cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Everest Youth Academy(EYA)

We strive for success

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
6 136
Suscriptores
+824 horas
+297 días
+13430 días
Archivo de publicaciones
Photo unavailableShow in Telegram
Photo unavailableShow in Telegram
Photo unavailableShow in Telegram
ለፈተና የቀረው ጊዜ #67_ቀናቶች #motivation #entrance_2016 በርቱ ጠንካራ መሆን አለባችሁ። ያደክማል ግን ትንሽ ጊዜ ነው ። ሂደቱ ላይ አተኩሩ ውጤቱ የሂደቱ ባሪያ ነው። 500+ ይቻላል ።
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
#MoE የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ 25 የክልል ከተሞች ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው። በወረቀት ከሚሰጠው ፈተና በተጨማሪ የሚሰጠው የኦንላይን ፈተና ተማሪዎች ከቦታ ቦታ ሳይጓጓዙ በየአካባቢያቸው ቤተሰቦቻቸው ጋር እያደሩ ፈተናውን እንዲወስዱ እንደሚያስችላቸው የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ ተናግረዋል። የፈተና አሰጣጡን ስኬታማ ለማድረግ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት በመስራት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ሚኒስትር ድኤታዋ ጠቁመዋል። የኦንላይን ተፈታኞች ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት ደጋግመው እንዲለማመዱ የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ተገልጿል። ትምህርት ሚኒስቴር
Mostrar todo...
ልጆች 13 ዓመት እስኪሞላቸው ድረስ ስማርት ስልኮችን ባይጠቀሙ ሲል በፈረንሳይ የተሰራ ጥናት አመለከተ። በተለያየ የእድሜ ደረጃ ላይ ያሉ ህፃናት እና ታዳጊዎች ስማርት ስልኮችን በመጠቀም የተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾችን ሲጠቀሙ አለፍ ሊልም በነዚህ የትስስር ገጾች ላይ ተሳትፎ ሲያደርጉ ይስተዋላል። የስማርት ስልክ አጠቃቀም ጥንቃቄ የሚያስፈልገው እንደሆነ ቢነገርም ሀገራችን ኢትዮጵያ ጨምሮ ስማርት ስልኮች ላይ የሚገኙት የማህበራዊ ትስስር ገጾች ህፃናትና ታዳጊዎችን ለሱስ ከመዳረግ ባለፈ በልጆች ላይ ስነልቦናዊ ጉዳት እያስከተለ ስለመሆኑ ይነገራል። ጉዳዩን አስመልክቶ በፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ማክሮን ሀሳብ አመንጪነት ታዳጊ ልጆችን ከአደጋ ለመጠበቅ ኒውሮሎጂስት እና የዘርፉ ባለሙያዎች የስልክ ስክሪን አጠቃቀም መመሪያዎችን ለመንግስት እንዲጠቁሙ  በማሰብ 3 ወራትን የፈጀ ጥናት ተሰርቷል። በጥናቱም ልጆች 13 አመት እስኪሞላቸው ድረስ ስማርት ስልኮችን እንዲጠቀሙ መፈቀድ እንደሌለበትና እንደ #ቲክቶክ፣ #ኢንስታግራም እና #ስናፕቻት የመሳሰሉ ማህበራዊ ሚዲያዎችን እስከ 18 አመት ድረስ መጠቀም እንደሌለባቸው ጥናቱ አመልክቷል። ጥናቱም ከ3 አመት በታች ያሉ ህጻናት የቴሌቪዥን ስክሪኖች ጨምሮ ለስልኮች ተጋላጭ መሆን እንደሌለባቸው የጠቆመ ሲሆን አንድ ህፃን 11 ዓመት ሳይሞላው ስልክ ሊኖረው እንደማይገባና ይህ ካልሆነ ህፃናት በልጅነታቸው ስሜታቸውን ከመግለፅ እና ነገሮችን ከመረዳት አኳያ ሊያዳብሯቸው የሚገባቸውን ችሎታዎች ሊጎዳ እንደሚችል ተገልጿል። የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ማክሮን ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በጥር ወር ህፃናትን ላይ ጉዳት እየዳረገ ስለሚገኘው የስማርት ስልክ እንዲሁም የስክሪን አጠቃቀም " እገዳዎች ወይም ገደቦች " ሊኖሩ ይችላሉ ማለታቸውም ነው የተነገረው። ይህ ጥናት በኢትዮጵያ ካለው የህፃናትና ታዳጊዎች ስማርት ስልክ አጠቀም አንፃር እንዴት ይታያል? @TikvahethMagazine
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
⭐️መጨነቁን አቁምና ጥናቱን ጀምር! 🌟ፈተና ደረሰ ብለህ መጨነቁን አቁምና የምትችለውን ሁሉ አድርግ! ፈጣሪም የሚረዳህ የምትችለውን ስታደርግ ነው! ጊዜ ደግሞ አለህ! ✅ከዚህ በፊት አጥንተህ ጥሩ ውጤት ያመጣህባቸውን ወቅቶች አስብ እስኪ.... እርግጠኛ ነኝ አሁንም በቆራጥነት ያኔ የለፋኸውን ልፋት ከደገምከው ማትሪክን ከ 500 በላይ ሚኒስትሪን ከ50 በላይ ታመጣለህ። ዛሬውኑ ጥናታችሁን ከጀመራችሁ ያላችሁ ግዜ በቂ ነው :: ✅✅ ዳይ ወደ 👉ጥናት ✅  መልካም ጥናት 📚📖📖📚
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
ያስቸገረኝ ጥቃቅኑ አሸዋ ነበር! ተወልዶ ካደገበት ሃገሩ በተፈጠሩ ማሕበራዊ ቀውሶች ምክንያት ወደሌላ ሃገር በስደት ለመሄድ የቆረጠ አንድ ሰው ረጅም፣ አድካሚና አስፈሪ የሆነን በረሃ ለቀናት በእግሩ በመሄድ ካቋረጠ በኋላ እጅግ ደክሞና ዝሎ ነበር፡፡ በመጨረሻም በደረሰበት አንዲት ከተማ ውስጥ በተሰጠው እርዳታ ትንሽ አገገመ፡፡ የዚህን ሰው ጉዞ የሰማና ለሕብረተሰቡ ለማቅረብ የፈለገ አንድ ጋዜጠኛ አገኘውና አንድን ጥያቄ ጠየቀው፡፡ “ተጉዘህ የመጣኸው በረሃ ብዙ ሰው የማይደፍረው በረሃ ነው፡፡ ለመሆኑ በመንገድህ ላይ በጣም የጎዳህና ያስቸገረህ ውኃ ጥም ነበር? ምግብ ማጣት ነበር? አውሬ ነበር? ሽፍቶች ነበሩ? ወይስ . . . ? የዚህ ስደተኛ መልስ ለጋዜጤኛው ያልተጠበቀ ነበር፡፡ በዚህ አደገኛ በረሃ አቋርጬ ስመጣ በጣም ያስቸገሩኝ የጠቀስካቸው ትልልቅ ነገሮች አልነበሩም፡፡ ጉዞየን በጣም አድካሚና አስቸጋሪ ያደረገብኝ በእርምጃዬ ወቅት ጫማዬ ውስጥ እየገባ የሚቆረቁረኝና አላራምድ ያለኝ ጥቃቅኑ አሸዋ ነበር፡፡ የሕይወት ጉዞም እንዲሁ ነው! አብዛኛውን ጊዜ የሚያስቸግረን፣ የሚቆረቁረን፣ አላራምድ የሚለንና ከዓላማችን የሚጎትተን ችግር ትልልቁ አይደለም፡፡ በየቀኑ የሚያጋጥሙን ጥቃቅን “አሸዋዎች” ናቸው፡፡ ትንንሽ አመለካከት ያላቸው ሰዎች ባህሪይ፣ ትንንሽና አናሳ ወሬን የሚያወሩ ሰዎች ሁኔታ፣ ትንንሽና ስሜትን የሚነካኩ የየቀን ገጠመኞች . . . ጉዟችንን አዳጋችና አድካሚ ያደርጉታል፡፡ “በትንንሽ” ሰዎችና ሁኔታዎች ሳትበገሩ ትልቁ የሕይወት ስእልና ዓላማችሁ ላይ በማተኮር ወደፊት መገስገስን ያወቃችሁበት ጊዜ ዋናውን የሕይወት ድል የተጎናጸፋችሁበት ጊዜ ነው፡፡ በርቱ! https://t.me/Dreyob
Mostrar todo...
ጎበዝ  ተማሪዎች የአጠናን ልምዳቸው ምን ይመስላል❓ 🎚️ 12 ወሳኝ ነጥቦች 1️⃣ጥናት ከመጀመራቸው በፊት ለምን ዓላማ እንደሚያጠኑ ቀድመው ዓላማ ያስቀምጣሉ። ይህ ማለት ምን ለማወቅ እንደሚያጠኑ ቀድመው ያቅዳሉ። 2️⃣መፅኃፍ ገልጠው ጥናት ከመጀመራቸው በፊት ስለሚያጠኑት ርዕሰ ጉዳይ የራሳቸውን ግምት ያስቀምጣሉ። መፅሀፍ ገልጠው ጥናት ከጀመሩ በኃላ የነበራቸውን ግምት እያጠናከሩ...የተሳሳተው ን እያስተካከሉ ይጓዛሉ። 3️⃣ ሲያጠኑ ያገኙትን አንኳር ነጥብ አጠር አድርገው ማስታወሻቸው ላይ ያሰፍራሉ። 4️⃣አንብበው ለ መረዳት ያስቸገራቸውን ነጥብ /ሀሳብ/ ደጋግመው ያነባሉ.... 5️⃣ጥናት ከ መጀመራቸው በፊት ማጥናት ስለ ፈለጉት ርእሰ ጉዳይ ጥያቄዎች ይፋጥራሉ። መፅኃፍ ገልጠው ጥናት ከጀመሩ በሃላ ለጥያቄዎቻቸው መልስ ይፈልጋሉ እንጂ ሁሉም ነገር በ ማንበብ ጊዜያቼውን አያጠፉም። 6️⃣ሲያነቡ ያገኙትን አዲስ ሀሳብ ወይም መረጃ ከ አሁን በፊት ከሚያወቁት ጋር አብሮ ሊሄድ የሚችል መሆኑን እና አለመሆኑን ይመረምራሉ:: 7️⃣ በአንድ ጊዜ ብዙ ነገር ለ ማጥናት አይሞክሩም፡፡ በ አንድ ጊዜ ብዙ ነገር ለ ማጥናት መሞከር ትርፉ ድካም መሆኑን ተረድተውታል፡፡ 8️⃣ ሁልጊዜም ቢሆን ለትምህርት ጉዳዮች የሚጠቀሙበት የተለየ ጊዜ አላቸው፡፡ 9️⃣ ያሰቡትን ነገር ተግባራዊ ለማድረግ ቁርጠኝነት አላቸው...አያፈገፍጉም፣ አያቅማሙም፡፡ 1️⃣🔠 ሲያጠኑ የሚከብዳቸውን ክፍል ቅድሚያ ሰጥተው ያነባሉ፡፡ 1️⃣1️⃣ ተባብሮ በመስራት ያምናሉ፡፡ ያግዛሉ፣ ይጠይቃሉ፡፡ 1️⃣2️⃣ እራሳቸው ይገመግማሉ፡፡ ደካማ ጎናቸዉ በፍጥነት ያስተካክላሉ።
Mostrar todo...
There are no secrets to success, "It is the result of preparation, hard work, and learning from failure". #hardwork #paysoff #students
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
Photo unavailableShow in Telegram
#Update የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ። የ2016 የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆኗል። የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ፤ ከሐምሌ  9 እስከ ሐምሌ 11/2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል። በወረቀት ላይ የሚፈተኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 01/2016 ዓ/ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ከሐምሌ 6 እስከ 7/2016 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ይሆናል።  መረጃው የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ነው። @tikvahethiopia
Mostrar todo...
10 Lessons from the book "Failing Forward" by John C. Maxwell: 1. The difference between average people and achieving people is their perception of and response to failure. 2. The successful person has a habit of doing the things failures don't like to do. They don't like doing them either necessarily. But their disliking is subordinated to the strength of their purpose. 3. Mistakes are painful when they happen, but years later, a collection of mistakes is what is called experience. 4. Success is not a destination, it's a process. It's not something you acquire, it's something you become. 5. If you're not failing, you're not growing. 6. Change is inevitable. Growth is optional. 7. The only real mistake is the one from which we learn nothing. 8. The more you know yourself, the more clarity you have about where you want to go. 9. You don't have to be great to start, but you have to start to be great. 10. Fear k!s dreams. Fear k!s hope. Fear puts people in the hospital. Fear can age you prematurely. Fear is the enemy of success.
Mostrar todo...
The Power of Now.pdf A Guide to spritual enlightenment "one of the best book to come along in years, every sentence rings with truth and power." over 2 million copies sold
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
🪐የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ 🌟የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦን ላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተገልጿል። 🟢የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ምክክር መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል ። 🌟የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ለመስጠት ባይቻልም በሁሉም ክልሎች በተመረጡ ከተሞች ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። 🟠በዚህም በሁሉም ክልሎች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን የሚወስዱ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ በተለመደው አግባብ ፈተናቸውን ይወስዳሉም ብለዋል። ⭐️የሀገር አቀፍ ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር (ዶ/ር) እሸቱ ከበደ በበኩላቸው ፈተናውን በኦንላይን ለመሥጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል። 🌟ተማሪዎች የሙከራ ፈተና የሚለቀቅላቸው ሲሆን ደጋግመው እንዲሞክሩና እንዲለማመዱ ይደረጋልም ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል። 🌟ለዚህም እንዲረዳ የአሰልጣኞች ስልጠና በመሥጠት ተማሪዎች ተደጋጋሚ ስልጠና እንደሚሠጣቸውም ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል። ⭐️ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት እንደሚጀምርም በመድረኩ ተገልጿል።
Mostrar todo...
📘CHEMISTRY GRADE 10 UNIT 2 OLD BOOK 🧑‍🏫 PART 1 AND PART 2
Mostrar todo...
📘CHEMISTRY GRADE 10 UNIT 2 OLD BOOK 🧑‍🏫 PART 1 AND PART 2
Mostrar todo...