cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Natnael Mekonnen

በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ሲፈልጉና ማስታወቂያ ማሰራት ከፈለጉ 👉 @NatnaelMekonnen7 Facebook.com/natnaelmekonnen.et Instagram.com/natnaelmekonnen21

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
173 041
Suscriptores
-3924 horas
-5107 días
-2 06730 días
Archivo de publicaciones
ሕዝብ ለሀገሩ ሁለት ጊዜ ግብር ይከፍላል፤ በጦርነት ጊዜ የደም፣ በሰላም ጊዜ የገንዘብ ግብር ይከፍላል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በጦርነት ጊዜ ከባዱን የደም ግብር የመክፈል ባህል ያለን ኢትዮጵያውያን፣ በሰላም ጊዜ ቀላሉን የገንዘብ ግብር ለመክፈል መቸገር የለብንም። ኢትዮጵያን ለማሳደግ፣ ለዜጎቿ መሠረታዊ ፍላጎቶችን በበቂ ሁኔታ ለማቅረብና ድህነትን በማሸነፍ ወደ ብልጽግና ለመገስገስ ከተፈለገ ስለግብር ያለው የተዛባ አመለካከት መቀየር ይኖርበታል፡፡ ከዛሬዋ ዕለት ጀምሮ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን እንደ ሀገር ለማስከበር ሲባል ታማኝ ግብር ከፋይ እንደ ዐድዋ ጀግና፣ ግብር የሚያጭበረብር ሰው ደግሞ እንደ ባንዳና ሰላቶ መቆጠር አለበት፡፡ በመሆኑም ግብር ከፋዩ ህብረተሰብ ግብር መክፈል ለራሱና ለሚወዳት ሀገሩ መሆኑን ተገንዝቦ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
የ2017 ዓ.ም የፌዴራል መንግሥት በጀት 971 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ሆኖ በሙሉ ድምፅ ጸደቀ! የ2017 ዓ.ም የፌዴራል መንግሥት በጀት 971 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ሆኖ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሙሉ ድምፅ ጸድቋል።በጀቱን አስመልክቶ የምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ ለምክር ቤቱ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ምክር ቤቱ በቀረበለት በጀት ላይ ተወያይቶ በሙሉ ድምጽፅ አጽድቆታል።በጀቱ ከአምናው በጀት ጋር ሲነጻጸር የ169 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ተመልክቷል።
Mostrar todo...
‚‘ኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች ታላቅ ሀገር በመሆኗ ማንም በማንም ላይ ጫና ፈጥሮ መኖር የሚችልበት ሀገር አይደለችም።“ ክቡር የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ክቡር የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች ታላቅ ሀገር በመሆኗ ማንም በማንም ላይ ጫና ፈጥሮ መኖር የሚችልበት ሀገር አይደለችም ያሉት በተቋሙ የ2016 በጀት ዓመት ማጠቃለያ ግምገማ ላይ ነው። የሀገራችንን ህዝብ ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅና ለሕገ-መንግስቱ ዘብ ለመቆም እንደ መለዮ ለባሽ በገባነው ቃል መሠረት በቁርጠኝነት እየሰራን እንገኛለን ብለዋል ክቡር ኮሚሽነር ጀነራሉ። በበጀት ዓመቱ የወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ገቢና ወጪ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን በመያዝ እና ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውር እና ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን ከመቆጣጠር አንፃር ውጤታማ ሥራዎችን መስራቱን አንስተዋል። ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል አያይዘውም የወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ ከፌደራልና ከክልል ፀጥታ አካላት ጋር ተቀናጅቶ አሽባሪዎችንና ፅንፈኞችን በመቆጣጠርና አኩይ ዓላማቸውን በማክሸፍ አንፃር ትላልቅ ሥራዎችን ያከናወነበት ዓመት ነበር ብለዋል። የኦፕሬሽን አቅም ለማሳደግ አመራሩንና አባሉን ጭምር በማሰልጠን ረገድ ከፍተኛ ሥራ የተሠራ ሲሆን በርካታ ሰልጣኞች በሥልጠና ውስጥ እንዲያልፉ በመደረጉ ኦፕሬሽን ላይ ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን አንስተው ስልጠናው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል። በተመሳሳይ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ ሀገራችንን ለማፍረስና ችግር ውስጥ ለመክተት የሚንቀሳቀሱ አሸባሪዎችና ፅንፈኛ ኃይሎችን በመቆጣጠር እና ዓላማቸውን በማክሸፍ በሕግ ተጣያቂ እንዲሆኑ የተለያዩ ችግሮችን በቁርጠኝነት ተሻግሮ ተጠያቂ እንዲሆኑ አድርጓል። ይህም የፖሊስ የምርመራ አቅም ምን ያህል እያደገ እንደመጣ ያሳየና ወንጀለኞች ይቺን ሀገር ማፍረስ እንደማይችሉ ያረጋገጠ ነው ብለዋል ክብር ኮሚሽነር ጀነራሉ። በመጨረሻም የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ለከፍተኛ አመራሮቹ ቀርቦ ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል በቀረበው ዕቅድ ላይ አንድ በአንድ ትንታኔ ከሰጡ በኋላ በዕቅዱ ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጎ ከሐምሌ 1 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በየደረጃው ያለው አመራር ተፈራርሞ ወደ ስራ እንዲገባ አቅጣጫ ተሰጥቷል።
Mostrar todo...
00:37
Video unavailableShow in Telegram
ELEGAS ENGINEERING PLC የእርስዎ አሳንሰር መፍትሄ ባለሙያዎች ለ Elevator እና ለEscalator ከፍተኛ ደረጃ የምህንድስና መፍትሄዎች ያስፈልጎዎታል? በኢንዱስትሪው ውስጥ ግንባር ቀደም ኩባንያ ከሆነው ELEGAS ኢንጂነሪንግ አለሎት። ባለን ሰፊ ልምድ እና እውቀት ላለፉት 17 አመታት በአስራ በአምስት ሀገራት በልዩ ጥራተ‍እ አገልግሎት ስናቀርብ ቆይተናል። አሁን ደግሞ ላለፉት ሁለት ዓመታት የአገር ውስጥ ገበያን እያገለገለ አዲሱን የግንባር መስሪያ ቤታችን በኢትዮጵያ መከፈቱን በደስታእንገልፃለን። በ ELEGAS ምህንድስና፣ ልዩ ፍላጎቶችዎን ለማሟላት የተዘጋጁ ምርጥ የምህንድስና መፍትሄዎችን በማቅረበ‍ኣችን እንኮራለን። የድርጅታችን ባለ ሞያዎች በምንሰራው እያንዳንዱ ፕሮጀክት የላቀ ጥራት ለማቅረብ ቁርጠኛ ናቸው። ሚለየን ምንድነው? የገጠማ ስራን ጨምሮ በአራት ወራት ውስጥ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን አሳንሰሮች ከቱርክ የማድረስ ችሎታችን። ጊዜ ወሳኝ ነዋ 🖊️ በተጨማሪም ከእያንዳንዱ ሊፍት ግዢ ጋር ጥቅል እናቀርባለን። በምርቶቻችን ላይ ለጋስ የሁለት ዓመት ዋስትና ያገኛሉ። በተጨማሪም የአሳንሰርህን ረጅም ዕድሜ እና ጥሩ አፈጻጸም ለማረጋገጥ የአንድ አመት ነጻ ጥገና እናቀርባለን። 🖊️ የዋጋ አወጣጥን በተመለከተ፣ የፕሮጀክትዎን ፍላጎት የሚያሟላ ተለዋዋጭነት እናቀርባለን። 🖊️ FOB፣ CIF፣ ወይም DDP፣ የዋጋ አወጣጥ አማራጮቻችንን ከተወሰኑ መስፈርቶች ጋር በማዛመድ እናዘጋጃለን። 🖊️ ገጠማ የሚደርጉላችሁ የበርካታ አመታት ከቱርክ የመጡ ልምድ ያላቸው crewዎች ናቸው። 🪄We Care አድራሻ:- ቡልጋሪያ ማዞሪያ የትራፊክ መብራት አጠገብ አዌባነ ህንፃ 1ኛ ፎቅ 📞 +251 971 71 71 71 +251 994 69 69 69 www.elegas.com.tr Email:- [email protected]
Mostrar todo...
IMG_9376.MP46.99 MB
Photo unavailableShow in Telegram
በግጭትና ጦርነት ኢትዮጵያ ውስጥ ስልጣን መያዝ ፈጽሞ አይቻልም፡፡ለኢትዮጵያ ዛሬም ነገም የሚበጀው በሰላምና በሰከነ መንገድ ተወያይቶ ችግሮችን መፍታት ነው፡፡ <<መፈንቅለ መንግስት በኢትዮጵያ ከዚህ በኋላ ጭራሽ አይሳካም፤ ጊዚያችሁን አታባክኑ።>> ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በዛሬ የፓርላማ ውሎ ከተናገሩት የተወሰደ
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
„ኢትዮጵያ የቆመችው በአርሶ አደር፣ ወታደር እና መምህራን ውለታ ነው“ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) „ኢትዮጵያ የቆመችው በአርሶ አደር፣ ወታደር እና መምህራን ውለታ ነው“ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአርሶ አደሩን ሕይወት ለማሻሻል በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ ነው ብለዋል፡፡ ነገር ግን መምህር እና ወታደር ለሀገር ከሚከፍሉት ውለታ ባሻገር የሚከፈላቸው ዋጋ እዚህ ግባ የሚባል አይደለም ነው ያሉት፡፡ በቀጣይ የመምህራንን ሕይወት ለማሻሻል የሚረዱ ሥራዎች እየተሠሩ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሚያበረክቱት አስተዋጽኦ ግን ኢትዮጵያ ታመሠግናቸዋለች ብለዋል፡፡
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
ናሽ ልዩ የጥርስ ህክምና ክሊኒክ ዘመኑ ባፈራቸው መሳሪያዎ ች በመታገዝ ሙሉ የጥርስ ህክምናን በመስጠት ላይ ይገኛል::  ከምንሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል በከፊል ➢ መጥፎ የአፍ ጠረንን ማከም ➢ የቆሸሹ ጥርሶችን በማሽን እናፀዳለን ➢ በህክምና መዳን የማይችሉትን ጥርሶች መንቀል ➢ ወጣ ገባ ያሉ ጥርሶችን በ ኦርቶዶንቲክ አፕላይንስ እና በብሬስ ማስተካከል ➢ የጥርስ ስር ህክምናን መስጠት ➢ የተቦረቦሩ ጥርሶችን እንሞላለን ➢ የተነቀሉ ጥርሶችን በሰው ሰራሽ አርተፊሻል መተካት ➢ የጥርስ ራጅ አገልግሎት መስጠት አድራሻ: ሜክሲኮ ቡልጋሪያ ጫፍ ትራፊክ ማብራቱ አጠገብ   Tel: 0913858561
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
ዲኤምሲ የተሰማራባቸው መስኮች 👉 ዲኤምሲ ኮንስትራክሽን         🏡43 ቪላ ቤቶችን         🛣️ በመንገድ ስራ ሀዋሳ, አርባምንጭ, ሻሸመኔ, አዳማ         🏢 በህንፃ ግንባታ የሀሮማያ ዪኒቨርሲቲ የተማሪዎች ዶርሚተሪ እና መማሪያ ክፍል ብሎኮች, የባህር ትራንዚት ማጓጓዣ ድርጅት ዋና መሥሪያ ቤት 👉 የማርብል ማምረት ኢንደስትሪ 👉 የጠጠር እና ብሎኬት ማምረት ኢንደስትሪ 👉 ዳሮን ኮንስትራክሽን ኢንደስትሪ 👉ዲኤምሲ ፋውንዴሽን 👉ቀለምዋ ፋውንዴሽን       በሴቶች ማጎልበት እና በወጣቶች ልማት ላይ የሚሰራ ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት አሁን ደግሞ በሪል እስቴት ዘርፍ 👉ዲኤምሲ ሪል እስቴት 📍📍📍 በለቡ መብራት ሀይል በቻድ ኤምባሲ እና በአፍሪካ ሲዲሲ መሀል የሚገኝ 🛫🛫🛫 ቦሌ ኤርፖርት 20ደቂቃ እርቀት 🛍️🛍️🛍️ መርካቶ 25 ደቂቃ እርቀት ላይ ⏳⏳⏳ማስረከቢያ ጊዜ 2 አመት ከስድስት ወር (30 ወር) ብቻ!!! በሰፊ የመኖሪያ ጊቢ ውስጥ አፓርትመንቶች 👉 ስቱዲዮ       56m2 👉ባለ 1 መኝታ     69m2,77m2, 85m2 👉ባለ 2 መኝታ 99m2,123m2, 128m2, 148m2 👉ባለ 3 መኝታ 139m2,146m2, 153m2, 159m2, 167m2 👉ባለ 4 መኝታ       177m2, 181m2 👉እንዲሁም ሱቆች በተለያየ የካሬ አማራጭ       35m2, 43m2, 67m2 🔥በ4%,8% እና 10% ቅድመ ክፍያ አከፋፈል ሂደት🔥 ከ50% የባንክ ብድር ጋር በአነስተኛ ወለድ እና ወለድ አልባ የሚለየን ምንጠቀመው BIM እና Aluminium Formwork ለግንባታችን ጥራት እና ቅልጥፍናን ይሰጠናል። ሰለ ሪልእስቴቱ የበለጠ መረጃ ⏱📞 ☎️ አሁኑኑ  በ0910054029/0987878256 በቀጥታ ወይንም በቴሌግራም በዋትሳፕ ይደውሉ
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
አቶ ካሳሁን ጎፌ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚንስትር በመሆን በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተሹመዋል:: መልካም የስራ ዘመን
Mostrar todo...
ወ/ሮ ሽዊት ሻንካን በጠሚ አብይ አህመድ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር አድርገው ሾመዋቸዋል። የባህልና ስፖርት ሚኒስትር የነበሩት አቶ ቀጀላ መርዳሳ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወጣቶች እና ስፖርት አማካሪ ሚኒስትር ሆነው ከዛሬ ሰኔ 26 /2016 ዓ/ም ጀምሮ እንደ ተሾሙ ታውቋል። መልካም የስራ ዘመን
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
አንጋፋው ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። ከ ‘ አዲስ አድማስ ጋዜጣ ‘ መሥራች አንዱ እና በዋና አዘጋጅነትም ጋዜጣዋን ተወዳጅ ያደረጋት ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን ባደረበት ህመም ህክምናውን ሲከታተል ቆይቶ ዛሬ ረቡዕ ረፋድ ላይ ድንገት ህይወቱ አልፏል። ነቢይ ተርጓሚ ፣ ገጣሚ ወግ አዋቂ የጥበብ ሰው እንደሆነ ይነገራል።
Mostrar todo...
የተጀመረው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች የለውጥ ስራዎች ጉብኝት ተጠናክሮ ቀጥሏል። በጉብኝቱ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፋት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ክቡር ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል ዘላለም መንግስቴ ጉብኝቱ ተቋሙ ወዴት እየሄደ እንዳለና ሥራው በምን አይነት ሁኔታ እየተመራ እንዳለ በሁሉም አመራር ዘንድ ወጥ ግንዛቤ እንዲፈጠር ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ሎጂስቲክስ ዋና መምሪያ ኃላፊ ክቡር ረዳት ኮሚሽነር እሼቱ ፊጣ በመንግስት በተጀመረው ሪፎርምና በተቋማችን ጠንካራ የማኔጅመንት አባላት በተሰጠ አቅጣጫ መሠረት የሎጂስቲክ የግብዓት አቅርቦት አቅምን በሁለንተናዊ መልኩ በማሳደግ ለፖሊስ ሰራዊቱ የጀርባ አጥንት እየሆነ እንዲቀጥልና የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በአፍሪካ ካሉ አምስት ምርጥ የፖሊስ ተቋማት መካከል አንዱ እንዲሆን በትጋትና በቁርጠኝነት 24/7 እየሠራን ነው ብለዋል። የፖሊስ ከፍተኛ አመራሮቹ በሎጂስቲክ ዋና መምሪያ ሲደርሱ ደማቅ የፖሊስ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን በተሽከርካሪ ጥገና፣ በኮንስትራክሽንና ምህንድስና ፣ በግዥና ፋይናንስ እና በንብረት አስተዳደር መምሪያዎች እና በአራት ዋና ክፍሎች የተከናወኑ ስኬታማ የለውጥ ስራዎችን ተዘዋውረው ጉብኝተዋል። ከሪፎርሙ በፊት ይባክን የነበረው የባለሙያ ጉልበት ፣ ጊዜ እና ሀብት ብክነትን ያስቀረው የተሽከርካሪ ዲጂታል ዳታ አያያዝ (vehicle management system)፣ የዳታ ቤዝ እና የንብረት አያያዝ እንዲሁም የግዥ ሥርዓት ወደ (Electronic Government Procurement (EGP) መቀየርን ጨምሮ በከባድና በቀላል ብልሽት የቆሙ ተሽከርካሪዎችን በመጠገንና ወደ ሥራ በማስገባት ተቋሙ ያወጣ የነበረውን ከ70 ሚሊየን ብር በላይ ከማዳኑም ባሻገር የሌሎች ተቋማት ተሽከርካሪዎችን እየጠገነ ለተቋሙና ለአባላቱ የገቢ ምንጭ መፍጠር የጀመረው የተሽከርካሪ ጥገና መምሪያን ጎብኝተዋል። በተመሳሳይ የማዕረግና የተለያዩ ልብስ ስፌት፣ የመኪና ወንበር አልባሳት ማምረቻ፣ የብረታ ብረትና የእንጨት ሥራ እንዲሁም የጦር መሣሪያ ማርኪንግ የሚሰራበትን ክፍሎችንና በሪፎርሙ የተፈጠሩ ምቹ የሥራ አካባቢዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። በተጨማሪም ከፍተኛ አመራሮቹ በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ቅጥር ግቢው ውስጥ እየተከናወኑ ያሉ ሰፋፊ የልማት ስራዎች እና በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ የፎረንሲክ ሳይንስ ኢንስቲትዩት እና ባለ አምስት ኮከብ የኢንተርናሽናል ፖሊስ ሊደርሺፕ ኢንስቲትዩት ፕሮጀክቶችን እንዲሁም የታደሰውን የፓሬል ግራውንድ (Parel ground) እንዲሁም የአከባቢውን ማህበረሰብ ችግር ለመፍታት እየተሠራ ያለው ተግባር እና እየተፈጠሩ ያሉ ምቹ የሥራ አካባቢዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። አመራሮቹ በዋና መምሪያው እና በዩኒቨርሲቲው የተከናወኑ ታላላቅ እና ሰፋፊ የሪፎርም ሥራዎችን ከጎበኙ በኋላ በሰጡት አስተያያት ተቋሙ ትክክለኛ፣ ተጨባጭና የሚታዩ ሥራዎችን እያካሄደ መሆኑን ተመልክተናል ካሉ በኋላ ለሬጅመንት አመራሮችም ዕድሉ ተመቻችቶ እነርሱም ቢጎበኙ መልካም ነው ብለዋል።
Mostrar todo...
የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የፖሊስ እና አባላቱን የጤና እክል ሲገጥማቸው ህክምና ሊያገኙ የሚችሉበት የክልሉን ኮሚሽን የፖሊሲ ጤና ጣቢያ ስራ አስጀመረ። በጤና ጣቢያው ሰራዊቱን በክብር አገልግለው በጡረታ የተሰናበቱ የሰራዊት አባላትና ቤተሰቦቻቸው ሁሌም በቀዳሚነት በዚህ ጤና ጣቢያ ጤናቸውን መጠበቅ የሚችሉበት ሁኔታ ያለ ሲሆን አሁንም በሰራዊቱ ውስጥ ያሉት የፖሊስ አላትም ከእነ ቤተሰባቸው መገልገል የሚችሉበት ጤና ጣቢያ መሆኑ ታውቋል። የጤና ጣቢያው ስራ መጀመር የራሳችንና የቤተሰቦቻችንን ጤና ለመጠበቅ የሚረዳን ከመሆኑ ባሻገር በሌሎች ጤና ተቋማት በክፍያ የምናገኘውን አገልግሎት የፖሊስ ጤና ጣቢያው አገልግሎቱን በነፃ በመስጠት የሚደርስብን እንግልትና ወጪን ያስቀርልናል ሲሉ የክልሉ የፖሊስ አባላት ገለፀዋል። ጤና ጣቢያው ከአባሉና ቤተሰቡ ባሻገር ለአካባቢው ማህበረሰብም በተመጣጣኝ ዋጋ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑ ታውቋል። የጤና ጣቢያው ስራ በይፋ መጀመርን አስመልክቶ የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ ፣ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሽመልስ ቶማስ እና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የክልሉ ጤና ቢሮ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች የተገኙ ሲሆን ስራ ማስጀመሪያው መድረክ ላይ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። በክብር እንግድነት የተገኙት የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ ከክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ጋር ጤና ጣቢያውን ተዘዋዉረው የጎበኙ ሲሆን ጤና ጣቢያው አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለው ደረጃ ላይ ስለመሆኑ መመልከታቸውን ገልፀው፤ በቀጣይም ለበለጠ አገልግሎት አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግ ተናግረዋል።ባለሙያዎችም አባሉንና ማህበረሰቡን በተገቢው በማገልገል ሁሉም ሀላፊነቱን መወጣት ይጠበቅበታል ብለዋል። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሽመልስ ቶማስ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን በዛሬው እለት በይፋ የፖሊስን ጤና ጣቢያ ስራ ሲያስጀምር የሰራዊቱንና ቤተሰቡን ጤና በመጠበቅ ተልኮውን በብቃት መወጣት የሚችል ሰራዊት ለመገንባት ፋይዳው የጎላ መሆኑን ገልፀዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም ጤና ጣቢያው በሰው ሀይልና ሎጀስቲክ አገልግሎቱን ለመስጠት የተሟላ መሆኑን ገልፀው፣ ያልተሟሉ የህክምና ቁሳቁሶችንም ለማሟላት በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። ያነጋገርናቸው የሰራዊቱ አባላት በሰጡት አስተያየት የጤና ጣቢያው ስራ መጀመር ሰራዊቱ የጤና ችግር ሲገጥመው በቅርበት በአፋጣኝ ህክምና እንዲያገኝ የሚረዳ ሲሆን በሌሎች የጤና ተቋማት የሚገጥምንም ወጪ የሚያስቀር በመሆኑ የጤና ጣቢያው መጀመር ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል።
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
ዲኤምሲ የተሰማራባቸው መስኮች 👉 ዲኤምሲ ኮንስትራክሽን         🏡43 ቪላ ቤቶችን         🛣️ በመንገድ ስራ ሀዋሳ, አርባምንጭ, ሻሸመኔ, አዳማ         🏢 በህንፃ ግንባታ የሀሮማያ ዪኒቨርሲቲ የተማሪዎች ዶርሚተሪ እና መማሪያ ክፍል ብሎኮች, የባህር ትራንዚት ማጓጓዣ ድርጅት ዋና መሥሪያ ቤት 👉 የማርብል ማምረት ኢንደስትሪ 👉 የጠጠር እና ብሎኬት ማምረት ኢንደስትሪ 👉 ዳሮን ኮንስትራክሽን ኢንደስትሪ 👉ዲኤምሲ ፋውንዴሽን 👉ቀለምዋ ፋውንዴሽን       በሴቶች ማጎልበት እና በወጣቶች ልማት ላይ የሚሰራ ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት አሁን ደግሞ በሪል እስቴት ዘርፍ 👉ዲኤምሲ ሪል እስቴት 📍📍📍 በለቡ መብራት ሀይል በቻድ ኤምባሲ እና በአፍሪካ ሲዲሲ መሀል የሚገኝ 🛫🛫🛫 ቦሌ ኤርፖርት 20ደቂቃ እርቀት 🛍️🛍️🛍️ መርካቶ 25 ደቂቃ እርቀት ላይ ⏳⏳⏳ማስረከቢያ ጊዜ 2 አመት ከስድስት ወር (30 ወር) ብቻ!!! በሰፊ የመኖሪያ ጊቢ ውስጥ አፓርትመንቶች 👉 ስቱዲዮ       56m2 👉ባለ 1 መኝታ     69m2,77m2, 85m2 👉ባለ 2 መኝታ 99m2,123m2, 128m2, 148m2 👉ባለ 3 መኝታ 139m2,146m2, 153m2, 159m2, 167m2 👉ባለ 4 መኝታ       177m2, 181m2 👉እንዲሁም ሱቆች በተለያየ የካሬ አማራጭ       35m2, 43m2, 67m2 🔥በ4%,8% እና 10% ቅድመ ክፍያ አከፋፈል ሂደት🔥 ከ50% የባንክ ብድር ጋር በአነስተኛ ወለድ እና ወለድ አልባ የሚለየን ምንጠቀመው BIM እና Aluminium Formwork ለግንባታችን ጥራት እና ቅልጥፍናን ይሰጠናል። ሰለ ሪልእስቴቱ የበለጠ መረጃ ⏱📞 ☎️ አሁኑኑ  በ0910054029/0987878256 በቀጥታ ወይንም በቴሌግራም በዋትሳፕ ይደውሉ
Mostrar todo...
የሆቴሎች የኮኮብ ደረጃ ምደባ በአዲስ መልክ ሊሰራ ነው:: ከመስከረም ጀምሮ ከዚህ በፊት የተሰጠው የኮከብ ደረጃ ስራ ላይ አይውልም:: የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የደረጃ ምደባ ደንብ ሆቴሎች በየሶስት አመቱ በዳግም የደረጃ ምደባ ሂደት ማለፍ እንዳለባቸው ይደነግጋል፡፡ በዚህም መሰረት ሚኒስቴር መ/ቤቱ በአዲስ አበባ ከተማ እና በክልሎች የሚገኙ ሆቴሎችን የደረጃ ምዘና ለማድረግ ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ ይህንን ለማድረግ የሚያስችለው መመሪያ ላይም ከሆቴል ባለቤቶች እና ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድርጏል:: የቱሪዝም ሚንስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ አሁን በሚያደረገው የዳግም ደረጃ ምዘና ሂደት ውስጥ የማያልፉ ሆቴሎች ከዚህ ቀደም የተሰጣቸው የኮከብ ደረጃ በህጉ መሰረት የአገልግሎት ጊዜው ያበቃ በመሆኑ የኮከብ ደረጃው እንደሚሰረዝ ተናግረዋል፡፡ ይህ ዳግም ምደባ በዋናነት ሆቴሎች የሚሰጡትን አገልግሎት ማሻሻል እና የሀገሪቱን የቱሪዝም አገልግሎት ተወዳዳሪነት ማሳደግ ላይ ትኩሩቱን ያደረገ መሆኑንም ገልፀዋል::
Mostrar todo...
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.