cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

የሔና ማስታወሻ፪፩፩፫

ማንኛውንም ሀሳብ ወይም ስነፅሁፍ Send for admin and share ur talent and idea Admin @Hen2M ከነ ምንጩ አደርሳለሁ

Mostrar más
El país no está especificadoEl idioma no está especificadoLa categoría no está especificada
Advertising posts
189Suscriptores
Sin datos24 hours
Sin datos7 days
Sin datos30 days

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

@HomeForPoem By @Hen2M #19 Quito
Mostrar todo...
@HomeForPoem Admin @Hen2M #17 Quito
Mostrar todo...
#ላንቺ የዋህ ነብስያሽን፤ በይሉኝታ አታርክሽ፣ የወደደ ይጠላል፤ በድሎ ቢክስሽ፤ የተገፋ ቀንሽ፤ ሲነጋ ይደምቃል፣ የገፋሽ ግን ዝሎ፤ ከጋን ስር ይወድቃል። ተመስገን ለማለት፤ ወደ አምላክ ለማየት፤ ሙሉ አካል እያለሽ፤ ውቡ ማንነትሽን ለምን ታስከፊያለሽ? መሄድ የለመደ፤ ደጅ አይቶ የመጣ፣ ልሄድ ነው ይልሻል፤ ጨርሶ ሳይመጣ፤ በሌላ እንጉርጉሮ፤ በተቃኘ ዜማው፣ ተቀበል ያልሽው ለት፤ መንገድ ነው 'ሚቃኘው። በተሰበረ ክንፍ፤ በሰራሽው ጎጆ፤ ፍርሀት አታንግሺ፣ ልብሽ የሚልሽን፤ አጥብቀሽ አውጊና፤ ትልቁን ተንፍሺ። ያኔ ገመዶችሽ፤ አስረው 'ሚያስቀምጡሽ፤ ይበጣጠሱና፣ ሁሉም ሰምሮ አምሮ፤ ነበርን ትያለሽ፤ ያንቺን ታበሪና። ይስመር😁 ተፃፈ 7 መጋቢት 2012 4:56 በ Enoch2113 ሄኖክ @HomeForPoem By @Hen2M
Mostrar todo...
#stay_home #ምንም_አትንካ የዘመን ማዕበል የግዜ ሽውታ ጠልፈው የሸመኑት የክፋትን ኩታ ደርበን ደራርበን እሪያነት አጠቃን የግዜን ማዕዘን መደገፊያ ጠፋን። @HomeForPoem By @Hen2M
Mostrar todo...
#17 Don't kill people with kindness, because not everyone deserves your kindness. Kill people with silence, because not everyone deserves your attention. @HomeForPoem Admin @Hen2m #17Quito
Mostrar todo...
የግድ ልታነበዉ ይገባል ብየ አስባለሁ! *+++* አንዳንዴ በጣም ጥሩ፥ ጭዋ፥ ስነ ስርአት ያለዉ፥ ቀናና ሃይማኖተኛ ሰዉ እንሆንና ግን በዙሪያችን ርባና ያላቸዉ ሰዎች እናጣ ይሆናል። የበለጠ ጥሩ ለመሆን በሞከርን ቁጥር ደግሞ ይባስ ሰዎች አይተዉ ይሸሹናል። እንዲያዉም አንድ ሰዉ ከልክ በላይ በጣም ጥሩ ሲሆን ያስፈራል። ባስ ሲልም ያስጠረጥራል። በዚህ አለም ሰዉ እንዲሁ መልካም ሊሆን አይችልም። ካንተ የሆነ ነገር ካልፈለገ በስተቀር። ለዚያም ነዉ በጣም መልካም የሚባሉ ሰዎችን አድናቂ እንጂ ወዳጅ ሲያፈሩ የማናየዉ። በጣም መልካም ባህሪን ሁሉም ሰው ይፈልጋል። ወላጆቻችን፥ ሃይማኖታችን፥ መምህሮቻችን፥ ማህበረሰባችን ሁሉም መልካም ባህሪ ያለዉ ተተኪ ይፈልጋል። ምክንያቱም መልካም ሰዎች ፍፁም የሚያስቸግሩ ሰዎች አይደሉም። በቀላሉ ትለዉጣቸዋለህ። በፈለከዉ መንገድ ይከተሉሃል። እነሱን መምራት ቀላል ነዉ። ነገር ግን ወደግለሰብ ደረጃ ወረድ ብለን በተለምዶ በጣም መልካም የሚባሉ ሰዎችን ባህሪ ስንመለከተዉ በዉስጣቸዉ እጅግ በጣም ስር የሰደደ የመወደድ፥ የመደነቅና ይሁንታ የማግኘት ፍላጎት አለ። ከሚፈልጓቸዉ ሰዎች ይህንን ትኩረት ካላገኙ እስከመጨረሻዉ ጥግ ድረስ ለመሄድ የተዘጋጁ ናቸዉ። እየሰደቧቸዉ፥ እየረገጧቸዉ፥ ክብራቸዉን ሁሉ እስከመሸጥ ይደርሳሉ። ጥቅማቸዉን አሳልፈዉ ይሰጣሉ። ሰዎች ያለአግባብ እየጎዷቸዉ እንኳ ሆነ ብለዉ ምንም እንዳልተፈጠረ ያስመስላሉ። ትህትናቸዉና መሽቆጥቆጣቸዉ ከልክ በላይ ያቅለሸልሻል። ከላይ ሲታይ ይህንን የሚያደርጉት ለሰዉና ፈጣሪ ያላቸዉን ክብርና ፍቅር ለማሳየት ይመስላል። እዉነታዉ ግን እሱ አይደለም። ሰዎች ስለመልካምነታቸዉ እንዲወዷቸዉና እንዲያደንቋቸዉ ካላቸዉ ፅኑ ፍላጎት እንጂ። ችግሩ ግን ሰዎችን በመልካምነትህ ለማሸነፍ ስትል ብዙ ርቀት በተጓዝክ ቁጥር ራስህን እያጣኸዉና ከእዉነት መንገድ ወጥተህ ግብዝ እየሆንክ መሄድህ ነው። ይህን ማቆም አለብህ። መልካምነት ልክ አለዉ። ትህትና ልክ አለዉ። ሰዎችን ማስደሰት ልክ አለዉ። ለዚያም ነዉ ከሰዎች ክብርንና ፍቅርን ፍለጋ መልካም እየሆንክላቸዉ በሄድክ ቁጥር እነሱ ላንተ ያለቸዉ ፍቅርና ክብር የሚወርደዉ። ይህን ስል ጭራሽ መልካም ሰዉ መሆን መጥፎ ነዉ እያልኩ እንዳልሆነ ይገባሃል። የምልህ ያለዉ በጣም ሲበዛ መልካም ሰዉ መሆንህን ለማሳየት አትሞክር ነዉ። ከማንም ቢሆን ክብርና ፍቅር ጠብቀህ ስራ መስራትህን ተዉ። ማንም ስላንተ የሚያስበዉ ነገር ግድ አይስጥህ። ቅዱስ አትናቲዮስ ፓትርያርክ ከመንበሩ ተባሮ "አለሙ ሁሉ ጠልቶሃል!" ሲሉት እሱም "እኔም አለምን ጠልቸዋለሁ!" እንዳለዉ አይነት ህይወት እንኑር። ይህ በጣም ጥግ የያዘ ምሳሌ ይሆናል። ግን በዚህ ምድር በስኬት፥ በደስታና በልበ ሙሉነት መኖር ከፈለግን ሰዎች ስለእኛ ስለሚያስቡት ነገር መጨነቃችንን ማቆም አለብን። ጠ/ሚ ሃ/ማርያም ደሳለኝ ፌስቡክ ላይ ስለእሱ የሚወራዉን አሉባልታና አንቋሻሽ ወሬ ወደልቡ ቢያስገባዉ ኖሮ አይደለም አራት አመት ይቅርና አራት ወር እንኳ ስልጣን ላይ አይቆይም ነበር። እሱ ግን ማንም ምንም ቢል ግድ የለዉም። የሚያስፈልገን እንዲህ አይነት ስነልቦና ነው። ሰዎችን ለማስደሰት አንኑር። ደስታችንና ስሜታችን ሌሎች ሰዎች ድርጊት ላይ እንዳይንጠለጠል እናድርግ። ምናልባትም እንደአስቴር "ስለሰዉ ስለሰዉ ቀድጀ ልልበሰዉ!" ማለት ካለብንም እናድርገዉ። ስለሰዎች አድናቆት፥ ክብርና ፍቅር መኖራችንን እናቁም። መሄድ ካለብህ ሌሎች በፈለጉትና በተመቻቸዉ መንገድ ሳይሆን አንተ በወደድከዉና ባመንከዉ ጎዳና ላይ ነዉ። መልካም ሰዉ መሆንህን ለማሳየት በአነጋገርህ፥ በአረማመድህ፥ በአለባበስህ ላይ ያልተገባና የተጋነነ ለዉጥ አድርገህ ከሆነ ራስህ ፈትሽ። በጊዜ ሂደት ሰዎች በሙሉ እንደነጭ አንሶላ እንዳያቆሽሹህ ፈርተዉ ተራ በተራ ጥለዉህ ነዉ የሚሄዱ። ሰዎችን ከልክ ባለፈ ትህትናና ጭዋነት ለመሳብና ለመመሰጥ የምናደርገዉ ልፋት በስተመጨረሻ የአድናቆትና የጭብጨባ እስረኛ ነዉ የሚያደርገን! መልካም ምሽት! ይቀላቀሉን 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @me_asne_j. @me_asne_j @me_asne_j. @me_asne_j @me_asne_j. @me_asne_j
Mostrar todo...
🗣🗣🗣ጆሮ ያለው ይስማ : ልብ ያለው ልብ ይበል ይህ የበረኸኞች ቅዱሳን አባቶቻችን የንስሐ ግቡ ጥሪ ነው። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ቢያንስ ለ 21 የተዋህዶ ልጆች Share በማድረግ ክርስትያናዊ ግዴታችንን እንወጣ ነገ ከባድ የመከራ ጊዜ አለና ዛሬውኑ ንስሐ ገብታችሁ ተዘጋጁ። 2012፣ 2013፣2014፣ የኢትዮጵያ የምጥ ዘመናት ናቸው። 😭ንስሐ ያልገባ በቶሎ ንስሐ ይግባ። ንስሐ የገባ ደግሞ በየሳምንቱ ለነፍስ አባቱ ራሱን ያስመርምር ✍ሥጋወደሙ የተቀበሉ፣ ንስሐ የገቡ ሰዎች ብቻ ጨለማውን ይሻገሩታል። ንጉሡ ከመምጣቱ በፊት አባጣ፣ ጎርባጣው የግድ መስተካከል አለበት። ተራራው ዝቅ ማለት አለበት። ጉድባው ጉድጓዱ መሙላት አለበት። በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር እስከ 2014 መጨረሻ ድረስ መከራው እንዲሁ ይቀጥላል። ዘመኑ የምንጣሮ ዘመን ነው። ከኢትዮጵያ መከራ ፍጻሜ በኋላ የመላዋ ዓለም መከራ ደግሞ ከዚያ በኋላ ይጀምራል። 🗣🗣በቶሎ ንስሐ ገብታችሁ የታዘዛችሁትን ቀኖና ፈፀሙ ። ✍ዜጎች ቀን በቀን ይታረዳሉ ። አለቃው ይበዛል። አዛዥ እንጂ ታዛዥ አይኖርም። ሁሉ አለቃ፣ ሁሉ አዛዥ ይሆናል። ፍትሕና ሕግ ስፍራቸውን ለቀው ይሰደዳሉ። ትርምስምሱ ይወጣል። የሚያዝ የሚጨበጠው ይጠፋል። ክስ አድማጭ አይኖረውም። ወታደር ግራ ይጋባል። ዜጎች አማራጭ ያጣሉ። የውስጥም የውጪም ጠላቶች መግቢያ ቀዳዳው ይሰፋላቸዋል። ✍በአራቱም አቅጣጫ ኢትዮጵያ ትወረራለች። ሰላም በማስከበር በሚል ሰበብም በ2 ሃያላን ሀገራት የሚመሩ ሰባት የሙስሊም ሀገራት በኢትዮጵያ ምድር ላይ እሳት ያዘንባሉ። በአሰብ ወደብ ላይ በልዩ ሁኔታ የተከማቸው የጦር መሣሪያ በኢትዮጵያ ምድር ላይ እንደበረዶ ይዘንባል። ብዙ ፍጅትም ይሆናል። ኦርቶዶክሳውያን በያሉበት፣ በየተገኙበት እንደከብት ይታረዳሉ። የኢትዮጵያ ምድር በደም ትጨቀያለች። የደም ጎርፍ፣ የደም አበላ በምድሪቱ ላይ ይፈሳል ። 🗣🗣ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ ✍ ክፉ ረሃብ በኢትዮጵያ ይመጣል። የሚበላ የሚጠጣ ከምድሪቱ ይጠፋል። ከጦርነቱ የተረፈውን ህዝብ ረሃብ ይፈጀዋል። በስደት ምክንያት የዐቢይ ጾም የማይጾምበት ጊዜም ይመጣል። በረሃቡ ጊዜ ግን ጥቂቶችን የመትረፊያ ገዳማት ግን አሉ። ሰው የሚተርፍባቸው ገዳማትና አድባራት አሉ። ታቦተ ኢየሱስ ያለባቸው ገዳማትና አድባራት በሙሉ ሰው ይተርፍባቸዋል። በጊዜው እስከ አሁን ዝግ የሆኑ ዋሻዎች ይከፈታሉ። የሚተርፉ ኢትዮጵያውያንም በዚያ ይጠለላሉ። ከአሁኑ ጨውና የማይነቅዙ እህሎች አከማቹ። 🗣🗣ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ ✍ ከዚያም ክፉ በሽታ ይመጣል። ክፉ ወረርሽኝ ይከሰታል። ወረርሽኙ የ12 ሁለት ሰዓት ዕድሜ ብቻ የሚሰጥ ክፉ በሽታ ሲሆን ይኼም ጦርነቱንና ረሃቡን ተከትሎ ይመጣል። 🗣🗣መፍትሄው ንስሐ መግባት፣ ሥጋወደሙ መቀበል ነው። ✍አባቶች እንዲህ አሉ: ነገ ንስሐህን የሚቀበል ካህንም ላታገኙ ትችላላችሁና ይሄን መልእክት የማንበብ ዕድል የገጠማችሁ ልጆቻችን ሆይ ጨርቄን፣ ማቄን፣ ሳትሉ፣ ወገቤን ደረቴን ሳትሉ፣ ምክንያት ሳትደረድሩ፣ ዕለቱኑ ዛሬውኑ ንስሐ ግቡ። 🗣🗣ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ ✍2015 በዘመነ ሉቃስ ንጉሱ ይመጣል። ለሳምንት ዝናብ ይዘንባል። የፈሰሰውን ደም አጥቦ ያስወግዳል። ምድር ትባረካለች። የተረፉት ሰዎች እርስ በእርስ ይፈቃቀራሉ። ጠማማ ሰው አይኖርም። ንጉሱ ቴዎድሮስ በፍቅር ለ40 ዓመታት ይመራል። 🗣🗣በመሀል ሀገር በአዲስ አበባ እና በመላው የኢትዮጵያ ከተሞች የምትኖሩ ልጆቻችን ሆይ እነሆ አስቀድሞ በአባቶቻችን የተነገረው ሊፈፀም ግድ ነውና ልብ ያለው ልብ ይበል። በሗለኛው ጊዜ አልሰማንም : አላየንም እንዳትሉ እነሆ ከመከራው አስቀድሞ ይህ መልዕክት ከብዙ በጥቂቱ ለአእምሮ በሚመጥን ልብን በሚገዛ መልኩ ለመላው ህዝበ ክርስቲያን አስተላልፈናል። ✍🗣በጸሎት የምንለምንና የምንማልድ ሁላችንንም በሰላም በመንፈስ ይጠብቀን ፍቅርንም ይስጠን ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን ፈቃዱም ሆኖ ጸሎታችንን ይቀበል ዘንድ ቀርበን እግዚአብሔርን እንለምነው! ዐውቀን በሃብቱ እናድግ ዘንድ በእርሱም ስም እንመካ ዘንድ...በነቢያት በሐዋርያትም መሰረት ላይ እንታነጽ ዘንድ እንግዲህ በመንፈስ ቅዱስ እንነሳ! ቀርበን አምላካችን እግዚአብሔርን እንለምነው ወዶ ጸሎታችንን ይቀበል ዘንድ። አሜን! 🗣🗣🗣ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ ቅዱስ አባ ዘወንጌል፣ ፍካሬ ኢየሱስ፣ ራዕየ ባሮክ ፣ የአባቶች ትንቢት 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 Share share share share share share 1 ሰው ለ 21 ምዕመን ለመላው ህዝበ ክርስትያን መልዕክቱ እንዲደርስ በማድረግ የአባቶቻችንን አደራ እንወጣ ✍🗣✍ጆሮ ያለው ይስማ : ልብ ያለው ልብ ይበል ✍🗣✍መንግስተ ሰማያት ቀርባለች እና ንስሐ ግቡ
Mostrar todo...
📢Share በማድረግ ይሳተፉ 💬አስተያየት በ@Hen2M አድርሱኝ 📝የእርስዎ ስራ ካለም ይላኩ በ @Hen2M 🙏🙏🙏🙏 Tnank u😍
Mostrar todo...