cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

አገረ ሻባካ

✍ኢትዮጵግዮን✍ የታላላቅ ሐበሻዊ ፈርዖናት ምድር፣ የጌራና የዮቶር አገር፣ የጥበብ አገሯ፣ የቀደመው የሰው ዘር መናገሻ፣ የኃይልና የምሥጢር ባለቤት፣ የኃያሉ ዮድ፣ የአለም ፈላስፋዎችና ምሁራን መገኛና የውዳሴ ቃል፣ የማትመረመር፣ የማትሸነፍ፣ አስፈሪ፣ ገናና፣ ድንቅ፣ ኅቡዕ ይህች የሻባካና የፒያንኪያ ምድር የጳዝቶዮን ባለሥልጣን የአለም ትንሣኤ ምንጭ እንቅዮጳዝዮን ናት!!!★

Mostrar más
El país no está especificadoEl idioma no está especificadoLa categoría no está especificada
Advertising posts
193Suscriptores
Sin datos24 hours
Sin datos7 days
Sin datos30 days

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

በዚህ ወር ብቻ ሁለት ታላላቅ የአገር ዋርካ የሆኑ #ሰዎችን አጣን።😭 የእነርሱን ፍኖት ያሳየን!🙏
Mostrar todo...
<< #የቀንና_የማታ_ሰው_ነው_የጊዜ_ጌታ >> 👉ከአንድሮሜዳ መርሐ ግብር ዝግጅት ላይ
Mostrar todo...
ኢትዮጵያ ውስጥ ጥሩ የሚመስል ነገር ግን የግለሰቦችን ነጻነት የሚጋፋ አንድ ነገር አለ። አብዝቶ በማይመለከተንና ለውጥ ማምጣት በማንችልበት የሰዎች ሕይወት ማሰብና መጨነቅ። ሁሉም የሚጓዘው በራሱ መንገድ ሲሆን ሁሉም የራሱ ግብና ዓላማ፣ የመሆንና ያለመሆን፣ የማድረግና ያለማድረግ ነጻነት አለው። ለምሳሌ እኔ ከአንድ ችግር ጋር 15 ዓመት ሙሉ እየተጋፈጥሁ ያንን ችግር ለምጄው መኖር ከጀመርኹ ወዲህ ሌላ ሰው መጥቶ ከዚህ ችግር ሊያወጣ እኔን መታገል አለበት ብዬ አላስብም። ቢታገልም ለውጥ ሊኖረው እንደማይችልና ምናልባትም ችግሩ ከችግርነት ወደአስፈላጊነት ተለውጦ እንደሆነ መረዳት አለበት። እኛ አሁንም ያልተረዳነው ነገር የምናስበው እንደግለሰብ ሳይሆን እንደቡድን መሆኑን ነው። ለውጥ ማምጣት የሚችሉ ጥቂት ሰዎች የራሳቸውን መንገድ ሲያስቀምጡ ማኅበረሰቡ አዲስ ከሆነበትና ተፈላጊ ነው ብሎ ካላመነ ግለሰቡን እንደቡድን ያወግዙታል። ''እንዲህ ማድረግህ ትክክል አይደለም፤ እኛ እንዲህ ዓይነት ባህል የለንም፤ አታፈንግጥ'' ይሉታል። ነገር ግን ዓለምን መቀየር የቻሉ ብዙኃንን ከተመለከትን ከአስተሳሰባቸው ውስጥ እንደቡድን ሲያስቡ አናገኝም። እነዚህ ልሂቃን ሐሳባቸው ግለሰባዊ ነው። ማኅበረሰቡ ሲነሱ አልተቀበላቸውም። ነገር ግን የእነርሱ እሳቤ ልቆ የቡድን ሐሳብን መሸፈን ቻለ። ስለዚህም የዓለሙ ማኅበረሰብ አማራጭ ሲያጣ በአስተሳባቸው አምኖ በድጋሚ ሐሳባቸውን የቡድን ሐሳብ ሊያደርግ ይራወጣል። ተሳስተህ እንኳን ከእነርሱ አስተሳሰብ ወጣ ያለ ነገር ብታደርግ እነሆ አንተ የእሳቤውና የዓለሙ በደለኛ ትሆናለህ። ባላቸው ነገር ሁሉ በአእምሯዊም ሆነ በአካላዊ መንገድ ፈርደው ያስፈርዱብሃል። ከዚያ ከቻሉ ከሌሎች ካልሆነም ከራስህ ጭምር ተጣልተህ እንድታብድ ያደርጉሃል። ስለዚህም ይህንን እያየ ማንም ደፍሮ የሚወጣ ጀግናና ልሂቅ ሳናገኝ ለብዙ መቶ ዓመታት ባለፈ፣ ባረጀና ባፈጀ ቡድናዊ ቅንጭብ ስኬት እየተኩራራን በዛሬ ላይ በመቆራመድና በመናቆር እንኖራለን። ወይ ትናንትን አንመልስ ወይ ዛሬን ተመልክተን ነገን አንለውጥ ባለንበት ምህዋር ያለእንቅስቃሴ እንቀራለን። እናም ወገኔ ትናንትን ተመልክተህ ከቻልህ ተማርበት፤ ካልሆነ በልብህ ይዘህ የዛሬ ችግሬ ምንድነው?...ነገን ምን ላድርግ ብለህ እንደቡድን ሳይሆን እንደግለሰብ አስብ። ጤናማ የሆነ ግለሰባዊ አስተሳሰብና ነጻነት ካለ ቡድናዊ የእሳቤ ነጻነትና መብትህ ይከበራል። መጀመሪያ ግን ራስህ ተመልከት። ራስህን አድን፤ በራስህ እንደራስህ ስለራስህ አስብ። ራስህን ስትለውጥ ያንተን ታላቅ ስታደርግ ሌላውን መለወጥ፤ የሌሎችን ታላቅ ማድረግ ትችላለህና ቅድሚያ ለራስህ ጊዜ ስጥ። ስለራስ ማሰቢያ ብሩኅ ሰንበት!🙏 @merbebt @AITOPIA
Mostrar todo...
እንዴት ነህ ህዝቤ? «ዘውድአለም ታደሠ» (አማን መዝሙር) እንዴት ውለሃል አንተ ስመ ብዙ ህዝብ? ሐገር አማን ነው ወይ? እንደው አንተን ህዝብ ዝም ብዬ የጎሪጥ ስሾፍህኮ እያናደድክ ታሳዝነኛለህ የምር! ደሞ የስምህ ብዛት ... ከሃምሳ ምናምን አመት በፊት ጃንሆይ ያቺን የባቄላ ፍሬ የምታህል ውሻቸውን ፀጉር ዳበስ እያረጉ «ኩሩው ህዝባችን» ብለው የጠሩህ .. ደርግ መጥቶ ኩሩው የሚለውን ስም ላሽ ብሎ «ጭቁኑ» እያለ የሰየመህ! በመራራ ትግል ደርግን ጥሎ የመጣው መንግስት ደግሞ ምስኪኑ .. ሰላም ወዳዱ ... ልማታዊው ምናምን እያለ የወል ስም የሰጠህ ... አንዳንዱ ደግሞ እንደሰንበቴ ድፎ እየቆራረሰህ ትምክህተኛ ፣ ጠባብ ፣ ዘረኛ ፣ እያለ እንደክርስትና ልጁ ስም ሲያወጣልህ አሜን ብለህ የኖርክ፣ ወሰድ ሲያደርግህ ደግሞ ባወጡልህ ስም እየተጠራራህ ስትቧቀስ የከረምክ! ጥሪትህ ትንሽ ስምህ ብዙ የሆንክ እንደኬኔዲ መንገሻ ድምፅ አንጀት የምትበላ ህዝብ! ኑሮ ካሉት መቃብር ይሞቃል የሚል ተረት እየተረትክ ስትፅናና የመቃብር ስፍራ 40 ሺ ብር ገብቶብህ ግራ የገባህ! ትከሻህ እንደሴቶች ቦርሳ ሁሉን የሚሸከም የችግር ቤተሙከራ የሆንክ ህዝብ እንዴት ነህ? ለዘመናት ረሀብና ችጋር መሃል ባልገባ እየተጫወተብህ «ጎተራው ሙሉ፣ ሐገሩ ጥጋብ» ምናምን በሚል ዘፈን ወገብህ እስኪሰበር እስክስታ የምትወርድ፣ ውሃ እንደሌባ በለሊት መጣች አልመጣች ብለህ ተሰልፈህ እየቀዳህ «እምዬ ሐገሬ ፏፏቴሽ ማማሩ» በሚል ዘፈን የምትቦርቅ፣ ጎንህን የምታሳርፍበት ሃሳብ መስጫ ሳጥን የምታህል ጎጆ ተነፍጎህ «ጋራው ሸንተረሩ» ምናምን እያልክ ራስህ ላይ ሙድ የምትይዝ .. የአለም ቀበሌ "የደሃ ደሃ" የሚል መታወቂያ የሰጣት ሐገር ላይ እየኖርክ ዘፈን ላይ ያለችውን ጥጋብ በጥጋብ የሆነች ሐገር የሙጥኝ ብለህ ግራ ተጋብተህ አለምን ግራ የምታጋባ ዘጠኝ የኔታ የማይፈታህ ቅኔ የሆንክ ፍጡር! ሐገር ውስጥ አቧራና ትቢያ አማሮህ በሊቢያ አቆራርጠህ ባህር ማዶ ከተሻገርክ በኋላ «የኩበቱ ሽታ ናፈቀኝ» እያልክ የምታለቃቅስ ፕሮፌሽናል አዝግ ህዝብ! የተሾመ ሁሉ ቫንዳም ቫንዳም ሲጫወትብህ፣ የእድር ዳኛንኳ ባቅሙ አናትህ ላይ ሱቅ ካልከፈትኩ እያለ ሲያማርርህ፣ ሐገርህ ላይ ሶስት ምስክር ጠርተህ ካገኘኸው የቀበሌ መታወቂያ ውጪ ቤሳ ቤስቲ አጥተህ እንዳልኖርክ ሁሉ ሰው ሐገር ሄደህ እህል በልተህ ነፍስህ መለስ ስትል «ምን አለኝ ሐገሬ?» እያልክ ነጠላ ዜማህን የምትለቅ አላጋጭ ፍጥረት! ዋሽተህ አጣልተህ ዋሽተህ የምታስታርቅ፣ እንደገና ዋሽተህ የምታጣላ ስራ ፈት፣ እንቦጭን በሚያስንቅ የመራባት ጥበብህ መቶ ሚሊዮን የዘለልክ! የምትበላው ሳይኖርህ የሚበሉ ልጆች ፈልፍለህ የምታሳድግ ታምረኛ ዜጋ! ምን የመሰለ የፍቅር ዘፈን ላይ ጦርና ጎራዴ ይዘህ የምትሸልል ጀብደኛ ማህበረሰብ! ብዙ ሰው ከፈወሰው አክሊሉ ለማ ይልቅ ብዙ ሰው የገደለን ሽፍታ የምታወድስ! «ገዳይ ገዳይ ያልሽው አባትሽ አይገድል፣ አርሶ ያብላሽ እንጂ ሆድሽ እንዳይጎድል» እያልክ ከገበሬ ይልቅ ነፍሰገዳይነትን ሙያ አርገህ በረሃብ የምታልቅ ምስኪን ማህበረሰብ! አያትህ ድንጋይን እንደዝግባ ዛፍ ጠርቦ የኪነህንፃ ህግን በመሻር ከላይ ወደታች ቤተመቅደስ ቀለሰ፣ አለት እንደቢላዋ ሞርዶ ጡብ እንደእርሳስ ቀርፆ ስልጣኔውን በአንድ ሃውልት ላይ አተመ፣ ከቅጠላ ቅጠል ውብ ቀለማትን ጨምቆ ፍልስፍናውን በብራና ላይ አኖረ! አንተ ድንጋይ ስታይ ወደጭንቅላትህ የሚመጣው ግዙፍ ቤተመቅደስ መቀለስ ሳይሆን እንደቃየን ወንድምህን መፈንከት ነው! አዎ አባትህ ንፋስ ስልክ ቀለም ፋብሪካ ከመፈጠሩ ከሺህ አመታት በፊት ከዛፍ ቅጠል ውብ ቀለማትን ፈጥሯል! አንተ ልጄ በለጬ ወይም ገለምሶ ካልሆነ ወደቅጠል ፊትህን አታዞርም! ላንተ ቅጠል ሁሉ የሚከፈለው በሁለት ነው ... የሚቃምና የማይቃም! አያቶችህ ከሺህ አመታቶች በፊት “ገዳ” የሚባል ድንቅ ስርአት ዘርግተው አለምን አስደመሙ! ከአለም ቀድመው ዘመኑ፣ ከአለም ቀድመው የሞራል ልእልናቸውን አስመሰከሩ! አለምን አስተማሩ! አለም "Adoption"ን ከማወቋ በፊት አያቶችህ “ጉዲፈቻ” ብለው ጀምረውታል! አሜሪካ asylum መስጠት ከመጀመሯ በፊት አያቶችህ “ሞጋሳ” ብለው በቀለምና በባህል ለማይመስላቸው ስደተኛ መኖሪያ ስፍራና ዜግነት ይሰጡ ነበር! አንተ ዘንድሮም ስለሰው ልጆች አልገባህም፣ ሁለት የህዝብ ሽንትቤትና አንድ ቦኖ ውሃ ካላት ቀበሌዬ ውጡ እያልክ ወገኖችህን ታሳድደለህ! አያቶችህ ግን በገዳ ህግ ውስጥ ከሺህ አመታት በፊት ስለእንስሳት መብትና አያያዝ አርቅቀው ነበር! አያቶችህ ፊደል ቀርፀው እውቀትና ጥበባቸውን በራሳቸው ቋንቋ ውስጥ ሸሸጉ፣ ግእዝ ፣ እዝል ፣ አራራይ ብለው የራሳቸውን ዜማ ቀመሩ፣ ሰባቴ በወደቁ ግዜ ከትሏ መነሳትን ተማሩ! ጥጥ አቅጥነው የራሳቸውን አልባሳት ፈበረኩ፣ ሸንበቆ ቦርቡረው ዋሽንት ሰሩ፣ ጅማት ወጥረው መሰንቆ ፈለሰፉ፣ ቆዳ ፍቀው ከበሮ ወጠሩ፣ አያቶችህ በራሳቸው ፍቅር የወደቁ፣ ማንንም የማይኮርጁ፣ ማንንም የማይመስሉ ነበሩ! ቋንቋቸው ፣ ህጋቸው፣ አልባሳቸው፣ የሙዚቃ መሳሪያቸው፣ ዜማቸው፣ ሁሉ ማንንም አይመስልም ነበር! አያቶችህ የሰውን የፈጠራ ውጤት እንደመና ተቀምጠው የሚጠባበቁ አልነበሩም! ራሳቸው ፈጣሪዎች ነበሩ! ፈላስፋና ልሂቃን ነበሩ! አንተስ? ደነዝ! እውቀት ጠል! ስልጣኔ ጠል! ሃሳብ ጠል ዶማ ነህ! በሃያአንደኛው ክፍለዘመን “ከተፀዳዳህ በኋላ እጅህን ታጠብ” ተብለህ የምትመከር ከኢኳቶሪያል ጊኒ ቀጥሎ በመሀይምነት አንደኛ ወጥተህ (ጊኒን ግን እንዴት በለጥካት?) ፖለቲካን ከፖለቲካ ልሂቃኑ በላይ ተዘፍዝፈህ የምትተነትን ደፋር! ጀነን ብለህ አደባባይ መሃል የመንግስት ስልክ እንጨት በሽንትህ የምታጠጣ “ሐገር ወዳድ” ህዝብ! «ጫልቱ»ን የመሰለ ውብ ስም ስድብ መስሎህ ልታንጓጥጥ ምትሞክር፣ የኢትዮጵያ ፓስፖርት ይዘህ “ዳውን ዳውን ኢትዮጵያ” ስትል የምትውል፣ «ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ» ስትል እየዋልክ ሱርማውን፣ ከፊቾውን፣ ሽናሻውን፣ መዠንገሩን፣ ከነመፈጠራቸው የማታውቅ፣ አንድ ደሃ በቆንጨራ ገድለህ ብሔርህን ነፃ ያወጣህ የሚመስልህ፣ ባጭሩ ብሔርተኝነቱንም፣ አሃዳዊነቱንም በቅጡ ሳትችልበት ቀርተህ የአለም መዝናኛ ሆነህ የቀረህ ድፍን መንጋ! ኑሮ እንዴት ይዞሃል? ረሃብና ድህነት እንዴት እያረገህ ነው? አሁንም ፀጉርህን በተልባ ፈርዘህ ቺክ ትጀነጅናለህ ወይ? አሁንም የነጋዴ በግ ቀምተህ ሆድህን ትሞላለህ ወይ? አሁንም ሽማግሌን በጠረባ እየጣልክ ቫንዳም ቫንዳም ትጫወታለህ ወይ? አሁንም ዋሊያ ቢራ ጠጥተህ ቆርኪውን ትፍቃለህ ወይ? አሁንም “እኔ ነኝ ያለ” በሚል ዘፈን ልብህ ተነፍቶ በባዶ ሜዳ ትወራጫለህ ወይ? አሁንም ሰው ለፍቶ የገዛውን ቦቴ መኪናና ግሮሰሪ እያቃጠልክ ሰልፊ ትነሳለህ ወይ? አሁንም ኳስ ሜዳ መሀል ምስኪን ዳኛ ደብድበህ በኩራት ትንጎራደዳለህ ወይ? ደህና ነህ ወይ? አማን ነህ ወይ? (እንደወረደ የተወሰደ)
Mostrar todo...
ጎንደር እዚህ ላይ በደንብ ልዩነቱ ይታያል። ግርዶሹ ካለፈ በኋላ እንዳይመስላችሁ!...ግርዶሹም አለ፤ ሙሉ የፀሐይ ብርሃንም አለ። ነው ጨረቃ ሁለት ስራ አላት ወይስ ጨረቃችን ሁለት ሆነች? ፍልስፍና አይደለም!😂 @merbebt
Mostrar todo...
ፉሪ ሁለት ፀሐይ አለን እንዴ?🤔 @merbebt
Mostrar todo...
ጎንደር፣ ሐዋሳ እና ፉሪ ግን ግራ አጋብቶኛል።🤔🤔🤔 ሁለት ነገር ይታያል፤ ምስሎቹን ተመልከቷቸው!👇👇👇 ግርዶሽም ሌላ የፀሐይ ብርሃንም አለ። ምንድነው ነገሩ...ፀሐይ ተከፍላ አይደለም መቼስ?😂 እስኪ ያያችሁትና ግንዛቤው ያላችሁ አጋሩን!🙏 @merbebt
Mostrar todo...
አዲስ አበባ @merbebt
Mostrar todo...
የላልይበላ ቀለበታማ የፀሐይ ግርዶሽ! እንዴት እንደሚያምር ተመልከቱት! በተፈጥሮ መደነቅ!!! @merbebt
Mostrar todo...
አሁን በአላማጣ ያለው የፀሐይ ግርዶሹ ትእይንት
Mostrar todo...
Inicia sesión y accede a información detallada

Te revelaremos estos tesoros después de la autorización. ¡Prometemos que será rápido!