cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

ሰበር መረጃ new ♥

አዳዲስ መረጃወችን ያሳውቃል በተጨማሪም የቻናላችን ቤተሰብ ይሁኑ እናመሰግናለን

Mostrar más
El país no está especificadoEl idioma no está especificadoLa categoría no está especificada
Publicaciones publicitarias
176
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

ቻዉ
Mostrar todo...
ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ሦስት ሳተላይቶችን ታመጥቃለች❗️ ⚡️ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ለተለያየ አገልግሎቶች የሚውሉ ሦስት ሳተላይቶችን እንደምታመጥቅ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ⚡️የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዲሳ ይልማ እንደገለፁት፤ በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ውስጥ ለተለያዩ አግልግሎቶች የሚውሉ ሦስት ሳተላይቶችን ለማምጠቅ ታቅዷል። በአሥር ዓመቱ ከሚመጥቁት ሳተላይቶች ውስጥ አንደኛው የኮሚዩንኬሽን እና ብሮድካስት ሲሆን፤ የተቀሩት ሁለቱ የመሬት ምልከታ ሳተላይቶች ናቸው። ⚡️እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለፃ፤ የኮሚዩንኬሽን እና ብሮድካስት ሳተላይት የሚባለው በብሮድካስት ሚዲያዎች ለኢንተርኔት፣ ለስክልና ለኮሚዩንኬሽን አገልግሎት የሚውል ነው። በአሁኑ ሰዓት ሀገራችን እነዚህን አገልግሎቶች ከውጭ በመከራየት በሚሊዮን ዶላር የሚገመት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ታወጣለች። ⚡️ለአብነትም፣ ከብሮድካስቲንግ በዓመት እስከ አሥር ሚሊዮን ዶላር ወጪ ይደረጋል። ለቴሌ ኮሚዩንኬሽን ደግሞ በርካታ ሚሊዮን ዶላሮች ወጭ ይሆናሉ። ስለዚህ ሳተላይት የመገንባት እቅዱን በተግባር በማረጋገጥ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪን መቀነስ ተገቢ ነው።
Mostrar todo...
የህወሀት ግለሰቦች የተደበቁበትን ለሚጠቁሙ ዜጎች አስር ሚሊዮን ብር መዘጋጀቱ ይታወቃል ❗️ ⚡️ለሚጠቁሙ ዜጎችም መከላከያ አስር ሚሊዮን ብር የማበረታቻ ሽልማት የመደበ ሲሆን ፣ ጠቋሚዎች ማንነታቸው አይገለጽም ። ⚡️ዜጎች ጥቆማ የሚያቀርቡበት ስልክ ቀጥሎ ተመልክቷል ፡፡ 09 43 47 13 36 ወይም 012 5 50 43 48
Mostrar todo...
ዛሬ የመቐለ ከተማ ጊዜያዊ ከንቲባ አቶ አታኽልቲ በወቅታዊ ገዳዮች ዙሪያ ለሚዲያዎች መግለጫ ሰጥተዋል። አቶ አታኽልቲ በመግለጫቸው ተከታዩን ብለዋል ፦ ⚡️ሰላምና መረጋጋት ለማረጋገጥ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ ከፌዴራል ፖሊስና ከነዋሪዎች ጋር በቅንጅት የተለያዩ ተግባራት እየተከናወነ ነው። ⚡️ የመደበኛ ፖሊስ አባላት በተደረገላቸው ጥሪ መሰረት ወደ ሥራ ገበታቸው ለመመለስ ሪፖርት እያደረጉ ነው። ⚡️በጎ-ፈቃደኛ እና መልካም ስነ-ምግባር ያላቸው ወጣቶች በከተማዋ ሰላምና መረጋጋት ላይ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ለማድረግ እየተሰራ ነው። ⚡️በከተማዋ የሚገኙ የህዝብ አገልግሎት ሰጭ ተቋማትም ተገቢው ጥበቃ እየተደረገላቸው ነው። ⚡️ ከሰባት ክፍለ ከተሞች መካከል በ5ቱ ለህብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት የሚሰጡ አመራሮች ተመድበዋል። በቀሪ 2 ክፍለ ከተሞች ላይ ምደባ ለማካሄድ ህዝባዊ ውይይት እየተደረገ ነው። ⚡️ ከ2 ሺህ 26 የመንግሥት ሠራተኞች መካከል እስካሁን 84 በመቶ የሚሆኑት ወደ ሥራ ለመመለስ ሪፖርት አድርገዋል። ⚡️ በወረዳ እና በቀበሌ ደረጃ ያሉ ምክር ቤቶች በነበሩበት እንዲቀጥሉ አቅጣጫ ተቀምጦ ጥሪ ቢደረግም ባለመምጣታቸው ምክር ቤቶቹ በህዝብ ምርጫ እንደ አዲስ እንዲቋቋሙ ተደርጓል። ⚡️ ምክር ቤቶችና አመራር የተመደበላቸው ክፍለ ከተሞች ሙሉ ለሙሉ ወደ ሥራ ገብተዋል። ⚡️ የመድኃኒት አቅርቦት እጥረት ችግሩ ተፈቷል። ⚡️ የዋጋ ንረት ችግር እንዲፈታ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተሰራ ነው።
Mostrar todo...
የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየዉን መደበኛ ስብሰባ አጠናቀቀ❗️ ⚡️ኮሚቴዉ በሁለቱ ቀናት መደበኛ ስብሰባዉ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ የሚከተሉትን አቅጣጫዎች አስቀምጧል።
Mostrar todo...
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መርሐግብሮች ሲያስተምራቸው የነበሩ ተማሪዎቹን አስመረቀ❗️ ⚡️ዩኒቨርሲቲው በዛሬው እለት ያስመረቃቸው ተማሪዎች ቁጥር 1 ሺህ 300 ተማሪዎች ናቸው፡፡ ⚡️ከዚህ ውስጥ 1 ሺህ 228 በመጀመሪያ ዲግሪ ሲሆን 70 በሁለተኛ ዲግሪ እንዲሁም ሁለት ተመራቂዎችን በሶስተኛ ዲግሪ አስመርቋል፡፡
Mostrar todo...
16 ሺህ 900 ሐሰተኛ የብር ኖቶችን ሲያዘዋውር የነበረ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ❗️ ⚡️በአማራ ክልል፣ ዋግ ኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር፣ አበርገሌ ወረዳ 16 ሺህ 900 ሐሰተኛ የብር ኖቶች በማዘዋወር የተጠረጠረ ግለሰብ ትናንት በቁጥጥር ሥር መዋሉን የወረዳው አስተዳደር የፀጥታ እና ሰላም ደህንነት ጽ/ቤት አስታወቀ። ⚡️ተጠርጣሪው ግለሰብ በቁጥጥር ሥር የዋለው በወረዳው ወርቃዲኑ ጥንስስ ከተማ ሐሰተኛ የብር ኖቶቹን ይዞ ለመገበያየት ሲሞክር ተደርሶበት መሆኑን የጽ/ቤቱ ሓላፊ አቶ ሸጌ መንግሥቴ ለኢዜአ ተናግረዋል። ⚡️በአሁኑ ወቅት ተጠርጣሪው ምርመራ እየተደረገበት መሆኑንም አስረድተዋል። ⚡️ኅብረተሰቡ ከአዲሱ ብር ኖት ጋር ተያይዞ የአጭበርባሪዎች ተግባር ሰለባ እንዳይሆን በግብይት ወቅት ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ⚡️በግብይት ወቅት በብር ኖቶች ላይ አጠራጣሪ ነገር ሲያጋጥም በአካባቢው ለሚገኙ የሕግ አስከባሪዎች እንዲጠቁም መልእክት አስተላልፈዋል።
Mostrar todo...
Fake News Alert ❗️ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በማይካድራ ተጨማሪ 54 አስክሬኖች ተገኙ በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ ሀሰት መሆኑን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ይገልጻል❗️ ⚡️በቁፋሮ የወጡት 23 አስክሮኖች በተጨማሪ የተገኙ ሳይሆኑ መንግስት በመግለጫው ቀድሞውኑ ለህዝብ ያሳወቃቸው እና የአስክሬን ምርመራ ባለሙያ በመጠባበቅ ላይ የነበሩ መሆናቸው እየገለጸን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ከፌዴራል ፖሊስ ጋር በመሆን በተለያዩ ቦታዎች ላይ ተጨማሪ የጅምላ መቃብሮች ካሉ እያጣራ እንዲቆፈር እና አስክሬኖች ወጥተው የአስክሬን ምርመራ እንዲደረግላቸው በማድረግ በቤተ እምነት የቀብር ስፍራዎች በክብር እንዲያርፉ የሚያደርግ መሆኑን ይገልጻል፡፡ ⚡️በተጨማሪም በቀጣይ በምናደርገው የወንጀል ምርመራ መሰረት ከአስክሬን ማፈላለግ እና መሰል የምርመራ ስራዎች ጋር በተያያዘ የምናገኛቸውን መረጃዎች ለህዝብ የምንገልጽ መሆኑን እናረጋግጣለን፡፡ ⚡️በመሆኑም ህዝቡ በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚሰራጩ ዜናዎች ትክክለኛነት ከተቋማችን እና ሌሎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ተቋማት ለማጣራት የተቻለውን ሁሉ እንዲያደርግ እንጠይቃለን፡፡
Mostrar todo...
በካቡል የሚገኘው የአሜሪካ የጦር ማዘዣ ካምፕ የሮኬት ጥቃት ደረሰበት❗️ ⚡️ከካቡል በሰሜን አቅጣጫ በቅርብ ርቀት በምትገኘው ፓርዋን ግዛት በሚገኘው የአሜሪካ ዋና የጦር ማዘዣ ካምፕ ላይ ነው የሮኬት ጥቃቱ የደረሰው። ⚡️ጥቃቱን ማን እንዳደረሰው የተባለ ነገር ባይኖርም በአፍጋኒስታን የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ሳይፈጽሙት እንዳልቀሩ ዥንዋ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል። ⚡️የሮኬት ጥቃቱ ስላደረሰው ጉዳትና ተያያዥ ጉዳዮች ከሁለቱም አገሮች ባለስልጣኖች በኩል የተባለ ነገር አለመኖሩንም አስነብቧል። ⚡️ባለፈው ወር የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ “ማብቂያ የሌለው ጦርነት” ብለው በገለጹት የአፍጋኒስታን ሰላም ማስከበር ተልዕኮ በአገሪቱ በሰላም ማስከበር ላይ ከሚገኙ ወታደሮች መካከል 2 ሺህ 500 ወታደሮች ብቻ ቆይተው የተቀሩት ግን ለቀው እንዲወጡ ማዘዛቸው ይታወቃል።
Mostrar todo...
#በቡራዩ ከተማ በደረሰ የእሳት አደጋ ግምቱ 10 ሚሊየን ብር የሆነ ንብረት ወደመ ❗️ ⚡️አደጋው የደረሰው በቡራዩ ከተማ ገፈርሳ ኖኖ ቀበሌ ልዩ ስሙ ገብርኤል በሚባል አካባቢ ሲሆን በ16 ሱቆች፣ በ3 መኖሪያ ቤቶችና 3 ባርና ሬስቶራንቶች ላይ ቃጠሎ ደርሷል። ⚡️የእሳት እና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ቡድን መሪ አቶ ጉልላት ጌታነህ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በአገዳው 10 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን ወድሟል። ⚡️“እሳቱ ተጨማሪ ጉዳት እንዳያስከተል በመቆጣጠር 25 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት ማዳን ተችሏል” ብለዋል። ⚡️በአደጋው በሰው ላይ ምንም ጉዳት እንዳልደረሰ ጠቁመው፤ እሳቱን ለመቆጣጠር ከአንድ ሰዓት ተኩል በላይ ጊዜ መውሰዱን ተናግረዋል። ⚡️እሳቱን በማጥፋት የኮሚሽኑ ሰራተኞች፣ የፌዴራልና የኦሮሚያ ክልል የጸጥታ አካላትና የአካባቢው ነዋሪዎች መሳተፋቸውንም ገልጸዋል። ⚡️የአደጋው መንስዔ ገና እየተጣራ ሲሆን ህብረተሰቡ ለእሳት አደጋ መንስዔ ከሆኑ ተቀጣጣይ ነገሮች እንዲጠነቀቅ አሳስበዋል።
Mostrar todo...