cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

ፍኖተ ጥበብ ሰንበት ት/ቤት

ይህ የሲኤምሲ አቡነ ተክለሐይማኖትና ቅድስት ልደታ ለማርያም የፍኖተ ጥበብ ሰንበት ት/ቤት በሰንበት ት/ቤቱ ግንኙነት ክፍል የተከፈተ የቴሌግራም ቻናላችን ነው።ለማንኛውም ሃሳብ አስተያየትና ጥያቄ @FinoteTebebBot የሚለውን ቦት ተጠቀሙ። የአቡነ ተክለሐይማኖት አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ከኛ ጋር ይሁን!!!

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
211
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
Photo unavailableShow in Telegram
" ጌታ ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያን እናደርጋለን ማለት ይገባችኋል።" ያዕ 4:15      🔔🔔🔔ጠቅላላ ጉባኤ🔔🔔🔔 👉የፊታችን እሑድ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3 :00 ጀምሮ የሰንበት ትምህርት ቤታችንን የ2016 ዓ.ም የስድስት ወር እቅድ ክንውን እንዲኹም ወቅታዊ ጉዳይ ላይ እንመክራለን! የፍኖተ ጥበብ ጉዳይ የኔ ጉዳይ ነው የምትሉ ልጆቿ ኹሉ በሰዓቱ በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ የምትገኙ ይኹን!           ✨✨✨✨✨✨✨✨ ''ለነገዋ የቤተ ክርስቲያን ገጽታ የምትጨነቁ ከሆነ፤ ዛሬ የሰንበት ትምህርት ቤትን አገልግሎት በልባችኹ አኑሩ '' ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካል
Mostrar todo...
👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
"የአምላካቸሁን የእግዚአብሔር የቃልኪዳን ታቦት ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ ከሰፈራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት።" መጽሐፈ ኢያሱ ፫-፪ "እንኳን ለጌታችን እና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል አደረሳችሁ🙏 የበረከት በዓል ይሁንልን🙏🙏🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
👍 3
"የማይበድል ባሪያ የማይምር ጌታ የለምና፤ ጌታ ሆይ:- አቤቱ እኔን ኃጢአተኛውን ይቅር በለኝ" 🙏🙏🙏 [አባ ዕብሎይ ] 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
🙏 2
Photo unavailableShow in Telegram
ጥር ፭❤️ በዓለ ልደቱ ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ እንኳን አደረሰን❤️🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
3
Photo unavailableShow in Telegram
💚💚💚💚💚💛💛💛💛💛❤️❤️❤️❤️❤️ በዚያም ሳሉም የምትወልድበት ቀን ደረሰ። የበኵር ልጇንም ወለደች አውራ ጣቱንም አሰረችው በጨርቅም ጠቀለለችው በበረትም አስተኛችው በማደርያቸውም ቦታ አልነበራቸውምና።" ሉቃ 2፥6-7 💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️ እንኳን ለጌታችን ለአምላካችን እና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ ። በዓሉን የሰላም የፍቅር የበረከት ያድርግልን መልካም በዓል 🙏🙏🙏🙏💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️🙏🙏🙏🙏 ፍኖተ ጥበብ ሰንበት ትምህርት ቤት ግንኙነት ክፍል 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
6
Photo unavailableShow in Telegram
እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና። ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ። ድንገትም ብዙ የሰማይ ሠራዊት ከመልአኩ ጋር ነበሩ። እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ። ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ።..."               ሉቃ ፪፥፬-፳ ይህ የጌታችን ልደት በዓለም ላይ ካሉ ልደቶች ሁሉ የላቀው፤ ለዓለም ህዝብ ሁሉ መዳን የሆነ ልደት ነው።        ወነዋ ተወልደ መድኃኔዓለም      ፍሥሐ ለኩሉ ዘየአምን ትርጉም፦ ዛሬ ተወለደ የዓለም መድኃኒት                ደስታ ነውና ለሚያምኑት እንኳን ለጌታችን ለአምላካችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሰን አደረሳችሁ የበረከት በዓል ይሁንልን አሜን🙏🙏🙏 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
3
++++እናስተውል በድጋሜ የዘላለም ቁጣ ሳይመጣ++++ ልጄ ሆይ ዛሬን ብትወድቅ ተስፋ አትቁረጥ ተነስ እንጂ ዛሬ እንደ ቃሉ በፍቅር መኖር ቢያቅትህ መፍትሔው ተስፋ መቁረጥ አይደለም፡፡ በእግዚአብሔር ተስፋ ማድረግ እንጂ ዛሬ በአገልግሎትህ ብትደክም ተስፋ ቆርጠህ ከቤቱ ከቶ አትውጣ፡፡ ከሐዋርያት ጋር ሆነህ ጌታ ሆይ ወደ ማን እሄዳለሁ?  አንተ የዘላለም ሕይወት ቃል አለህ በለው፡፡ ዮሐ 6፡68 ከዳዊት ጋርም ሆነህ አሁንስ ተስፋዬ ማነው አንተ እግዚአብሔር አይደለህምን በለው መዝ 38፡7 ፍሬ ለማፍራትም በእርሱ ተስፋ አድርግ፡፡ በተስፋ ለምትጠባበቀው ለምትሻውም ነፍስ ጌታ ቸር የሚራራም ነውና፡፡ ልጄ ሆይ አዳም ከገነት ቢሰደድ ይዞ የወጣው ሌላ አይደለም ተስፋን ነው፡፡ በጌታ ቀኝ የተሰቀለው ወንበዴ እድሜ ልኩን በክፉ ስራ ቢኖርም ተስፋን ግን አልጣለም በመጨረሻ ትንፋሽ ላይ ሳለ ወደ ሕይወት ያደረሰችው ይህች ተስፋ አለመቁረጥ ናት፡፡ በግራ ያለውማ ተስፋ በመቁረጡ የእምነትና የፍቅር ሻማዎቹ ሊበሩለት አልቻሉም፡፡ እንግዲህ ልጄ ሆይ በጊዜውም ያለጊዜውም እርሱን ተስፋ አድርገህ ኑር፡፡ በፍጹም ተስፋ አትቁረጥ። :ምናልባት ለመፆም፣ ለመፀለይ፣ ለማስቀደስ፣ ለመስገድ፣ የተለያዩ መንፈሳዊ ተግባራትን ለማከናወን ፍላጎታችን ፍቅራችን ጠፍቶ ይሆናል። እነዚህን መንፈሳዊ ተግባራትን ለማከናወንም እምነት አጥተን ይሆናል ግን ተስፋ ልንቆርጥ አይገባም በእግዚአብሔር። ፍቅር እንዲጨምርልን እንለምነው። አለማመኔን እርዳው እምነትን ጨምርልኝ፣ ትእዛዛቶችህን ለመፈፀም እምነት ይጎድለኛል። በመፆም በመፀለይ የሚገኘውን በረከት አላስብም እንዲሁ ለማድረግ ያክል ብቻ ነው። ዋጋም ያለው አይመስለኝም። አምላኬ ፍቅርህን አብዛልኝ አንተን ማመንንም ጨምርልኝ ብለን እንለምነው። የመበለቲቱን ሁለት ዲናር ሳይንቅ አክብሮ የተቀበለ አምላካችን ይለመነናል።  ‹‹እግዚአብሔርን ተስፋ የሚያደርጉ ግን እነርሱ ምድርን ይወርሳሉ›› መዝ 36፡9                                                                                    𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
4👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
ታህሳስ ፳፪ ብስራተ ገብርኤል❤️ ወእንዘ ትፈትል ወርቀ ወሜላተ አስተርአያ ገብርኤል ግብተ ወይቤላ እስመ ረከብኪ ሞገሰ በኅበ እግዚአብሔር ትርጉም፡- ሐርና ወርቅን አስማምታ ስትፈትል በድንገት መልአኩ ገብርኤል ታያት። በእግዚአብሔር ዘንድ ቧለሟልነት መወደድን አግኝተሻል አላት። ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ላበሰረበት ታላቅ ዓመታዊ በዓል እንኳን አደረሳችሁ በረከታቸውም ይደርብን🙏🙏🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
2👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
ታህሳስ ፲፱ ፥ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል❤️ እስመ ተለዓለ ዕበየ ስብሐቲከ መልዕልተ ሰማያት ፤ እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሐተ ፤ ባርካ እግዚኦ ለዛቲ መካን። ደጉ አባት ቅዱስ ገብርኤል በምድር ከሀጥያት እሳት በሰማይ ከማይጠፋው እሳት ያድነን🙏 በረከቱ አማላጅነቱ አይለየን🙏 እንኳን አደረሳችሁ🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
2👍 1🙏 1
Photo unavailableShow in Telegram
የኛ አባት ሚካኤል ምህረት ይለምናል🙏❤️ ቅዱስ ሚካኤል አባቴ ሆይ ጥበቃህ አይለየኝ 🙏❤️ @Finotetebebbb
Mostrar todo...
🙏 2
01:18
Video unavailableShow in Telegram
30.37 MB
Photo unavailableShow in Telegram
፮ ❤️አርሴማ ነይ ነይ ወደእኛ!🙏🙏🙏 እንኳን ለሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ አመታዊ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን! ጥበቃዋም አይለየን አሜን!🙏🙏🙏 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
2
Photo unavailableShow in Telegram
፩❤️ ቅድስት ልደታ ለማርያም❤️ የልደትሽ ቀን ልደታችን ነው!🙏🙏🙏    በረከቷ ይደርብን! የተባረከ ወር ይሁንልን አሜን! 🙏🙏🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
3👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
የልዑልን መንበር ያጥናሉ የፈጣሪን ቃል ይሰማሉ ብጹአን ካህናት(፪) ፅርዕ አርያም ያድራሉ ህዳር  ፳፬ ❤️እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ከሀያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር ሆነው የስላሴን መንበር ላጠኑበት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!   ጻድቁ አባታችን ኢትዮጵያን ይጠብቁልን! ሀዘናችንንም ያስወግዱልን! ረድኤት በረከታቸውም በኛ በኅጥዎቹ ላይ ይደርብን!!!      🙏🙏🙏🙏አሜን!🙏🙏🙏🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
4
Photo unavailableShow in Telegram
ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስ (ከ12ቱ ሐዋርያት ) "ፊልጶስም "ጌታ ሆይ አብን አሳየንና ይበቃናል አለው""። ጌታችን ኢየሱስም እንዲህ አለው "ፊልጶስ ይህን ያህል ዘመን አብሬያችሁ ስኖር አታውቀኝምን ? እኔን ያየ አብን አየ አንግዲህ እንዴት አብን አሳየኝ ትላለህ?..."ዮሐ 14:8-14 ዛሬ የሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስ በዓለ እረፍቱ ነው። በርከቱ በሁላችን ላይ ይደርብን። በአማላጅነቱም አይለየን🙏🙏🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
2👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
"ክብረ ሚካኤል ናሁ ተአውቀ በትህትናሁ አብየ ወልህቀ ዲበ አዕላፍ ዘተሰምየ ሊቀ ዘይትዐፀፍ መብረቀ ይተነብል ጽድቀ" ትርጉም፥"የሚካኤል ክብረ እነሆ አኹን ታወቀ፤ በትሕናውም ፈጽሞ ላቀ ከፍ ከፍ አለ፤ በአእላፍ ነገደ መላእክት ላይ አለቃን የተባለ መብረቅን የሚጐናፀፍ እርሱ ጽድቅን ይለምናል"መፅሐፈ ድጓ   እንኳን ለዚህ ታላቅ በዓል አደረሰን ጥበቃውም አይለየን🙏🙏🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
ደብረ ቁስቋም 👉 በደቡብ ግብፅ የሚገኝ ተራራ ነው፡፡ ደብረ ቁስቋም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲሁም ቅዱስ ዮሴፍንና ቅድስት ሰሎሜን ይዛ ከስደት ሲመለሱ ያረፉበት ቦታ ነው፡፡ 👉ይህም በቅዱስ ወንጌል እንደተጻፈ ሄሮድስ ክርስቶስን ለመግደል በፈለገ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለአረጋዊው ዮሴፍ በሕልሙ ‹‹ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ›› ባለው መሠረት የተፈጸመ ነው፡፡ (ማቴ. ፪፥፲፫-፲፭) 👉የክርስቶስ ስደቱ ቀድሞ በነቢዩ ኢሳይያስ ‹‹. . . እነሆ፥ እግዚአብሔር በፈጣን ደመና ተቀምጦ ወደ ግብፅ ይመጣል፡፡ የግብፅም ጣዖታት በፊቱ ይዋረዳሉ›› ተብሎ በተነገረው መሠረት የተፈጸመ ነው፡፡ ነቢዩ ፈጣን ደመና ያለው ጌታችን በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ጀርባ ላይ ሆኖ ወደ ግብፅ መውረዱን ለመግለጽ ነው፡፡ (ኢሳ. ፲፱፥፩) በስደቱም ጣዖታተ ግብፅ እየተሰባበሩ ሲወድቁ፤ በእነርሱም አድረው ሰውን ሲያስቱ የነበሩ አጋንንትም ሲሸሹ ታይተዋል፡፡ 👉ደግሞም ጌታችን ዳግማዊ አዳም ነውና በምክረ ከይሲ (ዲያብሎስ) ምክንያት ተሰዶ የነበረው ቀዳማዊ አዳምን ለመካስ ተሰደደ፤ በዚህም አጋንንትን ከሰው ልቦና አውጥቶ አሳደደ፡፡ 👉እመቤታችንም ልጇን ይዛ ከስደት ስትመለስ ያረፈችበትን ተራራ ደብረ ቁስቋምን ባረከችው ቀደሰችውም፤ ይህ ተራራ የተቀደሰ ተራራ ስለመሆኑ የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ታኦፊሎጎስ በድርሳነ ማርያም እንዲህ አለ፤ ‹‹ይህም ከሀገሮቹ ሁሉ ተራሮች የሚበልጥ (የተለየ) ከፍ ያለ ተራራ ነው፡፡ በውስጡ ቅዱስ አግዚአብሔር ያድራል፡፡ ይህንን ተራራ የእግዚአብሔር ልጅ ወዶታል፤ አክብሮታልምና፤ ከዓለም ሀገሮች ሁሉ ከተቀደሰች እናቱ ጋር አድሮባታልና፡፡ ከመላእክት ቤት ያድር ዘንድ አልወደደም፤ ቢታንያንም አልመረጠም፡፡ ከተራራው ላይ ባለች ገዳም ቤት ውስጥ አደረ እንጂ፤ ነቢዩ ዳዊት፤ የጽዮንን ተራራ ወደደ፤ በአርያምም መቅደሱን ሠራ እንዳለ፡፡›› 👉‹‹አንተ ተራራ ሆይ የእግዚአብሔር ማደሪያ በሆንህ ጊዜ በኪሩቤልና በሱራፌል መካከል ፍጹም ደስታ ተደረገ፡፡ የመላእክት ሠራዊት ቅዱስ የሆነ ፈጣሪያቸውንና ጌታቸውን ይታዘዙ (ያገለግሉ) ነበር፡፡ አንተ ተራራ ሆይ ያደረብህ ጌታችን ስለሆነ ከተራሮች ሁሉ ከደብረ ሲናም ይልቅ ከፍ ከፍ አልህ፤ ጌታችን በደብረ ሲና ባረፈ ጊዜ ፍጹም ደስታ፣ ታላቅ ብርሃንም በሆነ ጊዜ መቅረብና መመልከት ከሙሴ በቀር የቻለ የለም፡፡ እርሱም ቢሆን ፊቱን ማየት አልቻለም፡፡ ሥጋ ለባሽ ሁሉ እርሱን ዐይቶ በሕይወት መኖር የሚቻለው የለምና፡፡ እኛ ግን አየን፤ ከዚህ ማደሩንም ተረዳን፤ ዳግመኛም ንጽሕት በሆነች በማርያም ዘንድ አየነው፡፡ ቅድስት ከሆነች ከእመቤታችን ማርያም ዘንድ በቤተልሔም ስለ እኛ በተዋሐደው ሥጋ በጨለማና በሞት ጥላ ሥር ያለን እኛን ከቸርነቱና ሰውን ከመውደዱ የተነሣ መጥቶ አዳነን፤ ከዓለም ሁሉ ይልቅ ጣዖትን በማምለክ ሲበድሉም ወደ ግብፅ  ሀገር ወርዶ በእነርሱ ላይ የመለኮትነት ብርሃኑን በማብራት ታላቅ የሆነ ክብሩን ገለጠ››፡፡ (ድርሳነ ማርያም) 👉ኅዳር ፮ ቀንን የሚነበበው የመጽሐፈ ስንክሳር ክፍል ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግመኛም በኋላ ዘመን ሐዋርያትን በደብረ ቁስቋም ሰብስቦ፤ ታቦትንና ቤተ ክርስቲያኑን አክብሮ የቊርባን መሥዋዕትንም ሠርቶ ቅዱስ ሥጋው ክቡር ደሙን እንደ ሰጣቸው፤ እኛንም ለዚህ ክብር የበቃን እንሆን ዘንድ የእግዚአብሔር አምላክ ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን፤ አሜን🙏🙏🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
✔ተፈፀመ✔ተፈፀመ✔ተፈፀመ✔ " ሕብረ ሐመልሚል ቀይሕ ወጸአድዒድ አርአያ ኰሰኰስ ዘብሩር ተአምርኪ ንጹሕ በአምሳለ ወርቅ ግቡር ተፈጸመ ናሁ ማሕሌተ ጽጌ ሥሙር አስምኪ ቦቱ ንግሥተ ሰማያት ወምድር ከመ በሕጽንኪ ያሰምክ ፍቁር” ※     ※      ※      ※       ※       ※ የሚያብረቀርቅ ቀይና ነጭ ቀለም ያለው አርአያው የብር ዝንጒርጒር ጠቃጠቆ የኾነ ንጹሕ ተአምርሽ በወርቅ አምሳል የተሠራ ነው፤ እነሆ የተወደደ ማሕሌተ ጽጌ ደረሰ ተፈጸመ፤ የሰማይና የምድር ንግሥት ማርያም ሆይ የተወደደ ልጅሽ በጒያሽ በዕቅፍሽ እንዲጠጋ እንዲደገፍ፣ እንዲንተራስ በርሱ ዐማጽኚ። እመቤታችን ሁላችንን በምልጃዋ ከኃጢአት ወደ ጽድቅ ፣ከመርገም ወደ በረከት እንድንመለስ ቅዱስ ፈቃዷ ይሁንልን አሜን!!! እንኳን አደረሰን🙏🙏🙏 // ከሀሉም በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰሯት በአንዲት ክብርት ቅድስት ቤተክስቲያን እናምናለን // ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር!    ይቆየን! አሜን🙏🙏🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
#ተፈፀመ_ማህሌተ_ፅጌ "ናሁ ማህሌተ ፅጌ ሥሙር" "የተወደደ ማህሌተ ፅጌ እነሆ ተፈፀመ"         መዝሙር "#ንግሥተ_ሠማያት"                 ንግሥተ ሠማያት ወምድር ማርያም ድንግል(፪)                   ተፈፀመ (፬) ማህሌተ ፅጌ(፪) #ትርጉም :- የሠማይ የምድር ንግሥት የሆንሽ እመቤታችን ሆይ የአንቺ ማህሌት #ፅጌ ተፈፀመ::      #እመቤታችን_በስደቷ_ስደታችን_ትባርክልን አምላካችን የዓመት ሠው ይበለን ከማህሌተ ፅጌ በረከት ረድኤት ይክፈለን አሜን☺💒❤🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
3
Photo unavailableShow in Telegram
የማሕሌተ ፅጌ ፦ድንግል ማርያም በፍቅሯ በመቅደሱ ትሰብስበን! የብር ዝንጉርጉር የነጭና የቀይ ድብልቅ መልክ ያለው ንፁህ ተዓምርሽ በወርቅ አምሳል የተዘጋጀ ነው እነሆ ያማረ የተወደደ ማኅሌተ ጽጌ የተባለ ምስጋና መላ ተፈጸመ የሰማይና የምድር ንግስት ማርያም ሆይ ልጅሽ ወዳጅሽ በእቅፍሽ ውስጥ እንዳለ ይህንን የማሕሌተ ጽጌ ምስጋናን ተቀበይ ወደ ሰማይም አሳርጊ 🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
3
ተፈጸመ ➡️እነሆ ማህሌተ ጽጌ ልታልቅብን ነው፡፡ ቢሆንም ሊቁ አባ ጽጌ ድንግል  <ወርሃ ጽጌው ቢያልቅም በፍትሽ መቆምን አልተው >እንዳሉት መቆምን ባንተውም ቅሉ ነገር ግን የዚህች ግዜ ፍቅር ከልባችን የሚጠፋ አይደለም፡፡    ደሞም ዛሬ እንላለን <እለ ትነብሩ ተንስኡ ወእለ ታረምሙ አውስኡ ማርያምሃ በቃለ ስብሐት ጸውኡ> ስለዚ እስከዛሬ በረከቱ ያመለጣችሁ ሁሉ በአሁኑ እንዳያመልጣቺ እላለው፡፡እናም ምንም ማህሌቱን መቆም ያልጀመራችሁ ብትኖሩ "ናሁ ተፈጸመ" ሲባል አብረን ከእናታችን ስደት በረከት እንሳተፍ፡፡ ደግሞም እንላታለን "ተመየጢ  እግእዝትየ ማርያም ሀገርኪ  "የስደቱ ግዜ ይበቃል ወደ ልባችን ተመለሽ ሃጥያት ሄሮድስ ማንነታች አባሮሽ ነበርና እናታችን ተመለሽልን እንድንላት በቅኔ ማህሌቱ ቅዳሜ እንገናኝ፡፡     እግዚአብሔር አምላክ ያመት ሰው ይበለን፡🙏🙏🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
ጥቅምት ፴❤️ ነባቤ መለኮት ሐዋርያ ወሰማዕት ፣ ርእሰ ኤጲስቆጶሳት ወሊቃነ ጳጳሳት ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ የልደቱ መታሰቢያ ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው። ከእመቤታችንና ከቅዱስ ማርቆስ ከቅዱስ ዮሐንስ ረድኤት በረከት ያሳትፈን🙏🙏🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
3
Photo unavailableShow in Telegram
"አንቲ ውዕቱ ባላሂቱ ለማትያስ ላዕክ እምቤተ ሞቅህ ከማሁ እግዝእትነ ፍትህነ እማዕሰረ ጌጋይ ዘኢይትፈታ" "ሐዋርያው ቅዱስ ማትያስን ከእስር ቤት ያስፈታሽ እመቤታችን እኛንም ከማይፈታው የሀጥያት ማሰሪያ ፍቺን" የእመቤታችን አማላጅነት አይለየን🙏🙏🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
4
Photo unavailableShow in Telegram
ሊቀ-መላዕክት ከእግዚአብሔር ታዝዞ ገብርኤል መጣ ምህረትን ይዞ ድህነትን ሊሰጥ ለሰው ልጅ ሁሉ ዘምሩለት እልል በሉ ስሙንም ጥሩ ገብርኤል በሉ    ፲፱ ታላቁ ሊቀ-መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል ከምናየውና ከምንሰማው ክፋ ነገር ሁሉ ይጠብቀን! በአማላጅነቱም አይለየን! አሜን!🙏❤️🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
፲፯❤️ ሊቀ ዲያቆናት ሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ🙏❤️   በዚህች ቀን ሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ በሀዋርያት በአንብሮተ እድ ማዕረገ ድቁናን የተቀበለበት ቀን ነው።   እንኳን ለቀዳሜ ሰማዕት ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል አደረሰን! ጥበቃው አይለየን! የበረከት በዓል ይሁንልን አሜን!🙏🙏🙏 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
፲፮❤️ ኪዳነ ምህረት አምባ መጠጊያ ናት🙏🙏🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
፲፪❤️ ቅዱስ ሚካኤል፥ መኑ ከመ አምላክ (ማን እንደ እግዚአብሔር) ይህ የስሙ ትርጉም ነው።    ከመከራ ጠብቀን አባታችን ሆይ🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
🙏 2
የዚህ ሳምንት ማኅሌተ ፅጌ @Finotetebebbb
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
#ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዘይሰርር በአክናፍ/፪/ ሀበ አምደ ወርቅ /፪/ ስሙ ፅሁፍ   እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!  በረከታቸው ይደርብን! አሜን!🙏🙏🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
መስከረም ፳፱❤️ ቅድስት አርሴማ በዚህች ቀን እናታችን ቅድስት አርሴማ በንጉስ ድርጣድስ ፊት ዓይኗ ተጎልጉሎ ጡቷ ተቆርጦ አንገቷ በሰይፍ ተቆርጦ ሰማዕትነትን ተቀበለች። ከእርሷም ጋር የነበሩ ፳፯ቱ ደናግል ቅዱሳት አብረዋት ሰማዕትነትን ተቀብለዋል። ይህን አስመልክቶ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ " ሰላም ለአርሴማ ቅድስት ከመ በቀልት ዘይመስል ቆማ ወዘከለላ ወዘንፋስ ግርማ ዘፈፀምት ገድላ በፃማ ወበ መንግስተ ሰማይ አቢይ ስማ። (ገድሏን በስቃይ የፈፀመች የንፋስ ግርማ የጋረዳትና ቁመቷ እንደ ዘንባባ የሚመስል ለምትሆን ቅድስት አርሴማ ሰላምታ ይገባል። በመንግስተ ሰማይም ስሟ ታላቅ ነው።) በማለት ያወድሳታል። ከበዓሉ ረድኤት በረከት ያሳትፈን። የእናታችን የሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ አማላጅነቷ አይለየን አሜን!🙏🙏🙏 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
2
የዚህ ሳምንት ማኅሌተ ፅጌ @Finotetebebbb
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
የአምላክ እናት ሆኖ መሰደድ እንደምን ያለ ነገር ነው?...ስለ ልጇ ብላ መከራን ተቀበለች። ከበረሃ በረሃ ተንከራተተች። ረሃብ እና ጥሙ፤ የበረሃው ሙቀት፤የሽፍቶች በእነርሱ መጣላት...ብቻ ስንቱ ይነገራል?...የእርሷን መከራ ስናስብ ልባችን በሀዘን ይቆስላል። ለዛም ነው ዘማሪው፦ ስደትሽን ሳስብ ስላንቺ ልገፋ ለካ ስደት አለ ቀን በሰው ሲከፋ ወስዶ ሳያስቀርሽ ወንዝና ጅረቱ ምሳሌ ሆነሻል ድንገል ለፍጥረቱ ...ብሎ ያዜመው። እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የአምላክ እናት ሆኜ እንደምን ተሰደድኩ? እንደምን የጌታ እናት ሆኜ ይሄ ሁሉ መከራ ደረሰብኝ? አላለችም። መከራውን በጸጋ ተቀበለች እንጂ። ይሄም ለኛ አርያነት ነው። እናም መከራ ሲመጣብን በጸጋ ልንቀበል የግድ ይለናል። *ተመለሺ ሱላማጢስ* ተመለሺ ሱላማጢስ ተመለሺ እናይሽ ዘንድ ተመለሺ የአባትሽን ቤት አትርሺ አዝ... ስለ ልጅሽ ተርበሻል ጥማትንም ተጠምተሻል ድካም መንገድ እንግልቱ እንዴት ቻልሽው አዛኝቱ መሰደዱ ይበቃሻል ቅድስት ሀገር ይሻልሻል አዝ... የበደሌ ሸክም በዝቶ ብሰደድ ስንቄ ጠፍቶ በይ መልሽኝ ከደጃፍሽ በክንዶችሽ እቅፍ አርገሽ በአለም ስጓዝ አንቺን ትቼ ከኔ ርቆ ፍቅር ጣዕምሽ በበደሌ በኃጥያቴ ዛሬ እንኳን ብሸሽ ተመለስ በይኝ እመቤቴ በእናትነትሽ እንኳን ለጾመ-ፅጌ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን! የበረከት ጾም ይሁንልን! በሰላም አስጀምሮ በሰላም ያስፈጽመን!! @Finotetebebbb
Mostrar todo...
4
Photo unavailableShow in Telegram
መስከረም  ፳፬   እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ወርሃዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!   ጻድቁ አባታችን ኢትዮጵያን ይጠብቁልን! ሀዘናችንንም ያስወግዱልን! ረድኤት በረከታቸውም በኛ በኅጥዎቹ ላይ ይደርብን!!!      🙏🙏🙏🙏አሜን!🙏🙏🙏🙏 @Finotetebebbb
Mostrar todo...
👍 2 2
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.