cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegaciĂłn. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Gods Generals🔥🔥🔥🔥

👉 #አዳዲስ_መዝሙሮች_Audio_music 👉 #አዳዲስ_የመዝሙር_ቪዲዮች_Music_Video 👉 #የህይወት_ትምህርቶች

Mostrar mĂĄs
El paĂ­s no estĂĄ especificadoEl idioma no estĂĄ especificadoLa categorĂ­a no estĂĄ especificada
Publicaciones publicitarias
169
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 dĂ­as
Sin datos30 dĂ­as
Archivo de publicaciones
ዝና ዝናዬ(2×) 🙏በአገልግሎቴ ላይ ዝናዬ 🙏ክብር ያሳየኽኝ ዝናዬ 🙏የማትደርቅ ልብሴ ዝናዬ 🙏የክብር ሽልማት ዝናዬ
Mostrar todo...
ተለቀቀ በቂዬ ነህ 👉 ዘመር ታከለኝ
Mostrar todo...
ሳቄ ነዋ 😂😂😂😂😂😂😂🤣 "ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ" ማዘን እያለብህ ለምን ትስቃለህ ይሉኛል እንዳልስቅ እንኳንስ ለሚያዩኝ እኔም ያስቀኛል ለምን እንደምስቅ ያለሁበት አለም ለቅሶ አይታወቅም በፈረቃ አልቅሼ በፈረቃ አልስቅም ኢየሱስ የዘላለም ነዋ ኢየሱስ ሳቄ ነዋ ኢየሱስ የዘላለም ነዋ ዘላለሜ ነዋ
Mostrar todo...
ኤፍሬም አለሙ እንዲ ነው |2013
Mostrar todo...
🔥Without the Holy Spirit🔥 🔥ያለ መንፈስ ቅዱስ🔥 🔐ያለ መንፈስ ቅዱስ ምንም ዐይነት የክርስትና ሕይወት የለም፡፡ 🔐ያለ መንፈስ ቅዱስ፣ የክርስትና ሕይወት፣ ደረቅ፣ አታካችና አሰልቺ ነው፡፡ 🔐ያለ መንፈስ ቅዱስ ሥራችን፣ አድካሚና ፍሬ ቢስ ነው፡፡ 🔐ያለ መንፈስ ቅዱስ ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት የለም፡፡ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ መንፈስ ቅዱስ ተገቢ ቦታውን ካልያዘ ከሁለት ነገሮች አንዱ ይሆናል፡፡ ☢ቤተ ክርስቲያን ማኅበራዊ ክለብ ትሆናለች፡፡ ☢ወይም ተራ ሃይማኖታዊ ተቋም ትሆናለች፡፡ እውነቱ ግን… 🔐 ያለ መንፈስ ቅዱስ መገለጥ የለም፡፡ 🔐ያለ መንፈስ ቅዱስ ቅዱሳት መጻሕፍት ሕይወት ሰጪ አይሆኑም፤ ምክንያቱም፣ ‹‹ፊደል ይገድላል መንፈስ ግን ሕይወትን ይሰጣል›› ተብለናል (2 ቆሮንቶስ 3፥6)፡፡ 🔐 ያለ መንፈስ ቅዱስ ራእይ የለም፡፡ 🔐ያለ እርሱ ደስታ የለም፡፡ 🔐ያለ እርሱ ሰላም የለም፡፡ 🔐ያለ መንፈስ ቅዱስ ነጻነት የለም፡፡ ጌታ መንፈስ ነው፤ የጌታም መንፈስ ባለበት በዚያ ነጻነት አለ (2 ቆሮንቶስ 3፥17)፡፡ @Binarevivalist @Binarevivalist @Binarevivalist
Mostrar todo...
ማሚ እንኳን ተወለድሽ እንወሻለን 🎂Happy Birthday🎂 እሲቲ Happy Birth Day በሏት 🔅 Happy Birth Day🔅
Mostrar todo...
ከዛስ??? እኔ እጮኻለው አንተም ትሰማለክ እኔ አለቅሳለውአንተም ታየኛለክ እራባለው እጠማለው ናፍቃለው እጮሀለው እፈልጋለው እጓጓለው በእንባ ዘለላዎቼ ረሀቤ ይታይካል በጩኸቶቼ ውስጥ ናፍቆቴ ይሰማካል ከዛስ???????? ከዛማ………… ክብርህ በሀይል እኔ ላይ ወርዶብኝ የነፍሳት የትውልድ ኃላፊነት ከብዶብኝ ከክብርወደክብር ከቅባት ወፈርያለ ቅባት የእየሱስን ስም ተሸክሜ በህዝቡ ፊት ትውልዱን አስነሳለው ወደ ጌታ እርስት ከዛማ…………… ትውልዱን አንቅቼ ሰራተኞችን አስነስቼ ተልዕኮዬን እጨርስና እመጣለው ወዳንተ አሁን ቶሎ ናና
Mostrar todo...
ዝና ዝናዬ(2×) 🙏በአገልግሎቴ ላይ ዝናዬ 🙏ክብር ያሳየኽኝ ዝናዬ 🙏የማትደርቅ ልብሴ ዝናዬ 🙏የክብር ሽልማት ዝናዬ
Mostrar todo...
ለምን አልነገርሽኝም ? ከሲኦል የተፃፈ የፍቅር ደብዳቤ ! በዶ/ር ወዳጄነህ መሐረነ የተዘጋጀ ፅሁፍ ቤተልሔም ሰፈርዋ ስትደርስ ከምሽቱ 3 ሰአት ሆኖ ነበር፡፡ እጅግ ከምትወዳት ጓደኛዋ ከማኪ ጋ ነበር ያመሹት፡፡ ለሁለት የበሉት ትልቅ ፒዛ በጣም አጥግቧት ስለነበር ቤትዋ የቀረበላትን ራት ይቅርብኝ ብላ ለምሽት የምትመርጠውን የካሞሜል ሻይ ጠጥታ በቀጥታ ወደ መኝታ ቤቷ ገባች፡፡ እንደ ልማዷ አጭር ፀሎት አድርሳ ፣ ፒጃማዋን ለብሳ ለእንቅልፍ ራስዋን አመቻቸች፡፡ የቤቲ እንቅልፍ ሁል ጊዜ ጣፋጭ ነው፡፡ ፀጉሯ ትራስ ከነካ እርሷ የለችም… ወደ ሌላ አለም ትሔዳለች! ደግሞ ህልሞች ታልማለች…. ለዛውም የ 7Dህልሞች! በህልም የምትቀበላቸው መልዕክቶች መሬት ላይ ጠብ አይሉም፡፡ ሁሉም ሲፈፀሙ አይታለች፡፡ “ዛሬ ህልም አይቼ…” ብላ ከጀመረች ሁሉም ሰው በጉጉት ነው የሚሰማት፡፡ በዚህ ሌሊት ያየችው ህልም ግን እጅግ የተለየ ነው፡፡ አንድ ሰው ደብዳቤ ይዞላት ይመጣል…በህልሟ፡፡ ደብዳቤው የተፃፈው ከታች ከሲኦል ሲሆን የፃፈችላት ደግሞ አብራት ያመሸችው ባልንጀራዋ ማኪ ናት፡፡ ደብዳቤው አንዲህ ይነበባል፡፡ “ውድ ጓደኛዬ ቤቲዬ! በድንገት ሳላስበው ዛሬ ሌሊት ወደማላውቀው ስፍራ መጣሁ፡፡ ሲኦል ነው ብለው ነግረውኛል፡፡ የምፅፍልሽ ከዛ ነው፡፡ በጣም የሚያስፈራ፣ የሚያስጨንቅ ቦታ ነው፡፡ በቅጽበት ከመንገድ ወደዚህ ሲያመጡኝ ለምን ብዬ ጠይቄያለሁ፡፡ የሰጡኝም መልስ “ከጠላት አላመለጥሽም….የጉብኝትሽን ወራት አላወቅሽም… የተከፈለለልሽን አልተረዳሽም!” የሚል ነው፡፡ አንቺ ግን ታውቂ ነበር አይደል? ተረድተሽም ነበር አይደል? ግን ለምን አልነገርሽኝም? ቤቲዬ! አንዳንቺ የሚቀርበኝ ጓደኛ ኖሮኝ አያውቀም፡፡ ሚስጥረኛዬ አንቺ ነበርሽ! አንድ ቀን እንኳን ሳላገኝሽ ከዋልኩ ቅር ይለኝ… ትናፍቂኝ ነበር፡፡አሁንም በፍቅር ልውቀስሽ ብዬ እንጂ ተጣልቼሽ አይደለም፡፡ ቤቲዬ! ብዙ ቀን ሳውና አብረን ገብተናል… ጃዙኪ ውስጥ ተዝናንተናል፡፡ ስለ ብዙ ነገር አውርተናል… መካሪዬ ነበርሽ! ግን ቤቲዬ ልጠይቅሽ … ለምን ስለ ክርስቶስ አልነገርሽኝም? ፀጉራችንን፣ ጥፍራችንን ስንሰራ ሁሌም አጠገብ ላጠገብ ሆነን ነበር፤ ለብዙ ሰአታት እናወራ ነበር፡፡ አንቺ ግን ታውቂ ነበር አይደል…? መዳን ከቅድስት ማርያም በተወለደው በኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ? እስቲ አሁን እያነባሁ በፍቅር ልጠይቅሽ… ቤቲዬ የኔ ቆንጆ… ለምን አልነገርሽኝም? ምሳ አብረን ስንበላኮ ከ 3 እስከ 4 ሰአታት ይፈጅብን ነበር፡፡ ስለሔድሽባቸው ከተሞች… ስለ ፓሪስ፣ ስለ ለንደን፣ ስለ ኒውዮርክ፣ ስለ ባንኮክ ስታወሪልኝ አፌን ከፍቼ ነበር የምሰማሽ፡፡ ግን ቤቲዬ የኔ ጓደኛ… የኔ ማር… በመስቀል ላይ ስለተሰራው ስራ ለምን አልነገርሽኝም? አያስፈልጋትም ብለሽ ነው? በየ ጊዜው ከውጪ ስትመጪ ስጦታ ታመጪልኝ ነበር፡፡ ዛሬ እንኳን ይዤው የነበረው ቦርሳ አንቺ የሰጠሸኝ ነው… አንገቴ ላይ የነበረውም ሀብል እንዲሁ፡፡ ለእኔ ስጦታ መስጠት ደስታሽ ነበር፡፡ ግን ቤቲዬ! አህቴ! መጸሐፍ ቅዱስ ለምን አልሰጠሸኝም?አልዋሽም! መንፈሳዊ ወሬዎች ከሌሎች ጓደኞቻችን ጋ ሆነን ስታወሩ ሰምቻለሁ፡፡ ስለ ታዋቂ ሰባኪዎች… ስለ ቄሶች ፣ ስለ ፓስተሮች… ስለመጡላችሁ ትንቢቶች… ስላገኛችኋቸው በረከቶች ስታወሩ ሰምቼ አውቃለሁ… ግን ለምን ስለ መድሀኔያለም አልነገራችሁኝም? ለምን ከሞት እንደሚያድን፣ ከሲኦል እንደሚታደግ አልተረካችሁልኝም? ቤቲዬ! እሺ እል እኮ ነበር! ብታስረዱኝ እስማማኮ ነበር! ዛሬ እንደሆነው ሰይጣን ያለ እድሜዬ አይቀጥፈኝም ነበር! በደሙ እሸፈን ነበራ! መላዕክቱ ይጠብቁኝ ነበራ! አሁንማ አበቃ! ጊዜው አልፏል አሉኝ… ወደዚህ ስፍራ አመጡኝ፡፡ በጣም ያስፈራል ቤቲዬ… ለማሰረዳት እንኳን ያስቸግራል! ማንም ወደዚህ እንዲመጣ አልፈልግም፡፡ ጓደኛዬ ማሬ! ቤቲዬ ሚስጥረኛዬ! አንቺኮ ልብስሽን ሲነኩብሽ አትወጂም ነበር፡፡ እኔ ግን ሌዘር ጃኬትሽን ስለብስብሽ… ለዛውም ሳላስፈቅድሽ… ስካርፍሽንም ለብሼ ስወጣ… በነዚያ ትላልቅ አይኖችሽ አየት ታደርጊኝና ዝም ትይኝ ነበር፡፡ ሽቶሽ ሽቶዬ… ጥፍር ቀለምሽ ጥፍር ቀለሜ… ሊፕስቲክሽ ሊፕስቲኬ ነበር፡፡ እንቺኮ የልብ ጓደኛዬ… አሰተማሪዬ ነበርሽ፡፡ ሰለ ዳይት፣ ስለ ቫታሚኖች፣ ስለ ጂም … ያስተማርሽኝ አንቺው ነሽ፡፡ ግን ቤቲዬ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን አልነገርሽኝም? በእርሱ ሀጢያትሽ እንደተሰረየልሽ… የዘላለምን ህይወት እንደወረስሽ ለምን አላወራሸልኝም?ብዙ ቀን ሲኒማ ስንሔድ አንድ ቀን እንኳን ቤተክርስትያን እንሂድ ለምን አላልሽኝም? ልቤ አዘነብሽ… ተቀየምኩሽ ጓደኛዬ… ቤቲዬ! ምንም እንኳን ባዝንብሽም ሁሌም ጨክኜ አንቺን ማኩረፍ አልችልም… ታውቂ የለ፡፡ መልካም ህይወት ይሁንልሽ! አምላክሽ ያሰብሽውን ሁሉ ያሳካልሽ! ሁል ጊዜ እወድሻለሁ! አንዳንድ ቦታ አልነበብ ካለሽ ቀለሙን ያበላሸው የተንጠባጠበው እንባዬ ነው! ደህና ሁኚልኝ! አክባሪ እህትሽ… ጓደኛሽ… ሚስጥረኛ ባልንጀራሽ ማኪ ነኝ… ከታች… ከሲኦል!” ቤቲ ከእንቅልፏ በታላቅ ድንጋጤ ነቃች፡፡ ህልም ነበር! በህልሟ ያነበበችው የማኪ ደብዳቤ ግን በጣም አስደንግጧታል፡፡ ፊቷ ላይ ላብ ችፍ ብሏል! እየተንቀጠቀጠች ስልኳን አንስታ ወደማኪ ደወለች፡፡ ስልኩ ተነሳ … ያነሳችው ግን ማኪ አልነበረችም፡፡ እነ ማኪ ቤት ለቅሶ ይሰማል… “ጓደኛዬን ማኪን ፈልጌ ነው” አለቻቸው እየተርበተበተች፡፡ ስልኩን ያነሱት እናትም በሲቃ… “ አዬ! ማኪንማ የመኪና አደጋ ነጠቀኝ! ጉልበተኛ ሰይጣን ነጠቀኝ! ለማን አቤት ይባላል?” አሏት፡፡ የቤቲ ሞባይል ከእጇ ወደቀ…. ማኪን?… የሚኪና አደጋ? በህልሟ ያነበበችው የማኪ ጥያቄ ይጮህባት ጀመር…. ለምን አልነገርሽኝም?… ለምን?… ጓደኛዬ… ቤቲዬ… እህቴ… ባልንጀራዬ… ማሬ… ለምን አልነገርሽኝም?…. ለምን?!
Mostrar todo...
Endi aynet teweld mefter albet🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
Mostrar todo...
. ባለግርማ -||- ይትባረክ አለሙ sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀ
Mostrar todo...
..እግዚአብሔር የሚያስፈልጋችሁን አትረፍርፎ ይሰጣቿል.. “አምላኬም እንደ ባለ ጠግነቱ መጠን በክብር በክርስቶስ ኢየሱስ የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ ይሞላባችኋል።” ፊልጵስዩስ 4፥19 በዚህ ቃል መሰረት ባለፀጋ ለመሆን የምትጣጣሩ ሳትሆኑ ባለፀጋ ናችሁ ምን ያህል ወጪ እንደምታወጡ ምን ያህል ገንዘብ አካውንታችሁ ውስጥ መኖሩ ደፍሮ ይህ የእግዚአብሔርን ቃል ነክቶ በልጦ አይጥለውም:: ባለፀጋ ናችሁ ምክንያቱም የሚያስፈልጋችሁ ነገር በጨመረ ቁጥር የእግዚአብሔርም አቅርቦት እየጨመረ ይሄዳል:: በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ 2 ሙሽሮች ነበሩ በሰርጋቸው ቀን በጣም ትልቅ ነገር አስፈለጋቸው ለሰርጋቸው የተዘጋጀው ወይን አልቋል! ምን ያህል ሰው እንደሚመጣ የሚያውቁት እነሱ ናቸው በሕይወታቸው ትልቁ ቀን እና ሊደሰቱበት የሚገባቸው ቀን ነው ግን የሚያስጨንቅ ነገር መጣባቸው:: ግን ምንም ሆነ ምን ኢየሱስ ክርስቶስ ከጭንቀት እና ከሀፍረት አዳናቸው ኢየሱስ እንደ ብልጥግናው መጠን የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ ሞላባቸው 6 የድንጋይ ጋን ሙሉ ውሃ ነበር እየሱስ ሙሉ ወይን አደረገው እንዲያውም መልካም ወይን (ዮሐ 2:1-10) የእኛ ጌታ ኢየሱስ የእነዚህን ሙሽሮች ፍላጎት አትረፍርፎ ሰጣቸው:: የተወደዳችሁ ብዙ የሚያስፈልጋችሁ ነገር ይኖራል ኢየሱስ ግን እሱ አትረፍርፎ እንደሚሰጣችሁ እንድታውቁ ይፈልጋል! ለዚህ ደግሞ በቃሉ ተናግሯል:: እግዚአብሔር ቃል ገብቷል እንዲህ ብሎ የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ አንዳንዱን አይደለም የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ እንደ ብልፅግናው መጠን እንደ ብልፅግናው ግማሽ አይደለም መጠን ይሰጣቿል ይሞላቿል:: ወዳጄ ደስ ይበልህ እግዚአብሔር እንደ ባለፀግነቱ መጠን ከሰጠህ ባለጠጋ ነሕ ደግሞ የሚገርመው ሲሰጣችሁ የሚሰጣችሁ በክርስቶስ ነው (ፊል 4:19) ይህ በረከት የማይጠፋ በክርስቶስ የሆነ ፍፁም ብልፅግና ነው አሜን ::
Mostrar todo...
Fire team🔥🔥🔥 " እግዚአብሔር ይላል። በመጨረሻው ቀን እንዲህ ይሆናል፤ ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ፤ 🔥🔥🔥ክብር አለ🔥🔥 https://t.me/Fireteam0
Mostrar todo...
እንደገና ውውውውውውውው🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ክብር #እንደገና ቅባት #እንደገና ሀይል #እንደገና ሞገስ #እንደገና ከፍታ #እንደገና 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
Mostrar todo...
አትሄድም እያሉ #ሰዎች ያወራሉ ትቆማለች/ህ እያሉ #ሰዎች ያወራሉ ደክማለች/ሟል እያሉ #ሰዎች ያወራሉ እኔሳ............ አትሄድም እያሉ ቆማለች/ሟል እያሉ ደክማለች/ሟል እያሉ እኔ ግን ይዣለው #ቃሉ ተናግሮኛል ሟርተኛ እያየ እሄዳለው........... ወረኛው እያየ እሄዳለው......... አገር ምድሩ እያየ እሄዳለው....... 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
Mostrar todo...
5ደቂቃ ፀልዩ 😭😭 አሁን ለ አፍጋኒስታን ዛሬ በአፍጋኒስታን ከሰዓት በኋላ የሞት ፍርድ ለተፈረደባቸው 229 ክርስቲያን ሚስዮናውያን ጸልዩ ሊጎዱ ነው ብዙ ሰዎች መጸለይ እንዲችሉ እባክዎን ይህንን መልእክት በተቻለ ፍጥነት ያስተላልፉ። ይህ መልእክት የተላከው በጁዲት ካርሞና ሚስዮናዊው በአፍሪካ ከሚገኘው ከቺዋዋዋ ነው። መላው ፕላኔት በጸሎት አንድ ሆነ። እርስዎ ማስተላለፍ ከቻሉ እባክዎን በአፋጣኝ ጸሎት እኛን ይቀላቀሉ ፣ ምክንያቱም አክራሪ እስላማዊ ቡድኑ በኢራቅ ውስጥ ትልቁን የክርስቲያን ከተማ ኳራጎሽን ሰለተቆጣጠሩት አሁን በመቶዎች የሚቆጠሩ ክርስቲያን ወንዶች ፣ ሴቶች እና ልጆች ሊገደሉ ባሉበት ሰአት የጸሎት ሽፋን እየተጠየቀ ነው። እባክዎን አንድ ደቂቃ ወስደው ጸልዩላቸው። ለሚችሉት ሁሉ መልዕክቱን ያስተላልፉ። ኳራጎሽ ቀድሞውኑ ብዙ ጊዜ ተወስዷል። ፀሎት ጠይቀውናል እባክዎን ለሌሎች ሼር ሼር
Mostrar todo...
ዛሬ በሚያሳዝን ሁኔታ ይህንን አስከፊ ዜና በዚህ ጊዜ አረጋግጠዋል። እነሱ በዜና ውስጥ ሊያጠናክሩት ይችላሉ። እንዴት ያሳዝናል !! በአፍጋኒስታን እስላሞች ነገ ከሰዓት በኋላ የሞት ፍርድ ለተፈረደባቸው 229 ኛው ክርስቲያን ሚስዮናውያን ጸልዩ። ብዙ ሰዎች መጸለይ እንዲችሉ እባክዎን ይህንን መልእክት በተቻለ ፍጥነት ያስተላልፉ። ይህ መልእክት የተላከው በጁዲት ካርሞና ሚስዮናዊው በአፍሪካ ከሚገኘው ከቺዋዋዋ ነው። መላው ፕላኔት በጸሎት አንድ ሆነ። እርስዎ ማስተላለፍ ከቻሉ እባክዎን በአፋጣኝ ጸሎት እኛን ይቀላቀሉ ፣ ምክንያቱም አክራሪ እስላማዊ ቡድኑ በኢራቅ ውስጥ ትልቁን የክርስቲያን ከተማ ኳራጎሽን ስለወሰደ። በመቶዎች የሚቆጠሩ ክርስቲያን ወንዶች ፣ ሴቶች እና ልጆች አንገታቸውን እየቆረጡ ባሉበት። የጸሎት ሽፋን እየተጠየቀ ነው። እባክዎን አንድ ደቂቃ ወስደው ጸልዩላቸው። ለሚችሉት ሁሉ መልዕክቱን ያስተላልፉ። ኳራጎሽ ቀድሞውኑ ብዙ ጊዜ ተወስዷል። ፀሎት ጠይቀውናል እባክዎን ለሌሎች ያስተላልፉ። 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
Mostrar todo...
ከፊታችን ነሃሴ 21 በGGR የወንጌል አገልግሎት ስለተዘጋጀዉ ኮንፍረንስ የተላለፈ መልዕክት ነዉ:: 👇👇👇👇👇👇👇 @AKAElijahKenneth 0991116374 @Kathrynakhulman 0923027304 ብቻ ምን አስለፋቹ ክብር አለ
Mostrar todo...
አብሮ መሞትና መኖር.........! መጽሐፍ ስለ ኢየሱስ ሲናገር "ከእርሱ ጋር ከሞትን፥ ከእርሱ ጋር ደግሞ በሕይወት እንኖራለን፤" ይላል። (2 ጢሞ 2:11) በሌላ ስፍራ ደግሞ፥ እግዚአብሔር ኢየሱስን "የሞትን ጣር አጥፍቶ አስነሣው፥ ሞት ይይዘው ዘንድ አልቻለምና" ይላል። (ሐሥ 2:24) እንግዲህ ሞትን አልፎ በሕይወት ለመኖር፥ ሞትን ድል ነስቶ በሕይወት ከሚኖረው ኢየሱስ ጋር መሆን የግድ ነው። ሞትን ያልተሻገራ አካል መከተል ትርፉ፥ የሞት ሰለባ መሆን ነው። አሁንም ሆነ ወደ ፊት ከሞት በኋላ ያለውን ሕይወት ለመኖር፥ ዋና መንገድ የሆነውን እና የሞትና የሲኦል መክፈቻ ያለውን፥ ኢየሱስ ክርስቶስን እከተላለሁ። እናንተስ? (ራዕ 1፡18)
Mostrar todo...
😊 To all behagerlij family, we are happy to let you know that our animated short "Endegena" is nominated for the International Short Film Category @ FOCUS ON ABILITY short film festival, Australia. The voting will last till AUG 16. You can support us and our film by going to the link down below and voting😊. If you see its worth feel free to share it with friends and loved ones and spread it like a wild fire🔥🔥🔥 https://www.focusonability.com.au/FOA/films/2299.html When you do you can leave out the postcode and province requests unfilled. Just fill out your full name, email address, city and you are good to go! 😊 With your generous support we have come this far and we hope to push even further💪🏽 እ - ና- መ- ሰ- ግ - ና - ለ - ን!
Mostrar todo...
አንድ ሽማግሌ በባቡር ተሳፍሮ ሲሄድ ብድግ ብሎ ተነሳና ወደ ተሳፋሪዎች ዘውር ብሎ ሁላቹም ስሙ ኢየሱስ በቅርቡ ይመጣል ንስሀ ግቡ ብሎ ሰበከ አንድዋ ተሳፋሪ ሴት ብድግ ብላ ተነሳችና አፍህን ዝጋ አንተ ምንም የምታውቀው ነገር የለም የአንት ኢየሱስ እንዲያውም ከነጭራሹ የለም አላቸው ሽማግሌውም ተደናግጦ ቁጭ አለ ነገር ግን እንደገና ተነሰስቶ ኢየሱስ እንደሚመጣ እንዲሰበክ እግዚአብሔር ልቡን አነሳሳ እሱም የእግዚአብሄር ድምጽ ታዘዘና ተነስቶ እንደገና ኢየሱስ በቅርቡ ይመጣል ሁላቹም ንስሀ ግቡ በልባችሁም እርሱን ተቀበሉ ከዘላለም ሞትም ትድናላችው እያለ መስበኩን ቀጠለ ከዚያ ስትዮዋ እንደገና ተነስታ ከፍ ባለ ድምጽ ዝም በል አንተ ማትረባ ብላ በጥፊ ደጋግማ ስትመታው ካጠገብዋ ቁጭ ብሎ የነበረው ልጇ ተይ እንጂ እማዬ ይህ ሰው እኮ የእግዚአብሄር መልዕክተኛ ነው አላት ከዚያ ሴትይዋ በግንባሩዋ ተደፍታ መጮህ ማልቀስ ጀመረች ሽማግሌውም ለምን ታለቅሽያለሽ ለምንስ ጨውሽ ሲላት ልጁ መናገርም ሆነ መስማት አይችልም (ዲዳ) ነበር አሁን ግን መናገር ቻለ አለችው ቃሉ ሀይል አለው ቃሉን በድፍረት ስትናገር ተአምራት መሆን ይጀምራሉ በእርግጥም ኢየሱስ በቅርቡ ይመጣል
Mostrar todo...
...እግዚአብሔር ረጅምን እድሜ ያጠግብሃል... “ረጅምን ዕድሜ አጠግበዋለሁ፥ ማዳኔንም አሳየዋለሁ።” — መዝሙር 91፥16 እግዚአብሔር ለኛ ያለውን ልብ ልንገራችሁ እግዚአብሔር ያለ ጊዜያችን እንዳንሞት ይፈልጋል (መዝ 91:16) "ረጅምን እድሜ አጠግበዋለው ማዳኔንም አሳየዋለው" ይላል:: እግዚአብሔር ረጅምን እድሜ ብቻ አይደለም ለእኛ የሚያስበው ደግሞም በሰላሙ, በደስታው, በአቅርቦቱ እና የሚያረካ ሕይወትን እንድንኖርም ነው ያቀደልን:: እዚህ ቃል ላይ ማዳኔ የሚለው ቃል በ Hebrew "Yeshua" ነው የሚለው "Yeshua" የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስም ነው "ኢየሱስ" ማለት ነው ስለዚህ የሚያጠግበን በኢየሱስ ክርስቶስ በክብሩ "ሙላት" ረጅምን እድሜ እንድንኖር ነው የሚፈልገውም የሚያጠግበንም! ጭንቀት ሃዘን ምሬት በሽታ እነዚህ መቼም ለእኛ በ እግዚአብሔር የታሰቡልን አይደሉም እግዚአብሔር ረጅምን እድሜ ሙሉ ሕይወትን በረከቱን አቅርቦቱን በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንድንቀበል ይፈልጋል ሰጥቶናልም!
Mostrar todo...
ንግግሬ Azusa ነኝ
Mostrar todo...
ንግግሬ #Azusa ነኝ @sisayAzusaRevivall
Mostrar todo...
cj youth conference ነገ ያልቃል ሂዱና የቅባቱ ተካፋይ ሁኑ ከናይጄሪያ የተቀቡ ዘማሪያን ይገኛሉ። እንዳያመልጣችሁ!!!!!!
Mostrar todo...
የእድገት ሚስጥር በራሱ የተሞላ ሰው በመንፈስ ቅዱስ መሞላት አይችልም፥ መንፈስ ቅዱስ የሚሞላው ራሳቸውን ባዶ የሚያደርጉ ሰዎችን ነዉ። ጌታችን በማቴዎስ 5፥3 “በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና።” ያለን ያደግን እንኳ ቢመስለን ሁልጊዜ በመንፈሳችን የእግዚአብሔርን ነገር የምንመኝ እንድንሆን ነዉ፥ ድሃ ምንድነው የሚያደርገው? የተሻለ ነገር ሲያይ የእኔ በሆነ" ብሎ ይመኛል፥ ቁሳዊ ድህነት አይመከርም! ለእኔ ቁሳዊ ድህነት መንፈሳዊነትም ትህትናም አይደለም፥ በመንፈስ ድሃ መሆን ግን ትልቅ መንፈሳዊነት ነዉ🤗። ሁልጊዜ በመንፈስ ድሃ መሆን የማያቋርጥ የእድገት ሚስጥር እንደሆነ አምናለሁ። እኔ ጋር የሌለ የእግዚአብሔርን ፀጋ አንድ ወንድሜ ወይም እህቴ ጋር ስመለከት፥ እግዚአብሔርን ለማመስገን እና ለማድነቅ ወደ ኃላ አልልም፥ ምክንያቱም በዚህ ሰው ሕይወት ያለውን ፀጋ የምካፈለው እና የማድገው በዚህ መንገድ እንደሆነ አውቃለሁ፤ የእግዚአብሔር ልጆች አንዱ የምታድጉበት ሚስጥር ይህ ነዉ፥ የእግዚአብሔርን ፀጋ ስታዩ ማድነቅ፣ መቅናት ተለማመዱ። ምንም አይነት መንፈሳዊ ልምምድ ሰይኖረው ረክቶ እየኖረ በላ ትውልድ መካከል ነው ያላችሁት፥ እናንተ ግን በትልልቅ መንፈሳዊ ልምምዶች ሁሉ እንኳ አትርኩ በደረሳችሁበት አትቁሙ እግዚአብሔር ሌላ በዓይን ያልታየ፣ በጆሮ ያልተሰማ እና በልብ ያልታሰበ አለው
Mostrar todo...
💥💥💥እየሱስ💥💥💥 👉ይህ ስም....#ከስሞች ሁሉ በላይ ስም ነው 👉ይህን ስም... #መላእክቶች ያውቁታል 👉ይህን ስም... #ነገስታት ያውቁታል 👉ይህን ስም.... #ገዢዎች ያውቁታል 👉ይህን ስም... #ተመራማሪዎች ያውቁታል 👉ይህን ስም...#አለቆች ያውቁታል 👉ይህን ስም... #ሉሲፈር ያውቀዋል 👉ይህን ስም... #ሙታኖች ያውቁታል 👉ይህን ስም... #ፍጥረት ያውቀዋል 👉ይህን ስም... #ምድር ታውቀዋለች 👉ይህን ስም ...#ከምድር በታች ያሉት ያውቁታል 👉ይህን ስም....#ሰማይ ያውቀዋል 👉ይህን ስም....#አለም ታውቀዋለች ምክኒያቱም...... 👇👇👇👇👇👇👇👇 #እግዚአብሔር ያለ ልክ #ከፍ #ከፍ #አደረገው #ከስምም #ሁሉ በላይ #የሆነውን #ስም ሰጠው ይህም #በሰማይም #በምድርም #ከምድርም #በታች ያሉት #ሁሉ #በእየሱስ #ስም #ይንበረከኩ #ዘንድ #ምላስም ሁሉ #ለእግዚአብሄር #አብ #ክብር #እየሱስ #ክርስቶስ #እንደ #ሆነ #ይመሰክር #ዘንድ ነው። ፊሊ2፥9~11 #እየሱስ_ጌታ_ነው
Mostrar todo...
1ኛ ተሰሎንቄ 5 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ❝³ ሰላምና ደኅንነት ነው ሲሉ ያን ጊዜ ምጥ እርጕዝን እንደሚይዛት ጥፋት በድንገት ይመጣባቸዋል ከቶም አያመልጡም። ⁴ እናንተ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ቀኑ እንደ ሌባ ይደርስባችሁ ዘንድ በጨለማ አይደላችሁም፥ ⁵ ሁላችሁ የብርሃን ልጆች የቀንም ልጆች ናችሁና። እኛ ከሌሊት ወይም ከጨለማ አይደለንም፤ ⁶ እንግዲያስ እንንቃ በመጠንም እንኑር እንጂ እንደ ሌሎች አናንቀላፋ። ⁷ የሚያንቀላፉ በሌሊት ያንቀላፋሉና፥ የሚሰክሩም በሌሊት ይሰክራሉና፤ ⁸ እኛ ግን ከቀን ስለ ሆንን፥ የእምነትንና የፍቅርን ጥሩር የመዳንንም ተስፋ እንደ ራስ ቁር እየለበስን በመጠን እንኑር፤ ⁹ እግዚአብሔር ለቍጣ አልመረጠንምና፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መዳንን ለማግኘት ነው እንጂ።❞
Mostrar todo...
እኔስ እገረማለሁ -||- ዮርዳኖስ sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ
Mostrar todo...
. ባይሆን ኖሮ -||- ቢታንያ sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ
Mostrar todo...
. ኢየሱስ ተባረክልኝ -||- kiya sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ
Mostrar todo...
. ከሞት የበረታ -||- ሳሙኤል ንጉሴ sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ
Mostrar todo...
. ወደ አባቴ -||- ጌትሽ በየነ sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ
Mostrar todo...