የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
Ir al canal en Telegram
5 357
Suscriptores
Sin datos24 horas
-97 días
+730 días
Archivo de publicaciones
+4
የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ እና የዕውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡
(ጥር 4 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ እና የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር "7ቱ የብክነት አይነቶች "በሚል ርዕስ የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡
አቶ ሰለሞን ጥበቡ የባለስልጣኑ የእውቅና ፍቃድና እድሳት ባለሙያ "7ቱ የብክነት አይነቶች" በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን ብክነት ማለት ለምንሰራው ወይም ለምናመርተው ምርት ምንም ዓይነት እሴት የማይጨምሩ ወጪን ግን የሚጨምሩ አሠራሮች መሆኑን ገልጸው ለብክነት የሚያጋልጡንን አስራሮች ማስተካከል አስፈላጊ መሆኑን አክለው ገልጸዋል፡፡
አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ብክነትን ካላስወገድን ወደ ስኬት አንደርስም ስለዚህ እሴት የማይጨምሩ ስራዎችን በማስወገድ እንዲሁም እሴት ያላቸውን ስራዎች ከፍ በማድረግ ብክነትን ማሻሻል ጤናማ ውድድር በመፍጠር ስራዎቻችንን ማሻሻል አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
+6
ባለስልጣኑ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በጋራ በመሆን የአጠቃላይ ትምህርት ኢንስፔክሽን የኢንስፔክሽን መረጃ መሰብሰቢያ kobo Tool በተሰኘው ሶፍትዌር ዙሪያ ስልጠና ሰጠ፡፡
(ጥር 4 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የትምህርት ጥራት ማረጋገጥና ምርምር ዳይሬክቶሬት ከትምህርት ሚኒስተር ጋር በጋራ በመሆን የአጠቃላይ ትምህርት ኢንስፔክሽን የኢንስፔክሽን መረጃ መሰብሰቢያ kobo Tool በተሰኘው ሶፍትዌር ዙሪያ የማዕከልና የ9ኙም ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የተመረጡ የኢንስፔክሽን ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ፡፡
አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ በመክፈቻ ንግግራቸው ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የአገልግሎት ፈላጊውን ማርካት ቴክኖሎጂን መጠቀምና ተግባራዊ ማድረግ እንደተቋም አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው ስልጠናውን በአግባቡ በመውሰድ ለተቋማችን የሚታይ አመርቂ ውጤት ማምጣትና ከዘመኑ ጋር መራመድ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል ፡፡
አቶ ዳዊት ዘገየ የትምህርት ሚኒስቴር የኢንስፔክሽን ባለሙያ ሲሆኑ የአጠቃላይ ትምህርት ኢንስፔክሽን የኢንስፔክሽን መረጃ መሰብሰቢያ kobo Tool በተሰኘው ሶፍትዌር ላይ ስልጠና የሰጡ ሲሆን የኢንስፔክሽን ቼክሊስት መሰረት አድርጎ ስራውን ለማቅለል መረጃ መሰብሰብ የሚያስችል እንዲሁም ሌሎች በርካታ አገልግሎቶች ያሉት መሆኑን አክለው ገልጸዋል፡፡
አቶ በላይ አወቀ የትምህርት ሚኒስቴር የኢንስፔክሽን ዴስክ ሀላፊ ሲሆኑ ስራዎቻችንን ለማቅለል ቴክኖሎጂን መጠቀም ያስፈልጋል በመሆኑም ስልጠናው በአግባቡ በመሰልጠን የቴክኖሎጅውን በጎ አበርክቶ መውሰድ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
+8
ቋሚ ኮሚቴው የባለስልጣኑ የስድስት ወራት ስራ እቅድ ክንውን ላይ ግምገማ አካሄደ፡፡
(ታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ሴቶችና ህጻናት ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባላት በምዘና ጣቢያ የመስክ ምልከታ እንዲሁም የ2018 የመጀመሪያ የስድሰት ወር የስራ አፈጻጸም ላይ ግምገማ አካሂደዋል ፡፡
የባለስልጣኑ አማካሪ አቶ ሰለሞን አለማየሁ የባለስልጣኑን የ2018 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የስድስት ወራት አፈጻጸም ሪፖርት ለቋሚ ኮሚቴ አባላት በዝርዝር አቅርበው ውይይት ተካሂጿል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ሴቶችና ህጻናት ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክብርት ሶፊያ አለሙ ከተማችንን የመጠነ ብቁ ዜጋንና ተቋማትን ከማፈራት አንጻር ባለስልጣኑ ውጤታማ ስራዎች እያከናወነ መሆኑን ገልጸው አሰራሮችን በመፈተሽ ብልሹ አሰራሮችን ይበልጥ በመታገል ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ይገባል ብለዋል፡፡
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ አገልግሎት አሰጣጦችን በማዘመን በቴክኖሎጂ የታገዘ ከማድረግ እና ሌብነትና ብልሹ አሰራሮችን ከመቅረፍ አኳያ ብቁ ተቋማትን እና መዛኞችን ከማፈራት አንጻር ባለስልጣኑ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸው ቋሚ ኮሚቴው በየጊዜው ለሚያደርጋቸው ድጋፍና ክትትል ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በቋሚ ኮሚቴ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች የባለስልጣኑ አመራሮች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
+7
ባለስልጣኑ የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር አካሄደ፡፡
(ታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የገና በዓልን ምክንያት በማድርግ ለባለስልጣኑ ሰራተኞች የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር ያካሄደ ሲሆን፤ በመርሃ-ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የሴቶችና ህጻናት ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የሴቶችና ህጻናት ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሰቢ ክብርት ሶፊያ አለሙ በማዕድ ማጋራቱ መርሃ-ግብር ላይ ተገኝተው በዓሉ የሰላምና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡
አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት በዓልን ስናከብር በመደጋገፍና በመረዳዳት መሆን እንዳለበት ይህም ደግሞ የኢትዮጵያውያን የጋራ እሴት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
+5
የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ‒ግብር ተካሄደ፡፡
(ታህሳስ 27 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ‒ግብር "የማህበራዊ ሚዲያ ሱስ" በሚል ርዕስ የአሰራር ጥራት ባለሙያ አቶ ግዛት መኮንን አስረድተዋል፡፡
አቶ ግዛት መኮንን እንደገለጹት የማህበራዊ ሚዲያ ሱስ ምልክቶችና ስታትስቲክስ በዓለም ላይ የተጠቃሚዎችን ቁጥር እንዲሁም ማህበራዊ ሚዲያ ያለውን ጠቀሜታ እና ጉዳት በሰፊው ያብራሩ ሲሆን የማህበረዊ ሚዲያ ሱስ ማህበራዊ መስተጋብርን በመቀነስ ለብቸኝነት፣ድብርት፣ ለእንቅልፍ ማጣት እና ትኩረት መቀነስ በማስከተል ስነ-ልቦናዊ እና አካላዊ የጤና ጉዳቶችን ያስከትላል ብለዋል፡፡
አቶ አለልኝ ወንዴ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ እንደገለጹት ማህበራዊ ሚዲያ ጠቀሜታ እንዳለው ሁሉ በልክ እና በአግባቡ ካልተጠቀምን ጉዳቱ ከፍተኛ ነው ስለዚህ ገደቦችን በማውጣት ጊዜን በጥበብ በመጠቀም በአግባብ እና ሚዛናዊ አጠቃቀም ልናዳብር ይገባል ብለው መልካም የስራ ሳምንት ተመኝተዋል፡፡
ስራተኛው ስራውን በእውቀት በክህሎት እንዲሁም በስነ-ምግባር ያከናውን ዘንድ ወቅቱን የጠበቀ ስልጠና እና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች አስፈላጊ መሆናቸው ተገለጸ፡፡
(ታህሳስ 25 ቀን 2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ለ9ኙም ቅ/ጽ/ቤት እንዲሁም ለዋናው መስሪያ ቤት ሰራተኞች በተለያዩ ርዕሶች ላይ ስልጠና ሰጠ፡፡
አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ እንደገለጹት በስራ ላይ መስራት እየተገባን ምን አልሰራንም? ክፍተቶቻችን ምንድን ናቸው? ብለን ራሳችንን በመፈተሽ እና ስልጠናው ያለውን ሚና በመረዳት እንዲሁም ተግባራዊነት ላይ ትኩረት በማድረግና ተቋማዊ ለውጥ ማምጣት አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በዛሬው ዕለት የተሰጠው ስልጠና ባለስልጣኑ በሰራው ሪፎርም መሰረት በየስራ ዘርፉ የስራ መደብ ላገኙ ሰራተኞች መሆኑ ታውቋል፡፡
+3
ቅ/ጽ/ቤቱ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት እቅድ አፈፃጸም ሪፖርት ለቅ/ፅ/ቤቱ ስራተኞችና አመራሮች አቀረበ፡፡
(ታህሳስ 24 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የኮልፌ ቀራንዮ ቅ/ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት እቅድ አፈፃጸም ሪፖርት ለቅ/ፅ/ቤቱ ስራተኞችና አመራሮች አቀረበ፡፡
አቶ ሀፍቱ ገ/ሚካኤል የቅ/ጽ/ቤቱ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 6 ወራት አቅድ አፈፃጸም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በስድስት ወራት የተሰሩትን የተቋም ግንባታና አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማነት ማሳደግ፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍታት፣ የአቤቱታ መወሰንና ማስፈጸም አቅም ማጎልበት እና ተቋማዊ የቅንጅት የትብብርና ድጋፍ አስራር ስርዓት ማጎልበት የተሰሩ ስራዎች፣የእቅድ/ሪፖርት ዝግጅት የኢኒሼቲቭ ስራዎች አሰራር ስርዓት ማጎልበት፣የቅድመ ዝግጅት ስራዎች አፈጻጸም፣ ዋና ዋና ተግባራት፣አበይት ሰራዎች አፈጻጸም እንዲሁም የነበሩ ደካማ እና ጠንካራ ጎኖች ያጋጠሙ ችግሮችና የተፈቱበተት አግባብ በዝርዝር አቅርበዋል፡፡
አቶ አንዋር አብዲ የኮልፌ ቀራንዮ ቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በ2018 በጀት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የተሻለ አፈጻጸም እንደነበረው ገልጸው ተቋሙ ሪፎርም ላይ እንደመሆኑ ቀሪ ስራዎች በቀጣይ መጠናቀቅ እንዳለባቸው ገልጸው የቅ/ጽ/ቤቱን ጠንካራ ጎን በተነሳሽነት በማጠናከር የታዩ ክፍተቶችን ተጠያቂነትን በማስፈን ጥራቱንና ስታንዳርዱን በጠበቀ መልኩ ተግባራትን በማከናወን መልካም አስተዳደርን በማሰፈንና ተገልጋዮችን በማርካት የተሻለ ውጤትን ማስመዝገብ ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡
+3
የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ጠቅላላ ካውንስል አባላት የባለስልጣኑን የ2018 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ገመገሙ፡፡
(ታህሳስ 24 ቀን 2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ጠቅላላ ካውንስል አባላት በባለስልጣኑ የ2018 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ላይ የጋራ ውይይት አድርገዋል፡፡
የባለስልጣኑ አማካሪ አቶ ሰለሞን አለማየሁ የእቅድ አፈጻፀም፣ አገልግሎት አሰጣጥ፣የሌብነትና ብልሹ አሰራር ማክሰሚያ እቅድ ክንውን ስራዎችን በ2018 የመጀመሪያ ግማሽ አመት በቁልፍ ተግባራትና በአበይት ተግባራት የተከናወኑ ስራዎችን በዝርዝር አቅርበዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ እንደገለጹት ባለስልጣኑ ሪፎርም ላይ ቢሆንም በ2018 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የተሻለ አፈጻጸም መኖሩን ገልጸው አገልግሎቱን ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራት በመከናወናቸው በቀጣይም የነበሩ ጠንካራ አፈጻጸሞችን በማስቀጠልና በሂደት የተስተዋሉ ክፍተቶችን በማረም የተሻለ ስራ በመስራት አፈጻጸሙን የበለጠ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ የባለስልጣኑ ጠቅላላ ካውንስል አባላት ሃሳብና አስተያየቶችን የሰጡ ሲሆን በቀጣይም ሪፖርቱ ለባለስልጠኑ አጠቃላይ ሰራተኛና ለባድርሻ አካላት እንደሚቀርብ ታውቋል፡፡
+5
ባለስልጣኑ ለአዲስ አበባ ሴቶች ማህበር ድጋፍ አደረገ፡፡
(ታህሳስ 24 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን መጭው የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ መንግስታዊ ያልሆኑ የትምህርት ተቋማትን በማስተባበር ለአዲስ አበባ ሴቶች ማህበር ድጋፍ አድርጓል፡፡
የአዲስ አበባ ሴቶች ማህበር ፕሬዝዳንት እናታለም እንዳለ የማህበሩን አላማ እንደገለጹት የሴቶችን መብት በማስጠበቅ ግንባር ቀደም ተሳታፊ እና ተጠቃሚነትን ለማስቻል እንደ ተቋቋመ ገልጸው በተለይም የሴቶችን ጥቃት ችግር ለመፈታት ከመንግስት ጎን በመሆን ማህበራዊ ችግሮችን ለመቀነስ እየሰሩ መሆኑን ገልጸው ባለስልጣኑ ላደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ እንደገለጹት ባለስልጣኑ በተለያዩ ጊዜ የማህበራዊ እና የበጎ አድራጎት ስራዎች እየሰራ መሆኑን ገልጸው ሰው ተኮር ስራዎችን ባለስልጣኑ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል፤ እንዲሁም ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች በማገዝ የሴቶች ጥቃት በማውገዝ እና ለህግ በማቅረብ ሀላፊነታችንን መወጣት እንደሚገባ አሳስበዋል በተጨማሪም ማህበሩን እና ድጋፍ ላደጉ የግል የትምህርት ተቋማት ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን ስለተወጡ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ወ/ሮ ሳባ ሀ/ማርያም ከግል ትምህርት ቤት ኮሚቴ እንደገለጹት በተደረገው ድጋፍ እና እድሉን በማግኘታቸው መደሰታቸውን ገልጸው ባለስልጣኑ በሚያደርጋቸው በጎ ተግባራት ሁሌም ከጎናቸው መሆኑን ገልጸው ማህበሩንም ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
+3
የባለስልጣኑ ጠቅላላ ካውንስል የ2018 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የመልካም አስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥ አፈጻጸሙ ላይ ውይይት አደረገ፡፡
(ታህሳስ 23 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ጠቅላላ ካውንስል የ2018 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የመልካም አስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥ አፈጻጸሙ ላይ ውይይት አደረገ፡፡
አቶ ሰለሞን አለማየሁ የባለስልጣኑ አማካሪ ሪፖርቱን በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን በሪፖርቱ የመልካም አስተዳደር ችግሮች የሚፈቱበትን ስልቶች፣ችግሩ የሚፈታበትን አግባብ፣እንደ ባለስልጣን የተለዩትን የመልካም አስተዳደር ችግሮች መካከል በመጀመሪያው ስድስት ወር ውስጥ የተለዩትንና የተፈቱትን በሪፖርቱ አብራርተዋል፡፡ከዚህም ሌላ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት የመጣውን ለውጥ፣ያጋጠሙ ችግሮች፣ የወደፊት የትኩረት አቅጣጫ ባቀረቡት ሪፖርት ተካቷል፡፡
አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ እንደገለጹት መልካም አስተዳደርን ማስፈን ለከተማችን እድገት ወሳኝ በመሆኑ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በአግባቡ ልየታ በማከናወን ውጤታማ የሆኑ ስራዎችን መስራት ተገቢ እንደሆነ አስገንዝበዋል፡፡
+6
ባለስልጣኑ የ2018 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ሱፐርቪዥን ተከናወነ፡፡
(ታህሳስ 23 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የ2018 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የመንግስትና የፓርቲ ስራዎች ሱፐርቪዥን ተከናወነ፡፡
ከከተማ አመራር የተውጣጣው የሱፐርቪዥን ቡድን አባል ባለስልጣኑ በስድሰት ወራት ውስጥ ያከናወናቸውን ስራዎች ከአመራር አኳያ፣እቅድና ሪፖርት አዘገጃጀት፣የተቋማት ግንባታ፣አገልግሎት አሰጣጥ፣ሌብነትና ብልሹ አሰራር፣ሚዲያና ኮሙኒኬሽን፣የኢኒሼቲቭ ስራዎች እና በሌሎችም ርእሶች ላይ የተከናወኑ የመንግስትና የፓርቲ ስራዎችን በዝርዝር በመረጃ እንዲቀርብ ጠይቀዋል፡፡
በዚህም የባለስልጣኑ የዘርፍ ሃላፊዎች በቼክሊስቱ መሰረት በየዘርፉ የተከናወኑ ተግባራትን በዝርዝር አቅርበዋል፡፡የባለስልጣኑ የስራ ክፍል ሀላፊዎችም ማስረጃዎችን መሰረት በማድረግ በየስራ ክፍሉ የተከናወኑትን ተግባራት አሳይተዋል፤ማበራሪያ የሚያስፈልጋቸውን ሀሳቦች አብራርተዋል፡፡
የሱፐርቪዥን ቡድን አባላቱም የተለያዩ ሰነዶችን፣ ማስረጃዎችን የተመለከቱ ሲሆን ከባለስልጣኑ ሰራተኞችም ሃሳብና አስተያየቶችን ሰብስበዋል የስራ ላይ ምልከታም አድርገዋል፡፡
ሱፐርቪዥኑ ሲከናወን የባለስልጣኑ ጠቅላላ ካውንስል አባላት ተገኝተዋል፡፡
+5
ባለስልጣኑ የ2018 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ድጋፍና ክትትል ተደረገለት፡፡
(ታህሳስ 22 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የ2018 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ድጋፍና ክትትል ከፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ በመጡ የድጋፍና ክትትል ቡድን አባላት ድጋፍና ክትትል ተደረገለት፡፡
የድጋፍና ክትትል ቡድኑ አባላት ባለስልጣኑ በ2018 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ከሰራቸው ተግባራት መካከል የእቅድ ዝግጅት፣አገልግሎት አሰጣጥ፣የቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ምርጥ ተሞክሮ፣ ምቹ የስራ ሁኔታ፣መማክርት ጉባኤ፣ብልሹ አሰራርን መዋጋት፣የመገናኛ ብዙሃን አጠቃቀም እና በሌሎችም ርዕሶች ላይ የተሰሩ ስራዎችን ተመልክተዋል፡፡
በድጋፍና ክትትሉ ወቅት ለተነሱት ሀሳቦችና ማብራሪያ ለሚሹ ጥያቄዎች የባለስልጣኑ አመራሮችና የስራ ክፍል ሃላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን የተከናወኑ ተግባራትንም ሰነዶችን በማሰደገፍ አሳይተዋል፡፡
+5
የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ እና የዕውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡
(ታህሳስ 20 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ እና የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር "ራስን የማስተዳደር ጥበብ" በሚል ርዕስ የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡
አቶ መስፍን ሀይሉ የባለስልጣኑ የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማረጋገጥ ባለሙያ “ራስን የማስተዳደር ጥበብ “ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን ራስን ማስተዳደር ማለት የራሱን ስሜት፣ሃሳብ፣ጊዜ እና ድርጊት በተገቢው መንገድ የመቆጣጠርና የመምራት ይህም ደግሞ ስኬታማ ለመሆንና ሰላማዊ ህይወት ለመምራት መሰረት መሆኑን እና ትልቅ የሚባል ፋይዳ አለው በመሆኑም ራሳችንን በጥበብ በመምራት ተቋማዊም ግለሰባዊም ለውጥ ማምጣት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ራሳችንን ለማስተዳደር ያለን ጊዜ ዛሬ በመሆኑ ነገን ትተን ዛሬ ብሎም አሁን መሆን ማድረግና መለወጥ መቻል ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ እና የጥራት ዘርፍ ሀላፊ በንግግራቸው ለተቋማዊ ለውጥ የግለሰቦች መለወጥ እንዲሁም የአገልጋይነት መንፈስ አስፈላጊ መሆኑን ግልፀው ቁጭት በተሞላበት ለውጥን በመፈለግ እንዲህም የአገልጋይነት ብሎም ቁርጠኝነትን በመላበስ የተቋሙን ራዕይ መተግበር እንዲህም ማስተግበርና ማህበረሰባችንን ማገልገል ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
ዶ/ር ተስፋዬ ኢባ የአመራር አካዳሚ ም/ፕሬዝዳንትና የአመራር ልማት ዘርፍ ዋና ሃላፊ በመርሃ-ግብሩ እንደገለጹት የምንሰራው ለአንድ ሀገር እንዲህም ለከተማ ራዕይ ነው በመሆኑም የሠለጠነውን ስልጠና በመተግበርና በተቋም ግንባታ ትልቅ አስተዋፅኦ ማድረግ ለከተማችን እድገት ቁልፍ ሚና መጫወት አለብን ብለዋል፡፡።
ታህሳስ 13 እስከ ታህሳስ 18 ድረስ ለተከታታይ ለስድስት ቀናት ሲሰጥ የነበረው የባህሪ ግንባታ እና የተግበራ ክህሎት ስልጠና ሲጠናቀቅ ስልጠናው በአግባቡ ለተከታተሉና ላጠናቀቁ ሰልጣኞች ሰርተፍኬት የሚሰጥ መሆኑ ታውቋል ፡፡
+6
ባለስልጣኑ ለሰራተኞች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና መጠናቀቁ ተገለፀ፡፡
(ታህሳስ 20 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የባህሪ ግንባታና ትግበራ ክህሎትን አስመልክቶ 400 ለሚሆኑ የባለስልጣኑ ሰራተኞች ከአመራር አካዳሚ ጋር በመሆን ሲሰጥ የነበረው ስልጠና መጠናቀቁ ተገለፀ፡፡
አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ በንግግራቸው ሁላችንም መሪ ነን በመሆኑም በሄድንበት ሁሉ ለውጥ ማምጣት መቻል እንዲህም አወንታዊ ተፅህኖ መፍጠር መቻል ብሎም ተቋማዊ ለውጥ ማምጣት መቻልና በቅንነት ማገልገል ያሰፈልጋል ያሉ ሲሆን የሰለጠነውን ስልጠና ተግባር ላይ በማዋል ለውጥ እናምጣ የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
+5
ባለስልጣኑ ለሰራተኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡
(ታህሳስ 13 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የባህሪ ግንባታና ትግበራ ክህሎትን አስመልክቶ 400 ለሚሆኑ የባለስልጣኑ ሰራተኞች ከአመራር አካዳሚ ጋር በመሆን ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡
አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ በስልጠናው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር ባለስልጣኑ ባደረገው ሪፎርም ሂደቱን ጠብቆ ባደረገው የሰራተኞች ምደባ መሰረት ወደ ስራ ስንገባ ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ መልካም አስተዳደርን በማስፈን ወደስራ መግባት ስላለብንና ተቋማችንን የተሻለ ለማድረግ የተዘጋጀ ስልጠና በመሆኑ ስልጠናው ከራስ እውቀት ጋር ማዛመድ ያስፈልጋል፡፡በመሆኑም ስልጠናውን በጥብቅ ዲስፕሊን መከታተል ከሰራተኛው የሚጠበቅ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
ዶ/ር ተስፋዬ ኢባ የአመራር አካዳሚ ም/ፕሬዝዳንትና የአመራር ልማት ዘርፍ ዋና ሃላፊ በመርሃ-ግብሩ እንደገለጹት ሀገር በተቋም ግንባታ ትገነባለች፡፡በመሆኑም መዋቅርን ከስትራቴጂ ጋር ማናበብና የሰው ሃይልን መመደብ ያስፈልጋል፡፡በመሆኑም በስልጠናው የሰልጣኞች እውቀት፣ ክህሎትና ባህሪን በማሳደግ በትክክል ራሳችንን ማወቅና ለተቋማችን የምንጠቅም መሆን አለብን፤ራሳችንንም ማሰተካከል ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
እየተሰጠ ያለው ስልጠና ከዛሬ ታህሳስ 13 እስከ ታህሳስ 18 ድረስ ለስድስት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል፡፡
