cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

ISLAM IS UNIVERSITY

⭐️ሰው የሚገነዘብ አእምሮና የሚያፈቅር ልቦና ባለቤት ነው።እነዚህ ሁለቱ ካልተመጣጠኑ ስብእናው አደጋ ውስጥ ነው።የሚያገናዝበው አዕምሮው፣የሚያፈቅረው ልቡ፣የሚንቀሳቀሰው አካሉናወደ ሰማይ የሚወነጨፈው መንፈሱ በውህደት ካልተንቀሳቀሱ ሰውየው ላይ ችግር አለ ማለት ነው 📨የፍቅር እና የጥላቻ ስሜቱ፣የፍላጎት እናየፍርሃት መንፈሱ በአዕምሮ ብስለት ካልተገራ አስቸጋሪ ነው አስተያየት👇 T.me/Aisuu_bot

Mostrar más
Advertising posts
19 299Suscriptores
-624 hours
-367 days
-17630 days

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

የረመዳን ተአምራት እና ዮሺኖሪ ************************* በ አውሮፓያኑ አቆጣጣር 2016 የ አለማችንን ትልቁን ሽልማት Nobel Prize in Physiology or Medicine ሽልማት ያሸነፈው ፊዚዮሎጂስት Yoshinori Ohsumi ነው። ያሸነፈውም የ ሰውነትን controlled autophagy “የጽዳት ዘመቻ” ሳይንስ በድንቅ ምርምር ከደረሰበት በኋላ ነው። ታድያ ይህ ድንቅ ሰው የሰራው ስራ ስለ ረመዳን ጾም የተለየ ግንዛቤን የፈጠረ ነበር። እናብራራው... የሰው ልጅ ለ 12 ሰአትና ከዚያም በላይ ብቻ ከጾመ "ኦቶፋጂ" (autophagy) በመባል የሚታወቀውን የሴል ሂደት ለመጀመር ያስችለዋል። ይህን ሂደት "የ ሰውነት የጽዳት ዘመቻ" በማለት ልንጠራው እንችላለን። እናም በዚህ የ "ኦቶፋጂ ጽዳት ዘመቻ በ ሰውነት በየቦታው የወዳደቀ ፕሮቲን (Damaged protein) የተበላሹ ሴሎችን ሳይቀር በሙሉ ጠራርጎ በማቃጠል ያስወግዳል። በተፈጥሮ ያረጁ ሴሎች በ ህይወት እያሉ በምትካቸው ወጣት ሴል አይመረትም። ለምሳሌ ይህንን ሁኔታ በ መከላከያ ሴሎች (Immune system) አንጻር ብናይ የሰውነት ባረጁ ሴሎች መሞላት ተጸኖው ቀላል አይደለም። ሽማግሌ ፖሊስ ከሌባ እንደማያስጥለው ሁሉ ሽማግሌ የ መከላከያ ሴልም ከ በሽታ አያድንም። አንድ ሰው 12 ሰአት ጾም ሲጾም ሰውነት የ ምግብ ጉድለቱን ለመሙላት ሲል ሽማግሌ ሴሎችን ገድሎ ለምግብነት ይጠቀማቸዋል (ይበላቸዋል) (ሰው በተፈጥሮ የሚከሳው የራሱን አካል በልቶ ነው)። ሆኖም ስናፈጥር (ስንበላ) አዲስ ንቃት ያለው ወጣት ሴል እንዲፈጠር እድል ይሰጣል (immune cell recycling) ። በዚህም ሂደት ሁሉም ሴል ሲታደስ በዛውም የመከላከያ ሚኒስተር ታደሰ ማለት ነው። ያማለት የበሽታ መከላከል አቅም በ ጾም ምክኒያት ተሻሻለ ማለት ነው። ይህ ሂደት ሴሎች የራሳቸውን ክፍሎች የሚያድሱበትና እንደገና ጥቅም ላይ እንዲውሉ የሚያደርግም የተፈጥሮ አሠራር ነው።ይህ ሂደት በተለይ ኒውሮዲጀነሬቲቭ ሁኔታዎችን ካንሰርን ጨምሮ ገዳይ በሽታዎችን በመከላከል ረገድ ከፍተኛ ሚና ሊጫወት ስለሚችል ለሰው ልጅ እጅጉን አስፈላጊ ነው ።ይህም ሴሎችን ለመጠገንና ለማጽዳት የሚረዳ ከመሆኑም በላይ ለረጅም ዕድሜና እርጅናንም ለመከላከል ተጽእኖ አለው። እጅግ የሚገርመው ሰውነት autophagyን ለመጀመር በትንሹ ለ12 ሰዓት እና በላይ ያህል ይፈልጋል። ከሃይማኖት ጾም አንጻር ስናየው ከእስልምና ጾም ጋር ብቻ ትይዩ ነው (ፊጥራ)። ዛሬ ላይ ፈረንጆች እንደ ጤናማ ባህል promote እያደረጉት ነው።ዩሽነሪ በሽልማቱ ለጋዜጠኞች ስለ autophagy ሲያብራራ ጾሙ ለ4 ሳምንት ሲተገበር እጅግ የተዋጣለት ይሆናል። እናም አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ በጤና እንድንከርም በ ፊጥራ ይህንንም ሲስተም በዓመት አንድ ጊዜ ሰውነት ላይ ለአንድ ወር እንዲካሄድ የወሰነለት ሀቅ ይሆን እያልን ተገረምነ 😍😍😍 “ተባረከላሁ አህሰኑል ካሊቂን” አልን። ፎቶው የ ፕሮፌሰር Yoshinori Ohsumi ነው።
Mostrar todo...
26👍 9
👍 2
በአንድ እጁ ቁራጭ ብስኩት በሌላኛው እጁ ደግሞ የሽንት መሽኛ ከረጢጥ ተሸክሞ ኩላሊቱን እስኪታጠብ ተራውን እየጠበቀ በሆስፒታሉ ውስጥ ይንከራተታል። በሆስፒታሎች ውስጥ ሌላ ዓለም አለ ስለ ዱኒያ ፍቅር, ምኞት, ገንዘብ አያወሩም ጤናን ብቻ ይጠይቃሉ. አምላኬ ሆይ ታካሚን ሁሉ ፈውስ ያረብ!! . . ስላለህ ነገር ሁሌም አመስጋኝ ሁን ኢላሂ ምህረትህን ጌታዬ በሽታ ላደከመው ሁሉ🙏
Mostrar todo...
👍 37😢 1
🐝 የማር ነጋዴ አንድ የቆምጣጤ ነጋዴን እንዲህ ብሎ ይጠይቀዋል: ሰዎቹ ምን ሆነው ነው ካንተ እየገዙ እኔን ትተው የሚያልፉት ብሎ ጠየቀው !! ነጋዴው እንዲህ አለው አንተ የምትሸጠው ማር ነው ግን ምላስህን እንደቆምጣጤ ነው ምትጠቀመው እኔ የምሸጠው ቆምጣጤ ነው ግን ምላሴን ምጠቀመው እንደ ማር ነው ብሎ መለሰለት!! መልእክት : ሰዎችን በስነምግባርህ ተቆጣጠራቸው ¡¡
Mostrar todo...
👍 13
ፌሚኒስቶችን ጠይቃቸው ፦ == «አይፎንን በአንድሮይድ የአጠቃቀም መመሪያ (Manual) ወይም አንድሮይድን በአይፎን (አይ ኦ ኤስ)  Manual መጠቀም እንችላለን? » መልሳቸው አጭር ነው ፦ «አንችልም» ። ሁለቱም የስልክ ምርቶች ለተመሳሳይ አላማ የተፈበረኩ መሆናቸውን ያምናሉ።ነገር ግን አፈጣጠራቸው የተለያየ የአጠቃቀም መመሪያ እንዲወጣላቸው አስገድዷል። ፌሚኒስቶች ይህን ሐቅ ለአላህ ሲሆን የማይቀበሉበት ምክንያት አይገባኝም። አላህ ጀለ ጀላሉህ ወንድና ሴትን በተስተካከለ ቁመና ላይ ለአንድ አላማ ፈጥሯቸዋል። በአፈጣጠራቸውም ልክ መብትና ግዴታቸውን አለያይቶ ደንግጓል። የአንዱን መብትና ግዴታ  ለሌላው መስጠት በደል ነው። ለተለያዩ አፈጣጠሮች ተመሳሳይ ማንዋል እንጠቀም ማለትም ነው። ሴት ልጅ ከወንድ እኩል ናት በሚለው መፈክራቸው መብቷን እንዳስከበሩላት ይሞግታሉ። ነገር ግን ከወንድ ልጅ እኩል ነች ሲሉ የወንድን ግዴታም እያሸከሟት መሆኑን መቀበል አይፈልጉም። ለዚህም በሴት ላይ የሆነ በደል ሲከሰት «እንዴት ሴት ላይ ይህ ይፈፀማል?!» በማለት መልሰው ይጮሃሉ። ውስጣቸው በውጭ የሚያስተጋቡትን አቋም መልሶ ስለሚፃረረው ነው። እኩል ናቸው ብለው ካመኑ «እንዴት በሴት ላይ?» ብለው መጮህ አልነበረባቸውና!  ፌሚኒዝም ሀሰትን እውነት በማስመሰል እልኸኝነት ላይ የተመሰረተ ቆሻሻ እምነት ነው። የሰው ልጅ ያመረተውን እቃ ካምራቹ በላይ ስሪቱን አናውቅም በማለት ማኑዋሉን አክብረው ይጠቀማሉ። በትንሹ በሳምሰንግ ኬብል አይፎንን ቻርጅ አያደርጉም፤ አይሞክሩትምም።ስለማይሆንም ስህተት ነው ብለው ያምናሉ። የሰው ልጅን አስተካክሎ የፈጠረው አላህ ለፈጠራቸው ፆታዎች ያስቀመጣቸው መብትና ግዴታዎች ላይ ግን ጥያቄ ያነሳሉ፤ ይከራከራሉ! ለመሆኑ አላህ ወይስ እናንተ ናችሁ አዋቂዎች? አላህን ስለፈጠረው ነገር ልትከራከሩት ትፈልጋላችሁ?  «እናንተ ታውቃላችሁን? ወይንስ አላህ?» በላቸው፡፡ (አልበቀራህ 140) ነገሩ  ያለው ወዲህ ነው። እርሱም አላህ ወንድን ሲፈጥረው በጥንካሬ፣ በብርታትና ልፋትን በመቻል (በመቋቋም) ላይ እንዲሁም በማስተዳደር ሃላፊነት ሹመት ላይ ነው። ሴትን ደግሞ በልስላሴና በድካም ላይ ነው። ለዚህም አላህ ወንድን በሴት ላይ አብልጦታል። አላህ በተከበረ ቃሉ እንዳለው ፦ «ወንዶች በሴቶች ላይ ቋሚዎች (አሳዳሪዎች) ናቸው፡፡ አላህ ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ በማብለጡና (ወንዶች) ከገንዘቦቻቸው (ለሴቶች) በመስጠታቸው ነው፡፡» (አን ኒሳእ 34) የአላህ መልእክተኛ (ሰዐወ) እንዲህ ይላሉ፦ « አላህ ሆይ!  የሁለቱን ደካሞች ሐቅ ማጓደልን ወንጀል አድርጌያለሁ ፤ የቲምና ሴትን» (ነሳኢይ) ይህን የአላህ ህግ የጣሰ ፍልስፍናና አስተሳሰብ ሁሉ ውድቅና የጥመት አስተሳሰብ ነው። ፌሚኒዝምን ኢስላማዊ አድርገው በሚያቀርቡ ደናቁርቶች ልንሸወድ አይገባም ። አላህ ይምራን! Ismaiil Nuru
Mostrar todo...
👍 20 1
ዩሱፍ ጠፋ አባቱም የ ዓይን ብርሃኑን አጣ..!! ●ጉዳዮቼን ሁሉ ወደ አላህ አስጠጋለሁ ብሎ በተናገረ ሰዓት ግን  ....ዩሱፍንም አገኘ የ ዓይን ብርሃኑም ተመለሰለት!! . . ጉዳያቹን ሁሉ ወደ አላህ አስጠጉት ከዛማ ልክ እንደ ነቢዩላህ ያዕቁብ  መፍትሔን ታገኛላችሁ
Mostrar todo...
👍 21 5
ልክ ሚሽነሪዎች መጥተው በጥቅማ ጥቅም ሙሥሊሙን ሲያከፍር ዋይ ዋይ ከማለት ይልቅ ተምሮ ቅድመ ዝግጅት ማድረጉ አያዋጣምን? "ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ" የሚል አገሪኛ ብሒል አለ። ቀድመን አለመንቃታችን ዋጋ ያስከፍለናል። ከአፋር ክልል ከሱማሌ ክልል ከትግራይ ክልል መማር የምትፈልጉ ሙሥሊሞች እባካችሁ ገብታችሁ ተማሩ! ለመግባት ከታች የተዘረዘሩት አድሚናት በውስጥ ያናግሩ! ወንድም አቡ ኑዓይም፦https://t.me/arhmanu እኅት ሰላም፦ http://t.me/SeuweSe አኅት ዘሃራ፦ https://t.me/Zhara_mustefa እኅት አበባ፦ http://t.me/selemtewa
Mostrar todo...
👍 11
የቀለበት አደራረግ ሴት ልጅ የወርቅም ይሁን የብር ቀለበት በፈለገችው ጣት ላይ ማድረግ ትችላለች። ነገር ግን ቤት ውስጥም ይሁን ከቤት ውጪ ስትሆን ጌጧን ባዕድ/አጅነቢይ ወንድ እንዳያይ ጌጡን መሸፈን ግዴታ ይሆንባታል። ይህም የቁርኣን ህግና ትእዛዝ ነው። ወንድ ልጅ ግን የወርቅ ቀለብት ማድረግ አይችልም። ከወርቅና ከብረት ውጪ ካሉ ነገሮች የተሰራ (የብርም ይሁን ሌላ) ቀለበት ሲያደርግ በመጨረሻው ትንሹ ወይም ከሱ ቀጥሎ ባለው ጣት እንጂ በመሃለኛው ረጅሙ ጣት፣ ከሱ ቀጥሎ ባለው ሌባ (አመልካች) ጣትና አውራ ጣት ላይ ለወንድ ልጅ ቀለበት ማድረግ አይቻልም። በተለይ በመሃለኛው ረጅሙ ጣትና ቀጥሎ ባለው አመልካች ጣት ላይ ቀለበት ማድረግን ነቢዩ صلى الله عليه وسلم በግልጽ ከልክለዋል። ከመሆኑም ጋር ብዙ ወንዶች በነዚህ ጣቶች ቀለበት ሲያደርጉ ይታያል። ዲናችንን እንወቅ! እውቀት ብርሃን ነው፤ አላዋቂነት ጨለማ ነው። ኡስታዝ አሕመድ ኣደም
Mostrar todo...
👍 33 9
قَالُوا إِنَّا كُنَّا قَبْلُ فِي أَهْلِنَا مُشْفِقِينَ فَمَنَّ اللَّهُ عَلَيْنَا وَوَقَانَا عَذَابَ السَّمُومِ [አጥ-ጡር 26-27] “እኛ ፊት በቤተሰቦቻችን ውስጥ (ከቅጣት) ፈሪዎች ነበርን” ይላሉ። “አላህም በእኛ ላይ ለገሰ። የመርዛም እሳት ቅጣትንም ጠበቀን።”  ««የአላህ ፍርሃት ልብ ውስጥ ከሰፈረ፣የስሜታዊ ዝንባሌዎችንና የቁሳዊ ፍላጎቶችን ሰፈሮች አቃጥሎ ዱንያን ከልብ ያስወጣል። አላህም በዕለተ-ቂያማ የአርሽ ጥላ እንጂ ሌላ ጥላ በሌለበት ወቅት በዚሁ ጥላ ከሚጠለሉት ሰዎች መካከል ያደርገዋል። ورجل دعته امرأة ذات منصب وجمال فقال: إني أخاف الله “አንድ ሰው አንዲት በዘሯ የተከበረችና ውበት ያላት ሴት ለብልግና ስትጠራው እኔ አላህን እፈራለሁ ያለው ነው” ««አላህ ለሚጠነቀቀው ሰው መሃሪ ነው፣ በወንጀል ላይ ዘውትሯ አላህ ፊት መቆምን ለፈራና ለተፀፀተ ምህረቱ ብዙ ነው።
Mostrar todo...
👍 9
Inicia sesión y accede a información detallada

Te revelaremos estos tesoros después de la autorización. ¡Prometemos que será rápido!