cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

መረጃ//mergaa

@ethomergaa 🎩ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ ፣ 🎩የአስተሳሰብ ምህዳሮች ፣ 🎩የምሁራን እይታዎች እና መጽሐፈቶች ፣ 🎩የአለም ሙሉ መረጃ እና የታሪክ ልዩ መዛግብቶች ። ለማንኛውም መረጃ 👉 @Natiyt ኢትዮጵያዊ ሆኘ የተወለድኩ ኢትዮጵያዊ ሆኘ ያደኩ ኢትዮጵያዊ ሆኘ መሞት የምፈልግ ኢትዮጵያዊ ነኝ። ኢትዮጵያ በክብር ለዘለአለም ትኑር አሜን !!! የናንተው ቻናል ነው

نمایش بیشتر
Advertising posts
1 791مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-117 روز
-3230 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ደቡብ ጎንደር❗❗ በደቡብ ጎንደር ደብረታቦር ከተማ ዛሬ አዳሩን ወረቀት በመበተኑ አዲስ ውጥረት መኖሩን የደረሰኝ መረጃ ይጠቁማል። ነዋሪዎቹ እንደሚሉት የተበተነው ወረቀት "የሀገር መከላከያ ሰራዊት እስከ መስከረም 3 ለቆ እንዲወጣ እና ካልሆነ ግን ከተማ ውስጥ ውጊያ እንደሚከፈት" የሚል ነው ብለዋል። በዚህ የተነሳ ይሄን ወረቀት በትነዋል የተባሉ ግለሰቦች እየታሰሩ ነው ብለዋል። @ayuzehabeshaofficial
نمایش همه...
ደፈጣ ጥቃት❗👇 በሰሜን ሸዋ ዞን ከደብረሲና ከተማ ዝቅ ብሎ በዋናው መስመር ልዩ ስሙ አርማኒያ በሚባል አካባቢ ትናንት 11:00 አካባቢ ሎጂስቲክ በጫኑ የመከላከያ ሰራዊት ተሽከርካሪዎች ላይ የደፈጣ ጥቃት ተፈፅሞ ጉዳት ደርሷል ብለዋል። በዚህም ለአንድ ሰዓት የቆየ የተኩስ ልውውጥ የተደረገ ሲሆን መንገዱ እስከ ምሽቱ 1:00 ድረስ ዝግ እንደነበር የአዩዘሀበሻ ምንጮች ገልጸዋል።
نمایش همه...
በደቡባዊ የመን በኢትዮጵያዊያን ስደተኞች መካከል የተደረገው ደም አፋሳሽ ፀብ ይህን ይመስላል። ያሳዝናል።
نمایش همه...
በአዲሱ ዓመት የሰው ሕይወትን የሚቀጥፉ የመሳሪያ አፈ ሙዞች በሙሉ ወደ መጋዝን መግባት አለባቸው ሲሉ አቡነ #ማትያስ ጥሪ አቀረቡ‼️ #የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ የዘመን መለወጫ በዓልን አስመልክተው ከሰሜን አሜሪካን ባስተላለፉት ያሳለፍነው አመት ችግሮች ወደ ቀጣይ #አመት እንዳይሸጋገሩ በማድረግ አዲሱን አመት እንቀበል ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። ብጹእነታቸው ባስተላለፉት መልዕክት በአዲሱ ዓመት የሰው ሕይወትን የሚቀጥፉ የመሳሪያ አፈ ሙዞች በሙሉ ወደ መጋዝን መግባት አለባቸው ሲሉ አሳስበዋል። ያለፈው ዓመት ያሳረፈብንን ሁለንተናዊ ተጽዕኖ በሚገባ አስተውለን፣ ዳግም ወደ አዲሱ ዓመት እንዳይሸጋገርብን ካላደረግን አዲሱ ዓመት ለኛ የሚሰጠን ትርጉም ምንድን ነው ሲሉ የጠየቁት ብጹእነታቸው ባለፉት ዓመታት በሃይማኖት፣ በባህል፣ በታሪክ፣ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊና ፖለቲካዊ እንዲሁም በሕዝባችን ሥር የሰደደውን የእርስ በርስ መጠራጠር ከልብ መርምረን ወደ ድሮው እኛነታችን ካልተመለከትንስ አዲስ ዘመን እያልን ማክበራችን ምን ፋይዳ የለውም ብለዋል። ያለፈውን ጎጂ ነገር በመተው፤ ጠቃሚውን ግን ይበልጥ በማጠናከር አዲሱን ዓመት መቀበል አለብን ሲሉ አሳስበዋል።
نمایش همه...
በምንጃር እና በኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ ኢጀሬ እና ማክሰኞ ገበያ ዛሬ ከፍተኛ የሚባል ውጥረት እንዳለ የደረሰኝ መረጃ ይጠቁማል። ሰሞኑን የተካሄደው ውጊያ ቆም ብሎ የነበረ ቢሆንም ዛሬ ግን ለየት ያለ ውጥረት እንዳለ እና በማንኛውም ሰዓት ተኩስ ሊጀመር ይቻላል ብለዋል።
نمایش همه...
ጥንቃቄ❗️ ከባዕድ ነገሮች ጋር የተቀላቀለ 1 ሺህ 440 ኪሎ ግራም ቅቤ ተያዘ‼️ በአዲስ አበባ ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ከባዕድ ነገሮች ጋር የተቀላቀለ 1 ሺህ 440 ኪሎ ግራም ቅቤ መያዙን የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አስታወቀ፡፡ በተጨማሪም ከቅቤ ጋር ሊቀላቀል የነበረ ንጽህናው ያልተጠበቀ 3 ሺህ 360 ኪሎ ግራም የአትክልት ቅቤ እና ፓልም ዘይት መያዙን ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ አየርጤና እና ቻይና ካምፕ አካባቢዎች በተደረገ ቁጥጥር እንዲሁም በህብረተሰቡ ጥቆማ ነው ከባዕድ ነገር ጋር የተቀላቀለ 1 ሚሊየን ብር ዋጋ ያለው ቅቤ የተያዘው፡፡ በተጨማሪም ከ650 ሺህ ብር በላይ ዋጋ ያለው ከቅቤ ጋር ለመቀላቀል የተዘጋጀ ንጽህናው ያልተጠበቀ የአትክልት ቅቤ እና የፓልም ዘይት መያዙን የባለስልጣኑ መረጃ ያመላክታል፡፡ከበዓላት ጋር በተያያዘ እንደዚህ አይነት ሕገ ወጥ ድርጊቶች ሊስተወሉ ስለሚችሉ ህብረተሰቡ የምግብ ምርቶችን ሲገዛ ፈቃድ ካላቸው ተቋማት መሆን እንዳለበት ባለስልጣኑ አሳስቧል፡፡እንዲሁም አጠራጣሪ ሁኔታዎችን ሲመለከትም በ8482 ነፃ የስልክ መስመር በመደወል ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል፡፡
نمایش همه...
አልሸባብ በኢትዮጵያ ላይ ሥጋት ደቅኗል ተባለ‼️ በሶማሊያ የሚገኘው የአፍሪካ ህብረት የሽግግር ተልዕኮ ወታደራዊ ኃይል (አትሚስ) በፈረንጆች 2024 ሙሉ ለሙሉ ከሶማሊያ ለቆ ሊወጣ በመሆኑ አልሸባብ ለኢትዮጵያ ስጋት ሆኗል ሲል ዓለም አቀፍ ጥናትና ትንታኔዎች በመስራት የሚታወቀው ዘጀምስ ታውን ፋውንዴሽን ባወጣው ዘገባ ገልጿል። ይህም የሽብር ቡድኑ ከሶማሊያ ጋር ረዥም ድንበር የምትዋሰነውን ኢትዮጵያ በመጪዎቹ ዓመታት ረጅም የሆነ ግጭት ዉስጥ ሊያስገባት እንደሚችል ጠቁሟል። አልሸባብ ከፈረንጆች 2006 እስከ 2009 በሶማሊያ ባደረገው ወረራ ይዞት ከነበረው በሞቃዲሾ የሚገኘው እስላማዊ ፍርድ ቤቶች ህብረት ከስልጣን እንዲወርድ መደረጉን ተከትሎ፤ በኢትዮጵያ ላይ ሰፊ ቅሬታ እንዳለውም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ ለ15 ዓመታት በሶማሊያ በቆየው የአፍሪካ ህብረት ወታደራዊ ኃይል ውስጥ ትልቅ ተሳትፎ የነበራት መሆኑን እና በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት ተልዕኮ እንዲሳካ ቁልፍ ሚና መጫዎቷምን ዘገባው ገልጿል። አልሸባብ ለኹለት አስርት ዓመታት በሶማሊያ እያደረሰ ባለው ጥቃት ኢትዮጵያ የምትጫወተው ሚና የአልሸባብ የረጅም ጊዜ ዒላማ እንድትሆን አድርጓታል የተባለ ሲሆን፤ ታጣቂ ቡድኑ በኢትዮጵያ ላይ ያለው ጥላቻ እየጨመረ የመጣ ይመስላልም ነው የተባለው። የአፍሪካ ህብረት የሽግግር ተልዕኮ ኃይል (አትሚስ) ባለፈው ሰኔ ወር ከ22 ሺሕ ወታደሮች መካከል 2 ሺሕ የሚሆኑትን ከሶማሊያ ያስወጣ ሲሆን፤ በመጪው መስከረም ወር 3 ሺሕ ወታደሮችን ሙሉ ለሙሉ ለማስወጣት ማቀዱን አመላክቷል። ምንም እንኳን የአፍሪካ ህብረት የሽግግር ተልዕኮ ኃይል ዋነኛ ዓላማ የሶማሊያን ደህንነት በማረጋጋት ኃላፊነቱን ለሶማሊያ ፌደራል መንግሥት ማስተላለፍ ቢሆንም፤ የአልሸባብ ጥቃት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱ ተገልጿል። ኢትዮጵያ በአትሚስ ካላት ወታደራዊ ተሳትፎ በተጨማሪ ባለፈው መጋቢት ወር ኢትዮጵያ፣ ጅቡቱና ኬንያ ሞቃዲሾ ላይ ተገናኝተው ባደረጉት ምክክር ተጨማሪ 1000 ወታደሮችን ወደ ሶማሊያ ልካለች። በዚህም አልሸባብ የጥቃቱን ዋነኛ ትኩረት በውጭ ወታደሮች ላይ አንጣጥሮ ቆይቷል። አልሸባብ ካለፉት ቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ ድንበር ጥቃት ለማድረስ ሲሞክር የሚስተዋል ሲሆን፤ ባለፈው ሰኔ ወር ላይም በሶማሌ ክልል ዶሎ ከተማ ጥቃት ማደረሱ ይታወሳል። በተለይም ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ሰፊ ድንበር የሚጋሩ በመሆናቸው፤ ቡድኑ በኢትዮጵያ ላይ ጥቃት ለመፈጸም ካለው ጽኑ ፍላጎት እና ኢትዮጵያ ውስጥ ካለው የጸጥታ ችግሮች ጋር ተዳምሮ አልሸባብ በሚቀጥሉት ወራትና ዓመታት ተከታታይ የሽብር ጥቃት ሊከፍት እንደሚችል ነው የተጠቆመው። የምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ዋነኛ ስጋት የሆነው እስላማዊ ቡድን በተለይ በሶማሊያ በሚፈጽማቸው አውዳሚ ጥቃቶች የብዙዎችን ሕይወት እየቀጠፈ ይገኛል። አዲስ ማለዳ
نمایش همه...
ትናንት በማዕከላዊ ጎንደር ከአዘዞ ወደ ማራኪ ከተማ በሚያስገባው የፍተሻ ኬላ ላይ በተፈፀመ የደፈጣ ጥቃት በፀጥታ አካላት ላይ ጉዳት መድረሱን የደረሰኝ መረጃ ይጠቁማል። የተሰውም አሉ።
نمایش همه...
በ#ጋምቤላ ክልል በተከሰተው  ጥቃት 13  አመራሮች ከኃላፊነታቸው ተነሱ‼️ በጋምቤላ ክልል ስሞኑን ተከስቶ በነበረው የፀጥታ ችግር ምክንያት በተደረገ ግምገማ 13 አመራሮች ከኃላፊነታቸው ሲነሱ ለ55 አመራሮች ደግሞ አዲስና የሽግሽግ ሹመት መሰጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ ገለፁ። ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ኡሞድ ኡጁሉ እንደገለጹት አዲስና የሽግሽግ ሹመት መስጠት ያስፈለገው በክልሉ በተወሰኑ አካባቢዎች ተከስቶ በነበረው የጸጥታ ችግር ምክንያት በተደረገ ግምገማ ነው ብለዋል። ቀደም ሲል አዩዘሀበሻ በክልሉ ማጃንጋ ዞን ስር በምትገኘው #ጎደሬ ወረዳ ሰኞ ነሃሴ 29 ቀን 2015 ዓ.ም ምሽት ላይ ታጣቂዎች በሰነዘሩት ጥቃት ስድስት የወረዳዋ ነዋሪዎች ህይወት ማለፉን ዘግቧል። ከኃላፊነታቸው የተነሱት 13ቱ አመራሮች በብልሹ አሰራር፣ በአፈፃፀማቸውና በፀጥታ ችግር ክፍተት የታየባቸው መሆናቸውን ርዕሰ መስተዳደሩ አስታውቀዋል። የክልሉ መንግስት በመግለጫው በክልል ማዕከል የተጀመረው አመራሩን የማጥራት ተግባር በቀጣይ በዞንና በወረዳ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብሏል። @ayuzehabeshaofficial
نمایش همه...