cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

TIKVAH-ETHIOPIA

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

Mostrar más
Advertising posts
1 340 953Suscriptores
+55824 hours
+3 1737 days
+28 72930 days
Archivo de publicaciones
📱 ባይትዳንስ ' #ቲክቶክ ' ን #ለአሜሪካ ከመሸጥ አሜሪካ ውስጥ #ቢዘጋው እንደሚመርጥ ሮይተርስ ለኩባንያው ቅርብ የሆኑ ምንጮችን ዋቢ አድርጎ ዘገበ። ኩባንያው በ' ቲክቶክ ' ጉዳይ እስከመጨረሻው ያሉትን የህግ አማራጮችን ተጠቅሞ እንዳይታገድ ማድረግ ካልቻለ ፤ ለአሜሪካ ከመሸጥ ይልቅ እስከመጨረሻው #መዝጋት ይመርጣል ተብሏል። አሁን ' ቲክቶክ ' የሚሰራበት #አልጎሪዝም ለኩባንያው እንደ ዋናው ነገር እንደሚቆጠርና በዚህ አልጎሪዝም መተገበሪያውን የመሸጥ እድሉ እጅግ ሲበዛ አነስተኛ እንደሆነ የኩባንያው ምንጮች ገልጸዋል። በዚህም ፤ ለአሜሪካ ገዢ ከመሸጥ አሜሪካ ውስጥ እስከወዲያኛው ድረስ መዝጋትን እንደሚመርጥ ተጠቁሟል። አሜሪካ ' ቲክቶክ ' እንዲሸጥ ከ9 ወር እስከ 1 ዓመት ገደብ አስቀምጣለች ካልሆነ ግን እስከ ወዲያኛው እንዲታገድ ሕግ አጽድቃለች። በርካታ ጉዳዩን የሚከታተሉ የዘርፉ ሰዎች አሁን ባለው የአሜሪካ አቋም 170 ሚሊዮን ተጠቃሚዎች ያሉት ' ቲክቶክ ' እስከ ወዲያኛው ድረስ የመወገዱ ነገር እውን መሆኑ አይቀርም ብለዋል። @tikvahethiopia
Mostrar todo...
👏 350 91😡 19🥰 11😭 11🤔 7🙏 7😢 4🕊 4😱 2
#ATTENTION🔔 በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፤ ወላይታ ዞን ባሉ ወረዳዎች ያሉ መምህራን ከደመወዝ ጋር በተያያዘ ስራ እንዳቆሙ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር ፕሬዝዳንት አማኑኤል ጳውሎስ ፦ " ... ጉዳዩ ስር የሰደደና የቆየ ነው። አሁን ላይ ' በተራበ አንጀታችን መስራት አልችልም ' በሚል መምህራኑ ስራ አቁመዋል። በፐርሰንት እየተቆራረጠ የሚከፈላቸው ደመወዝ በዚህ ወር ለ16 ቀን ዘግይቷል። ከደመወዝ በላይ የሌሎች ጥቅማጥቅሞች ፥ የወዝፍ ደሞዝ ፣ ከደረጃ እድገት ጋር ተያይዞ የሚመጣ የደሞዝ ጭማሪና የእርከን ጭማሪ መቅረት ፈተና ሆኖባቸዋል። " ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ተጨማሪ መረጃዎችን ይልካል። ከዚህ ቀደም ወላይታ ዞን ስለሚገኙ መምህራን ቅሬታ የቀረበ ፦ https://t.me/tikvahethiopia/86484?single @tikvahethiopia
Mostrar todo...
😢 277 48👏 34😡 29😭 18🥰 16😱 7🙏 7🕊 7🤔 1
#ኢትዮጵያ " የስፖርት ውርርድ / የቤቲንግ ቤቶች #ሊታገዱ ይገባል " ሲል የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር አሳሰበ። ሚኒስቴሩ ዛሬ የ9 ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ለተ/ም/ቤት አቅርቦ ነበር። በዚህ ወቅት ፤ " የወጣቶች ሱሰኝነት በሀገር ደረጃ እየተባባሰ መጥቷል ፤ በተለይ አሉታዊ መጤ ልማዶች እና አደንዛዥ ዕጽ እንደ ሀገር እየተስፋፋ መጥቷል " ሲል ገልጿል። ይህም ብዙ ወጣቶችን እያሳጣን ነው ሲል አስረድቷል። ወጣቶች ሰብዕና ግንባታ ላይ ተግዳሮት እየፈጠረ ከሚገኘው አንዱ የስፖርት ውርርድ እንደሆነ ያመለከተው ሚኒስቴሩ " የስፖርት ውርርድ ለሀገሪቱ ከሚያስገባው ገቢ አኳያ ብቻ መታየት የለበትም " ብሏል። " ' ስፖርት ቤቲንግ ' ላይ ያሉት፣ ካሁን በፊት የወጡት መመሪያዎች፣ ደንቦች፤ ጥናትን መሰረት አድርገው ሊታገዱ ይገባል " ሲል ገልጿል። ፓርላማውም በዚህ ረገድ እገዛ ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስቧል። " ገቢ አንድ ነገር ነው። ሀገር ገቢ ማግኘት አለባት " ያለው መ/ቤቱ ነገር ግን ፦ ➡️ በወጣቶቹ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያስከተለ ስለሆነ፣ ➡️ ብዙ ወጣቶች እያሳጣ ስለሆነ፣ ➡️ ብዙ ቤተሰብም #እየፈረሰ ስለሆነ ሊታገድ እንደሚገባ ገልጿል። በህ/ተ/ም/ቤት የጤና ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ፤ " ብሔራዊ ሎተሪ ከገቢ ጋር አይቶታል። በዚህም በኩል ደግሞ ሌላ ችግር እየፈጠረ ነው " ያለ ሲሆን " ተማሪዎች ዩኒፎርማቸውን እያወለቁ የስፖርት ውርርድ ቤት ይገባሉ። ስለዚህ መቼ ያጥኑ። አእምሮአቸው ሊጎዳ ስለሚችል ጥንቃቄ ተደርጎ መሰራት አለበት " ብሏል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስፖርት ውርርድ ላይ በተሰማሩ አገልግሎት ሰጪዎች ላይ በቅርቡ የወሰደውን እርምጃ " ጥሩ ስራ " ሲል አወድሷል። በሌሎች አካባቢዎች በተሞክሮ ሊወሰድ ይገባል ሲል ጠቁሟል። የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴርም ፤ ከስፖርት ውርርድ ጋር በተያያዘ ያለውን የወጣቶች ሁኔታ የወደፊት የትኩረት አቅጣጫ አድርጎ እንዲያየው እና ጠንካራ ክትትል እንዲያደርግ መክሯል። ከዚህ ቀደምም የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የስፖርት ውርርድ / ቤቲንግ / ' #ቁማር ' ነው ብሎ እንደሚያምን ገልጾ እንዲታገድ ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል። የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ግን ፤ " ቤቲንግ " ' #ጨዋታ ' እንጂ ' ቁማር ' ነው ብሎ እንደማያምን ገልጾ ነበር። ቤቲንግ አትራፊና ብዙ ወጣቶች ስራ እንዲያገኙ ያደረገና በከፍተኛ ሁኔታ ገንዘብ እንዲንቀሳቀስ የሚያደርግ መሆኑንም አስረድቶ ነበር። በስርዓት እንዲመራም መመሪያዎች ወጥተውለት እየተሰራ መሆኑን በመግለጽ " እኛ ጨዋታውን አቅርበናል ተጫዋቹ ደግሞ በኃላፊነት መጫወት አለበት " ሲል ነበር የመለሰው። @tikvahethiopia
Mostrar todo...
#AddisAbaba አዋኪ ድርጊት በሚፈፀምባቸው ንግድ ቤቶች ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል። ሰሞኑን በቦሌ ክፍለ ከተማ ከ3 ሺህ 80 የሺሻ ዕቃ እና 80 ኪሎ ግራም አደንዛዥ ዕፅ ተይዞ መወገዱን ገልጿል። በህጋዊ ንግድ ሽፋን ሺሻ እና አደንዛዥ ዕፅ ሲጨስባቸው ከተገኙ ቤቶች ነው ይሄ የተያዘው። ፖሊስ በሰጠው መረጃ በድንገተኛ ቁጥጥር ከተደረገባቸው መካከል ፦ - መኖሪያ ቤቶች -  ፔንሲዮኖች፣ - ማሳጅ ቤቶች እና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ይገኙበታል፡፡ ይህ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል። ከዚህ ጋር በተያያዘ በተለይም በአዲስ አበባ በጋራ መኖሪያ ቤቶች ያለው አዋኪ ድርጊት እጅግ ትኩረት የሚሻ እንደሆነ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቤተሰቦቹ የደረሰው መልዕክት ያስረዳል። በተለይ ተማሪዎች፣ ህፃናት፣ የወለዱ እናቶች፣ ቀን ስራ ደክመው የሚገቡ በርካታ ዜጎች ባሉባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ ብዙ አዋኪ ድርጊቶች በመኖራቸው ትኩረትን ያሻል። የግል መኖሪያ ቤቶች ለሺሻ ማጬሻ ፣ ለመጠጥ መጠቻ፣ ለሲጋራ ማጬሻ እየዋሉ ማህበረሰቡ እንደሚታወክ ተጠቁሟል። ምሽት ላይም ቢሆን ከጭፈራ ቤቶች የሚወጣው ድምጽ ማህበረሰቡን ሰላም የሚነሳ በመሆኑ ቁጥጥር እንዲደረግ ተጠይቋል። #TikvahFamilyAddisAbaba @tikvahethiopia
Mostrar todo...
“ ... 1,500 ካ/ሜ ግሪን ኤርያውን 12 ወጣቶች መጥተው አጠሩት ” - ቅሬታ አቅራቢዎች በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፤ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 አካባቢ በሚገኘውና በ1979 ዓ/ም ለ “ አዲስ አበባ 100ኛ ዓመት ቤት ሥራ ማኀበር ” ተሰጥቶ ነበር የተባለ 1500 ካ/ሜ መሬት የመከነ ማስረጃ ባቀረቡ ሰዎች መታጠሩን ማኅበሩ ገለጸ። ቦታው በ1979 ዓ/ም ለማኀበሩ ከተሰጠ ጊዜ ጀምሮ “ የአዲስ አበባ 100ኛ ዓመት ግሪን ኤሪያ ” እየተባለ ይጠራ እንደነበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድቷል። “ በፊት የአዲስ አበባ 100ኛ ዓመት ግሪን ኤሪያ ነበረ። በኋላ ‘ የአካባቢው ማህበረሰብ ይጠቀምበት ’ ተባለ ” ብሏል። በዚህም የማኀበሩ አባላት በግንብ እንዳሳጠሩት ፣ ጥበቃም ቀጥረው ጥበቃ ያስደርጉለት እንደነበር ፣ ቦታው ላይ የተለያዩ ስራዎችን ለመስራት የሚመለከታቸውን አካላት ቢጠየቅም ፣ “ ለጊዜው ቆዩ ስንወስንላችሁ ትሰራላችሁ ” ተብለው እየጠበቁ እንደነበር ገልጿል። ይህ በሆነበት ግን ወጣቶች መጥተው ቦታውን እንዳጠሩት ቅሬታ አቅራቢዎቹ ገልጸዋል። ማኀበሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፥ “ ጥበቃውም ሰሞኑን ጥሎ ሄደ አስገድደውት ይሁን ተስማምቶ ይሁን አናውቅም። ልክ እሱ እንደሄደ 1,500 ካሬ ግሪን ኤሪያውን 12 ወጣቶች መጥተው አጠሩት ” ብሏል። ማኅበሩ እጄ ላይ አሉ ያላቸውን ዶክመንቶችም ልኳል። “ ‘አረንጓዴው እንዳይሸፈን’ ብለውን እኛ ባጭሩ በግንብ አጥረን ከላይ ብረት አድርገንበት ነበር ” ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎች ፥ “ አሁን ግን እነርሱ ሙሉ ለሙሉ #በቆርቆሮ ግጥም አድርገው አጠሩት ” ብለዋል። አክለው “  2 ጊዜ ፎርጂድ ካርታ አሰርተውበት የማኀበሩ ተጠሪዎች ሂደው አምክነውታል በ2011 እና በ2014 ዓ/ም ” ሲሉ አስታውሰው፣ ቦታውን ያጠሩት ወጣቶች ለደንቦች ያቀረቡት በ2011 ዓ/ም ማኀበሩ ያመከነውን ሰነድ እንደሆነ፣ ማኀበሩ ከቦታው የምስክር ወረቀት ሁሉ እንዳለው አስረድተዋል። ግሪን ኤሪያው በማኀበሩ አማካኝነት ፦ - መብራትና ውሃ እንደገባለት፣ - ወይራ፣ ፅድ የመሳሰሉ አገር በቀል እፅዋቶች እንደለሙበት፣ - ህጻናትም በየወቅቱ እየገቡ #የሚናፈሱበት አረጓዴ መናፈሻ እንደሆነ የገለጹት ቅሬታ አቅሬቢዎቹ፣ “ ይሄ እያለ ነው ሰዎቹ መጥተው ያጠሩት ” ብለዋል። ቅሬታ አቅራቢዎቹ ጉዳዩን መንግሥት ትኩረት እንዲሰጠው የጠየቁ ሲሆን፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያ በበኩኩ ለተነሳው ቅሬታ ምላሽ ለማግኘት ወደ ክፍለ ከተማው ያደረገው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም። #TikvahEthiopiaFamilyAA @tikvahethiopia
Mostrar todo...
#DStvEthiopia 💥በቀን 12 ብር ምን ያደርጋሉ? አንድ ስኒ ቡና ይገዛሉ? ፓርኪንግ ይከፍላሉ? የቀንዎን ትራንስፖርትስ ይችላል? ለዲኤስቲቪ ግን ይበቃዎታል! 🥳🥳 ተወዳጁን ሀገርኛ ድራማዎችን እና መዝናኛዎችን የምናገኝበት አቦል ቲቪ ከሜዳ ወደ ጎጆ ፓኬጅ መጣ! ምን ይሄ ብቻ ኒክ ጁኒየር በአማርኛ፥ ዚ-ዓለም የተከታታይ ድራማ ቻናል እና ሌሎችም የዲኤስቲቪ ቻናሎችን በጎጆ ፓኬጅ ያገኛሉ። አሁን ጎጇችን ሞላ፤ በወር 350... በቀን 12ብር ብቻ #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #AbolTV #NickJrAmh #TraceMuzika #Zeeዓለም
Mostrar todo...
😡 55 32🤔 6🕊 6😭 3🥰 2
300 ቢሊዮን ብር ዕዳ ! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 300 ቢሊዮን ብር ብድር #እዳ እንዳለበት ተሰምቷል። ይህ የተሰማው በህ/ተ/ም/ቤት የመንግስት ልማት ድርጅቶች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይልን የ9 ወራት የስራ አፈፃጸም ሪፖርት ባዳመጠበት ወቅት ነው። የተቋሙ የብድር ጫና በጣም ከፍተኛ ነው ተብሏል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢ/ር አሸብር ባልቻ  ባቀረቡት ሪፖርት ፤ ተቋማቸው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 300 ቢሊዮን ብር ብድር እንዳለበት ተናግረዋል። የዕዳ ጫናውን ለማቃለል የባንክ ወልዱም ጭምር ተፅእኖ እያሳደረ መሆኑ አስረድተዋል፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ተቋሙ ካለበት የዕዳ ጫና ለመውጣት ፦ ➡ #የታሪፍ_ማሻሻያዎችን በማድረግ ➡ የውጭ የሃይል ሽያጭ አቅሞችን በማጠናከር ➡ የውስጥ ገቢን በመሳደግ ለዕዳ ቅነሳው ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበት አሳስቧል። ኢ/ር አሸብር ፥ በቀጣይ ከጅቡቲ፣ ከኬኒያ እና ከሱዳን በተጨማሪ ለታንዛኒያ እና ደቡብ አፍሪካ ኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ የዕዳ ጫናውን ለመቀነስ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት በዕቅድ መያዙን  ተናግረዋል። ℹ #HouseofPeoplesRepresentatives #CapitalNewspaper @tikvahethiopia
Mostrar todo...
#ጥንቃቄ🚨 " በተጣሉ ተተኳሾች እና ፈንጂዎች 103 ሰዎች #ሞተዋል ፤ አካላቸው ጎድሏል " - የቆላ ተምቤን ወረዳ በትግራይ ማእከላይ ዞን የቆላ ተምቤን ወረዳ በጦርነቱ ምክንያት በርካታ ተተካሾች እና ፍንጂዎች ይገኛሉ። እጅግ አስከፊውና ደም አፋሳሹን ጦርነት ተከትሎ በአከባቢው የተቀበሩትና የተጣሉት ተተካሾችና ፈንጂዎች በበርካታ ሰዎችና እንስሳት ላይ የሞትና የአካል ጉዳት አደጋ በማድረስ ላይ እንደሆኑ ተነግሯል። በወረዳው በተቀበሩትና በተጣሉት ተተኳሾችና ፈንጂዎች እስካሁን 103 ሰዎች #ሞተዋል ፤ አካላቸው ጎድሏል። አሁን ላይ አደጋውን ለመቀነስ ነዊና ጉያ  በተባሉ የቀበሌ አስተዳደሮች በባለሙያዎች የተደገፈ የማምከን ስራ መጀመሩን የወረዳው አስተዳደር አሳውዋል። ህዝቡ በአከባቢው ከተለመደው የተለየ ብረት ሲያገኝ ከመንካትና ከመቀጥቀጥ ተቆጥቦ ለጸጥታ አካላት እንዲያሳውቅ ማሳሰቢያ ተለልፏል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከቆላ ተምቤን ወረዳ አስተዳደር የኮሙኒኬሽን ያገኘው መረጃ ያሳያል። #TikvahEthiopiaFamilyMekelle @tikvahethiopia
Mostrar todo...
#ጊብሰን #GibsonSchool የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በጊብሰን ትምህርት ቤት የሚማሩ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎችን ከተማ አቀፉን የሚኒስትሪ ፈተና ትምህርት ቤቱ ማስፈተን እንደማይችል እንዳሳወቀው ት/ቤቱ ገልጿል። ጊብሰን ትምህርት ቤት " ባጠፋቸው ጥፋቶች ምክንያት እግድ ስለተጣለበት ተማሪዎችን ማስፈተን አይችልም " የተባለ ሲሆን ትምህርት ቢሮው ተማሪዎችን ሌላ ትምህርት ቤት ወስዶ በማስፈተን የሚኒስትሪ ካርዱ ላይም " በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ስር " የሚል እንደሚፃፍበት ተገልጿል። ይህን ውሳኔ ወላጆች እንደማይቀበሉት ገልጸዋል። ወላጆች ምን አሉ ? - ልጆቻችን በተማሩበት ት/ቤት ስር ነው መፈተን ያለባቸው - የተነገርን ነገር የለም - ባለቀ ሰዓት ነው ይህን የሰማነው - በተቀመጠው ካሪኩለም እንደሚማሩ ነው እኛ የምናውቀው - ልጆቻን ካሪኩለሙ የሚፈቅደውን ነው የሚማሩት - ቋንቋ ችግር አለ ወይ ? የለም - ሌሎች ት/ቤት የሚተገበረው ነው እዚህም ያለው - ከሌሎች የመንግስት ትምህርት ቤቶች የሚለየው ሳይንስ እና ሂሳብን በተጨማሪ እንግሊዘኛ ቋንቋ ያንኑ ካሪኩለም ጠብቆ ማስተማሩ ነው። እኛ ትምህርት ቤቱን የመረጥነው ተጨማሪ ቋንቋ ስለሚያስተምር ነው። - በተቀመጠው አማራጭ ሁለት ቋንቋ እያስተማረ ነው። አፋን ኦሮሞ እና አማርኛ በትምህርት አይነት ደረጃ እየተማሩ ነው። የቀረ ነገር የለም። - በመደበኛው ፕሮግራም ምንም የተጣሰ ነገር የለም። የአዲስ አበባ ከተማ የትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ አድማሱ ደቻሳ ትምህርት ቤቱ ብዙ ጥሰት ፈጽሟል ብለዋል። አቶ አድማሱ ደቻሳ ምን አሉ ? ° የትምህርት አይነት ጨምሮ ማስተማር ° የክፍለ ጊዜ ጥሰት ° የትምህርት ቋንቋ አለማክበር ° የአፍ መፍቻ ቋንቋ የሀገራችን " እንግሊዘኛ ነው " ብሎ ስታንዳርድ እስከመያዝ መድረስ፤ ° በእንግሊዝኛ አፋቸውን የፈቱ ካሉ ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት አለ እዛ መማር ይችላሉ ግን በከተማው ፍቃድ የወሰደ ት/ቤት " የአፍ መፍቻ ቋንቋው እንግሊዝኛ ነው " በሚል ማስተማር አይችልም። ° የሀገር በቀል ቋንቋ ጠል መሆን ተገቢ አይደለም። ° ተጨማሪ ቋንቋ በጥናት የተመለሰ ነው ይህንም እንዲታወቅ ብዙ ተሰርቷል ይህ ሆኖ እያለ ' አናውቅም፣ አልሰማንም ፣የሚመጣ ነገር የለም ' የማለት ነገር አለ። አንድ ወር ለቀረው የትምህርት ጊዜ ይህን ውሳኔ ለምን አሳለፋችሁ ? ለምን አልታገሳችሁም ? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ ፦ አቶ አድማሱ ደቻሳ ፦ " እኛ እልህ እየተጋባን አይደለም። የተወሰደው እርምጃ ከ4 ወር በፊት ነው። ነገር ግን ት/ቤቱ ተማሪና ወላጆችን መጠቀሚያ ለማድረግ ጥረት አድርጓል። እርምጃው ከተወሰደ ግን ቆይቷል። ከፈተና ጋር ተያይዞ ግልጽ ነው አንድ የትህምህርት ተቋም እውቅና ፍቃድ ኖሮት ወደ ፈተና ስርዓት ሲገባ ኮድ ይሰጠዋል ይህ የትምህርት ተቋም የእውቅና ፍቃዱ ቀድሞ የተነሳ ስለሆነ ኮድ ሊሰጠው አይችልም። ኮድ ባልተሰጠበት ትምህርት ተቋም ተማሪዎች ይፈተኑ ቢባል ፈተናቸው ሊታረም አይችልም። ስለዚህ ኮድ ወዳለው ትምህርት ተቋም ወስደን ነው የምናስፈትናቸው።  " ሲሉ መልሰዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 መሆኑን ይገልጻል። @tikvahethiopia
Mostrar todo...
#AddisAbaba ምንም አይነት የገቢ ምንጭ ለሌላቸው 1,051 ሴቶች ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የቴክኖሎጂ እቃዎች ድጋፍ ማድረጉን የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ቢሮ ገልጿል። ድጋፉ የተደረገላቸው በቤት ለቤት በተካሄደ ልየት ነው ተብሏል። ቢሮው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል፣  " ሴቶችን ኢኮኖሚ ላይ ስናያቸው ከ153 አገራት 153ኛ ደረጃ ላይ ናት ኢትዮጵያ። ይሄ ማለት ከግማሽ በመቶ በላይ ሴቶች የኢኮኖሚ ተደራሽነታቸው በጣም ዝቅተኛ ነው " ሲል ገልጿል። ይህን ታሳቢ ተደርጎ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑና በቢሮው ካፒታል አማካኝነት በተሸፈነ በጀት ከአኗኗራቸው ጋር ይስማማል ብለው ሴቶች የመረጧቸውን ኦቨን፣ የኤሌክትሪክ ምጣድና ሌሎች እቃዎችን ለ1,051 ሴቶች ድጋፍ መደረጉ አሳውቋል። በቀጣይ 2,000 ያህል ተስማሚ ቴክኖሎጂዎችን ለሴቶች ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱን አመልክቷል። ከ2012 ዓ/ም ጀምሮ ከ400ዐ በላይ ለሚሆኑ ሴቶች ድጋፍ መደረጉን፣ ድጋፉ የሚደረገው የአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪነት መታወቂያ ላላቸው፣ ምንም አይነት ገቢ ለሌላቸው፣ ለአካል ጉዳተኞች ነው ተብሏል። #TikvahEthiopiaFamilyAA @tikvahethiopia
Mostrar todo...
#SamiTech አዳዲስ ላፕቶፕች  ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!! @samcomptech በአገልግሎት አሰጣጣችን ላይ እና  በዕቃዎቻችን ጥራት ላይ  ደንበኞቻችን ምስክሮቻችን ናቸው። ዛሬም ብዛትንም ጥራትንም ሳንቀንስ እያስተናገድን እንገኛለን። ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች ፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች ፣ ለጌመሮች ወ.ዘ.ተ አቅምን ካገናዘቡ እስከ ቅንጡ ላፕቶፖች ይህ ቀረ ሳይሉ የሚያገኙበትን ሱቃችንን ይጎብኙ። የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ ባሉበት ሆነው ይዘዙን እናደርሳለን። የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት ይሄን 👉 @samcomptech ተጭነው በቴሌግራምው ማየት ይችላሉ። @sww2844 0928442662 / 0940141114 https://maps.app.goo.gl/H3PM1NrTcQ4SWkK17
Mostrar todo...
15😢 3🕊 1😡 1
Addis Ababa University- Cisco Networking Academy @CiscoExams www.netacad.com www.cisco.com Online Live class - Cybersecurity Training & Certification Preparation. Registration Date: April 22 to May 26, 2024 Class start date: May 27, 2024. Course Recognitions:- Trainees will receive 4 certificates of training completion; 4 digital badges & 32% discount for LPI Linux Essentials and 58% discount for CyberOps Associate Certification exam voucher. Mobile 0902-340070/ 0935-602563/ 0945-039478 Office : 011-1-260194 Follow our telegram channel: @CiscoExams
Mostrar todo...
15😡 4🥰 2😱 2
" ሰላም እና ፍትህ ለማስፈን ያጠፋ መጠየቅ አለበት " - አቶ ጌታቸው ረዳ በማህበራዊ ሚዲያ " ህወሓት ከብልፅግና ፓርቲ ጋር ሊዋሃድ ድርድር እየተካሄደ ነው " የሚሉት መረጃዎች ፍጹም ሐሰተኛ ናቸው ሲሉ አቶ ጌታቸው ረዳ ለ ' ቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ' ተናግረዋል። ብልፅግና እና ህወሓት ንግግር ማድረግ መጀመራቸውን የገለጹት አቶ ጌታቸው "  እነዚህ ንግግሮች ከውህደት ጋር የተያያዙ አይደሉም " ብለዋል። " የቅርብ ጊዜው ንግግራችን የፕሪቶሪያውን ስምምነት ተግባራዊ ስለማድረግ ነው። ውህደት አጀንዳም ሆኖ አያውቅም " ሲሉ ገልጸዋል። አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ ከጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ጋር ስላላቸው የስራ ግኝኑት በተመለከተ ፥ " ጥሩ የሥራ ግንኙነት ነው ያለን። የራሳችን የሆነ ልዩነት አለን። በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የተለያዩ አመለካከቶች አሉን " ብለዋል። " የፕሪቶሪያው ስምምነት #አብረን_እንድንሠራ ዕድል ስለሰጠን፤ ለሕዝብ ጥቅም ሲባል ልዩነቶቻችን ምንም ይሁኑ ምን አብረን እንድንሠራ አስችሎናል። ይህም ወደፊት ይቀጥላል ብዬ አስባለሁ " ሲሉ ተናግረዋል። በሌላ በኩል ፤ አቶ ጌታቸው በጦርነቱ ወቅት የሰብዓዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ በሙሉ ተጠያቂ መሆን አለባቸው ብለዋል። " ማንም ሰው ቢሆን፤ እኔን ጨምሮ መጠየቅ አለብን። ማንም ነጻ እንዲሆን መፈቀድ የለበትም። ሰላም እና ፍትህ ለማስፈን ያጠፋ መጠየቅ አለበት " ሲሉ ገልጸዋል። #BBC #FocusonAfrica @tikvahethiopia
Mostrar todo...
👏 918😡 332 230🕊 113🤔 72🙏 54😭 28😢 25😱 22
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት  አቶ ጌታቸው ረዳ ከ ' ቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ' ጋር ቃለ ምልልስ አድርገው ነበር። በቃለምልልሱ ፥ ባለፉት ሳምንታት በአማራ እና ትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎች የነበረው ግጭት በ " የሚሊሻ አባላት " መካከል እንጂ መደበኛ ኃይሎች የተሳተፉበት አልነበረም ብለዋል። " አማራ ክልል በኩል የነበሩ ሚሊሻዎች የተለያዩ አስጊ እንቅስቃሴያዎችን ሲያደርጉ ነበር። በእኛ በኩል ያሉ የሚሊሻ አባላት ምላሽ ሰጥተዋል " ሲሉ ገልጸዋል። የአማራ ክልል ያወጣውን መግለጫም  " መሬት ላይ ያለውን እውነታ ያላገናዘበ " ብለዋል። የሰላም ስምምነቱ #ተፈጻሚ_እንዳይሆን እያደረገ ያለው " ሕጋዊ የልሆነ የአማራ አስተዳደር ነው " ሲሉ ተደምጠዋል። አቶ ጌታቸው በዚሁ ቃለ ምልልስ ፥ በሰላም ስምምነቱ መሰረት በጦርነት ምክንያት የተፈናቀሉትን ሰዎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ከስምምነት መደረሱን አስታውሰዋል። " ሕጋዊ ያልሆኑ አስተዳደሮችን ለማፍረስ ከፌደራል መንግሥቱ ጋር አብረን እየሠራን ነው። ከአማራ ክልል ጋርም ቢሆን በተወሰነ ደረጃ አብረን እየሠራን ነው " ብለዋል። " የፕሪቶሪያው ስምምነት ተፈጻሚ እንዳይሆን የሚሹ አካላት እንዳሉ ግን በጣም እርግጠኞች ነን " ሲሉ ተደምጠዋል። አቶ ጌታቸው እነዚህ አካላት እነማን እነደሆኑ በግልጽ በስም ጠርተው አልጠቀሱም። #BBC #FocusonAfrica @tikvahethiopia
Mostrar todo...
😡 498 334👏 68🕊 61😭 22😱 11🤔 10🙏 10🥰 7😢 1
#Raya እንደ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ሪፖርት መሰረት ከራያ አላማጣ ገጠራማ አካባቢዎች የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ከ50 ሺህ በልጧል። 42 ሺህ ዜጎች ቆቦ ፤ 8,300 ሰዎች ሰቆጣ ይገኛሉ። የተፈናቀሉት ከራያ አላማጣ፣ ዛታ፣ ኦፍላ ነው። አብዛኞቹ ህጻናት ፣ ሴቶች ፣ ወጣቶች እና በእድሜ የገፉ አዛውንቶች ናቸው። #UNOCHA @tikvahethiopia
Mostrar todo...
😭 413👏 39😡 38😢 34 28🤔 19🕊 19🙏 9🥰 7😱 5
#Update ባይደን ፊርማቸውን አኑረዋል ፤ ቲክቶክ " ፍርድ ቤት እንተያይ " ብሏል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በባይት ዳንስ ባለቤትነት ያለው " #ቲክቶክ " ድርሻው ለአሜሪካ ኩባንያ ተሽጦ ከቻይና ካልተፋታ በመላው አሜሪካ #እንዲታገድ የቀረበላቸው ረቂቅ ሕግ ላይ ፊርማቸውን በማኖር ሕግ ሆኖ  እንዲወጣ አድርገዋል። " ቲክቶክ " ድርሻው ለአሜሪካ ኩባንያ እንዲሸጥ የተሰጠው ጊዜ ከ9 ወር እስከ 1 ዓመት ብቻ ነው። በዚህ ጊዜ ይህንን ካላደረገ #እስከወዲያኛው ከአሜሪካ እንደሚታገድ ተገልጿል። አሁን በአሜሪካ ብቻ 170 ሚሊዮን ተጠቃሚዎች ያሉት " ቲክቶክ " ሙሉ በሙሉ የመታገዱ ነገር #እውን ወደ መሆኑ ተቃርቧል። የቲክቶክ ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ሹ ዚ ቼው ፥ " የትም አንሄድም። ለመብታችን በፍርድ ቤት እንታገላለን። ሀቁ እና ህገ መንግስቱ ከጎናችን ናቸው፣ እናሸንፋለን ብለን እንጠብቃለን " ሲሉ ተናግረዋል። በሌላ በኩል ፤ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ለዩክሬን ፣ እስራኤል እና ታይዋን የቀረበው የ95 ቢሊዮን ዶላር የድጋፍ ጥቅል ረቂቅ ሕግ ላይ ፊርማቸውን አኑረዋል። @tikvahethiopia
Mostrar todo...
" ሰዎቹ ናቸው አታልለውኝ እዚያ ድረስ የወሰዱኝ " - ቀሲስ በላይ መኮንን የቀሲስ በላይ መኮንን ጠበቃ አቶ ቱሊ ባይሳ ስለ ዛሬው የፍርድ ቤት ውሎ ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ቃላቸውን ሰጥተው ነበር። በዚህም ወቅት ፥ ደንበኛቸው ቀሲስ በላይ መኮንን በሐሰተኛ ሰነድ ከ6 ሚሊዮን ዶላር በላይ ለማውጣት ሙከራ ተደርጎበታል የተባለው ቦታ የተገኙት " ሰዎች አታልለዋቸው " እንደሆነ ለፍ/ቤት መናገራቸውን ገልጸዋል። ጠበቃ ቱሊ ፤ " እሳቸው በቦታው ከመገኘት ውጪ ደብዳቤውን በማዘጋጀት፣ በመቀበል በዚህ ወንጀል ውስጥ ተሳትፎ የላቸውም " ያሉ ሲሆን " ደብዳቤው ላይ የእሳቸው ስም፣ የባንክ ቁጥር የለም። የቤተ ክርስቲያን የሂሳብ ቁጥር የለም " ብለዋል። " ከመጀመሪያውም ወንጀሉ በሌሎች ሰዎች የተሞከረ ቢሆንም እሳቸውን አይመለከትም " ሲሉ ገልጸዋል። በችሎቱ ላይ ለመናገር ዕድል ያገኙት ቀሲስ በላይ የአፍሪካ ኅብረት ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገኙት " ሰዎች ወስደዋቸው " እና " #ተታልለው " እንደሆነ ተናግረዋል። " በዚያ ቦታ ላይ ከመገኘት ውጪ ምንም የፈጸሙት ድርጊት እንደሌለ " ገልጸዋል። ቀሲስ በላይ ፦ " ሰዎቹ ናቸው አታልለውኝ እዚያ ድረስ የወሰዱኝ። እኔ ወደዚያ የሄድኩት ለመተባበር፣ ይህ ሰነድ ‘ትክክለኛ ሰነድ ነው አይደለም’ የሚለውን የባንክ ማናጀሮችን ለመጠየቅ ነው እንጂ በምንም ሁኔታ በሰነዱ ለመገልገል አስቤ አይደለም። ጉዳዩ ዞሮ እኔ ታሳሪ ሆንኩኝ እንጂ፤ ሰነዱ ‘ትክክል አይደለም’ የሚል የባንክ ማናጀሩ ሲገልጹልኝ ወዲያው ፖሊስ ያስጠራሁት እኔ ነኝ " ማለታቸውን ጠበቃው ተናግረዋል። ቀሲስ በላይ ሰነዱን አዘጋጅተዋል የተባሉ ሰዎች " ማምለጣቸውን " እንዲሁም ስለ ሰነዶቹ " የሚያውቁት እና መመርመር ያላባቸው " እነሱ እንደሆኑም ለፍርድ ቤቱ አንስተዋል ተብሏል። በዛሬው የፍ/ ቤት ውሎ የቀረበው የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ተደርጎ ለመርማሪ ፖሊስ ስምንት ተጨማሪ ቀን መሰጠቱ ይታወቃል። የመረጃው ምንጭ ቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ነው። @tikvahethiopia
Mostrar todo...
" ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ ሩዋንዳ መላክ እንጀምራለን፤ ... የንግድ ቻርተር አውሮፕላኖችንም ተከራይተናል " - ጠ/ሚር ሪሺ ሱናክ ዩናይትድ ኪንግደም በቁጣዮቹ ከ10 እስከ 12 ሳምንታት ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ #ሩዋንዳ መላክ ትጀምራለች። የዩናይትድ ኪንግደም ፓርላማ ስደተኞች/ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ ሩዋንዳ ለመመለስ የተያዘውን እቅድ መጀመር የሚያስችለውን " የሩዋንዳ እቅድ " የተሰኘውን ረቂቅ ሕግ ትላንት አጽድቋል። ጠ/ሚር ሪሺ ሱናክ፥ " በቀጣዮቹ ከ10 እስከ 12 ሳምንታት ባለው ጊዜ ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ ሩዋንዳ መላክ እንጀምራለን " ብለዋል። ለዚህም ፤ የንግድ ቻርተር አውሮፕላኖች ኪራይ መፈጸሙና ስደተኞችን ወደ ሩዋንዳ የሚወስዱ ሰራተኞችም መሰልጠናቸው ተነግሯል። 52,000 ጥገኝነት ጠያቂዎች ወደ ምስራቅ አፍሪካዋ ሩዋንዳ ይዘዋወራሉ ተብሎ ይጠበቃል። በቅርብ አመታት ፦ - #ከአፍሪካ ፣ - ከመካከለኛው ምስራቅ - ከኢስያ ጦርነት እና ድህነት የሚሸሹ በ10 ሺህ የሚቆጠሩ ስደተኞች ዩናይትድ ኪንግደም ገብተዋል። እነኚህ ስደተኞቹ በህገ ወጥ የሰው አዘዋዋሪዎች አማካኝነት በትንንሽ ጀልባዎች ተጉዘው ነው የሚገቡት። #ሮይተርስ @tikvahethiopia
Mostrar todo...
#AddisAbaba በአዲስ አበባ ከተማ የግንባታ ድንጋይ እና አፈር ተደርምሶ የ7 ሰዎች ሕይወት አፏል። አደጋው የደረሰው በአዲስ ከተማ ክ/ ከተማ ወረዳ 12 " ጠሮ መስጂድ " አካባቢ ነው። ለሊት 11 ሰዓት ገደማ ለቤት ግንባታ የተከመረ ድንጋይ እና አፈር ከላይ ወደ ታች (ወደ ቤቱ) ተንዶ 3 ክፍል ያለው ቤት ላይ አደጋ ደርሷል። በዚህም ቤት ውስጥ ተኝተው የነበሩ 7 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል። ሟቾቹ ፦ ➡ የ4 ዓመት ህጻን ፣ ➡ ሶስት የ11 እና የ12 ዓመት ታዳጊዎች  ➡ ከ25 እስከ 30 ዓመት ያሉ 3 ወጣቶች ናቸው። ሕይወታቸው ያለፈው ሰዎች የሁለት ቤተሰብ አባላት እንደሆኑ ታውቋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ አደጋው የደረሰበት ምክንያት ምን እንደሆነ ለማወቅ ምርመራ ላይ ነው። መረጃው የአዲስ አበባ እሳት እና ድንገተኛ አደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን ነው። @tikvahethiopia
Mostrar todo...
ከፊታችን ሚያዚያ 25 ቀን 2016 ጀምሮ ወደ ሶማሌ ክልል #ቀብሪደሃር ከተማ በሳምንት ሁለት ቀን የበረራ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚጀምር የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሳውቋል። አየር መንገዱ በሶማሌ ክልል ከጅግጅጋና ጎዴ ቀጥሎ #ቀብሪደሃር ሶስተኛው መዳረሻው ይሆናል። @tikvahethiopia
Mostrar todo...
248👏 92🙏 13🤔 8🥰 7😡 7🕊 5😱 3
“ ገዳሙ በከፍተኛ ችግር ላይ ይገኛል ” - አቡነ ሐራ ድንግል አንድነት ገዳም አቡነ ሐራ ድንግል አንድነት ገዳም በዙራያው በሰፈሩ ሰዎች የታዘ መሬቱን ለማስመለስ የካሳ ክፍያ መጠየቁን አስታወቀ። በአማራ ክልል የሚገኘው ገዳመ ወንያት አቡነ ሐራ ድንግል አንድነት ገዳም ከ30,000 እስከ 50,000 የሚሆኑ ፀበልተኞች እንደሚጸበሉበት ይሁን እንጂ የገዳሙ መሬት ሰዎች ስለሰፈሩበት እንኳን ለጸበልተኞች ለመነኮሳቱም እጅግ በመጣበቡ፣ “ ገዳሙ በከፍተኛ ችግር ላይ ይገኛል ” ተብሏል። የገዳሙ ይዞታ የጠበበው ከበርካታ ዓመታት ጀምሮ ለመፈወስ ወደ ስፍራው የሚሄዱ ፈውስ ያገኙ ጸበልተኞችና አርሶአደሮች ከሕመማቸው ከተፈወሱ በኋላ በገዳሙ መሬት ቤት እየሰሩ እዚያው በመኖራቸው መሆኑን የገዳሙ መነኮሳት አስረድተዋል። ሰዎቹ በአንድ ሳይሆን ቀስ በቀስ እዛው መኖር እንደጀመሩ ጠቁሟል።   በገዳሙ ይዞታ የሰፈሩ ከ250 በላይ አባውራዎች ይነሱ ዘንድ ለጠየቁት ካሳና ለሌሎች አገልግሎቶች ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ አሳውቋል። ለዚህም ሚያዚያ 19/2016 ዓ/ም በካፒታል ሆቴል የገቢ ማሰባሰብ መርሀ ግብር እንደተዘጋጀ፣ በመሆኑም በውስጥም በውጪ ያሉ ኢትዮጵያዊያን እርብርብ እንዲያደርጉ ገዳሙ ጥሪ አቅርቧል። #TikvahEthiopiaFamilyAA @tikvahethiopia
Mostrar todo...
#SafaricomEthiopia መልካሙን ዜና ከሳፋሪኮም ሰምተዋል?! 🎁ዕለታዊ የዳታ ጥቅል ስንገዛ ቀኑን ሙሉ፣ ሳምንታዊ የዳታ ጥቅል ስንገዛ ሳምንቱን በሙሉ እንዲሁም ወርሃዊ የዳታ ጥቅል በምግዛት ወሩን ሙሉ ከሳፋሪኮም ወደ ሳፋሪኮም መስመር በነጻ እንደዋወል! ዳታ እንግዛ! በነጻ እንደዋወል! የሳፋሪኮም ኢትዮጵያን ትክክለኛ መረጃዎችን በቀላሉ ለማግኘት ቀጥሎ በሚገኙት ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲከታተሉ  እንጋብዛለን። 👉 Facebook 👉Telegram 👉 Twitter 👉Instagram 👉 YouTube
Mostrar todo...
73😡 18🙏 8🥰 6👏 4🕊 2😱 1