቲክቶክ " በሀገሪቱ እንዳይሰራ ተደርጓል። ውሳኔው የተቃወሙ አካላት ይህ ተገቢ እንዳልሆነ በመግለጽ ገደቡ እንዲነሳ ጠይቀዋል። ከገደብ ይልቅ ቁጥጥር ይደረግበት ብለዋል። ከዚህ ቀደም የኪርጊስታን የባህል፣ ወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴር ፥ " ቲክቶክ " የተሰኘው መተግበሪያ ለልጆች አእምሯዊ እድገት እና አጠቃላይ ደህንነት ጠንቅ እየሆነ ነው " ማለቱ ይታወሳል። መተግበሪያው #ህጻናት እጅግ ጎጂ ሊሆኑ የሚችሉ ይዘቶችን እንዳያገኙ ለመከላከል በቂ #መቆጣጠሪያ እንደሌለው ነበር የገለጸው። በተጨማሪም ለተጠቃሚዎቹ ትክክለኛ የዕድሜ ማረጋገጫ እርምጃዎች እንደለለው እና ተጠቃሚዎችን በአጫጭር የቪዲዮ ክሊፖች ወደ ምናባዊ ግዛት በመሳብ #ሱስ የሚያስይዝ ይዘት እንዳለው አስረድቶ ነበር። ሚኒስቴሩ " ቲክቶክ " በወጣቱ ትውልድ ደህንነት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንዳለው በአጠቃላይም ለትውልዱ ጠንቅ እየሆነ እንደመጣ አሳውቆ ነበር። በሌላ በኩል ፤ አሜሪካ ውስጥ ከመረጃ ደህንነት ጋር በተያያዘ መተግበሪያው እንዲታገድ ከፍተኛ ግፊት እየተደረገ ሲሆን  " ቲክቶክ " ከቻይናው ኩባንያ ካልተፋታ / አሜሪካ የምትቆጣጠረው አይነት ካልሆነ በመላ ሀገሪቱ መታገድ ዕጣ ፋንታ ሊገጥመው ይችላል ተብሏል። @tikvahethiopia
138 83443Loading...
02
የከባድ መኪና ሆነ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ሹፌሮች በተለያዩ ወቅቶችና ቦታዎች በታጣቂዎች የሚደርስባቸውን ፦ - ግድያ ፣ - እገታ ፣ እምዲሁም የተሽከርካሪዎች ቃጠሎ በተመለከተ በተደጋጋሚ መረጃዎችን መለዋወጣችን ይታወሳል። ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን መቂ አካባቢ “ የታጠቁ ኃይሎች ” በአሽከርካሪና ረዳት ላይ ጉዳት እንዳደደረሱ ፣ ከወራት በፊትም በርካታ ተሽከርከርካሪዎች ታቃጥለው እንደነበር ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ ነዋሪዎች ገልጸዋል። ቃላቸውን የሰጡ የመቂ ነዋሪ ፥ አንድ የአይሱዚ ሹፌር ሲገደል ፣ ረዳቱ አካላዊ ጉደት እንደረሰበትና ሌሎች ተሽከርካሪዎች በጥይት እንደተበሳሱ አስረድተዋል። " የተኩስ እሩምታ ተከፍቶባቸው ሹፌሩ ተገደለ። ሚያዚያ 9 ቀን 2016 ዓ/ም ነው የተቀበረው ፤ ረዳቱም ቆሰለ " ሲሉ ነው የተናገሩት። የተኩስ እሩምታ የተከፈተባቸው ከ7 በላይ ተሽከርካሪዎች መሆናቸውን ጠቁመው " ተዘግቦ እንኳን አየዋለሁ ብዬ ነበር የዘገበው ሚዲያ የለም " ብለዋል። ሟቹ ሹፌር መነሻውን አዲስ አበባ በማድረግ እየተጓዘ በነበረበት ወቅት መቂ አካባቢ ማታ ላይ በታጣቂዎች ተኩስ እንደተከፈተበት አስረድተዋል። " ሌሎቹ ሹፌሮች ፈጣሪ አትርፏቸው አልተጎዱም። ተሽከርካሪዎቻቸው ግን በጥይት ተበሳስተዋል። ጎማው እስከ 15 ጥይት  ያረፈበት አለ " ብለዋል።   እኚሁ ነዋሪ ታጣቂዎች " ወደ ኦሮሚያ ተሽከርካሪ እንዳይሄድ ሰሞኑን እቀባ ጥለዋል " ያሉ ሲሆን ጥቃቱን በከፈቱ በማግስቱ  " ከመከላከያ ጋ ተታኩሰዋል "  ሲሉ ገልጸዋል። ሌላኛው ነዋሪ ፤ የዛሬ ወር ገደማ በተመሳሳይ እዛው ቦታ/መቂ ብዙ ተሽከርካሪዎች ተቃጥለዋል ሲሉ አስታውሰዋል። " ጥቃቱ አለ አሁንም አልቆመም። የተወሰነ ጊዜ መከላከያ ሲመጣ ጋብ ይላል እንጂ። ሹፌሮች ስቃይ ላይ ናቸው " ብለዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ እጅግ ትኩረት ይሻል የተባለውን የሹፌሮችን ጥቃት በተመለከተ ከክልሉም ሆነ ከዞኑ ኃላፊዎች ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ተደጋጋሚ ጥረት ለጊዜው ያልተሳካ ሲሆን፣ ምላሽ የሚሰጡ ከሆነ የሚያስተናግዳቸው መሆኑን ያሳውቃል። NB. መቂ ከሰሞኑን ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር ፓርቲ (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር ግድያን ያስተናገደች ከተማ ናት። #TikvahEthiopiaFamilyAA @tikvahethiopia
48 17337Loading...
03
" የመምህራን የስነ-ልቦና ቁስል ሳይሽር ስለ የትምህርት ጥራት ማረጋገጥ ማሰብ ይከብዳል "  - ማህበሩ የትግራይ መምህራን ማህበር በድጋሚ የመምህራን የ17 ወራት ውዙፍ ደመወዛቸው እንዲከፈል ጠየቀ። የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደርንም ዳግም አስጠነቅቋል።  ማህበሩ ሚያዚያ 8 በኣክሱም ከተማ 33ኛው ጉባኤውን አካሂዶ ነበር። በጉባኤው ማጠቃለያ ባወጣው የአቋም መግለጫ " የትግራይ መምህራን የ17 ወራት ውዙፍ ደመወዛቸው እንዲከፈል " ሲል ጠይቋል።   የማህበሩ ስራ አስፈፃሚ እስከ ግንቦት 7 ቀን 2016 ዓ.ም ባለው ጊዜ ከሚመለከታቸው የጊዚያዊ አስተዳደሩ አመራሮች ጋር በመገናኘት ስለ ውዙፍ ደመወዝ መከፈል የመጨረሻ አቋሙ እንደሚያሳውቅ አመልክቷል። ለጥያቄው በጊዜ ገድብ የተወሰነ አሳማኝ መልስ ካላገኘ ጠበቃ አቁሞ ክስ እንደሚመሰርት አሳውቋል። " ተቃውሟችን እና ጥያቄያችን ትምህርት ቤቶች በመዝጋትና ተተኪ ዜጋ በመጉዳት የማሳካት ፍላጎት የለንም " ያለው ማህበሩ " ግዴታችን እየፈፀምን መብታችን እስከ ጫፍ እንጠይቃለን " ብሏል። " የመምህራን የስነ-ልቦና ቁስል ሳይሽር በትምህርት ስለሚገነባው ትውልድና የትምህርት ጥራት ማረጋገጥ ማሰብ ይከብዳል "  ሲልም አክሏል። ማህበሩ የመምህራን ጥያቄ እስኪመለስ ህጋዊ ተቋውሞ ማሰማቱን እንደሚቀጥል አረጋግጧል። መረጃውን የመቐለው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ፥ ድምጺ ወያነ ቴሌቪዥንን ዋቢ አድርጎ ነው የላከው።        @tikvahethiopia            
145 51729Loading...
04
" ልጄን አድኑልኝ " - መምህርቷ እናት መምህርት አልሻምጌጥ ንጉስ ፤ ልጇ የአብቃል በተወለደ በሀያ አንድ ቀኑ ነው የልብ ህመም እንዳለበት ያወቀችው። ላለፉት 5 አመታት የህጻናት የልብ ቀዶ ጥገና መዕከል አስመዝባ ብጠብቅም ወረፋ ሊደርሳት አልቻለም። " አሁን ልጄ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ደረሰ " ስትል ገልጻለች። ከሀያ አንድ ቀኑ ጀምሮ ከሀዋሳ አዲስ አበባ እየተመላለሰች ሰርጀሪውን ስትጠብቅና ማስታገሻ መድሀኒት ስትጠቀም ብትቆይም እንደልጅነቱ መቦረቅ ያልቻለው የአብቃል  " አሁን ላይ የልቡ ክፍተት አራት ሚሊ በመድረሱ እብጠት ፈጥሮበታል " ስትል አስረድታችለ። ይህ እብጠት ምግብ እንዳይረጋለት ከማድረጉ በላይ በአፍና በአፍንጫዉ ደም መውጣት መጀመሩ እና ድንገት በየሰአቱ እራሱን ከመሳቱ በተጨማሪ ፍጹም የድካም ስሜት ውስጥ እንዲገባ በማድረጉ ለቤተሰቡ ታላቅ ድንጋጤ ፈጥሯል። ይህን ተከትሎ ጤና ባለሙያዎች በቶሎ ሰርጀሪዉ መሰራት እንዳለበት ቢናገሩም የመምህር ደሞዙን ከእለት ጉርስ አበቃቅቶ ለመድሀኒት ሲጠቀም ለቆዉ የመምህር አልሻምጌጥ ቤተሰብ ዱብ እዳ ሆኖበታል። ቤተሰብም አሁን ላይ የሚያደርገዉ ጠፍቶበታል። በጉዳዩ ላይ ለኢትዮጵያ ህዝብ በቲኪቫህ ኢትዮጵያ በኩል መልእክት አስተላልፉልኝ የምትለው እናት አሁን ላይ በግል ሆስፒታል ለሰርጀሪዉ ብቻ 650 ሽህ ብር እንደተጠየቀ በአጠቃላይ ከ800 እስከ 900  ሽህ ብር እንደሚያስፈልግ ገልጸለች። ይህን ማድረግ ባለመቻሏ እና ገንዘብም ስለሌላት ልጇን አይኗ እያዬ ልታጣዉ መሆኑን በእንባ ተናግራለች። በመሆኑም ፥ " ደጉ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚቻለዉን አድርጎ ልጄን ያድንልኝ " በማለት ተማጸናለች። መምህር አልሻምጌጥ ንጉስን በስልክ ማነጋገር የሚፈልግ የግል ስልክ ቁጥሯ 0916155490 ነው። ይህ ደግሞ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000243926053 የሂሳብ ቁጥሯ ነው። @tikvahethiopia
149 625105Loading...
05
የፋሲካ ኤክስፖ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል የመግቢያ ትኬትዎን በቴሌብር *127# ወይም http://onelink.to/fpgu4m በመግዛት ጎራ ይበሉ፤ እስከ ብር 2500 ለሚደርሰው ግብይትዎ የአየር ሰዓት እና ጥቅል የሚገዙበት 10% ተመላሽ ያግኙ፡፡ #Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
130 0450Loading...
06
#BankofAbyssinia በተለያዩ ቦታዎች በአፖሎ ሲከፍሉ ቅናሽ ያገኛሉ! አሁኑኑ መተግበሪያውን በማውረድ ይጠቀሙ። ለአንድሮይድ ስልኮች https://play.google.com/store/apps/details?id=com.boa.apollo&hl=en&gl=US ለአፕል ስልኮች https://apps.apple.com/us/app/apollo-digital/id1601224628#Apollodigitalbank #Apollodigitalproduct #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
139 5931Loading...
07
#Update " የሟች ቤተሰብ ተገኝቷል " - ፖሊስ በሟች ኪስ ማንነቱ የሚጠቅስ መረጃ በማጣቱ  ምክንያት የሟችን ፎቶ በመለጠፍ  ቤተሰቦቹን አፋልጉኝ ያለው የዓዲግራት ከተማ ፓሊስ የሟች ቤተሰብ መገኘቱ አስታውቋል። የማህበራዊ የትስስር ገፆችና ሚድያዎች በሟች ቤተሰብ ፍለጋ ያደረጉት የነቃ ወገናዊ ተሳትፎና ጥረት አመስግኗል። ለሟቹ ቤተሰብ ክብር ሲባል ፎቶውን ከገፃቸው በማጥፋት እንዲተባበሩ ጥሪ አቅርቧል። በዚህም መሰረት ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለሟች ቤተሰብ ክብር የሟችን ፎቶ #ማጥፋቱን ለመላ አባላቱ መግለጽ ይወዳል። ምናልባት በውስጥ የተቀባበላችሁም የሟችን ፎቶ ከስልካችሁ እንድታጠፉ እንጠይቃለን። ሚያዝያ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ሌሊት በዓዲግራት ከተማ አንድ ወጣት ተገድሎ ተጥሎ መገኘቱንና በግድያው የተጠረጠሩ 3 ግለሰቦች ሟቹ ከወደቀበት አቅራቢያ በሚገኝ አንድ መጠጥ ቤት በቁጥጥር ስር መዋላቸው መረጃ እንደላክልንላችሁ ይታወሳል። #TikvahEthiopiaFamilyMekelle @tikvahethiopia
245 29345Loading...
08
#Update በኢራን " ኢስፋሃን ከተማ " ዛሬ ማለዳ ፍንዳታዎች የተሰምተው ነበር። ይህች ከተማ የአገሪቱ አየር ኃይል መቀመጫ ፣ በርካታ ወታደራዊ ተቋማት ያሉባት ናት። የኢራን መገናኛ ብዙኃን በደፈናው 3 ድሮኖች በኢራን የአየር መከላከያ ሥርዓት ወድመዋል ሲሉ ገልጸዋል። #የአሜሪካ ባለልስጣናት እስራኤል ቅዳሜ ለተፈጸመባት ጥቃት ኢራን ላይ የሚሳኤል የአጸፋ ጥቃት ፈጽማለች ብለዋል። የኢራን በይፍ የሰጠችው ማብራሪያ ባይኖርም የተሰማው ፍንዳታ ጥቃትን የማክሸፍ እንደነበር አሁን ላይ ከተማዋ በመደበኛ እንቅስቃሴ እንደምትገኝ ገልጸዋል። የደረሰ አንዳች ጉዳት እንደሌለ ጠቁመዋል። በኑክሌር ተቋማት ላይ ምንም ጉዳት አለመድረሱን ተነግሯል። ምንም እንኳን በመገናኛ ብዙሃን እና በአሜሪካ ባለስልጣናት እስራኤል የጸፋ እርምጃ መውሰዷ ቢነገርም ሀገሪቱ እስካሁን በይፋ " ኃላፊነት እወስዳለሁ " አላለችም። ኢራንም ፥ " እስራኤል ናት ይህንን ያደረገችው ቀጣይ እርምጃዬ ይሄ ነው " የሚል ይፋዊ ቃል አልሰጠችም። ነገር ግን ጉዳዩ አሁንም በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ስጋትን እንደደቀነ ይገኛል። ሀገራት ከወዲሁ በእስራኤል ላሉ ዜጎቻቸው ማስጠንቀቂያ እየሰጡ ናቸው። ኢራን እስራኤልን ከቀናት በፊት መደብደቧን ተከትሎ እስራኤል የአፀፋ እርምጃ እንደማይቀርላት ተናግራለች። ኢራንም እስራኤል የአጸፋ እርምጃ እወስዳለሁ ካለች እስከ ዛሬ ጥቅም ላይ ያልዋለ መሳሪያ እንደምትጠቀምና እርምጃዋ ከመጀመሪያው እየከፋ እንደሚሆን አስጠንቅቃለች። ኢራን ፥ ጦርነቱ እንዲስፋፋ እንደማትፈልግ ነገር ግን ደፍሮ የሚያጠቃት የትኛውም አካል ካለ " እጁን እንቆርጥለታለን " ስትል ነው ከሰሞኑን የዛተችው። @tikvahethiopia
222 01536Loading...
09
#ሴጅ_ማሠልጠኛ 10ኛ ዙር ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Modern Accountancy and Auditing) ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን። 👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና 👉 መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ 👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት ☎️   0906777799 / 0906777755 አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute Facebook: https://www.facebook.com/sagetraininginstitute Instagram: https://www.instagram.com/sage_training_institute/ Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
188 15294Loading...
10
ንጹሕ_ምንጭ _ኢትዮጵያ ሊፈፀም ጥቂት ቀናት ብቻ ቀረው። በግዮን ሆቴል እስከ ሚያዚያ 13 ብቻ፡፡ ለልጆችዎ ቦታ አለን 📌ማስታወሻ :- በተለይ ሚያዚያ 12 እና 13 ምሽት 11ሰአት ጀምሮ በዓይነቱ ልዩ የሆነ የኪነጥበብ ምሽት ከ ዐውደ ርእዩ ጋር በጥምረት ይቀርባል። 📌ማስታወሻ :- በተለየ መንገድ ቅዳሜ ሚያዚያ 12/2016ዓ.ም. የልጆች ልዩ የመዝናኛ ኪነ ጥበባዊ ዝግጅቶች ይካሄዳል። በእነዚህ መርሐ ግብሮች ላይ እንዲገኙ ለሌሎችም እንዲያጋሩ በታላቅ አክብሮት እንጋብዛችኋለን። ለበለጠ መረጃ ፦0966767676 ወይም 0944240000 ይደውሉ። INSTAGRAM | TELEGRAM | YOUTUBE | TWITTER | TIKTOK |WEBSITE
219 856146Loading...
11
#ኢትዮጵያ ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ አንድ አባት  በጎረምሶች ተከበው ሲደበደቡ ፣ ሰደበደቡ ፣ ሲዋከቡ ታይቷል። ይህን እጅግ አሳፋሪና በምን አይነት ሁኔታ ላይ እንዳለን ሚያሳይ ቪዲዮ ያጋሩት ደግሞ እራሳቸው የድርጊቱ ፈጻሚዎች ናቸው። ድርጊቱ ብዙዎችን ክፉኛ አስቆጥቷል። በርካቶች ስለ ነገ በማሳብ ፍርሃት ውስጥ ከቷቸዋል። በእርግጥ በሀገራችን ያላየነው ግፍ ፣ ያልሰማነው ክፉ ተግባርና ጭካኔ ምን አለ ? እንዘርዝር ብንልስ ቦታው፣ ጊዜው  ይበቃናል ? በፍጹም ! ከዚህ በፊት እንደምንለው በቪዲዮ ተቀርጾ የምናየው ምናልባትእድለኞች ሆነን ከብዙ አንዱ እንጂ ስንት ያላየነው ይኖራል። ወደ ቪድዮው ስንመለስ ተከበው ሲመቱ፣ ሲዋከቡ ፣ ሲዘለፉ የነበሩት አባት ' እንጀራ ፍለጋ እግር ጥሏቸው እንደመጡ ' ይገልጻሉ የሚጠይቀን የለም ባዮች ጎረምሶች ' እዚህ አካባቢ ምን ትሰራለህ ? ለምን እዚህ መጣህ ? ከመጣህበት ቦታስ እንጀራ የለም ? ' ሲሉ እጅግ በንቀት ያዋክቧቸዋል። ይህን ተግባራቸውን እንደ በጎ ስራ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ አጋርተውታል። የትኛውም ዜጋ በገዛ ሀገሩ የመንቀሳቀስ መብት አለው ? ካልሆነ ስለምን #ኢትዮጵያዊ ይባላል ? ጥፋት ካለበት ፣ ከተጠረጠረ የሚጠይቀው ህግ እንጂ የሰፈር ጎረምሳ አይደለም። ግለሰቦቹ ጥርጣሬ አለን ካሉ ህግን ማሳወቅ እንጂ ማነው ፤ የትኛው ህግ ነው ይህንን መብት የሰጣቸው ?  ይህ ተግባር በተለይ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየተነዛ ያለው የጥላቻ ስብከት ምን ያህል ስር እንደሰደደ እንደሆነ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ሲሆን ነገን እጅግ አስፈሪ ያደርገዋል። ግልጽ የሆነ የብሄርና የግለሰቦች ጥላቻ ፣ ልብም አእምሮም በጥላቻ መሞላት፣ አይንም በጥላቻ መታወር ፦ - ሌላው ይቅር ታላላቆቻችን እንዳናከብር - ለእምነታችን ፣ ለሃይማኖታችን ቦታ እንዳይኖረን - ለሰው ልጅ ትንሽ እንኳን ቦታ እንዳንሰጥ - ለህግ እና ስርዓት ቅንጣት ታክል ደንታ እንዳይኖረን - ባህል፣ ወግ ፣ አብሮነት ለሚባለው ጉዳይ ቦታ እንደሌለን - ነገ እኔስ ምን ይገጥመኛል ? ምን እሆን ይሆን ? በህይወት አጋጣሚ የት እሄዳለሁ ፣ ምን አካባቢ እገኛለሁ የሚለውን ለማገናዘብ እንኳን እንዳንችል ያደርገናል። ሰዎች ወደው ሳይሆን በስርዓት፣ በግለሰቦች፣ በአንቂዎች ፣ በሚዲያዎች... አማካኝነት ነው ጥላቻ እንዲውጣቸው እና ማገናዘብ ፣ ቆም ብሎ ማሰብ የሚባለውን መሰረታዊ ነገር እንዲያጡት የሚሆነው። ሰዎች ከመሰል ድርጊታቸው እንዲታቀቡ አብሮነት ፣ ፍቅር ፣ መግባባት፣ መከባበር ፣ ህግ ፣ ስርዓት፣ ወንድማማችንነትን ከማስተማር ባለፈ በህግ ማረም ፣ ነገ መዘዙ የከፋ እየሆነ ስለሚሄድ ከወዲሁ እንዲገታ በአንድ ላይ ማውገዝ ፣ ተበዳይን መካስ ፣ እውነት ህግ የበላይ ነው የምንል ከሆነም ለራሳችን ስንል ህግን ሁሌም ማስከበር ነው። ዛሬ ላይ እንዲህ ያሉና ከዚህ ቀደምም በየሀገሪቱ ክፍሎች የሰማናቸው ፍጹም አደገኛ የሚባሉ ጉዳዮች የሳምንት አጀንዳ እየሆኑ እያለፉ ይመስለን ይሆናል ግን በእርግጠኝነት መዘዛቸው የከፋ ሊሆን ይችላል። ውጤታቸው ዛሬ ሳይሆን ውሎ አድሮ ምናልባትም አመታትን አልፎ ይታይ ይሆናል ስለሆነም እናስብበት ! ትውልዱን ከስህተቱ እናርመው ፤ ወገኑን እንዲጠላ ሳይሆን እንዲወድ ፣ እንዲያከብር እናስተምረው። በሁሉም ዘንድ አውቀናል ታውቀናል ፣ ዛሬ ስልጣን አለን፣ ሚዲያውም የኛው ነው የምንል ሰዎችም ' አይ የኔ ወገን ስለሆነ ፍጹም ጻዲቅ ነው ፣ አይሳሳትም ፣ ጀግና ነው ፣ ቢሳሳትም ምንም ችግር የለውም እኔ እከላከልለታለሁ ' ከሚል አደገኛ እና ብዙ መዘዘ ካለው አመለካከት መራቅ ይገባናል። #TikvahFamily #Ethiopia @tikvahethiopia
256 258195Loading...
12
#ATTENTION🚨 “ የካንሰር ሕመም እየጨመረ ነው ” - ዶክተር አስቻለው ወርቁ በኢትዮጵያ የካንሰር ተጠቂዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን፣ በተለይም ማኀበረሰቡ ትንቦሆ፣  አልኮል ነክ ነገሮችን ከመጠቀም እንዲታቀብ ጥሪ ቀረበ። ለካንሰር ሕሙማን የሕክምና አገልግሎት እየተሰጠ ቢሆንም በተለይ በኢትዮጵያ በኩል የፋይናንስ እጥረት ችግር እንደፈተነው ማቲዎስ ወንዱ ካንሰር ሶሳይቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል። ተቋሙ የ20ኛ ዓመት ምስረታውን በማስመልከት መግለጫ ሰጥቶ ነበር። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ካንሰር #በኢትዮጵያ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል ? በበሽታው የተጠቂ ሰዎች ቁጥር ቀነሰ ወይስ ጨመረ ? ሲል ጥያቄ አቅርቧል። የተቋሙ የቦርድ አባልና የውስጥ ደዌ ባለሙያው ዶክተር አስቻለው ወርቁ ምን አሉ ? “ በጣም እየጨመረ ነው ያለው። ለመጨመሩ የተለያዩ ምክንያቶች ይኖራሉ። በአጠቃላይ ተላላፊ ያልሆኑ በሽዎች እየጨመሩ ነው። የካንሰር ህመምም እየጨመረ ነው። ለምሳሌ፦ የሳንባ ካንሰርን ብናዬው ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ነው ያለው። የምንመረምረው ጥቂት ሰዎችን ስለሆነ በዚያችው ዳታ ተመርኩዘን ነው የምንገልጸው። ማኀበረሰቡን ያማከለ የዳሰሳ ጥናት ካልሰራን ቁጥሩን በትክክል መግለጽ ከባድ ነው። 10 ሰዎችን መርምሮ 5 ሕሙማን ቢገኝ 50 በመቶ ማለት አይቻልም። ምክንያቱም ያልተመረመሩ ብዙ ስለሚኖሩ። እንደ አጠቃላይ ካየነው ግን ፦ - የሳንባ፣ - የአንጀት፣ - የጉበት፣ - የማህፀን፣ - የደም ሴል ካንሰር ታማሚሞች ቁጥራቸው እጅግ ባጣም እየጨመረ ነው ያለው። ” ብለዋል። ካንሰር ዋነኛ የሞት እና የስቃይ ምክንያት እየሆነ መምጣቱን ቁጥሮች እንደሚያመላክቱ ተገልጿል። ለአብነት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ከሞቱ ሰዎች ካንሰር የመገኘት እድሉ ከፍ ብሏል። ምክንያቱም የሳንባ ካንሰር ካሉት የካንሰር ዝርዝሮች ወደ 6ኛ ደረጃ ላይ ነው ያለው ተብሏል። የማቲዎስ ወንዱ ካንሰር ሶሳይቲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወንዱ በቀለ ምን አሉ ? “ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትንባሆ መሸጥም መግዛትም እንዳይችል የሚነገርበት ጊዜ መቼ ነው ? ትንባሆ ነክ ነገሮች፣ አልኮል በሽታውን እያስፋፉት ነው።   ከ3,000 በላይ የካንሰር ሕሙማንና ቤተሰባቸውን እረድተናል። በአሁኑ ወቅት 175 ለካንሰር ሕሙማንና ለቤተሰባቦቸው፦ ° ከአገራቸው የሚመጡበት ሙሉ የትራንስፖርት፣ ° ከውጪ የሚገዙ መድኃኒቶች፣  ° በሆስፒታል ውጪ በግል ተቋማት ለሚሰሩ የላብራቶሪ ምርመራ፣  ° ሆስፒታል ለተኙት ሕሙማን ለአንዳንድ ነገር መሸፈኛ በወር 1,000 ብር፣ ° እየታከሙ ለሚማሩ ተማሪዎች በወር 1,000 ብር፣ ° 24 አልጋ ባለው የካንሰር ሕክምና ማዕከል በየዕለቱ ለቁርስ፣ ምሳ፣ በክሰስና እራት ወጪዎችን እየሸፈንን ነው። ” NB. ማቲዎስ ወንዱ የኢትዮጵያ ካንሰር ሶሳይቲ የአቶ ወንዱ በቀለ የ4 ዓመት ጨቅላ ልጃቸው በካንሰር በሽታ ሕይወቱ ማለፉን ተከትሎ ቤተሰቦቹ የደረሰባቸውን መሪር ሀዘን “ ማቲዎስ ቢሞትም ብዙ ማቲዎሶችን ማዳን እንችላለን ” በሚል መልካም አስተሳሰብ በመቀየር በ15 መስራች አባሎች ሚያዚያ 9 ቀን 1996 ዓ/ም የተመሠረተ ለካንሰር ሕሙማን የሕክምና አገልግሎት የሚሰጥ ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት ነው። #TikvahEthiopiaFamilyAA @tikvahethiopia
262 998206Loading...
13
#ATTENTION🚨 “ የካንሰር ሕመም እየጨመረ ነው ” - ዶክተር አስቻለው ወርቁ በኢትዮጵያ የካንሰር ተጠቂዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን፣ በተለይም ማኀበረሰቡ ትንቦሆ፣  አልኮል ነክ ነገሮችን ከመጠቀም እንዲታቀብ ጥሪ ቀረበ። ለካንሰር ሕሙማን የሕክምና አገልግሎት እየተሰጠ ቢሆንም በተለይ በኢትዮጵያ በኩል የፋይናንስ እጥረት ችግር እንደፈተነው ማቲዎስ ወንዱ ካንሰር ሶሳይቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል። ተቋሙ የ20ኛ ዓመት ምስረታውን በማስመልከት መግለጫ ሰጥቶ ነበር። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ካንሰር #በኢትዮጵያ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል ? በበሽታው የተጠቂ ሰዎች ቁጥር ቀነሰ ወይስ ጨመረ ? ሲል ጥያቄ አቅርቧል። የተቋሙ የቦርድ አባልና የውስጥ ደዌ ባለሙያው ዶክተር አስቻለው ወርቁ ምን አሉ ? “ በጣም እየጨመረ ነው ያለው። ለመጨመሩ የተለያዩ ምክንያቶች ይኖራሉ። በአጠቃላይ ተላላፊ ያልሆኑ በሽዎች እየጨመሩ ነው። የካንሰር ህመምም እየጨመረ ነው። ለምሳሌ፦ የሳንባ ካንሰርን ብናዬው ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ነው ያለው። የምንመረምረው ጥቂት ሰዎችን ስለሆነ በዚያችው ዳታ ተመርኩዘን ነው የምንገልጸው። ማኀበረሰቡን ያማከለ የዳሰሳ ጥናት ካልሰራን ቁጥሩን በትክክል መግለጽ ከባድ ነው። 10 ሰዎችን መርምሮ 5 ሕሙማን ቢገኝ 50 በመቶ ማለት አይቻልም። ምክንያቱም ያልተመረመሩ ብዙ ስለሚኖሩ። እንደ አጠቃላይ ካየነው ግን ፦ - የሳንባ፣ - የአንጀት፣ - የጉበት፣ - የማህፀን፣ - የደም ሴል ካንሰር ታማሚሞች ቁጥራቸው እጅግ ባጣም እየጨመረ ነው ያለው። ” ብለዋል። ካንሰር ዋነኛ የሞት እና የስቃይ ምክንያት እየሆነ መምጣቱን ቁጥሮች እንደሚያመላክቱ ተገልጿል። ለአብነት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ከሞቱ ሰዎች ካንሰር የመገኘት እድሉ ከፍ ብሏል። ምክንያቱም የሳንባ ካንሰር ካሉት የካንሰር ዝርዝሮች ወደ 6ኛ ደረጃ ላይ ነው ያለው ተብሏል። የማቲዎስ ወንዱ ካንሰር ሶሳይቲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወንዱ በቀለ ምን አሉ ? “ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትንባሆ መሸጥም መግዛትም እንዳይችል የሚነገርበት ጊዜ መቼ ነው ? ትንባሆ ነክ ነገሮች፣ አልኮል በሽታውን እያስፋፉት ነው።   ከ3,000 በላይ የካንሰር ሕሙማንና ቤተሰባቸውን እረድተናል። በአሁኑ ወቅት 175 ለካንሰር ሕሙማንና ለቤተሰባቦቸው፦ ° ከአገራቸው የሚመጡበት ሙሉ የትራንስፖርት፣ ° ከውጪ የሚገዙ መድኃኒቶች፣  ° በሆስፒታል ውጪ በግል ተቋማት ለሚሰሩ የላብራቶሪ ምርመራ፣  ° ሆስፒታል ለተኙት ሕሙማን ለአንዳንድ ነገር መሸፈኛ በወር 1,000 ብር፣ ° እየታከሙ ለሚማሩ ተማሪዎች በወር 1,000 ብር፣ ° 24 አልጋ ባለው የካንሰር ሕክምና ማዕከል በየዕለቱ ለቁርስ፣ ምሳ፣ በክሰስና እራት ወጪዎችን እየሸፈንን ነው። ” NB. ማቲዎስ ወንዱ የኢትዮጵያ ካንሰር ሶሳይቲ የአቶ ወንዱ በቀለ የ4 ዓመት ጨቅላ ልጃቸው በካንሰር በሽታ ሕይወቱ ማለፉን ተከትሎ ቤተሰቦቹ የደረሰባቸውን መሪር ሀዘን “ ማቲዎስ ቢሞትም ብዙ ማቲዎሶችን ማዳን እንችላለን ” በሚል መልካም አስተሳሰብ በመቀየር በ15 መስራች አባሎች ሚያዚያ 9 ቀን 1996 ዓ/ም የተመሠረተ ለካንሰር ሕሙማን የሕክምና አገልግሎት የሚሰጥ ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት ነው። ThikvaEthiopiaFamilyAA @tikvahethiopia
10Loading...
14
" የሟች ኪስ ውስጥ #ማንነቱን የሚገልጽ መረጃ ስላላገኘን ፎቶውን ለማሰራጨት ተገደናል "  - የዓዲግራት ከተማ ፓሊስ በትግራይ ምስራቃዊ ዞን ዓዲግራት ከተማ  ቀበሌ 03 በተባለ መጠጥ ቤቶች በብዛት በሚገኙበት ቦታ ሚያዝያ 9/2016 ዓ.ም ሌሊት አሰቃቂ ግድያ ተፈፅሟል። አስቃቂ ግድያው በመፈፀም የተጠረጠሩ 3 ግለሰቦች በህዝብ ጥቆማ የሟቹ አስከሬን በወደቀበት አከባቢ በሚገኝ መጠጥ ቤት በቁጥጥር ስር ውለው የሟች አስከሬን ወደ ዒድግራት ሆስፒታል ተወስደዋል። የዓዲግራት ከተማ ፓሊስ ምርመራው ጨርሶ ለቀብር የሟቹ ቤተሰብ ቢያፈላልግም ዜናው እስከ ተጠናቀረበት ቀን ሰዓትና ደቂቃ የሟች ቤተሰብ አልተገኙም። በሟቹ ኪስ ማንነቱ የሚጠቅስ መረጃ እንዳላገኘ የገለፀው የዓዲግራት ፓሊስ ፤ የሟቹ ፎቶ በሚድያና በማህበራዊ የትስስር ገፅ ለማስራጨት መገደዱን ገልጿል። ሟቹን የሚያውቅ ካለ ወደ ዓዲግራት ከተማ ፓሊስ ፅህፈት ቤት ደውሎ እንዲያሳውቅ ፖሊስ ትብብር ጠይቋል። #TikvahEthiopiaFamilyMekelle ፍቶ፦ የዓዲግራት ከተማ ፓሊስ ፅህፈት ቤት                                                @tikvahethiopia            
238 33473Loading...
15
" የሟች ኪስ ውስጥ #ማንነቱን የሚገልጽ መረጃ ስላላገኘን ፎቶውን ለማሰራጨት ተገደናል "  - የዓዲግራት ከተማ ፓሊስ በትግራይ ምስራቃዊ ዞን ዓዲግራት ከተማ  ቀበሌ 03 በተባለ መጠጥ ቤቶች በብዛት በሚገኙበት ቦታ ሚያዝያ 9/2016 ዓ.ም ሌሊት አሰቃቂ ግድያ ተፈፅሟል። አስቃቂ ግድያው በመፈፀም የተጠረጠሩ 3 ግለሰቦች በህዝብ ጥቆማ የሟቹ አስከሬን በወደቀበት አከባቢ በሚገኝ መጠጥ ቤት በቁጥጥር ስር ውለው የሟች አስከሬን ወደ ዒድግራት ሆስፒታል ተወስደዋል። የዓዲግራት ከተማ ፓሊስ ምርመራው ጨርሶ ለቀብር የሟቹ ቤተሰብ ቢያፈላልግም ዜናው እስከ ተጠናቀረበት ቀን ሰዓትና ደቂቃ የሟች ቤተሰብ አልተገኙም። በሟቹ ኪስ ማንነቱ የሚጠቅስ መረጃ እንዳላገኘ የገለፀው የዓዲግራት ፓሊስ ፤ የሟቹ ፎቶ በሚድያና በማህበራዊ የትስስር ገፅ ለማስራጨት መገደዱን ገልጿል። ሟቹን የሚያውቅ ካለ ወደ ዓዲግራት ከተማ ፓሊስ ፅህፈት ቤት ደውሎ እንዲያሳውቅ ፖሊስ ትብብር ጠይቀዋል። #TikvahEthiopiaFamilyMekelle ፍቶ፦ የዓዲግራት ከተማ ፓሊስ ፅህፈት ቤት                                                @tikvahethiopia            
10Loading...
16
#Ethiopia #Attention🚨 የትራፊክ አደጋ የበርካቶች ህይወት እየቀጠፈ ይገኛል። በዚህ ወር ብቻ ፦ - በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ 2 ሰዎች ሲሞቱ 5 ሰዎች ተጎድተዋል። - በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን ዶዶላ ወረዳ ከኔጌሌ ወደ ዶዶላ ተሳፋሪዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ መኪና 'አላንቱ' ላይ ከ " ሲኖትራክ " የጭነት መኪና ጋር ተጋጭቶ የ15 ሰዎች ህይወት አልፏል። ሌሎችም ተጎድተዋል። - በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በካፋ ዞን ጨና ወረዳ ፤ ከዋቻ ወደ ቦንጋ ሲጓዝ የነበረ ዶልፊን ተሸከርካሪ እና ከሚዛን ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ #ሲኖ_ትራክ ተሸከርካሪ በጨና ወረዳ ቦባ በላ ቀበሌ ተጋጭተው 5 ሰዎች ሲሞቱ 13 ሰዎች ተጎድተዋል። -  በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን በእዣ ወረዳ ወርት በተባለች ቀበሌ እንጨት ጭኖ ሲጓዝ የነበረ #ሲኖ_ትራክ የጭነት ተሽከርካሪ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ   የ6 ወጣቶች ህይወት ወዲያዉ ሲያልፍ በ10 ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሷል። አደጋዉን የከፋ ያደረገው ሲኖ ትራኩ  ወጣቶችን እንጨት ላይ አሳፍሮ እየተጓዘ ባለበት ወቅት አደጋው በመድረሱ ነው። ከላይ በተጠቀሰው እና በይፋ በታወቀው ብቻ 28 ዜጎች በትራፊክ አደጋ ህይወታቸውን አጥተዋል። በርካቶች የአካል ጉዳተኛ ሆነው። እባካችሁ ጥንቃቄ አይለያችሁ ! @tikvahethiopia
234 41639Loading...
17
#Ethiopia #Attention🚨 የትራፊክ አደጋ የበርካቶች ህይወት እየቀጠፈ ይገኛል። በዚህ ወር ብቻ ፦ - በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ 2 ሰዎች ሲሞቱ 5 ሰዎች ተጎድተዋል። - በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን ዶዶላ ወረዳ ከኔጌሌ ወደ ዶዶላ ተሳፋሪዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ መኪና 'አላንቱ' ላይ ከ " ሲኖትራክ " የጭነት መኪና ጋር ተጋጭቶ የ15 ሰዎች ህይወት አልፏል። ሌሎችም ተጎድተዋል። - በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በካፋ ዞን ጨና ወረዳ ፤ ከዋቻ ወደ ቦንጋ ሲጓዝ የነበረ ዶልፊን ተሸከርካሪ እና ከሚዛን ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ #ሲኖ_ትራክ ተሸከርካሪ በጨና ወረዳ ቦባ በላ ቀበሌ ተጋጭተው 5 ሰዎች ሲሞቱ 13 ሰዎች ተጎድተዋል። -  በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን በእዣ ወረዳ ወርት በተባለች ቀበሌ እንጨት ጭኖ ሲጓዝ የነበረ #ሲኖ_ትራክ የጭነት ተሽከርካሪ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ   የ6 ወጣቶች ህይወት ወዲያዉ ሲያልፍ በ10 ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሷል። አደጋዉን የከፋ ያደረገው ሲኖ ትራኩ  ወጣቶችን እንጨት ላይ አሳፍሮ እየተጓዘ ባለበት ወቅት አደጋው በመድረሱ ነው። ከላይ በተጠቀሰው እና በይፋ በታወቀው ብቻ 28 ዜጎች በትራፊክ አደጋ ህይወታቸውን አጥተዋል። በርካቶች የአካል ጉዳተኛ ሆነው። እባካችሁ ጥንቃቀ አይለያችሁ ! @tikvahethiopia
50Loading...
18
የረቂቅ መንገድ እራሳችንን እንደመስታወት የምናይበት…ሌሎችን እንደ መፅሐፍ የምናነብበት! የጠፋብን ያልተገለጠልን ነገር ካለ ያለጥርጥር የረቂቅ መንገድ ላይ እናገኘዋለን። በቅርብ ቀን በአቦል ቲቪ 465! የዲኤስቲቪ ዲኮደር በ1,999 ብር ከ1 ወር ነፃ የሜዳ ፓኬጅ ጋር ያገኛሉ። የዲኤስቲቪ የተለያዩ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram ሊንክ ይጫኑ! 👇 https://bit.ly/2WDuBLk #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #YerekikMenged #የረቂቅመንገድ
202 83222Loading...
19
"ጥበብ እንደ መፈወሻ መንገድ/  Art as a path to healing" ኦላይን የስዕል ኤግዚቢሽን በትግራይ መቐለ ከተማ ከወርሃ የካቲት እስከ ሚያዝያ 2016 ዓ.ም ሲካሄድ የቆየውና ከ387 ተመዝጋቢዎች የተመረጡ 61 ታዳጊና ወጣት ሰአልያን የተሳተፉበት የቡድን የስእል ውድድር አሸናፊዎችን በመለየት ተጠናቋል። በውድድሩ ወጣቶቹ በ10 ቡድን በመከፋፈል 10 ስዕሎችን ያቀረቡ ሲሆን፤ ስዕሎቹም ጦርነትን፣ ዘረኝነትን፣ የእርስ በርስ ግጭትና ጠባብነት በማውገዝ ሰላም አንድነት ስር እንዲሰድ የሚሰብኩ ነበሩ። እነዚህን ስዕሎች ኦላይን በተዘጋጀው ኤግዚቢሽን እንድትመለከቷለቸው እንጋብዛለን። ወደ ኤግዚቢሽኑ ጎራ ለማለት ተከታዩን ሊንክ ይጠቀሙ https://redeem.tikvahethiopia.net/paintings #USAID     #RTG   #TikvahEthiopia
235 86137Loading...
20
" ጥናቱ ሙሉ በሙሉ ቆሟል " - የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር የሚገኙ የመንግሥት ተቋማት አገልግሎት የሚሰጡበትን ሰዓት ከስምንት ወደ 16 ሰዓት ለማራዘም የተጀመረው ጥናት መቆሙን የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታውቋል። ጥናቱ የተጀመረው በከተማ አስተዳደሩ ሥር በሚገኙ የመንግሥት ተቋማት የሚሠሩ ሠራተኞች የግል ገቢ እንዲኖራቸው፣ እንዲሁም የከተማዋን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማነቃቃት ታስቦ መሆኑን ቢሮው ማስታወቁ ይታወሳል። አሁን ላይ ግን የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የሥራ ሰዓት ለማራዘም የተጀመረው ጥናት ሙሉ ለሙሉ ቆሟል፡፡ የከተማው የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ጣሰው ገብሬ (ዶ/ር) ፥ " የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችን የሥራ ሰዓት ለማራዘም መነሻ ጥናት ተደርጎ ነበር ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ የለም " ሲሉ ለሪፖርተር ጋዜጣ ተናግረዋል። ኃላፊው በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ መስጠት እንደማይፈልጉ ተናግረዋል። ወደፊት የታሰበው አሠራር ተግባራዊ ይደረጋል አይደረግም የሚለውን እንደማያውቁ ገልጸዋል። ጥናቱ የተጀመረው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር የሚገኙ መሥሪያ ቤቶችን የሥራ ሰዓት ከጠዋቱ 2፡30 አስቀድሞ ለማስጀመርና ከ11፡30 በኋላ እስከ ምሽት ለማስቀጠል ታቅዶ ነበር፡፡ ዕቅዱ ይፋ የተደረገው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ የከተማዋ መ/ቤቶች አገልግሎት አሰጣጥን አስመልክቶ መሆኑን ቢሮው ግንቦት 3 ቀን 2015 ዓ.ም. ከባለድርሻ አካላት ጋር ባደረገው ውይይት መግለጹን ሪፖርተር ጋዜጣ በዘገባው አስታውሷል። @tikvahethiopia
270 151191Loading...
#Update የ " ቲክቶክ " እገዳ በኪርጊስታን ተግባራዊ ሆነ። ኪርጊስታን " ቲክቶክ " በመላ ሀገሪቱ  እንዲታገድ ውሳኔ ማስለፏ ይታወሳል በዚሁ ውሳኔ መሰረት የቴሌኮም አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶች ትዕዛዙን ወደ መፈጸም #እርምጃ ገብተዋል። በሀገሪቱ " ቲክቶክ " መስራት እንዳቆመም ተነግሯል። ሰዎች መተግበሪያውን ሲከፍቱን የሚያገኙት መልዕክት " Unable to load, please try again." የሚል ነው። ውሳኔው በሀገሪቱ ብሔራዊ ደህንነት መ/ቤት የተላለፈ ነው። የኪርጊስታን ዲጂታል ሚኒስቴር ቲክቶክን የሚያስተዳድረው ' ባይት ዳንስ ' ኩባንያ ፥ " #የልጆችን ፦ - አእምሯዊ፣ - አካላዊ፣ - መንፈሳዊ እና #ሥነምግባራዊ እድገትን ለመጠበቅ በህግ የተዘረዘሩ ህጋዊ መስፈርቶችን ማክበር አልቻለም " ብሏል። በዚህም ምክንያት " ቲክቶክ " በሀገሪቱ እንዳይሰራ ተደርጓል። ውሳኔው የተቃወሙ አካላት ይህ ተገቢ እንዳልሆነ በመግለጽ ገደቡ እንዲነሳ ጠይቀዋል። ከገደብ ይልቅ ቁጥጥር ይደረግበት ብለዋል። ከዚህ ቀደም የኪርጊስታን የባህል፣ ወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴር ፥ " ቲክቶክ " የተሰኘው መተግበሪያ ለልጆች አእምሯዊ እድገት እና አጠቃላይ ደህንነት ጠንቅ እየሆነ ነው " ማለቱ ይታወሳል። መተግበሪያው #ህጻናት እጅግ ጎጂ ሊሆኑ የሚችሉ ይዘቶችን እንዳያገኙ ለመከላከል በቂ #መቆጣጠሪያ እንደሌለው ነበር የገለጸው። በተጨማሪም ለተጠቃሚዎቹ ትክክለኛ የዕድሜ ማረጋገጫ እርምጃዎች እንደለለው እና ተጠቃሚዎችን በአጫጭር የቪዲዮ ክሊፖች ወደ ምናባዊ ግዛት በመሳብ #ሱስ የሚያስይዝ ይዘት እንዳለው አስረድቶ ነበር። ሚኒስቴሩ " ቲክቶክ " በወጣቱ ትውልድ ደህንነት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንዳለው በአጠቃላይም ለትውልዱ ጠንቅ እየሆነ እንደመጣ አሳውቆ ነበር። በሌላ በኩል ፤ አሜሪካ ውስጥ ከመረጃ ደህንነት ጋር በተያያዘ መተግበሪያው እንዲታገድ ከፍተኛ ግፊት እየተደረገ ሲሆን  " ቲክቶክ " ከቻይናው ኩባንያ ካልተፋታ / አሜሪካ የምትቆጣጠረው አይነት ካልሆነ በመላ ሀገሪቱ መታገድ ዕጣ ፋንታ ሊገጥመው ይችላል ተብሏል። @tikvahethiopia
نمایش همه...
👏 354 20😭 13😡 10🙏 6🕊 6😢 4😱 3🤔 1
የከባድ መኪና ሆነ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ሹፌሮች በተለያዩ ወቅቶችና ቦታዎች በታጣቂዎች የሚደርስባቸውን ፦ - ግድያ ፣ - እገታ ፣ እምዲሁም የተሽከርካሪዎች ቃጠሎ በተመለከተ በተደጋጋሚ መረጃዎችን መለዋወጣችን ይታወሳል። ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን መቂ አካባቢ “ የታጠቁ ኃይሎች ” በአሽከርካሪና ረዳት ላይ ጉዳት እንዳደደረሱ ፣ ከወራት በፊትም በርካታ ተሽከርከርካሪዎች ታቃጥለው እንደነበር ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ ነዋሪዎች ገልጸዋል። ቃላቸውን የሰጡ የመቂ ነዋሪ ፥ አንድ የአይሱዚ ሹፌር ሲገደል ፣ ረዳቱ አካላዊ ጉደት እንደረሰበትና ሌሎች ተሽከርካሪዎች በጥይት እንደተበሳሱ አስረድተዋል። " የተኩስ እሩምታ ተከፍቶባቸው ሹፌሩ ተገደለ። ሚያዚያ 9 ቀን 2016 ዓ/ም ነው የተቀበረው ፤ ረዳቱም ቆሰለ " ሲሉ ነው የተናገሩት። የተኩስ እሩምታ የተከፈተባቸው ከ7 በላይ ተሽከርካሪዎች መሆናቸውን ጠቁመው " ተዘግቦ እንኳን አየዋለሁ ብዬ ነበር የዘገበው ሚዲያ የለም " ብለዋል። ሟቹ ሹፌር መነሻውን አዲስ አበባ በማድረግ እየተጓዘ በነበረበት ወቅት መቂ አካባቢ ማታ ላይ በታጣቂዎች ተኩስ እንደተከፈተበት አስረድተዋል። " ሌሎቹ ሹፌሮች ፈጣሪ አትርፏቸው አልተጎዱም። ተሽከርካሪዎቻቸው ግን በጥይት ተበሳስተዋል። ጎማው እስከ 15 ጥይት  ያረፈበት አለ " ብለዋል።   እኚሁ ነዋሪ ታጣቂዎች " ወደ ኦሮሚያ ተሽከርካሪ እንዳይሄድ ሰሞኑን እቀባ ጥለዋል " ያሉ ሲሆን ጥቃቱን በከፈቱ በማግስቱ  " ከመከላከያ ጋ ተታኩሰዋል "  ሲሉ ገልጸዋል። ሌላኛው ነዋሪ ፤ የዛሬ ወር ገደማ በተመሳሳይ እዛው ቦታ/መቂ ብዙ ተሽከርካሪዎች ተቃጥለዋል ሲሉ አስታውሰዋል። " ጥቃቱ አለ አሁንም አልቆመም። የተወሰነ ጊዜ መከላከያ ሲመጣ ጋብ ይላል እንጂ። ሹፌሮች ስቃይ ላይ ናቸው " ብለዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ እጅግ ትኩረት ይሻል የተባለውን የሹፌሮችን ጥቃት በተመለከተ ከክልሉም ሆነ ከዞኑ ኃላፊዎች ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ተደጋጋሚ ጥረት ለጊዜው ያልተሳካ ሲሆን፣ ምላሽ የሚሰጡ ከሆነ የሚያስተናግዳቸው መሆኑን ያሳውቃል። NB. መቂ ከሰሞኑን ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር ፓርቲ (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር ግድያን ያስተናገደች ከተማ ናት። #TikvahEthiopiaFamilyAA @tikvahethiopia
نمایش همه...
😭 179 23😢 17🕊 13😡 10🤔 7🙏 2👏 1
" የመምህራን የስነ-ልቦና ቁስል ሳይሽር ስለ የትምህርት ጥራት ማረጋገጥ ማሰብ ይከብዳል "  - ማህበሩ የትግራይ መምህራን ማህበር በድጋሚ የመምህራን የ17 ወራት ውዙፍ ደመወዛቸው እንዲከፈል ጠየቀ። የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደርንም ዳግም አስጠነቅቋል።  ማህበሩ ሚያዚያ 8 በኣክሱም ከተማ 33ኛው ጉባኤውን አካሂዶ ነበር። በጉባኤው ማጠቃለያ ባወጣው የአቋም መግለጫ " የትግራይ መምህራን የ17 ወራት ውዙፍ ደመወዛቸው እንዲከፈል " ሲል ጠይቋል።   የማህበሩ ስራ አስፈፃሚ እስከ ግንቦት 7 ቀን 2016 ዓ.ም ባለው ጊዜ ከሚመለከታቸው የጊዚያዊ አስተዳደሩ አመራሮች ጋር በመገናኘት ስለ ውዙፍ ደመወዝ መከፈል የመጨረሻ አቋሙ እንደሚያሳውቅ አመልክቷል። ለጥያቄው በጊዜ ገድብ የተወሰነ አሳማኝ መልስ ካላገኘ ጠበቃ አቁሞ ክስ እንደሚመሰርት አሳውቋል። " ተቃውሟችን እና ጥያቄያችን ትምህርት ቤቶች በመዝጋትና ተተኪ ዜጋ በመጉዳት የማሳካት ፍላጎት የለንም " ያለው ማህበሩ " ግዴታችን እየፈፀምን መብታችን እስከ ጫፍ እንጠይቃለን " ብሏል። " የመምህራን የስነ-ልቦና ቁስል ሳይሽር በትምህርት ስለሚገነባው ትውልድና የትምህርት ጥራት ማረጋገጥ ማሰብ ይከብዳል "  ሲልም አክሏል። ማህበሩ የመምህራን ጥያቄ እስኪመለስ ህጋዊ ተቋውሞ ማሰማቱን እንደሚቀጥል አረጋግጧል። መረጃውን የመቐለው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ፥ ድምጺ ወያነ ቴሌቪዥንን ዋቢ አድርጎ ነው የላከው።        @tikvahethiopia            
نمایش همه...
🥰 242 83👏 69🙏 36🕊 29😢 27😡 17😭 15😱 3
" ልጄን አድኑልኝ " - መምህርቷ እናት መምህርት አልሻምጌጥ ንጉስ ፤ ልጇ የአብቃል በተወለደ በሀያ አንድ ቀኑ ነው የልብ ህመም እንዳለበት ያወቀችው። ላለፉት 5 አመታት የህጻናት የልብ ቀዶ ጥገና መዕከል አስመዝባ ብጠብቅም ወረፋ ሊደርሳት አልቻለም። " አሁን ልጄ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ደረሰ " ስትል ገልጻለች። ከሀያ አንድ ቀኑ ጀምሮ ከሀዋሳ አዲስ አበባ እየተመላለሰች ሰርጀሪውን ስትጠብቅና ማስታገሻ መድሀኒት ስትጠቀም ብትቆይም እንደልጅነቱ መቦረቅ ያልቻለው የአብቃል  " አሁን ላይ የልቡ ክፍተት አራት ሚሊ በመድረሱ እብጠት ፈጥሮበታል " ስትል አስረድታችለ። ይህ እብጠት ምግብ እንዳይረጋለት ከማድረጉ በላይ በአፍና በአፍንጫዉ ደም መውጣት መጀመሩ እና ድንገት በየሰአቱ እራሱን ከመሳቱ በተጨማሪ ፍጹም የድካም ስሜት ውስጥ እንዲገባ በማድረጉ ለቤተሰቡ ታላቅ ድንጋጤ ፈጥሯል። ይህን ተከትሎ ጤና ባለሙያዎች በቶሎ ሰርጀሪዉ መሰራት እንዳለበት ቢናገሩም የመምህር ደሞዙን ከእለት ጉርስ አበቃቅቶ ለመድሀኒት ሲጠቀም ለቆዉ የመምህር አልሻምጌጥ ቤተሰብ ዱብ እዳ ሆኖበታል። ቤተሰብም አሁን ላይ የሚያደርገዉ ጠፍቶበታል። በጉዳዩ ላይ ለኢትዮጵያ ህዝብ በቲኪቫህ ኢትዮጵያ በኩል መልእክት አስተላልፉልኝ የምትለው እናት አሁን ላይ በግል ሆስፒታል ለሰርጀሪዉ ብቻ 650 ሽህ ብር እንደተጠየቀ በአጠቃላይ ከ800 እስከ 900  ሽህ ብር እንደሚያስፈልግ ገልጸለች። ይህን ማድረግ ባለመቻሏ እና ገንዘብም ስለሌላት ልጇን አይኗ እያዬ ልታጣዉ መሆኑን በእንባ ተናግራለች። በመሆኑም ፥ " ደጉ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚቻለዉን አድርጎ ልጄን ያድንልኝ " በማለት ተማጸናለች። መምህር አልሻምጌጥ ንጉስን በስልክ ማነጋገር የሚፈልግ የግል ስልክ ቁጥሯ 0916155490 ነው። ይህ ደግሞ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000243926053 የሂሳብ ቁጥሯ ነው። @tikvahethiopia
نمایش همه...
😭 855🙏 255 95😢 34🕊 26🥰 9😡 4👏 3😱 2
የፋሲካ ኤክስፖ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል የመግቢያ ትኬትዎን በቴሌብር *127# ወይም http://onelink.to/fpgu4m በመግዛት ጎራ ይበሉ፤ እስከ ብር 2500 ለሚደርሰው ግብይትዎ የአየር ሰዓት እና ጥቅል የሚገዙበት 10% ተመላሽ ያግኙ፡፡ #Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
نمایش همه...
👏 7 2
#BankofAbyssinia በተለያዩ ቦታዎች በአፖሎ ሲከፍሉ ቅናሽ ያገኛሉ! አሁኑኑ መተግበሪያውን በማውረድ ይጠቀሙ። ለአንድሮይድ ስልኮች https://play.google.com/store/apps/details?id=com.boa.apollo&hl=en&gl=US ለአፕል ስልኮች https://apps.apple.com/us/app/apollo-digital/id1601224628#Apollodigitalbank #Apollodigitalproduct #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
نمایش همه...
18🕊 1
#Update " የሟች ቤተሰብ ተገኝቷል " - ፖሊስ በሟች ኪስ ማንነቱ የሚጠቅስ መረጃ በማጣቱ  ምክንያት የሟችን ፎቶ በመለጠፍ  ቤተሰቦቹን አፋልጉኝ ያለው የዓዲግራት ከተማ ፓሊስ የሟች ቤተሰብ መገኘቱ አስታውቋል። የማህበራዊ የትስስር ገፆችና ሚድያዎች በሟች ቤተሰብ ፍለጋ ያደረጉት የነቃ ወገናዊ ተሳትፎና ጥረት አመስግኗል። ለሟቹ ቤተሰብ ክብር ሲባል ፎቶውን ከገፃቸው በማጥፋት እንዲተባበሩ ጥሪ አቅርቧል። በዚህም መሰረት ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለሟች ቤተሰብ ክብር የሟችን ፎቶ #ማጥፋቱን ለመላ አባላቱ መግለጽ ይወዳል። ምናልባት በውስጥ የተቀባበላችሁም የሟችን ፎቶ ከስልካችሁ እንድታጠፉ እንጠይቃለን። ሚያዝያ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ሌሊት በዓዲግራት ከተማ አንድ ወጣት ተገድሎ ተጥሎ መገኘቱንና በግድያው የተጠረጠሩ 3 ግለሰቦች ሟቹ ከወደቀበት አቅራቢያ በሚገኝ አንድ መጠጥ ቤት በቁጥጥር ስር መዋላቸው መረጃ እንደላክልንላችሁ ይታወሳል። #TikvahEthiopiaFamilyMekelle @tikvahethiopia
نمایش همه...
😢 685🙏 159 147😭 85👏 55🕊 38😱 16🥰 14🤔 7😡 7
#Update በኢራን " ኢስፋሃን ከተማ " ዛሬ ማለዳ ፍንዳታዎች የተሰምተው ነበር። ይህች ከተማ የአገሪቱ አየር ኃይል መቀመጫ ፣ በርካታ ወታደራዊ ተቋማት ያሉባት ናት። የኢራን መገናኛ ብዙኃን በደፈናው 3 ድሮኖች በኢራን የአየር መከላከያ ሥርዓት ወድመዋል ሲሉ ገልጸዋል። #የአሜሪካ ባለልስጣናት እስራኤል ቅዳሜ ለተፈጸመባት ጥቃት ኢራን ላይ የሚሳኤል የአጸፋ ጥቃት ፈጽማለች ብለዋል። የኢራን በይፍ የሰጠችው ማብራሪያ ባይኖርም የተሰማው ፍንዳታ ጥቃትን የማክሸፍ እንደነበር አሁን ላይ ከተማዋ በመደበኛ እንቅስቃሴ እንደምትገኝ ገልጸዋል። የደረሰ አንዳች ጉዳት እንደሌለ ጠቁመዋል። በኑክሌር ተቋማት ላይ ምንም ጉዳት አለመድረሱን ተነግሯል። ምንም እንኳን በመገናኛ ብዙሃን እና በአሜሪካ ባለስልጣናት እስራኤል የጸፋ እርምጃ መውሰዷ ቢነገርም ሀገሪቱ እስካሁን በይፋ " ኃላፊነት እወስዳለሁ " አላለችም። ኢራንም ፥ " እስራኤል ናት ይህንን ያደረገችው ቀጣይ እርምጃዬ ይሄ ነው " የሚል ይፋዊ ቃል አልሰጠችም። ነገር ግን ጉዳዩ አሁንም በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ስጋትን እንደደቀነ ይገኛል። ሀገራት ከወዲሁ በእስራኤል ላሉ ዜጎቻቸው ማስጠንቀቂያ እየሰጡ ናቸው። ኢራን እስራኤልን ከቀናት በፊት መደብደቧን ተከትሎ እስራኤል የአፀፋ እርምጃ እንደማይቀርላት ተናግራለች። ኢራንም እስራኤል የአጸፋ እርምጃ እወስዳለሁ ካለች እስከ ዛሬ ጥቅም ላይ ያልዋለ መሳሪያ እንደምትጠቀምና እርምጃዋ ከመጀመሪያው እየከፋ እንደሚሆን አስጠንቅቃለች። ኢራን ፥ ጦርነቱ እንዲስፋፋ እንደማትፈልግ ነገር ግን ደፍሮ የሚያጠቃት የትኛውም አካል ካለ " እጁን እንቆርጥለታለን " ስትል ነው ከሰሞኑን የዛተችው። @tikvahethiopia
نمایش همه...
👏 658🕊 122 119😡 54😱 37😭 29🤔 23🥰 16🙏 9😢 8
#ሴጅ_ማሠልጠኛ 10ኛ ዙር ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Modern Accountancy and Auditing) ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን። 👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና 👉 መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ 👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት ☎️   0906777799 / 0906777755 አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute Facebook: https://www.facebook.com/sagetraininginstitute Instagram: https://www.instagram.com/sage_training_institute/ Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
نمایش همه...
25😡 1
ንጹሕ_ምንጭ _ኢትዮጵያ ሊፈፀም ጥቂት ቀናት ብቻ ቀረው
በግዮን ሆቴል እስከ ሚያዚያ 13 ብቻ፡፡
ለልጆችዎ ቦታ አለን
📌ማስታወሻ :- በተለይ ሚያዚያ 12 እና 13 ምሽት 11ሰአት ጀምሮ በዓይነቱ ልዩ የሆነ የኪነጥበብ ምሽት ከ ዐውደ ርእዩ ጋር በጥምረት ይቀርባል። 📌ማስታወሻ :- በተለየ መንገድ ቅዳሜ ሚያዚያ 12/2016ዓ.ም. የልጆች ልዩ የመዝናኛ ኪነ ጥበባዊ ዝግጅቶች ይካሄዳል። በእነዚህ መርሐ ግብሮች ላይ እንዲገኙ ለሌሎችም እንዲያጋሩ በታላቅ አክብሮት እንጋብዛችኋለን። ለበለጠ መረጃ ፦0966767676 ወይም 0944240000 ይደውሉ። INSTAGRAM | TELEGRAM | YOUTUBE | TWITTER | TIKTOK |WEBSITE
نمایش همه...
230🙏 16👏 12😡 8🥰 4😱 4🕊 3🤔 2😢 1😭 1