cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

KiraAbigaro(Kisaraye Ere lash)

ኪራ አቢጋሮ ነኝ።ይሄ የኔ የግል ቻናል ሲሆን ቻናሉን በመቀላቀል ቤተሰብ እንሁን።Hello I m Kira Abigaro:-A Poet, producer&singer.let u join ma channel

Mostrar más
El país no está especificadoEl idioma no está especificadoLa categoría no está especificada
Publicaciones publicitarias
140
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

Mostrar todo...
ኪራ አቢጋሮ (@QPJfFz4TuWzpgFF) | Twitter

The latest Tweets from ኪራ አቢጋሮ (@QPJfFz4TuWzpgFF). I am a singer,poet and producer.Have my twit

Mostrar todo...
Log in to Facebook

Log in to Facebook to start sharing and connecting with your friends, family and people you know.

ኦርቶዶክስ ሆኜ ሙስሊሙን በማክበሬ; ኦሮሞ ሆኜም አማራን በመውደዴ ያጣሁት አንድም ነገር የለም! ካላመንከኝ ሞክረው!! ሰው ሆይ በመጨረሻም ትሞታለህ #ኪራአቢጋሮ
Mostrar todo...
#ይቅርታ አንዳንድ ሰው አለ:- በዝምታው መሀል እውነትን ያፈነ እራሱን አዋርዶ ሌሎች ያጀገነ አንዳንድ ሰው አለ በርባን ያደረግነው ቅዱስ ሆኖ ሳለ። አለ አንዳንድ ሰው:- ልጆቹን ሲጠብቅ ከ'ንቅልፍ የተጣላ ራሱን የሚያስርብ ሌሎች እያበላ! ደሞ በየህ ግድም:- አሉ እኔን መሳዮች ከምንም የሚያንሱ ጥድፊያ የጣላቸው ቀንድ እየነከሱ ለማየት ያልበቁ ለጽድቅ ያልደረሱ! እናም አባቴ ሆይ:- የገባኝ ሲመስለኝ ያልገባኝን እውነት እርሶን በማብቃቴ ላደባባይ ስቅለት ንስሃየን ሰምተው የበደሌን ዋይታ ምሬሃለው በሉኝ ይፍቱኝ በሉ የኔታ!! #ኪራአቢጋሮ እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ከክፉ አይኖች ይሰውራት ማስታወሻ:- #ይድረስ_ለጳጳሱ በሚለው ግጥሜ ላስከፋኋችሁ ወንድሞች ይቅርታ እጠይቃለሁ ፔጄን like ጽሁፌንም share በማድረግ ይቅርታዬንም ያጋሩ ዘንድ በትህትና እጠይቃለሁ
Mostrar todo...
በመጨረሻም በyoutube መጥቻለሁ። subscribe ያድርጉ https://www.youtube.com/channel/UC6MP10ybN2sP58cZlrUexSw
Mostrar todo...
#ተረት_ተረት የሰው ስጋ በልቶ መልኩ የጠቆረ በቤንሻንጉል ምድር አንድ ሰው ነበረ #እሺ____ ቀይ ስጋ በልቶ መልኩ በመጥቆሩ የመንደሩም ሰዎች ብዙ ስላወሩ ተጨንቆ ተጠቦ ድንገት ዞር ብሎ ቢያይ ያማራውን ስጋ ተከምሮ አገኘው ጓደኛው ቦርጭ ላይ!! ተረቴን መልሱ ደሞ ቀስት አታንሱ!!______- #ኪራአቢጋሮ እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ከክፉ አይኖች ይሰውራት
Mostrar todo...
#ደግነት_ብሔር_የለውም አንድ አርቲስት በራሱም ተነሳስቶ ይሁን ሰው አነሳስቶት ለበጎ ነገር ሲበረታ ማየት መልካም ነው።በጎነት ደግሞ ብሄር የለውም።ለተጎዱ መድረስ;የተራቡትን ማብላት;የታረዙትን ማልበስ የስብእናው ጥግ ነው። ይሄንን ደግሞ ከአበበች ጎበና እስከ ቢኒያም ያልነጠፈ ሰውነትን አይተናል።ዘመን ከፍቶ ወንድማማቾች ደም ሲቃቡም ሴቶችና ህጻናት አይራቡ አይታረዙ ሲል ያሬድ ሹመቴም ቀለብ መለመን ከጀመረ ሰነባበተ። ሰው ነውና ሰው የሆነ ሁሉ ይታገዝ ሲል ለተጎጂዎች ደግነቱን ለገሰ። እኔም ጥሪውን በመጋራት በአቅሜ የጉልበትና የልገሳ ስርአቱን በውሃ ጠብታ መጠን ተቀላቀልኩ።#ሰው_ያሬድ_ሹመቴም የሚዲያና የፖለቲካ አጨብጫቢዎች ሳያውቁት በየዋሆቹ ምርቃት ሀሴት አደረገ። ዛሬ ግን አንድ ነገር አየሁና በአርቲስቶቻችን አዘንኩ።".....የማር እጅ" የሚል ለ 1 ብሄር ድጋፍ ማድረግን የሚጠራ የደግነት መፎክር አየሁ።ኢትዮጵያውያንን በማገዝ ስነ ስርአት ያልተሳተፉ ከያኒያን; አማራው ሲታረድ;በቀስት ሲገደል;እርጉዝ ሚስቱን በአደባባይ ሲደፍሩ;በወለጋ;በድባጤ;በማይካድራ;በመተከል... ቤት ንብረታቸው ጋይቶ አንድ ቃል ካፋቸው ያልወጣ "አርቲስት" ተብዬዎች አገልግል ይዘው 1 ብሄር ሊያቋቁሙ መሆኑን ነገሩን። አኔም አልኩ "የቄሳርን ለቄሳር የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር" ነውና የበላችሁትን ትፋት ለቄሳር ገብሩ። የእግዚአብሔር የሆነውን ደግሞ ለሰዎች ሁሉ ህዝብ ይሰጣል!! #ኪራአቢጋሮ እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ከክፉ አይኖች ይሰውራት
Mostrar todo...
#መጻፍ_ድንበር_ሄዶ_ከመዋጋት_በብዙ_ይለያል!! ማንን እየወቀስን እንደሆነ አልገባኝም!! የማን ሞት ደስ ብሎን ጮቤ እንደምንረግጥም አልተረዳሁም!ነገ የመሪዎች ሁለት ቀኝ እጆቻቸው ሲጨባበጥ ሁሉም ነገር ለሚረሳው ዛሬ "ጦርነት" ብለን ጎራ ይዘናል። የጠገቡትን ለማስራብ የተራበውን እንገላለን።ህጻናትና ሴቶች ያለጥፋታቸው ድንበር አቋርጠው ይሰደዳሉ።ይራባሉ;ይጠማሉ;ይታረዛሉ;ይደፈሩማል!! አንተም "ያላዋቂ ሳሚ" ይሉት እውቀት መስሎህ"በለው" በሚል ድንዛዜ ጦርነቱን በጽሁፍህ ትመራለህ። ፍጻሜው ምን እንደሆነ የማታውቀውን የዜጎች እልቂት በወታደሮች ፎቶ አጀብህ ታጋግላለህ። እሳቱ አልነካህምና ወላፈኑ አያገኘኝም ብለህ ዘንግተሃል። ነገ የምትረግጣት ምድር ዶግ አመድ ስትሆን; አማራው ምርቱ ነጥፎ የምትበላው ስታጣ;ትግራዋይ ፈራርሳ ጽዮን ማርያምን መሳለም ታሪክ ሆኖ ሲናፍቅህ; ጎንደርን እንደጓጓህ ሳታያት ስትኖር; መቀሌን ከነምኞትህ እስከወዲያኛው ስትሰናበታት ያኔ ዋይታህ ፋይዳ የለውም። አካልጉዳተኛ የሞላት ሀገር ስትኖርህ;ተስፋ የቆረጡ እናቶች ሲከቡህ; ለማኝ የሞላት ከተማ ስትውጥህ; የሚበላ ያጡ ህጻናት ፍርስራሽ ከተማ መሀል ሆነው ሲያነቡ ስታይ ትእቢትህን ብትረግመው አይረባህም!! ጌታ ሆይ ህዝብህ ማስተዋልን ተነጥቋል።ባለስልጣናት ደም ግብራቸው ከሆነም ሰንብቷልና መልካሙን እንሻ ዘንድ አቤቱ በቁጣህ ጎብኘን!! "ሰላም ለትግራይ;ሰላም ለአማራ;ሰላም ለኢትዮጵያ!!" #ኪራአቢጋሮ እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ከክፉ አይኖች ይሰውራት!!
Mostrar todo...