521Suscriptores
Sin datos24 hours
-77 days
-1530 days
- Suscriptores
- Cobertura postal
- ER - ratio de compromiso
Carga de datos en curso...
Tasa de crecimiento de suscriptores
Carga de datos en curso...
Mostrar todo...
DroJob | Get paid doing simple tasks
Make money online by watching ads, filling out surveys, sharing your opinion, solving captcha, answering questions and more.
👆😆እሪ ብዬ ጮኩ😆👆
ኢትዮጵያ ሀገራችን ካፈራችው መንገድ
አንድ መንገድ አለ ሁሌ መገድምበት
ከቤቴ ስወጣ ስመለስም ሆነ
ይችን መንገድ ማለፍ
ምርጫዬ ግድ ሆነ
በዛ ስመላለስ ያየኝ ሰው በሙሉ
ጓደኛው መስዬው ሰላም ነህ ይላሉ
እኔም በተራዬ አፀፋውን መልሼ
መንገዴን ስቀጥል የሱስ አለህ ጋሼ
የሚል ድምፅ ይመጣል ከወደ ኃላዬ
በዚህ እድሜ ብትሰራ
ለኔም በሰጠኸኝ የሚበላ እንጀራ
ብዬ የበኩሌን ምክር መሳይ ቁጣን
ከሰጠሁ በኃላ መንገዴን ጀመርኩኝ ደግሞ እንዳይጠንቀኝ
ልጁም በበኩሉ ግብራበር ሰብስቦ
መንገዴን ዘጋብኝ ግራ ተጋባውኝ
እነዚህ ጠብደሎች ሁለት እጄን ይዘው
አንዱ በጥፊ ሲል አንዱ ኪስ ሲገባ
በመሀል ከተማ ግራ እስክጋባ
አየር ለመተንፈስ አፌ ሲለኝ እንቢ
ከነሱ ስታገል ለነብስ ውጪ ግቢ
እጅኩን ደከምኩኝ ተስፋዬን ቆረጥኩኝ
የግዴን አምጬ እየተፍጨረጨርኩኝ
ባለኝ በሌለኝ ሀይል እሪሪሪ ብዬ ጮኩ!!
Note;አርዕስቱ ገጣሚው በማላስታውሰው ከሌላ ግጥም ላይ የተወሰደ ነው።
@Bekiwdu
👍
✝ዛሬም ፋሲካ ነው✝
@lelasw
በሕግ ተወጥሬ - በኀጢአት ታስሬ
ከፅድቅ ተገፍቼ - ለኩነኔ ሞቼ
ለድካም ዘብ ቆሜ - ቀንበር ተሸክሜ
ምርኩዜ ሸንበቆ - የሚሰበር ወድቆ
ፍሬ የሌለበት - በደረቅ ሰውነት
በጨለማ ህይወት - በድንግዝ መሰረት
ሁሌ እንደሚናፍቅ - እንደሚሻ ልቡ
ከከነሀን ወተት - የግብፅን ባርነት
የሶስቱን ቀን መንገድ - አርባ እደሆነበት
እንደዛ ነበረ - የሁላችን ህይወት
@lelasw
ይህን ተመልክቶ - አልችል ቢለው ልቡ
እንደተስፋ ቃሉ - ሊታደገን ወዶ
ከሰማይ ሰማያት - ከዙፋኑ ወርዶ
እኛኑ ሊያነፃ - ሊታደገን ወዶ
በሸላቾቹ ፊት - ቃልም አላወጣ
እሱ ፃድቅ ሳለ - ቀንበር የበዛብን
እኔና እናንተን - ነፃ ሊያወጣ
የእግዚአብሔር ልጅ እሱ - እኛን መስሎ መጣ
@lelasw
ይሄ ሆኖ ሳለ - በመስቀል መሞቱ
ሞቱን የአንድ ቀን - እያደረጋቹ እንዳትሳሳቱ
እለት እለት እንጂ - መዳን የሚሆነው
ለአንድ ቀንማ - ለአንድ ለሊትማ
አይደል መጠረቁ - ኀጥያት መውሰዱ
ለዘመናት መርገም - ነውንጂ መሞቱ
እርቃኑን በስቃይ - በመስቀል መዋሉ
አይደለም የአንድ ቀን - እውነት አታብሉ
@lelasw
እርግማን ስለኛ - የሆነው መድህኔ
ህይወትን ሊቸረን - ፅድቅን ሊያስታጥቀን
መሀዛ ጠረኑን - ለኛ ያለበሰን
በህይወት ሊቀይረው - እንዳዲስ ሊያስውበው
መች ሆነ የአንድ ቀን - የመስቀል ላይ ስራው
ለአዲስ ኪዳን ትዉልድ - መስቀሉን ለያዝነው
በእየሱስ ስራ - ዘመን ለተቸረው
በክርስቶስ አምነን - በስሙ ለዳንነዉ
ልጁ የሞተበት - ደም የፈሰሰበት
አትርሱ አስታውሱ - ዛሬም ፋሲካ ነዉ!!
@lelasw
✝ ✝
😍😍😍😍 ተባረኩ 😍😍😍😍
✍በረከት አለማየሁ
@Bekiwdu ...... ☺️☺️☺️
👍
😘😘ባልኩልሽ😘😘
@lelasw @lelasw
ፍቅር ላንቺ ቃላት ጠፋ
መውደድ ላንቺ ቅኔ ታጣ
የቅርፅሽን ውበት ገልፆ የሚያወጣ
የሰራ አካላትሽን ጥበብ የሚያወራ
አንዳች ቅኔ ጠፋ አንቺን የሚያብራራ
ያ ወለላ ከንፈር በምን ይገለፃል
ያ ተክለ ሰውነት እንዴት ይተረካል
ያ ተረከዝ ባትሽ በምን ይናገራል
እንኳን ጎረምሳውን ቄሱን ያስከጅላል
@lelasw
እነዛ ወይዛዝርት አንቺን ሲሳደቡ
ወይባ እየታጠኑ ሂና እየተቀቡ
ያንቺ ውበት ደብዝዞ እነሱ ሲያብቡ
ቃላት ጠፍቶኝ እንጂ አይደለም ፈርቼ
ያልተደባለቀ የተፈጥሮ ውበት አንቺ ላይ አይቼ
በሀገሬም እንዳለው የተፈጥሮ ውበት
ያልተቀላቀለ የእግዜር ሸማ ጥለት
እንደ ፀደይ ዘመን እንደብራው ወራት
እንደ እቡጥ አበባ የፈካ አካላት
እንደ አባይ ጅረት እንደ እጣን ጢሱ
ባልኩልሽ ውበትሽን ለሚያንኳስሱ!!
@lelasw @lelasw
✍በረከት አለማየሁ(ቤኪ ውዱ)
@Bekiwdu.......😍😍😍
👍
@Lelasw
ስኮትላንዳዊውና እንግሊዛዊው ዱር ውስጥ እየተንሸራሸሩ ሳሉ አንበሳ ከፊት ለፊታቸው ሲመጣ አዩ። ይኼኔ ስኮትላንዳዊው ያደረገውን ትልቅ የቦት ጫማ በፍጥነት አውልቆ ቀለል ያለ ሸራ ጫማ ማጥለቅ ጀመረ።
<<ይኼ ምን ይጠቅምሃል ወዳጄ??>> አለ እንግሊዛዊው በመገረም <<መቼም አንበሳን ሮጠህ ማምለጥ አትችልም??>>
<<ልክ ነህ እሱንማ አልቀድመውም
አንተን ግን እቀድምሃለው>>። አለው አሉ
አረፈዓይኔ ሐጎስ (የስኮትላንዳዊያን ቀልዶች 2005)
👇👇
https://t.me/Lelasw
ሌላ ሠው
ሁሉም ሠው ሌላ ሠው ሌላውም ሠው አንደኛው ሠው ነው፡፡
👍