cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Ahmedin Jebel - አሕመዲን ጀበል

ይህ ይፋዊ የአሕመዲን ጀበል የቴሌግራም ገፅ ነው!

Mostrar más
Advertising posts
60 155Suscriptores
-2224 hours
-467 days
+3 60130 days

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

ስለ ወለጋ 100 ጊዜ ብፅፍም ውንጀላው የሚቆም አይደለም
Mostrar todo...
153👍 59
በመስጊድ ብቻ በመወሰኑ ከበርካታ ሀገራዊ ጉዳዮች ወደ ኋላ ተመለሰ። በርግጥ እውነታውን ካየነው የሀገሪቱ አጠቃላይ ችግሮች ሳይቀረፉ የሙስሊሙ ሃይማኖታዊ ጥያቄ ብቻውን ተለይቶ ሊመለስ የሚችልበት ሁኔታ እንደሌለ በመረዳት በሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮችም ላይ ከሌሎች ዜጐች ጋር በጋራ መታገል ነበረባቸው። የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች እንደተጨቆኑ፣ እንደተገፉና በስርዓቱ ውስጥ ተገቢ መብታቸው እንዳልተከበረ በማመናቸው ተደራጅተው ሲታገሉ ለዘመናት ሲጨቆን የነበረው፣ መብቶቹ ያልተከበሩለት እና ከብዙ ሀገራዊ ጉዳዮች ወደ ኋላ የቀረው ህዝበ ሙስሊሙ መብቱን ለማስከበርና እኩልነቱን በሁሉም ዘርፍ በተግባር ለማረጋገጥ የሚታገልለት አካል መፍጠር አልቻለም።በጣት የሚቆጠሩ ሙስሊሞች በወቅቱ ከተቃዋሚ ጐራ ተሰልፈው የነበሩ ቢሆንም የሙስሊሙን አጀንዳዎች የፖርቲዎቹ አጀንዳ ማድረግ አልቻሉም። ቁጥሩ ከሌሎች አንፃር እጅግ አናሳ ቢሆንም ከተቃዋሚዎቹ ይልቅ በደርግ ውስጥ በመጠኑ የተሻለ ቁጥር ያላቸው ሙስሊሞች ነበሩ። ይህ የሆነው ተቃዋሚነት ዋጋ የሚያስከፍል በመሆኑ ዋጋ በመክፈል ለአጀንዳቸው ለመቆም የተዘጋጁ ባለመሆናቸው ሳቢያም ሊሆን ይችላል። በነኝህና መሰል ሌሎች ምክንያቶች የተነሳ ያ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሶ የነበረው መነቃቃት እየቀዘቀዘ የሚገባውን ያህል ውጤት ሳያስመዘግብ ቀርቷል። ይህ ሊሆን የቻለው የዓለም ታሪክ እንደሚያስገነዝበው የትኛውም ሕዝብ መብቱንና እኩልነትን በልመናና ተማጽኖ ሊያገኝ የቻለበት ሁኔታ ያልታየ በመሆኑ ነው። ሂደቱን ስንመለከት የ1966ቱ የሙስሊሙ ንቅናቄ መሪዎች የላቀ ባይሆንም በተግባር ግን ካነሷቸው 13 የመብት ጥያቄዎች ምላሽ ሲሹ የነበሩበት በዋናነት መንግስትን በመማፀን፣ በመለመንና ምላሽ እንደሚያገኙ ተስፋ በማድረግ ነበር፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሕዝበ ሙስሊሙ ልሂቃንን በማፍራት እና በማብቃት ሥራ ላይ በቀጣይነት ሲንቀሳቀሱ አናይም። እነኝህን በመተግበር እንደሌሎቹ የመብት አስከባሪ ታጋዮች ሁሉ በሀገሪቷ ሁለንተናዊ ጉዳዮች ውስጥ በተለይም በፖለቲካው በመሳተፍ ትግል ቢያካሂዱ ኖሮ የተሻለ ለውጥን ማምጣት በቻሉ ነበር። ምክንያቱም በሀገሩ ፖለቲካ ላይ እኩል ተሳታፊ ያልሆነ አካል ሁሌም በሀገሪቱ እጣፈንታ ላይ እኩል የመወሰን እድል አይኖረውም። ይህ ሲሆን ደግሞ በሀገሩ እጣፈንታ ላይ ሚናው አነሳ ከመሆኑም በተጨማሪ የራሱ እጣፈንታ ጭምር በሌሎች መዳፍ ስር ይወድቃል። በዚህ ሁኔታ ውስጥ ደግሞ የቱንም ያህል ቅንና ፍትሓዊ ጥያቄዎች ቢኖሩትም እኩል ተጠቃሚ የመሆን ዕድሉ ሩቅ ነው። በርግጥ የደርግ መንግስት የአፄ ኃይለ ሥላሴን ሥርዓት በማስወገድ ለኢስላም እና ለሙስሊሞች በብሔራዊ ደረጃ እውቅና በመስጠቱ አንፃር ብቻ ስናየው ሥርዓቱ ለሙስሊሞች ባለውለታ ነበር። ይሁን እንጂ በቀድሞ ሥርዓቶች የማግለል ፖሊሲ ምክንያት ሙስሊሙ ማህበረሰብ ከሀገሪቷ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ተቋማት በመገለሉ ምክንያት የተፈጠረበትን በደልና በብዙ መልኩ ወደ ኋላ የመቅረቱን እውነታ የሚያካክስ አዎንታዊ እርምጃዎችን (Affirmative Actions) ባለመወሰዱ ልዩነቱ በብዙ መልኩ ቀጥሏል፡፡ በመሆኑም በደርግ ስርአት ውስጥ አብዛኞቹ የመንግስት አስተዳደር፣ የፖለቲካ ተቋማት እና በመንግስታዊ መስሪያ ቤቶች ውስጥ የሙስሊሞች ቁጥር አናሳ እንደሆነ ዘልቋል። ያም ሆነ ይህ በደርግ የመጀመሪያዎቹ የስልጣን ዘመናት ሕዝበ ሙስሊሙ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በጣት ሊቆጠሩ የሚችሉ አንኳር ጥቅሞችን አግኝቷል። በዝርዝር በዚህ መጽሐፍ ውስጥ የተጠቀሱትና በሕዝበ ሙስሊሙ ላይ ሲደርሱ የነበሩትን ጭቆናዎች አብዛኛዎቹን ያስወገደው የደርግ መንግስት ነበር። የኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞች መሪ ድርጅት የሆነው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጉባኤ (መጅሊስ) ለመጀመሪያ ጊዜ የተቋቋመው በዚሁ በደርግ ዘመን በመጋቢት 4 ቀን 1968 ዓ/ል ነበር። ህዝበ ሙስሊሙም በካድሬዎች ሳይሆን እንደነ ሐጅ ሙሐመድ ሳኒ ሐቢብ ባሉና ቁርኣንን ወደ አማርኛ በተረጎሙ ስመጥር ሊቃውንት እንዲመራ የደርግ መንግስት ፈቅዷል። የሃይማኖት እኩልነትን እሳቤ በሕዝቡ ውስጥ ለማስረፅም ጥሯል። ኋላ ላይም ሥርዓቱ ከተከተለው የሶሻሊስት ርዕዮተ ዓለም ፍልስፍና አንፃር ሁሉንም ሃይማኖት በጥርጣሬና በስጋት ቢያይም እንደ መንግስት ሙስሊሙን ብቻ ነጥሎ የሥርዓቱ እና የሀገሪቷ ስጋት አድርጎ ባለመፈረጁና የማግለል ስልትን ባለመከተሉ ለሙስሊሙ የደርግ ሥርዓት ከአፄ ኃይለ ሥላሴ ሥርዓት በእጅጉ የተሻለ መሆኑን አሳይቷል። አክሱምን ጨምሮ በአንዳንድ ሰሜናዊው የሀገሪቷ ክፍሎች የሚገኙ ሙስሊሞች ሕጋዊ የሙስሊሞች መካነ መቃብር እንኳን ማግኘት የቻሉት በአፄ ኃይለ ሥላሴ መንግስት ውድቀት ማግስት ነበር። በነኝህና በሌሎች በርካታ ቆራጥ እርምጃዎቹ የደርግ መንግስት በመጀመሪያዎቹ ጥቂት የአገዛዝ ዘመኑ ለሙስሊሞች ውለታ ቢውልም ኋላ ላይ ግን በሙስሊሙም ሆነ በሌሎች በርካታ ጉዳዮች የሚያስወቅሱ በርካታ ተግባራትን ፈጽሟል። ይህን ርዕስ ስናጠቃልልም ያኔ አስተዋፅኦ ያደረጉትን ሙስሊሞች የተቻለንን ያህል ስማቸውን መጥቀስ ያሻል ብለን ስላሰብን በዚሁ መሰረት ዝርዝራቸውን እነሆ ብለናል፡- እነ ሐጂ ሙሐመድ ሳኒ ሐቢብ፣ ሐጂ ዩሱፍ ዐብዱረሕማን፣ ዐብዱ በሽር፣ ዐብዱ አደም፣ ሐጂ ሻሚል ኑርሰቦ፣ ጀማል ዐሊ፣ ዐብደላ ሐሰን፣ ዐብደላ ዐብዱልቃዲር፣ አሕመድ ሸኽ አወል፣ ሲራጅ ሱለይማን፣ አሕመዲን ዩሱፍ፣ ዐብዱሶመድ ሰመረዲን፣ ሰዒድ ዩሱፍ፣ አሕመድ ዋሴ፣ ሲቲሚያ ሙሐመድ /ሴት/፣ አቶ ዐሊ አሕመድ፣ አቡበክር ሱለይማን፣ ሙሐመድ ሐጂ ሙሐመድ ሳኒ፣ ዒዘዲን ሙሐመድ /የአል ቁድስ አዘጋጅ የነበረው/፣ በድሩ ሡልጣን /የቃጥባሬ ሸኽ ልጅ/፣ አባቢያ አባጆቢር፣ አቶ አሕመድ ሰዒድ ዐሊ፣ አቶ ሙሐመድ አሕመድ ሸሪፍ እና ሐጂ ነጂብ ሙሐመድ ወዘተ ለሙስሊሙ መብት መከበር ከታገሉት መካከል ይገኙበታል። በሕይወት የሌሉትን አላህ ይማራቸው! ያሉትንም ያቆያቸው! በወቅቱ የታገሉት ከላይ የተጠቀሱት ብቻ ናቸው ማለት አይደለም። ሥማቸው እዚህ ያልተጠቀሱትም በርካቶች አሉ። ***************************** ደካማ ይልቃል ኃይለኛ ሲዋረድ ቡቃያ ይበቅላል ያፈራው ሲታጨድ ሰፊው ይቀንሳል ጠባቡ ሲስፋፋ ጨረቃ ታምራለች ፀሐይ ስትጠፋ ከንቅልፉ ሲነቃ ደግሞ የፈዘዘ የሞቀው ይሄዳል እየቀዘቀዘ እንደሕልም ታይቶ ያልፋል እንደጥላ ለዚህ ዓለም ነገር ምንም የለው መላ መታወቅ መረሳት ማርጀት መታደስ ይህ ሁሉ ልማድ ነው አይደለም አዲስ፡፡ (ዶ/ር ከበደ ሚካኤል)
Mostrar todo...
139👍 90
እስካሁን ስንዳስስ የቆየነው ይህ የ1966ቱ የሙስሊሞች መብት የማስከበር ሰልፍ ለህዝበ ሙስሊሙ የተለያዩ ጥቅሞችን ማስገኘት ችሏል። ሙስሊሙ ማህበረሰብ ከፍተኛ መነቃቃትን ከመፍጠሩ በተጨማሪ ከህዝበ ክርስቲያኑ ጋር በጋራ አጀንዳ ላይ አብረው መቆም እንደሚችሉ በማሳየት ፈር ቀዳጅ ነበር። ስልጣን ላይ የሚወጣው ቀጣዩ መንግስትም የሙስሊሙን ማህበረሰብ ጥያቄዎችንና ብዛቱን እንዲረዳ ከማድረጉ በተጨማሪም የሚቋቋመው መንግስትም ሐይማኖታዊ ያልሆነ፣ ሁሉንም በእኩልነት የሚያስተናግድና ዓለማዊ መንግስት (Secular State) መሆን እንዳለበት አመላክቷል። የአፄ ኃይለ ሥላሴ መንግስት ሌላ ሽፋን ቢሰጠውም በዋናነት እስልምናን እና ሙስሊሞችን ለማዳከም የተቋቋመውን የሕዝባዊ ኑሮ እድገት ሚኒስቴር መስሪያ ቤትን ቀጣዩ መንግስት ፀረ-ኢስላም ዓላማውንና ድብቅ ተግባሩን በመቀልበስ ‹‹ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር›› በሚል እንደገና እንዲቋቋም አግዟል። በንቅናቄው ማግስት ስልጣን ላይ የወጣው የደርግ መንግስት የእምነት እኩልነትን ሕግ እንዲያውጅ በማድረጉ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ባህሉንና እምነቱን ሳይሸማቀቅ እንደ ሌሎች ዜጐች እንዲተገብር አስችሎታል። ከዚህ በተጨማሪም በንቅናቄው ንቃተ ሕሊናቸውን ያዳበሩ የተለያዩ ግለሰቦች ሰልፉ ያነሳቸውን ጥያቄዎች በማንሳት ሕዝቡ ይበልጥ ተነቃቅቶ ለመብቱ እንዲታገል እንዲያነሳሱ አስችሏቸዋል። ለአብነትም በአዲስ አበባ ከተማ ከተክለሃይማኖት በታች በስልጤ ሰፈር የሚገኘው የሐጂ አሕመድ መሒሊ መስጊድ ከሰልፉ ከሁለት ዓመታት በኋላ መስጊዱ የተመሰረተበትን 27ኛ ዓመት በነሐሴ 9 ቀን 1968 ዓ.ል ባከበረበት ጊዜ የመስጊዱ ኮሚቴ አመራር ያደረገውን ንግግር እንመልከት። በዕለቱ የመስጊዱ ኮሚቴ በጽሁፍ ያደረገው ንግግር የወቅቱን የንቃተ ሕሊና ደረጃ እንድንረዳ ዘንድ ስለሰልፉና ስለሙስሊሙ ጥያቄ የሚያወሳውን እንይ፡- ‹‹ከዚህ በቀር ትዝታው ከማይጠፋንና እያንዳንዱ ምእመናን ከፍተኛ በሆነ አንክሮዋዊ ስሜት ሲያስታውሰው የሚኖር የእስላሙ ህብረተሰብ ለሀይማኖቱ እኩልነት ያደረገው ከፍተኛ ሰላማዊ ሰልፍ ነበር። ጭቁኖች የጋራ ጠላታቸውን ለመቋቋም እንዲተባበሩ የሕብረተሰብ ዕድገት ሕግ ነውና አመፁ በሥርዓቱ ላይ ነውና ተራማጅ የሆኑ የህብረተሰብ አባሎችና ክርስቲያን ወንድሞችም በዚህ ሰልፍ መካፈላቸው ሌላው ትዝታ ነበር። በሰልፉ ወቅት ከቀረቡት መፈክሮች ውስጥ ‹ሃይማኖት ከመንግስት አስተዳደር ይገንጠል›፣ ‹በዓላችን በብሔራዊ ደረጃ ይከበር›፣ ‹እስልምና ወንጀል አይደለም›፣ ‹የሃይማኖት እኩልነት ይኑር›፣ የሚሉ ይገኙበታል። በዚያን በወቅት ነበር የአክሊሉ ካቢኔ አይንህን ላፈር የተባለው። በዚያን ጊዜ ነበር ጭቁኖች ቢተባበሩ አንድም ኃይልሊቋቋማቸው እንደማይችል የታወቀው። ያኔ ነበር ያንድን ሕብረተሰብ ስንኩል አስተዳደር የግለሰብ መለዋወጥ ሊለውጠው እንደማይችል ያሳወቀው። ከዚያን በኋላ ነበር እኩልነት እስካልተመሠረተ ድረስ ሰላም እንደማይኖር፣ ያንዲት ሴኮንድ እፎይታ እንደሌለ፣ ጭቁኑ ከትግሉ የተማረበት፣ በአንፃሩም ለአድርባዮች፣ ለባንዳዎችና፣ ለአሽቃባጮች፣ ለመሳሰሉትም ሁሉ የትግል ሚናውን፣ የእኩልነት መርሆውን፣ የአንድነት አርማውን፣ የታሪክ ባለ አደራነቱን ያስተማረበት ወቅት። ከዚያ በኋላ የእስላሙ ሕብረተሰብ ካቀረባቸው ባለአሥራ ሦስት ነጥብ ጥያቄዎች ውስጥ መልስ ያገኘው አንዱ ብቻ ነው። ይኸውም የእስልምና በዓል በብሔራዊ ደረጃ በማክበሩ ብቻ ተወስኖ መቅረት እንደሌለበት እያንዳንዱ ምእመናን መገንዘብ ሲኖርበት ይህንንም የሚወሰነው የራሱ ንቃትና የአንድነት ክንዱ ነው።›› (ዐብዱልፈታህ ዐብደላ፣ የአዲስ አበባ መስጂዶች ታሪክ፣ ቁጥር 2፣ ግንቦት 2002፣ አማን ኘሮሞሽን፣ ድሬ ማተሚያ ቤት፣ ገጽ 21) ይህ የመስጊድ ኮሚቴ አመራር ንግግር የወቅቱን የንቃት ደረጃ፣ንቅናቄው ሁሉንም ጥያቄዎች ሊያስመልስ አለመቻሉንና የሰልፉን ትዝታ በማንሳት ሙስሊሞች የተቀሩትንም ጥያቄዎቻቸውን ማስመለስ የሚችሉት በተባበረ ትግላቸው እንደሆነ ለማስገንዘብ እንደነበረ ያስረዳናል። ጥያቄዎቹ በሙሉ ሊመለሱ ላለመቻላቸው በርካታ ምክንያቶችን መዘርዘር እንችላለን። በዋናነት የትግሉ አለመቀጠል፣ የሙስሊሙ በትንሽ ነገር ተደስቶ የመዘናጋት ባህሪና መብቱን ሌሎች እንዲሰጡት አልያም ታግለው እንዲያስከብሩለት ከመፈለግ ዝንባሌ ሙሉ በሙሉ መላቀቅ ያለመቻሉ ችግር ተጠቃሽ ናቸው። አፄ ኃይለ ሥላሴ መንግስታቸው በሕዝባዊ ማዕበል እየተንገዳገደ በነበረበት ጊዜም ሆነ ሥርዓቱ ከተወገደ በኋላ ሙስሊሙ ህብረተሰብ እንደሌላው ሁሉ ራሱ ጥያቄዎቹን ለማስመለስ ተደራጅቶ ከመታገል ይልቅ የመረጠው አዲሱ መንግስት መብቱን እንዲሰጠው እየጠየቀ በተስፋ መቀጠልን ነበር። በርግጥ ያ ንቅናቄ ጠንካራ፣ ማደራጀት የሚችል፣ በሕዝቡ ዘንድ ተቀባይነት የነበረው እና ዋጋ ለመክፈል የተዘጋጀ አመራር ቢያገኝ ኖሮ ሕዝበ ሙስሊሙን ጥያቄውን ከማስመለስ አልፎ በሀገሪቱ ላይ ተጽእኖ ፈጣሪ፣ ተደማጭ እና የፖለቲካ ኃይልያለው ህብረተሰብ ሊያደርገው ይችል ነበር። ይሁን እንጂ ይህ እንዳይሆን እንቅፋት የሚሆኑ ነገሮች ነበሩ። ከነዚህ መካከል ሕዝበ ሙስሊሙ ከንግድ መስክ ውጭ ሀገራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ የተሳትፎ ልምድ ማጣት፣ በአፄ ኃይለ ሥላሴ አግላይ ፖሊሲ የተነሳ በሁሉም ዘርፍ በቂ ሊባል የሚችል ልሂቃን (Elites) አለማፍራት እና የትምህርት እድል ያገኙትም ብዙዎቹ ተመልሰው ወደ ንግዱ መስክ መመለሳቸውን በዋናነት መጥቀስ እንችላለን። ከዚህ የተነሳ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ በመንግስት መስሪያ ቤቶች፣ በጦር ሠራዊቱ እና በሌሎች ወሳኝ መስኮች የሙስሊሙ ቁጥር እጅግ በጣም አናሳ ከመሆኑ የተነሳ ከግምት የሚገባ አልነበረም። በአዲሱ የደርግ መንግስትም ወሳኝ ቦታዎችን የያዙት አፄ ኃይለ ሥላሴ ሥርዓት ውስጥ በተለያዩ መስክ እድል ያገኙት ነበሩ። ለምሳሌ ከጦሩ የተለያየ ክፍለ ጦር ተወጣጥቶ ከፍተኛውን የሀገሪቱ ሥልጣን ከዚያው የደርግ ምክር ቤት አንድ መቶ ሀያ አባላት መካከል ሙስሊም አንዱ ብቻ ነበር። ይህ ግለሰብም ሆነ ኋላ ላይ በተለያየ የታችኛው እርከን ደርግን የተቀላቀሉ ጥቂት ሙስሊሞችም ቢሆኑ ሙስሊምነታቸው ከስም በዘለለ በእምነታቸው ሳይሸማቀቁ የወገኖቻቸውን አጀንዳ ለማንሳት የሚደፍሩ ነበሩ ለማለት ያስቸግራል።በመሆኑም የነርሱ በሥርዓቱ ውስጥ መታየት ለሙስሊሙ ያስገኘው ጥቅም ይህ ነው ብሎ ለማስቀመጥ ያዳግታል። በወቅቱ በሀገሪቱ በተፈጠረው መነቃቃት ምክንያት የተለያዩ አካላት የራሳቸውንና የወገናቸውን አጀንዳዎች በማንሳት ተደራጅተው በይፉም ሆነ በሕቡዕ ሲንቀሳቀሱ ሕዝበ ሙስሊሙ ግን የራሱን አጀንዳ ይዞ የሚታገልለት ለአዲሱ መንግስት አጋርም ሆነ ተቃዋሚ ድርጅትም ሆነ ፖርቲ አልነበረም። በወቅቱ እንደ መኢሶን ያሉት ገዢውን መንግስትከመቃወም ይልቅ አጋር ፓርቲ ሆነው ለተሻለ ለውጥ መሥራትን ሲመርጡ እንደ ኢህአፓ ያሉት ደግሞ ወታደራዊው መንግስት ከስልጣኑ ወርዶ ሕዝባዊ መንግስት ይቋቋም በሚል ተቃዋሚ ሆነው በሕቡዕ ይታገሉ ነበር። ከዚህ አንፃር የሙስሊሙ ለሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮች ከመሳተፍ ወደኋላ መቅረቱ ብቻ ሳይሆን እንቅስቃሴውም በሃይማኖትታዊ አጀንዳ ላይ እየተገደበ ሄደ። በወቅቱ ሙስሊሙ ከራሱ የእምነት ጥያቄ በተጨማሪ ‹‹መሬት ላራሹ››፣ ‹‹ሃይማኖት ከመንግስት አስተዳደር ይገንጠል››፣ ‹‹እኩልነት በተግባር ይተርጎም›› እና መሰል ጥያቄዎችን እንዳላነሳ ሁሉ ገፍቶ ባለመሄዱ እና ሂደቱ ሁሉ ዳግም
Mostrar todo...
👍 75 8
"አትነሳም ወይ አትነሳም ወይ ይህ ጥያቄ ያንተ አይደለም ወይ?" ክፍል 7 (የመጨረሻው ክፍል) 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 የትግሉ ውጤት 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 በአፄ ኃይለ ሥላሴ መንግስት ላይ ሕዝባዊ የተቃውሞ ማዕበል ተጠናክሮ ቀጠለ፡፡ ሥርዓቱን ይፈራ የነበረው ሁሉ በድፍረት ለመብቱ መነቃነቅ ቀጠለ፡፡ ይህ እየሆነ ባለበት ጊዜ እንኳ ንጉሡ ሕዝቡ ይህን ማድረግ መብቱ እንደሆነ አምነው ተቀብለው ችግሩን ለመፍታት ከመሞከር ይልቅ ሕዝቡን በንቀት ይመለከቱ ነበር፡፡ ሕዝቡ ለመብቱ መታገሉን እንደመባለግ የቆጠሩት አፄ ኃይለ ሥላሴ እንዲህ ሲሉ ተናግረው ነበር፡- ‹‹በርግጥ የኢትዮጵያ ሕዝብ አንድ ጊዜ ለከቱን መክፈት ሲጀምር ባቄላ የቋጠረ ስልቻ ቁልቁል ዘቅዝቆ መቋጠሪያውን መፍታት እንደማለት ስለሆነ መናገሩን አያቆምም፡፡ ሕዝቡ ከልክ በላይ እንደባለገ ይታያል፡፡›› (ኮለኔል ቃለ ክርስቶስ ዓባይ፣ የ1953ቱ የመንግስት ግልበጣ ሙከራና ከ1908-1966 ዓ.ም የኢትዮጵያ ታሪካዊና ፖለቲካዊ ሂደት፣ የመጀመሪያ ዕትም፣ ነሐሴ 1997፣ አዲስ አበባ፣ ገጽ 399) ሕዝባዊው አመፅና ተቃውሞ ከየአቅጣጫው ተጠናክሮ ቀጠለ። ደርግም ሕዝቡ በከፊል ሥልጣኑን የነጠቀውን የአጼ ኃይለ ሥላሴን አስተዳደር ገርሥሶ ለመጣል የሙስሊሙ ሰልፍም አጋዥ ሆኖታል። የሕዝቡ ጸረ-ኃይለ ሥላሴ አቋም የልብ ልብ ሰጠው። ሚያዚያ 18 ቀን 1966 ዓ.ል ደርግ ‹‹አገርንና ሕዝብን በድለዋል›› ያላቸውን የአፄ ኃይለ ሥላሴ ባለሥልጣናትን ከያሉበት እየለቀመ በቁጥጥር ሥር አዋለ። በሐምሌ 15 ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስተር እንዳልካቸው በደርግ ከሥልጣኑ ተወገደ። ነሐሴ 15 ቀን 1966 ዓ.ል የዙፋን ችሎት፣ የዘውድ ምክር ቤት እና የፍርድ አጣሪ ጉባዔ እንዲፈርስ ተደረገ። በሲ.አይ.ኤ ባለሙያዎች አማካኝነት የሰለጠነውና የተቋቋመው የኃይለ ሥላሴ ‹‹ልዩ ኤታማዦር›› /የሥለላም ጭምር ነው/ ተጠሪነቱ ለመከላከያ ሚኒስትር እንዲሆን ተደረገ። ጳጉሜ 4 ቀን 1966 ቀደማዊ ኃይለ ሥላሴ ከዙፋናቸው እንዲወርዱ በደርግ ተወሰነ። መስከረም 2 ቀን 1967 ዓ.ል ከጠዋቱ 4 ሰዓት ላይ አፄው ከሥልጣናቸው ተወገዱ። በቮልስ ዋገን መኪና ከቤተ መንግሥት ቅጥር ጊቢ ወደ 4ኛ ክፍለ ጦር ተወሰዱ። ተበዳዩ ሕዝብም እንደዚያ በሚሰቀጥጥ ሁኔታ ከፍርሃት የተነሳ ይሰግድላቸው የነበረውን ንጉሥ ኃይለ ሥላሴን በድፍረት ‹‹ይሰቀል! ሌባ! ይሰቀል! ሌባ!›› እያለ ሸኛው። ታሰሩም። (ዘነበ ፈለቀ፣ ነበር፣ ነሐሤ 2000፣ አዲስ አበባ፣ ገጽ 60-80) ታኅሳስ 14 ቀን 1967 በብሔራዊ ደረጃ ስለሚከበሩ በዓላት ዝርዝር መግለጫ ወጣ። የሙስሊሙ ትግል በከፊል ፍሬ ማፍራት ጀመረ። ኢስላማዊ በዓላትም ብሔራዊ በዓላት ሆነው ተቆጠሩ። ‹‹የሕዝብ በዓላት አዋጅ›› የተሰኘ አዋጅ ወጣ። ቀደም ብሎ በ1948 የወጣው አዋጅ ቁጥር ‹‹151/19481/15/9/1948 አ.151›› ተሻረ። በአዋጁ እውቅና ከተሰጣቸው አሥራ ሁለት በዓላት መካካል ሦስቱ የሙስሊሞች በዓላት ነበሩ። እነሱም ዒድ አል ፊጥር፣ ዒድ አል አድሃና የመውሊድ በዓላት ነበሩ። (የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ማኅደር ቁጥር 3432) ታኅሳስ 15 ቀን 1967 የዐረፋ /ዒደል አደሃ/ በዓል የሙስሊሙ የመጀመሪያው በዓል ሆኖ በብሔራዊ ደረጃ ተከበረ። ለአዲሱ መንግስት መመሪያነት ሕገ መንግስት ለማርቀቅ የሕገ-መንግሥት አርቃቂ ኮሚቴ ተቋቋመ። ሐጂ ሙሐመድ ሳኒ ሐቢብ፣ ሐጂ ዩሱፍ ዐብዱረሕማን፣ ሐጂ ሱለይማን ወዘተ… አባል ሆኑ። በሐሳብ የሚረዷቸው የወጣት ምሁራን ኮሚቴ አቋቋሙ። ኮሚቴው የሌላን አገር ተሞክሮ ከታሪክ አኳያ፣ እንዲሁም ስለ ሕገ-መንግሥት እና ሃይማኖት ከቤተ-መጽሐፍት በማንበብ በሐሳብና በምክር ከበስተጀርባ ሆኖ ያግዛቸው ጀመር። ለስድስት ወራትም በዚሁ ሁኔታ ቀጠለ። ለክርስትና ብቻ እውቅና የሚሰጠው ሕገ-መንግሥትም ተሻረ። ሙሉ ለሙሉ ባይሆንም የሙስሊሙ መብት መከበር ጀመረ። ኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞች ለረጅም ጊዜ የታገሉለትና የደከሙበት ‹‹መጅሊሰል አዕላ›› (የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ጉባዔ) በ 1968 ተቋቋመ። የአፄው ሥርዓት በሕዝቦች አብዮት ተገርስሶ የደርግ መንግሥት ሥልጣኑን ሙሉ በሙሉ ሲረከብ በ1966 ክርስትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሃይማኖት መሆኑ አከተመ። የመንግሥትና ቤተ-ክህነት የጋብቻ ሰማንያ ተቀደደ። የሙስሊሙ በዓላት በራሱ በሙስሊሙ ትግል እውቅና አግኝተው ብሔራዊ በዓል ሆኑ። ‹‹በኢትዮጵያ የሚኖሩ እስላሞች›› የሚለው አጠራር ‹‹ኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞች›› በሚል ተተካ። ከፊል የሕዝበ-ሙስሊሙ ጥያቄዎች በትግሉ ተረጋገጡ። ለመጀመሪያ ጊዜ በብሔራዊ ደረጃ የሙስሊሙ በዓል ተከበረ። በሙስሊሙ በዓልም እንደ ክርስትያኑ በዓል ሥራ ተዘጋ። ተማሪው ዒድን አክብሮ ዋለ። እንደ ከዚህ ቀደሙ በዒድ ቀን ፈተና መሰጠቱ አከተመ። የመጀመሪያው የደርግ ሊቀመንበር ጄኔራል ሚካኤል አማን አንዶም በዓለም አቀፍ የጋዜጠኞች ጉባዔ ላይ በሰጠው የፕሬስ መግለጫ የኢትዮጵያ ሙስሊም ኅብረተሰብ ከአጠቃላይ የአገሪቷ ሕዝብ ውስጥ 55 (ሐምሳ አምስት) በመቶ መሆኑን አምኖ ልዩ እንክብካቤ እንደሚያስፈልጋቸው ይፋ ማድረጉን አዲስ ዘመን ጋዜጣ በመስከረም ስድስት 1967 እትሙ ማስፈሩን ሙሐመድ ዩሱፍ ያዕቁብ ‹‹የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የመከራና የስቃይ ታሪክ›› በተሰኘው መጽሐፉ አስፍሯል። ያ ታሪካዊ ሰልፍ ሙስሊሙ አንገቱን ቀና ያደርግ ዘንድ አስችሎታል። ወኔውን አዳብሮለታል። ከሰልፉ በፊት አንድ ተራ ፖሊስ ሠላሳና ሐምሳ ሙስሊሞችን እንደከብት ነድቶ ያስር ነበር፤ ያ ሁሉ ቀረ። ዛሬ ላይ ላገኘነው ነጻነት ትልቁ ባለ ድርሻ ያኔ የታገሉት አባቶቻችን ናቸው። ይህ የሙስሊሙ የመብት ትግል የአንድ ጀንበር ብቻም አይደለም። የዘመናት ብሶትና በደል፣ እንዲሁም ማነቃቃት ውጤት ነበር። ምንም እንኳን በወቅቱ የተነሱት ጥያቄዎች ሙሉ ለሙሉ ባይመለሱም ክስተቱ ሙስሊሙ አንገቱን ቀና እንዲያደርግና ለመብቱ መታገል እንዳለበት እንዲያውቅ አድርጓል። ሙስሊም መሆን መዋረድን ያስከትል የነበረው ያኔ አክትሟል። መብትም በትግል እንጂ በልመና እንደማይገኝ አሳይቶ አልፏል።
Mostrar todo...
👍 72 18
ት ሳያስመዘግብ ቀርቷል። ይህ ሊሆን የቻለው የዓለም ታሪክ እንደሚያስገነዝበው የትኛውም ሕዝብ መብቱንና እኩልነትን በልመናና ተማጽኖ ሊያገኝ የቻለበት ሁኔታ ያልታየ በመሆኑ ነው። ሂደቱን ስንመለከት የ1966ቱ የሙስሊሙ ንቅናቄ መሪዎች የላቀ ባይሆንም በተግባር ግን ካነሷቸው 13 የመብት ጥያቄዎች ምላሽ ሲሹ የነበሩበት በዋናነት መንግስትን በመማፀን፣ በመለመንና ምላሽ እንደሚያገኙ ተስፋ በማድረግ ነበር፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሕዝበ ሙስሊሙ ልሂቃንን በማፍራት እና በማብቃት ሥራ ላይ በቀጣይነት ሲንቀሳቀሱ አናይም። እነኝህን በመተግበር እንደሌሎቹ የመብት አስከባሪ ታጋዮች ሁሉ በሀገሪቷ ሁለንተናዊ ጉዳዮች ውስጥ በተለይም በፖለቲካው በመሳተፍ ትግል ቢያካሂዱ ኖሮ የተሻለ ለውጥን ማምጣት በቻሉ ነበር። ምክንያቱም በሀገሩ ፖለቲካ ላይ እኩል ተሳታፊ ያልሆነ አካል ሁሌም በሀገሪቱ እጣፈንታ ላይ እኩል የመወሰን እድል አይኖረውም። ይህ ሲሆን ደግሞ በሀገሩ እጣፈንታ ላይ ሚናው አነሳ ከመሆኑም በተጨማሪ የራሱ እጣፈንታ ጭምር በሌሎች መዳፍ ስር ይወድቃል። በዚህ ሁኔታ ውስጥ ደግሞ የቱንም ያህል ቅንና ፍትሓዊ ጥያቄዎች ቢኖሩትም እኩል ተጠቃሚ የመሆን ዕድሉ ሩቅ ነው። በርግጥ የደርግ መንግስት የአፄ ኃይለ ሥላሴን ሥርዓት በማስወገድ ለኢስላም እና ለሙስሊሞች በብሔራዊ ደረጃ እውቅና በመስጠቱ አንፃር ብቻ ስናየው ሥርዓቱ ለሙስሊሞች ባለውለታ ነበር። ይሁን እንጂ በቀድሞ ሥርዓቶች የማግለል ፖሊሲ ምክንያት ሙስሊሙ ማህበረሰብ ከሀገሪቷ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ተቋማት በመገለሉ ምክንያት የተፈጠረበትን በደልና በብዙ መልኩ ወደ ኋላ የመቅረቱን እውነታ የሚያካክስ አዎንታዊ እርምጃዎችን (Affirmative Actions) ባለመወሰዱ ልዩነቱ በብዙ መልኩ ቀጥሏል፡፡ በመሆኑም በደርግ ስርአት ውስጥ አብዛኞቹ የመንግስት አስተዳደር፣ የፖለቲካ ተቋማት እና በመንግስታዊ መስሪያ ቤቶች ውስጥ የሙስሊሞች ቁጥር አናሳ እንደሆነ ዘልቋል። ያም ሆነ ይህ በደርግ የመጀመሪያዎቹ የስልጣን ዘመናት ሕዝበ ሙስሊሙ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በጣት ሊቆጠሩ የሚችሉ አንኳር ጥቅሞችን አግኝቷል። በዝርዝር በዚህ መጽሐፍ ውስጥ የተጠቀሱትና በሕዝበ ሙስሊሙ ላይ ሲደርሱ የነበሩትን ጭቆናዎች አብዛኛዎቹን ያስወገደው የደርግ መንግስት ነበር። የኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞች መሪ ድርጅት የሆነው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጉባኤ (መጅሊስ) ለመጀመሪያ ጊዜ የተቋቋመው በዚሁ በደርግ ዘመን በመጋቢት 4 ቀን 1968 ዓ/ል ነበር። ህዝበ ሙስሊሙም በካድሬዎች ሳይሆን እንደነ ሐጅ ሙሐመድ ሳኒ ሐቢብ ባሉና ቁርኣንን ወደ አማርኛ በተረጎሙ ስመጥር ሊቃውንት እንዲመራ የደርግ መንግስት ፈቅዷል። የሃይማኖት እኩልነትን እሳቤ በሕዝቡ ውስጥ ለማስረፅም ጥሯል። ኋላ ላይም ሥርዓቱ ከተከተለው የሶሻሊስት ርዕዮተ ዓለም ፍልስፍና አንፃር ሁሉንም ሃይማኖት በጥርጣሬና በስጋት ቢያይም እንደ መንግስት ሙስሊሙን ብቻ ነጥሎ የሥርዓቱ እና የሀገሪቷ ስጋት አድርጎ ባለመፈረጁና የማግለል ስልትን ባለመከተሉ ለሙስሊሙ የደርግ ሥርዓት ከአፄ ኃይለ ሥላሴ ሥርዓት በእጅጉ የተሻለ መሆኑን አሳይቷል። አክሱምን ጨምሮ በአንዳንድ ሰሜናዊው የሀገሪቷ ክፍሎች የሚገኙ ሙስሊሞች ሕጋዊ የሙስሊሞች መካነ መቃብር እንኳን ማግኘት የቻሉት በአፄ ኃይለ ሥላሴ መንግስት ውድቀት ማግስት ነበር። በነኝህና በሌሎች በርካታ ቆራጥ እርምጃዎቹ የደርግ መንግስት በመጀመሪያዎቹ ጥቂት የአገዛዝ ዘመኑ ለሙስሊሞች ውለታ ቢውልም ኋላ ላይ ግን በሙስሊሙም ሆነ በሌሎች በርካታ ጉዳዮች የሚያስወቅሱ በርካታ ተግባራትን ፈጽሟል። ይህን ርዕስ ስናጠቃልልም ያኔ አስተዋፅኦ ያደረጉትን ሙስሊሞች የተቻለንን ያህል ስማቸውን መጥቀስ ያሻል ብለን ስላሰብን በዚሁ መሰረት ዝርዝራቸውን እነሆ ብለናል፡- እነ ሐጂ ሙሐመድ ሳኒ ሐቢብ፣ ሐጂ ዩሱፍ ዐብዱረሕማን፣ ዐብዱ በሽር፣ ዐብዱ አደም፣ ሐጂ ሻሚል ኑርሰቦ፣ ጀማል ዐሊ፣ ዐብደላ ሐሰን፣ ዐብደላ ዐብዱልቃዲር፣ አሕመድ ሸኽ አወል፣ ሲራጅ ሱለይማን፣ አሕመዲን ዩሱፍ፣ ዐብዱሶመድ ሰመረዲን፣ ሰዒድ ዩሱፍ፣ አሕመድ ዋሴ፣ ሲቲሚያ ሙሐመድ /ሴት/፣ አቶ ዐሊ አሕመድ፣ አቡበክር ሱለይማን፣ ሙሐመድ ሐጂ ሙሐመድ ሳኒ፣ ዒዘዲን ሙሐመድ /የአል ቁድስ አዘጋጅ የነበረው/፣ በድሩ ሡልጣን /የቃጥባሬ ሸኽ ልጅ/፣ አባቢያ አባጆቢር፣ አቶ አሕመድ ሰዒድ ዐሊ፣ አቶ ሙሐመድ አሕመድ ሸሪፍ እና ሐጂ ነጂብ ሙሐመድ ወዘተ ለሙስሊሙ መብት መከበር ከታገሉት መካከል ይገኙበታል። በሕይወት የሌሉትን አላህ ይማራቸው! ያሉትንም ያቆያቸው! በወቅቱ የታገሉት ከላይ የተጠቀሱት ብቻ ናቸው ማለት አይደለም። ሥማቸው እዚህ ያልተጠቀሱትም በርካቶች አሉ። ***************************** ደካማ ይልቃል ኃይለኛ ሲዋረድ ቡቃያ ይበቅላል ያፈራው ሲታጨድ ሰፊው ይቀንሳል ጠባቡ ሲስፋፋ ጨረቃ ታምራለች ፀሐይ ስትጠፋ ከንቅልፉ ሲነቃ ደግሞ የፈዘዘ የሞቀው ይሄዳል እየቀዘቀዘ እንደሕልም ታይቶ ያልፋል እንደጥላ ለዚህ ዓለም ነገር ምንም የለው መላ መታወቅ መረሳት ማርጀት መታደስ ይህ ሁሉ ልማድ ነው አይደለም አዲስ፡፡ (ዶ/ር ከበደ ሚካኤል)
Mostrar todo...
ቄዎች በማንሳት ሕዝቡ ይበልጥ ተነቃቅቶ ለመብቱ እንዲታገል እንዲያነሳሱ አስችሏቸዋል። ለአብነትም በአዲስ አበባ ከተማ ከተክለሃይማኖት በታች በስልጤ ሰፈር የሚገኘው የሐጂ አሕመድ መሒሊ መስጊድ ከሰልፉ ከሁለት ዓመታት በኋላ መስጊዱ የተመሰረተበትን 27ኛ ዓመት በነሐሴ 9 ቀን 1968 ዓ.ል ባከበረበት ጊዜ የመስጊዱ ኮሚቴ አመራር ያደረገውን ንግግር እንመልከት። በዕለቱ የመስጊዱ ኮሚቴ በጽሁፍ ያደረገው ንግግር የወቅቱን የንቃተ ሕሊና ደረጃ እንድንረዳ ዘንድ ስለሰልፉና ስለሙስሊሙ ጥያቄ የሚያወሳውን እንይ፡- ‹‹ከዚህ በቀር ትዝታው ከማይጠፋንና እያንዳንዱ ምእመናን ከፍተኛ በሆነ አንክሮዋዊ ስሜት ሲያስታውሰው የሚኖር የእስላሙ ህብረተሰብ ለሀይማኖቱ እኩልነት ያደረገው ከፍተኛ ሰላማዊ ሰልፍ ነበር። ጭቁኖች የጋራ ጠላታቸውን ለመቋቋም እንዲተባበሩ የሕብረተሰብ ዕድገት ሕግ ነውና አመፁ በሥርዓቱ ላይ ነውና ተራማጅ የሆኑ የህብረተሰብ አባሎችና ክርስቲያን ወንድሞችም በዚህ ሰልፍ መካፈላቸው ሌላው ትዝታ ነበር። በሰልፉ ወቅት ከቀረቡት መፈክሮች ውስጥ ‹ሃይማኖት ከመንግስት አስተዳደር ይገንጠል›፣ ‹በዓላችን በብሔራዊ ደረጃ ይከበር›፣ ‹እስልምና ወንጀል አይደለም›፣ ‹የሃይማኖት እኩልነት ይኑር›፣ የሚሉ ይገኙበታል። በዚያን በወቅት ነበር የአክሊሉ ካቢኔ አይንህን ላፈር የተባለው። በዚያን ጊዜ ነበር ጭቁኖች ቢተባበሩ አንድም ኃይልሊቋቋማቸው እንደማይችል የታወቀው። ያኔ ነበር ያንድን ሕብረተሰብ ስንኩል አስተዳደር የግለሰብ መለዋወጥ ሊለውጠው እንደማይችል ያሳወቀው። ከዚያን በኋላ ነበር እኩልነት እስካልተመሠረተ ድረስ ሰላም እንደማይኖር፣ ያንዲት ሴኮንድ እፎይታ እንደሌለ፣ ጭቁኑ ከትግሉ የተማረበት፣ በአንፃሩም ለአድርባዮች፣ ለባንዳዎችና፣ ለአሽቃባጮች፣ ለመሳሰሉትም ሁሉ የትግል ሚናውን፣ የእኩልነት መርሆውን፣ የአንድነት አርማውን፣ የታሪክ ባለ አደራነቱን ያስተማረበት ወቅት። ከዚያ በኋላ የእስላሙ ሕብረተሰብ ካቀረባቸው ባለአሥራ ሦስት ነጥብ ጥያቄዎች ውስጥ መልስ ያገኘው አንዱ ብቻ ነው። ይኸውም የእስልምና በዓል በብሔራዊ ደረጃ በማክበሩ ብቻ ተወስኖ መቅረት እንደሌለበት እያንዳንዱ ምእመናን መገንዘብ ሲኖርበት ይህንንም የሚወሰነው የራሱ ንቃትና የአንድነት ክንዱ ነው።›› (ዐብዱልፈታህ ዐብደላ፣ የአዲስ አበባ መስጂዶች ታሪክ፣ ቁጥር 2፣ ግንቦት 2002፣ አማን ኘሮሞሽን፣ ድሬ ማተሚያ ቤት፣ ገጽ 21) ይህ የመስጊድ ኮሚቴ አመራር ንግግር የወቅቱን የንቃት ደረጃ፣ንቅናቄው ሁሉንም ጥያቄዎች ሊያስመልስ አለመቻሉንና የሰልፉን ትዝታ በማንሳት ሙስሊሞች የተቀሩትንም ጥያቄዎቻቸውን ማስመለስ የሚችሉት በተባበረ ትግላቸው እንደሆነ ለማስገንዘብ እንደነበረ ያስረዳናል። ጥያቄዎቹ በሙሉ ሊመለሱ ላለመቻላቸው በርካታ ምክንያቶችን መዘርዘር እንችላለን። በዋናነት የትግሉ አለመቀጠል፣ የሙስሊሙ በትንሽ ነገር ተደስቶ የመዘናጋት ባህሪና መብቱን ሌሎች እንዲሰጡት አልያም ታግለው እንዲያስከብሩለት ከመፈለግ ዝንባሌ ሙሉ በሙሉ መላቀቅ ያለመቻሉ ችግር ተጠቃሽ ናቸው። አፄ ኃይለ ሥላሴ መንግስታቸው በሕዝባዊ ማዕበል እየተንገዳገደ በነበረበት ጊዜም ሆነ ሥርዓቱ ከተወገደ በኋላ ሙስሊሙ ህብረተሰብ እንደሌላው ሁሉ ራሱ ጥያቄዎቹን ለማስመለስ ተደራጅቶ ከመታገል ይልቅ የመረጠው አዲሱ መንግስት መብቱን እንዲሰጠው እየጠየቀ በተስፋ መቀጠልን ነበር። በርግጥ ያ ንቅናቄ ጠንካራ፣ ማደራጀት የሚችል፣ በሕዝቡ ዘንድ ተቀባይነት የነበረው እና ዋጋ ለመክፈል የተዘጋጀ አመራር ቢያገኝ ኖሮ ሕዝበ ሙስሊሙን ጥያቄውን ከማስመለስ አልፎ በሀገሪቱ ላይ ተጽእኖ ፈጣሪ፣ ተደማጭ እና የፖለቲካ ኃይልያለው ህብረተሰብ ሊያደርገው ይችል ነበር። ይሁን እንጂ ይህ እንዳይሆን እንቅፋት የሚሆኑ ነገሮች ነበሩ። ከነዚህ መካከል ሕዝበ ሙስሊሙ ከንግድ መስክ ውጭ ሀገራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ የተሳትፎ ልምድ ማጣት፣ በአፄ ኃይለ ሥላሴ አግላይ ፖሊሲ የተነሳ በሁሉም ዘርፍ በቂ ሊባል የሚችል ልሂቃን (Elites) አለማፍራት እና የትምህርት እድል ያገኙትም ብዙዎቹ ተመልሰው ወደ ንግዱ መስክ መመለሳቸውን በዋናነት መጥቀስ እንችላለን። ከዚህ የተነሳ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ በመንግስት መስሪያ ቤቶች፣ በጦር ሠራዊቱ እና በሌሎች ወሳኝ መስኮች የሙስሊሙ ቁጥር እጅግ በጣም አናሳ ከመሆኑ የተነሳ ከግምት የሚገባ አልነበረም። በአዲሱ የደርግ መንግስትም ወሳኝ ቦታዎችን የያዙት አፄ ኃይለ ሥላሴ ሥርዓት ውስጥ በተለያዩ መስክ እድል ያገኙት ነበሩ። ለምሳሌ ከጦሩ የተለያየ ክፍለ ጦር ተወጣጥቶ ከፍተኛውን የሀገሪቱ ሥልጣን ከዚያው የደርግ ምክር ቤት አንድ መቶ ሀያ አባላት መካከል ሙስሊም አንዱ ብቻ ነበር። ይህ ግለሰብም ሆነ ኋላ ላይ በተለያየ የታችኛው እርከን ደርግን የተቀላቀሉ ጥቂት ሙስሊሞችም ቢሆኑ ሙስሊምነታቸው ከስም በዘለለ በእምነታቸው ሳይሸማቀቁ የወገኖቻቸውን አጀንዳ ለማንሳት የሚደፍሩ ነበሩ ለማለት ያስቸግራል።በመሆኑም የነርሱ በሥርዓቱ ውስጥ መታየት ለሙስሊሙ ያስገኘው ጥቅም ይህ ነው ብሎ ለማስቀመጥ ያዳግታል። በወቅቱ በሀገሪቱ በተፈጠረው መነቃቃት ምክንያት የተለያዩ አካላት የራሳቸውንና የወገናቸውን አጀንዳዎች በማንሳት ተደራጅተው በይፉም ሆነ በሕቡዕ ሲንቀሳቀሱ ሕዝበ ሙስሊሙ ግን የራሱን አጀንዳ ይዞ የሚታገልለት ለአዲሱ መንግስት አጋርም ሆነ ተቃዋሚ ድርጅትም ሆነ ፖርቲ አልነበረም። በወቅቱ እንደ መኢሶን ያሉት ገዢውን መንግስትከመቃወም ይልቅ አጋር ፓርቲ ሆነው ለተሻለ ለውጥ መሥራትን ሲመርጡ እንደ ኢህአፓ ያሉት ደግሞ ወታደራዊው መንግስት ከስልጣኑ ወርዶ ሕዝባዊ መንግስት ይቋቋም በሚል ተቃዋሚ ሆነው በሕቡዕ ይታገሉ ነበር። ከዚህ አንፃር የሙስሊሙ ለሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮች ከመሳተፍ ወደኋላ መቅረቱ ብቻ ሳይሆን እንቅስቃሴውም በሃይማኖትታዊ አጀንዳ ላይ እየተገደበ ሄደ። በወቅቱ ሙስሊሙ ከራሱ የእምነት ጥያቄ በተጨማሪ ‹‹መሬት ላራሹ››፣ ‹‹ሃይማኖት ከመንግስት አስተዳደር ይገንጠል››፣ ‹‹እኩልነት በተግባር ይተርጎም›› እና መሰል ጥያቄዎችን እንዳላነሳ ሁሉ ገፍቶ ባለመሄዱ እና ሂደቱ ሁሉ ዳግም በመስጊድ ብቻ በመወሰኑ ከበርካታ ሀገራዊ ጉዳዮች ወደ ኋላ ተመለሰ። በርግጥ እውነታውን ካየነው የሀገሪቱ አጠቃላይ ችግሮች ሳይቀረፉ የሙስሊሙ ሃይማኖታዊ ጥያቄ ብቻውን ተለይቶ ሊመለስ የሚችልበት ሁኔታ እንደሌለ በመረዳት በሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮችም ላይ ከሌሎች ዜጐች ጋር በጋራ መታገል ነበረባቸው። የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች እንደተጨቆኑ፣ እንደተገፉና በስርዓቱ ውስጥ ተገቢ መብታቸው እንዳልተከበረ በማመናቸው ተደራጅተው ሲታገሉ ለዘመናት ሲጨቆን የነበረው፣ መብቶቹ ያልተከበሩለት እና ከብዙ ሀገራዊ ጉዳዮች ወደ ኋላ የቀረው ህዝበ ሙስሊሙ መብቱን ለማስከበርና እኩልነቱን በሁሉም ዘርፍ በተግባር ለማረጋገጥ የሚታገልለት አካል መፍጠር አልቻለም።በጣት የሚቆጠሩ ሙስሊሞች በወቅቱ ከተቃዋሚ ጐራ ተሰልፈው የነበሩ ቢሆንም የሙስሊሙን አጀንዳዎች የፖርቲዎቹ አጀንዳ ማድረግ አልቻሉም። ቁጥሩ ከሌሎች አንፃር እጅግ አናሳ ቢሆንም ከተቃዋሚዎቹ ይልቅ በደርግ ውስጥ በመጠኑ የተሻለ ቁጥር ያላቸው ሙስሊሞች ነበሩ። ይህ የሆነው ተቃዋሚነት ዋጋ የሚያስከፍል በመሆኑ ዋጋ በመክፈል ለአጀንዳቸው ለመቆም የተዘጋጁ ባለመሆናቸው ሳቢያም ሊሆን ይችላል። በነኝህና መሰል ሌሎች ምክንያቶች የተነሳ ያ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሶ የነበረው መነቃቃት እየቀዘቀዘ የሚገባውን ያህል ውጤ
Mostrar todo...
የሰልፉ ንዝረት ክፍል 6 ⚫️⚫️⚫️⚫️⚫️⚫️⚫️⚫️⚫️⚫️⚫️⚫️⚫️⚫️ ቤተ-ክህነት በሰልፉ ክፉኛ ደነገጠች። ወደ መቃብር እየወረደ የነበረው የአፄ ኃይለ ሥላሴ ሥርዓት ውድቀቱ ተፋጠነ። ሙስሊሙ ራሱ ‹‹ለካስ ይህን ያህል እንሆናለን?›› ሲል ተገረመ። በእምባ የተሞሉ ሙስሊሞች በርካቶች ነበሩ። ከቤተ ክህነት በተበተነው ወረቀት የሙስሊሙን ሰልፍ ለማክሸፍ የተወጠነው ሤራ ራሱ ከሸፈ። በዩኒቨርሲቲ የሚማሩ ክርስቲያን ተማሪዎች የቤተ ክህነትን ጥሪ ወደ ጎን ትተው ከሙስሊሙ ጎን ቆሙ። ፕሮፌሰር ሑሴን አሕመድ “Islam and Islamic Discourse in Ethiopia; 1973-1993” በሚለው ጽሑፋቸው ‹‹ኢትዮጵያ የክርስቲያን አገር እንደሆነችና ሙስሊሙ ከቁጥር የሚገባ እንዳልሆነ በአፄው ሲነገር የነበረውን ቅዠት ሰልፉ በተሳካ ሁኔታ እርቃኑን አስቀርቶታል›› ሲሉ ጽፈዋል። ( Hussien Ahmed, Islamic and Islamic Discourse in Ethiopia, 1973-1993, P.779) በሰልፉ ከሦስት መቶ ሺህ በላይ ሙስሊም ተሳትፎ ብሶቱን አሰማ። የተለያዩ ሚዲያዎች ዜናውን ለዓለም አሠራጩ። የሕዝቡን ቁጥር ቢቢሲ በሁለት መቶ ሺህ ገምቶ ዜናውን ለዓለም አሠራጨ። የኢትየጵያዉያን ሙስሊሞች ሰልፍ በተለያየ ሚዲያ ተዘገበ። አዲስ ዘመን በማግስቱ በሚያዚያ 13/1966 ዓ.ል እትሙ ‹‹ኢትዮጵያዉያን እስላሞች በአዲስ አበባ ከፍተኛ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ›› በሚል ርዕስ ዜናውን ጽፏል። እንዲህ ሲልም ገልጿል፡- ‹‹የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ የሆኑት ኢትዮጵያዉያን የሃይማኖት እኩል መብት እንዲኖራቸው በማሳሰብ ትናንት ከቀትር በፊት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ከዚህ በፊት ተደርጎ የማይታወቅ ከፍተኛ ሰላማዊ ሰልፍ አድርገዋል። በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ከአንድ መቶ ሺህ የሚበልጡ ሰዎች ተካፋይ ሆነዋል። … በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ሽማግሌዎች፣ ባልቴቶች፣ ጎልማሶችና ወጣቶች ሳይቀሩ ተካፋይ ሆነዋል። በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ከዚህ በፊት በአዲስ አበባ ታይቶ የማይታወቅ የሕዝብ ብዛት ቢገኝም አንድም የፀጥታ መታወክ አለመድረሱን ብዙዎቹን አስደንቋል። ይሁን እንጂ የፀጥታውን ሁኔታ ለመቆጣጠር የፖሊስ ሠራዊት አባሎች ከሰላማዊ ስልፈኞች ፊትና ኋላ በመሆን ሁኔታውን ተከታትለዋል።› (አዲስ ዘመን ጋዜጣ፣ ሚያዚያ 13፣ 1966 ) ይህ ሁሉ ሲሆን አፄ ኃይለ ሥላሴ በከፊል ሥልጣናቸው በደርግ እየተነጠቀ ነበር። ሚያዚያ 1 ቀን 1966 የቀረቡት ጥያቄዎች በአፋጣኝ እንዲመለሱ አሳስቦ ያለ ፀጥታ ችግር በሰላም ተበተነ። የቤተ-ክህነት አመራሮችም በሙስሊሙ ሰልፍ የተሰሙት መፈክሮች ቅር እንዳሰኛቸው ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቤቱታቸውን አሰሙ። በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ 42 አብያተ ክርስትያናት ሙስሊሙ ‹‹ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ሳትሆን የኢትዮጵያዉያን ደሴት ናት!›› በሚል በሰልፉ ያሰማውን መፈክር ተቃውመው የአብያተ ክርስትያናቱን ተወካይ በመምረጥ ወደ ፓትሪያርኩ ጽ/ቤት ላኩ። አዲስ ዘመን ጋዜጣ ‹‹ምእመናንና ካህናት ለፓትሪያርኩ ተቃውሞ አሰሙ›› በሚል ርዕስ እንዲህ ሲል ዜናውን ጽፏል፡- ‹‹በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙት 42 አብያተ ክርስትያናት የተወከሉ ካህናትና ምእመናን ትናንት ጧት በመንበረ ፓትሪያርክ ተገኝተው ባለፈው ቅዳሜ ኢትዮጵያዉያን እስላሞች ባደረጉት ሰላማዊ ሰልፍ የሠነዘሯቸውን አንዳንድ ሃይማኖት ነክ ጉዳዮች የሚቃወሙ መሆናቸውን ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን ፓትሪያርክ ገልጠዋል። በዚሁ ጊዜ ካህናቱና ምእመናኑ ለብጹእነታቸው ባቀረቡት የተቃውሞ ሐሳብ፣ ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ የክርስቲያኖች ደሴት መሆኗን ጠቅሰው፣ እስላሞቹ ‹ኢትዮጵያ የክርስትያን ደሴት አይደለችም› ያሉትን ተቃውመዋል። እንዲሁም ‹ኢትዮጵያ የክርስትያን ደሴት ናት› የተባለው ከአክሱም፣ ከጎንደርና ከሸዋ ነገሥታት ሲያያዝ በመጣው የአገሪቱ ጽኑ ሃይማኖት መሠረት መሆኑን አስገንዝበው ይህን ለመሻር የሚደረገው ጥረት የመንግሥቱንም አቋም የሚያናጋ መሆኑን ገልጠዋል። ካህናቱ ውሳኔውን በተግባር ላይ ሆነው የሚጠባበቁ መሆናቸውን ገልጠዋል። ቀጥሎም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ለካህናቱ ተጠሪዎች በሰጡት መልስ ‹የኢትዮጵያ ሕዝብ ሃይማኖቱ ፅኑ፣ ለንጉሠ ነገሥቱ ታማኝ ለመሆኑ ታሪክ ምስክር ነው› ብለዋል። (አዲስ ዘመን ጋዜጣ፣ ሚያዚያ 15 ቀን 1966) ከሁለት ቀናት በኋላ ሚያዚያ 14 ቀን 1966 ዓ.ል ቤተ-ክህነት በመላ አገሪቱ የሙስሊሙን ሰልፍና ጥያቄዎች ለመቃወም ሰልፍ ጠራች። ሙስሊሞች የአፄውን ሥርዓት ለመናድ ከመንቀሳቀስ እንዲቆጠቡና እንደድሮው ‹‹አርፈው መኖር እንዲቀጥሉ›› አሳሰበች። ጭራሽ ሙስሊሙ በሃይማኖት ምክንያት ምንም በደል እንዳልደረሰበት ተናገረች። አፄ ኃይለ ሥላሴ የሃይማኖት ነጻነትን አክብረዋል የሚል ወረቀትም ተበተነ። የወረቀቱ ሙሉ ይዘት የሚከተለው ነበር፡- ‹‹ለወንድሞቻችንና እህቶቻችን እስላሞች! እኛ ኢትዮጵያዉያን ክርስቲያኖች ወንድሞቻችሁና እኅቶቻችሁ እስከ ዛሬ ድረስ ሲፈጸም የኖረውን አገልግሎታችንና ሥራችን፣ እንዲሁም ትብብራችን የሃይማኖት ልዩነት ሳናሳይ መኖራችን የታወቀ ነው። እኛ አሁን የተነሣንበት ዋናው ዓላማ አብዛኛው የዓለም ክፍል እንዳለው ሁሉ የመንግሥቱ ሃይማኖት በዲሞክራቲክ ሕግ መሠረት የሕዝብ ሃይማኖት መሆኑ አያጠራጥርም። ከዚህም በቀር ግርማዊ ንጉሠ ነገሥት ‹ሃይማኖት የግል አገር የጋራ› ብለው ሙሉ መብት መስጠታቸውና ማወጃቸው በኢትዮጵያ የሃይማኖት ነጻነት መኖሩን ለመመስከር እንደሆነ ለማንኛውም የተሠወረ አይደለም። ይህን ዲሞክራቲካዊ አስተያየታችን ለመብት፣ ለፍትሕ፣ ለአንድነትና ለዕድገት ተቆርቋሪ በሆነው ሁሉ በኅብረትም ሆነ በግለሰብነት በመደገፍ በሰላም ያደረግነውንና የምናደርገውን ጥረት እንድታውቁልን እንጠይቃችኃለን። ሥጋችሁ ከሥጋችን፣ ደማችሁ ከደማችን፣ መልካችሁ ከመልካችን፣ መቼም ቢሆን ሊለያይ እንደማይችል እምነታችን ሲሆን በእምነት አስተሳሰብ ብቻ ብንለያይም በመሠረቱ አንድ ሕዝብ፣ አንድ ዜጋ መሆናችንን ሊፍቀው የሚችል የለም። ስለዚህ ይህንኑ ለአንድነታችን ማጠናከሪያ፣ ለውዲቱ አገራችን መገንቢያ ዓይነተኛ መሣሪያ የሆነውና የነበረውን ጥንታዊ ክርስቲያናዊ እምነታችን፣ ጥንታዊና ብሔራዊ ለሆነው ቅርሳችን ጠባቂ፣ የፊደልን ቅርጽና የአጻጻፍን ሥልት፣ የባህልን አቋምና የታሪክን መሠረት ጠብቆ የቆየውን ለመናድ የምታደርጉትን ፕሮፓጋንዳ በመቃወም ሚያዚያ 14 ቀን 1966 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማና በአጠቃላይ ግዛቶች ሁሉ ሰላማዊ ሰልፍ የምናደርግ መሆናችንና እንድትተባበሩን በቅድሚያ እናሳውቃለን።››(የኢት/ የጥናትና ምርምር ተቋም፣ ማኑስክሪፕት ክፍል፣ ማኅደር ቁጥር 2396/01/7) የአዲስ አበባ አብያተ ክርስትያናት ፊርማ አሰባስበው ለጠቅላይ ሚኒስትር እንዳልካቸው አቤቱታ አስገቡ። አዲስ ዘመን ጋዜጣ በሚያዚያ 15 ቀን 1966 እትሙ ‹‹ጠቅላይ ሚኒስትሩ የክርስቲያንን ተወካዮች አቤቱታ ተቀበሉ›› በሚል ርዕስ ሥር እንዲህ ሲል ዘግቧል፡-
Mostrar todo...
👍 63 30
‹‹ክቡር ልጅ እንዳልካቸው መኮንን ጠቅላይ ሚኒስትር ኢትዮጵያዉያን እስላሞች ባለፈው ቅዳሜ ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ ያደረጉትን ሰላማዊ ሰልፍ መነሻ በማድረግ የአዲስ አበባ ከተማ የክርስትያን ተወካዮች ያቀረቡትን አቤቱታ ትናንት ጧት ተቀበሉ። በዚሁም ጊዜ ተወካዮቹ በዚሁ ሰልፍ የታየውን ሁናቴ መሠረት በማድረግ የክርስትያንን ሃይማኖት አቋም የሚመለከቱ ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አቤቱታዎች ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀረቡ ሲሆን፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ስላቀረቡት አስተያየቶችና ጥያቄዎች ከተወካዮቹ ጋር በሰፊው ተነጋግረዋል። ተወካዮቹም ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሰሙት በዚሁ አቤቱታ ኢትዮጵያዉያን እስላሞች ሰላማዊ ሠልፍ ባደረጉበት አንዳንድ ሰሌዳዎች ላይ የሠፈሩት ጽሑፎች የአገሪቷን ታሪካዊ አቋም የሚያቃውሱ፣ በብዙም ድካም ተመሥርቶ የተገነባውን ጽኑ አንድነት የሚያናጉና ዝንባሌያቸውም ወደ ሌላ አቅጣጫ የሚያመሩ መሆናቸውን ገልጠው ይኸው አድራጎታቸው የከተማውን ክርስትያን ቅር ማሰኘቱንና ማሳዘኑን አስገንዝበዋል።›› (አዲስ ዘመን ጋዜጣ በሚያዚያ 15 ቀን 1966 እትም) የሙስሊሙ የመብት ጥያቄ ለአገሪቷ አደገኛና ለኢትዮጵያ አንድነት አሥጊ እንደሆነ ተደርጎ ተወሰደ። የሙስሊሙን ሰልፍ ቤተ- ክህነት እንዳልወደደችውና ነገር ግን ቁጥብነትና ታጋሽነትን መምረጣቸውን ተወካዮቹ አስረዱ። አዲስ ዘመን እንዲህ ሲል ይገልጸዋል፡- ‹‹ይሁን እንጂ የከተማው ሕዝበ ክርስትያን የአገሪቷን ፀጥታ ለመጠበቅና ሰላምን ለማክበር በሰላማዊ ሠልፍ የታየውን መንፈስ በፍቅር፣ በትዕግሥት ያሳለፈው መሆኑን ተወካዮቹ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ከገለጡ በኋላ፣ ሕዝቡ በከተማው በሚገኙት አብያተ ክርስትያናት ተሰብስቦ ፀሎት ምሕላ በማድረስ ሁናቴውን በዚሁ ማሳለፉን አስረድተዋል።› (አዲስ ዘመን ጋዜጣ በሚያዚያ 15 ቀን 1966 እትም) በሳምንቱ የሙስሊሙን ሰልፍ የሚቃወም ሰልፍ ቤተ-ክህነት መጥራቷ ታወቀ። ጠቅላይ ሚኒስትሩም የቤተ-ክህነት አመራሮችን አግባብተው ሐሳብ አስለወጡ። በዚህም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ልጅ እንዳልካቸው መኮንን ክርስቲያኖች ታጋሽና ቁጥብ መሆናቸውን አመስግነው በሳምንቱ የሙስሊሙን ሰልፍ በመቃወም የጠሩትን ሰልፍ ለርሳቸው ጥያቄ ፈቃደኛ በመሆን ስለ ሰረዙ አመሰገኗቸው። አዲስ ዘመን እንዲህ ሲል ዘግቧል፡- ‹‹ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ጊዜ ለተወካዮቹ ባደረጉት ንግግር፣ ኢትዮጵያዉያኑ እስላሞች ያደረጉትን ሰላማዊ ሰልፍ ምክንያት በማድረግ የከተማው ክርስትያን ለማድረግ ያቀደው ተመሳሳይ ሰልፍ እንዲቀር ያስተላለፉትን የአደራ መልእክት ሕዝቡ የተቀበለውና ያከበረው በመሆኑ፣ ያለውንም የጨዋነትና የአስተዋይነት ባህሉን አክብሮ በመገኘቱ ከልብ አመስግናለሁ ብለዋል። ከዚህም በማያያዝ በተናገሩት ቃል የአገሪቷን አንድነት፣ ዕድገትና ብልፅግና በይበልጥ ለማስከበርና ለማረጋገጥ ኢትዮጵያዉያን ሁሉ የሃይማኖት ትብብርና ፍቅር ለወደፊቱ በይበልጥ እየጠነከረ እንዲሄድ ለመረዳት የተለየ ኃላፊነትና ጥረት ማሳየት አለባቸው በማለት አሳስበዋል።›› (አዲስ ዘመን ጋዜጣ በሚያዚያ 15 ቀን 1966 እትም) በአማኞች መካከል መቻቻልና መተባበር እንደሚያስፈልግ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለክርስቲያኑ ተወካዮች አሳስበዋል። በአ/አበባ የሚገኙ አርባ ሁለት አብያተ ክርስቲያናት ለኦርቶዶክሱ ጳጳስ አቡነ ቴዎፍሎስ ደብዳቤ አስገብተዋል። በደብዳቤዎቻቸውም የሙስሊሙን ሰልፍ አውግዘዋል። ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት አለመሆኗን ሙስሊሙ በመፈክሩ ማሰማቱን ኮንነዋል። (Islam and Islamic discourse in Ethiopia p. 782) አብያተ ክርስቲያናቱን ይበልጥ ያበሳጫቸው ከክርስቲያኑ ወገን ሙስሊሙን ደግፈው በሰልፉ የተገኙት ነበሩ። ክርስቶፎር ክላፋም የተባሉት ምሁር “Transformation and Continuity in Revolutionary Ethiopia” በሚለው ጽሑፋቸው ገጽ 107 ላይ ‹‹ሙስሊሙና ክርስቲያኑ ጎን ለጎን ሆነው መፈክር እያሰሙ መሰለፋቸው ለትምክተኛው ክርስቲያን ወገን ከጥቃቶች ሁሉ የላቀው ጥቃት ነበር›› ሲሉ ጽፈዋል። ሰልፉ የሙስሊሙ መብት ተከብሮ ኢስላምም እንደ ክርስትና ቦታ ካገኘ አገሪቷ እንደምትበጣበጥና አንድነቷ እንደሚናጋ ተደርጎ በአፄውና በግብረአበሮቹ የተንፀባረቀው ዕይታ ከንቱና ደካማ አስተሳሰብ መሆኑን አሳይቷል። ጥንካሬ ከአንድነት እንደሚመጣ፣ ኃይል ከእኩልነት እንደሚነሳ የሕዝበ-ሙስሊሙ ሰልፍ አስተምሯል። (ሙሐመድ ዩሱፍ የዕቁብ፣ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የሥቃይና የመከራ ታሪክ፣ 1987፣ ገጽ 21) ይቀጥላል………
Mostrar todo...
👍 187 92
"አትነሳም ወይ አትነሳም ወይ ግፍ አገዛዝ አይበቃህም ወይ?" ክፍል አምስት ★★★★★★★★★★★★★★★★★★★★★ የሕዝቡ ስሜት ያስደነግጣል፤ ብዛቱ ያስገርማል። ‹‹ይህን ያህል ሙስሊም እስከ ዛሬ የት ነበር?›› አስባለ። የሰልፉ ጫፍ አራት ኪሎን አልፎ ቤተ መንግሥቱን ቁልቁል ቢወርድም የኋለኛው ጫፍ ገና ከአንዋር መስጂድ ንቅንቅ አላለም ነበር። ሌላው አካል ቀርቶ አዘጋጆቹ እንኳ በሕዝቡ ብዛት ተገርመዋል። መፈክሩ ቀጠለ፡- ‹‹ሕጉን ውስጣዊ ደንብ አይጫነው! አንድነት የሚገኘው በእኩልነት ነው! እኩልነት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ! የአትዮጵያ ችግር ለመላው ኢትዮጵያዉያን ችግር ነው! ኢትዮጵያ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ! እኩልነት የዕድገት መክፈቻ ቁልፍ ነው! የሃይማኖት ልዩነት የአንድነት እንቅፋት ነው! ፍትሕ በኢትዮጵያ ይስፈን! ተባብረን እንሥራ! የሃይማኖት ልዩነት ይቅር! ሃይማኖት ከመንግሥት አስተዳደር ይገለል! እኩልነት ከሌለ ብልጽግና አይኖርም! የሰላም መሠረት እኩልነት ነው! በአስተዳደር ፍትሕ ይስመር! የእኩልነት መብት መጠየቅ ወንጀል አይደለም! አንድ ነው ደማችን! ኃይላችን አንድ ይሁን! አትነሳም ወይ አትነሳም ወይ! የግፍ አገዛዝ አይበቃህም ወይ?›› (የኢትዮጵያ የጥናትና ምርምር ተቋም፣ ማኑስክሪፕት ክፍል፣ ማኅደር ቁ. 2400/01/4) ከአማርኛ መፈክሮች በተጨማሪ የእንግሊዘኛ መፈክሮችም ቀጠሉ፡- “Equality is the basis of unity! We can not afford to remain second class citizens! We demand for equal participation in administration! Out of 14 Enderases none of them is a Muslim! Out of 20 Ministers only two are Muslims! No Muslim is a General! Our demand is for equality, not superiority! The constitution discriminates against the majority of the population! Ethiopia is not only a “Christian Island!” we too are Ethiopians! Go away with religious discrimination! Ethiopia can not afford to have second class citizens! Declare secular state! Liberty, equality and fraternity! Men are born free and equal in rights!” ( የኢትዮጵያ የጥናትና ምርምር ተቋም፣ ማኑስክሪፕት ክፍል፣ ማኅደር ቁጥር 2396/02/5) የነዚህ መፈክሮች ትርጉም እንደሚከተለው ነው፡- ‹‹እኩልነት የአንድነት መሰረት ነው! ሁለተኛ ደረጃ ዜጋ ሆነን መቀጠል አይቻለንም! በአስተዳደር ውስጥ እኩል ተሳትፎ እንዲኖረን እንጠይቃለን! ከ14ቱ እንደራሴ ውስጥ አንዱም ሙስሊም አይደለም! ከ20ዎቹ ሚኒስትሮች ውስጥ ሙስሊሞች ሁለት ብቻ ናቸው! አንድም ሙስሊም ጄኔራል የለም! ጥያቄያችን እኩልነት እንጂ የበላይነት አይደለም! ሕገ መንግስቱ አብዛኛውን ሕዝብ ያገለለ ነው! ኢትዮጵያ ‹የክርስቲያን ደሴት› ብቻ አይደለችም፤ እኛም ኢትዮጵያዉያን ነን! ከሃይማኖት አድሎ ጋር አብራችሁ ተወገዱ! ኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ዜጋ እንዲኖራት አትታገስም! ዓለማዊ መንግስጥ ይታወጅ! ነፃነት፣ እኩልነትና ወንድማማችነት! የሰው ልጆች የተወለዱት ነፃ ሆነውና እኩል መብት ኖሯቸው ነው!›› የሙስሊሙ ሰልፈኛ ስሜት እየተጋጋለ ነው። መፈክሩ ቀጠለ። መዝሙርም ተስተጋባ፡- 1. መብታችን ይሰጠን የእምነት መብታችን እኩልነታችን ይጠንክር ኃይላችን ከወገኖቻችን! 2. አንድ ይሁን ደማችን ከወንድሞቻችን ተባብረን እንገስግስ ከገዛ ሕዝባችን ልዩነቱም ይጥፋ ከሥር መሠረቱ አጥንት ደማችን አንድ ነው በውነቱ 3. አገር የጋራ ነው ሃይማኖት የግል ነው የሚለው መሪ ቃል ይሠራበት ምነው? 4. ከአንድ አባትና ከአንድ እናት ነው! በምን ነገር ነው የተለያየን አስተካክሉን አስተካክሉን! ከአንድ ባንዲራ አትነጣጥሉን! 5. ክርስቲያኑ ወገናችን ተጠብቆ መብታችን እንድንሠራ ላገራችን ተሰለፉ ከጎናችን! 1. ኢትዮጵያ የሁላችን እኩል ይሁን መብታችን እንድንሠራ ላገራችን ይጠበቅ መብታችን! 2. እኩል ነው ልፋታችን እኩል ነው ግብራችን እኩል ነው መሞቻችን እኩል ይሁን ድጋፋችን! የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ እና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች መፈክር በመያዝ ሚያዚያ 27 አደባባይ ላይ ሰልፉን ተቀላቀሉ። (አዲስ ዘመን ጋዜጣ፣ ሚያዚያ 13፣ 1966 ዓ.ል) ከሙስሊሙ ሰልፍ የተቀላቀሉ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በበኩላቸው ሙስሊሞችም ክርስቲያኖችም በጋራ ሆነው ድምጻቸውን ያሰማሉ። ከያዟቸው መፈክሮች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡- ‹‹ሕዝባዊ መንግሥት ይቋቋም! ለእስላም ሴቶች የሃይማኖት ጭቆና ይቅር! መሬት ላራሹ! የፖለቲካ ፓርቲዎች ይቋቋሙ! ባላባታዊ መንግሥት ይውደቅ! አትነሳም ወይ! አትነሳም ወይ! የግፍ አገዛዝ! አይበቃህም ወይ! ምርጫ ለሕዝብ! እንዳልካቸው ይውረድ! እኛ ክርስቲያኖች በሃይማኖት እየከፋፈሉ መግዛትን እናወግዛለን! የሃይማኖት መብታችን ይጠበቅና በኢትዮጵያዊነታችን እንኩራ!›› የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎች የራሳቸው መፈክሮችን ይዘው ሰልፉን ተቀላቅለዋል። እነርሱም መፈክራቸውን ጮክ ባለ ድምጽ ያስተጋባሉ፡- ‹‹የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ጥያቄዎች ይሟሉ! የሕዝብ ጥያቄዎች በአስቸኳይ ይፈጸሙ! የመሬት ይዞታ በፍጥነት ይሻሻል! የዘርና የሃይማኖት አድልኦ ይውደም! ኢትዮጵያ የእስላምና የክርስቲያን አገር ናት! አይገባም ማድረግ እንደጋሻ ሃይማኖት! በእውነት ተነስተን አገርን ለማልማት! አንድነት ኃይል ነው! ተነስ! ነጻነት! እኩልነት! ወንድማማችነት! ‹አስተዳደርና ሃይማኖት ይለያዩ› የሚለው ጥያቄ የእኛም የክርስቲያኖች ነው! ሃይማኖት የፖለቲካ መሣሪያ አይደለም! ሃይማኖቶች ሁሉ በዴሞክራታዊ መንገድ ይከበሩ! ሠራተኛ ባሪያ አይደለም! መሬት ላራሹ! የመናገርና የጽሑፍ ነጻነት ለሕዝብ ይሰጥ! ሃይማኖት የፖለቲካ መሣሪያ መሆን የለበትም!›› ከአማርኛው በተጨማሪ የሁለተኛ ደረጃ እና የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ተማሪዎች በጋራ ሆነው የእንግሊዝኛ መፈክሮችን ያስተጋባሉ። ካሰሙት መፈክሮቻቸው መካከል፡- “Secularize the state! Ethiopia is not only to the Christians! We Christians support this democratic demand of our Muslim brothers! No state interferes in religion! Unity is the basis of equality! Separate the church and the state!” በእንግሊዘኛ የተሰሙት የነዚህ መፈክሮች ትርጉም እንደሚከተለው ነው፡- ‹‹መንግስቱ (ሥርዓቱ) ዓለማዊ ይደረግ! ኢትዮጵያ የክርስቲያኖች ብቻ አይደለችም! የሙስሊም ወንድሞቻችንን ዲሞክራሲያዊ ጥያቄዎችን እኛ ክርስቲያኖችም እንደግፋለን! በሃይማኖት የመንግስት ጣልቃ ገብነት አይኑር! አንድነት የእኩልነት መሰረት ነው! መንግስትና ቤተ-ክርስቲያን (ሃይማኖትና መንግስት) ይነጠሉ!›› ‹‹በሌሎች ገበታ የሚተማመን ሁሌም ዘግይቶ ይመገባል።›› (ጣልያኖች) ይቀጥላል....
Mostrar todo...
141👍 80
“ሌሊት መስገድን አስቦ ወደ ፍራሹ የሄደ ከዚያም እስከ ንጋት ዓይኑ ያሸነፈችው ያሰበውን አላህ ይፅፍለታል፤ እንቅልፉም ከጌታው ዘንድ ሶደቃ ይሆንለታል” ረሱል ﷺ (ነሳኢ 1787ና ኢብኑ ማጀህ 1344)
Mostrar todo...
👍 226 123