cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Amen Gospel

#ሰዎችን #በክርስቶስ #ለክርስቶስ #ማድረግ #ነው 💥💥💥💥💥💥💥 #WELCOME TO OUR BLESSING CHANNEL 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ለበለጠ መረጃ +251941810160 ደውሉልን To our belssing telegram group https://t.me/+YcqErTQrE6M2NzFk Join as 🙏 https://t.me/helingjesus

Show more
Advertising posts
916Subscribers
No data24 hours
+47 days
+1030 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

የእግዚአብሔር ወንጌል ❝ሐዋርያ ሊሆን የተጠራ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ጳውሎስ በነቢያቱ አፍ በቅዱሳን መጻሕፍት አስቀድሞ ተስፋ ለሰጠው ለእግዚአብሔር ወንጌል ተለየ።❞ —ሮሜ 1፥1-2። ጳውሎስ ... ራሱን "ተለየ" ያለው ለእግዚአብሔር ወንጌል ነው! የጳውሎስ መልእክት ደግሞ "የእግዚአብሔር ጸጋ ወንጌል ነው" የኖረውም የሞተውም ይህን መልእክት ሰዎች ጋር ለማድረስ ነው! ያኖረውም ጸጋ ነው! ❝ነገር ግን ሩጫዬንና ከጌታ ከኢየሱስ የተቀበልሁትን አገልግሎት እርሱም የእግዚአብሔርን ጸጋ ወንጌልን መመስከር እፈጽም ዘንድ ነፍሴን በእኔ ዘንድ እንደማትከብር እንደ ከንቱ ነገር እቆጥራለሁ።❞ —ሐዋርያት 20፥24። ስለዚህ የእግዚአብሔር ወንጌል የተባለው የጸጋ ወንጌል ነው! ለምን የጸጋ ወንጌል የእግዚአብሔር ወንጌል ተባለ? 1) ከእኛ ምንም ሳይጠብቅ እግዚአብሔር እኛን መውደዱን ስለሚያወራ፤ 2) ያለ ሥራ የመጽደቅን እውነት ስለያዘ፣ 3) በጸጋ (በነፃ) መዳንን ስለሚናገር እና 4) የወንጌሉ ባለቤት እግዚአብሔር ስለሆነ ነው። በነገራችን ላይ ወንጌል የሆነ ትምህርት አይደለም! ወንጌል እግዚአብሔር ከዘላለም ጀምሮ ለእኛ ያለው ልብ (አሳብ) ነው! ይህም በክርስቶስ ተፈጽሞ ምስራቹ እኛ ጋር ደርሶአል!! ❝ይህም በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን የፈጸመው የዘላለም አሳብ ነበረ፥❞ —ኤፌሶን 3፥11። ✍️ messager kaleb
Show all...
1
ነገ እሑድ ወደ ቤተክርስቲያን ስንሄድ አንድ ያላመነ ሰው ይዘን ወደ ቤተክርስቲያን የምንሄድበት ቀን። https://t.me/healingjesus11 https://t.me/healingjesus11 https://t.me/healingjesus11 https://t.me/healingjesus11
Show all...
ሶስተኛ ቀን የአንጾኪያ ሙቭመንት‼️ ዛሬ አርብ = አር ..ብ = አርትን ለወንጌል በተለያዩ የኪነጥበብ ውጤቶች የምንሰብክበት ቀን ነው። ለማያምኑ ወገኖቻችን የተለያዩ የኪነጥብ ውጤቶችን በማቅረብ ወንጌልን የምናደርስበት ቀን።
Show all...
ሶስተኛ ቀን የአንጾኪያ ሙቭመንት ዛሬ አርብ = አር ..ብ = አርት ወንጌልን በተለያዩ የኪነጥበብ ውጤቶች የምንሰብክበት ቀን ነው ለማያምኑ ወገኖቻችን የተለያዩ የኪነጥብ ውጤቶችን በማቅረብ ወንጌልን የምናደርስበት ቀን ከታች የምታዩትን ወንጌል በሰዓሊያን ቪዲዮ ለሌሎች እንዲደርስ ሼር አድርጉ
Show all...
#ቤተክርስቲያን #ታማለች 💥 አሁን ላይ ያሉ መጋቢዎች : ዘማሪያን በተለያየ የአገልግሎት ዘርፍ የሚያገለግሉ አገልጋዩች እና ምዕመናን በሙሉ ታመናል ይሄም በሽታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እርስ በእርስእየያጨራረሰን ይገኛል። ❝ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ፥ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥❞ —ኤፌሶን 2፥5። አንድ ሰው የሆነ ጥፋት አጥፍቶ ... ላጠፋው ጥፋት የሚገባው ቅጣት ሲቀርለት ... ምሕረት ተደረገለት እንላለን። በአጭሩ ምሕረት ማለት "የሚገባንን ቅጣት አለመቀበል" ነው። እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለጠጋ ነው፤ ያ ማለት ለመተላለፋችን የሚገባንን ቅጣት ባለመስጠት ... አይቶ እንዳላየ #በማለፍ ባለጸጋ ነው!! እግዚአብሔር "በጥፋታቸው ይጥፉ" ቢል ማን ይተርፍ ነበር? ማንም!! ❝ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው፤ ርኅራኄው አያልቅምና።❞ —ሰቆ. 3፥22። #ያልጠፋነው #ስላላጠፋን አይደለም፤ #ከምሕረቱ ብልጽግና የተነሣ ነው!! ሐዋርያው ጳውሎስ አሕዛብ በክርስቶስ ከመሆናችን በፊት ምን እንደነበርን ኤፌሶን 2፥1-3 ካብራራ በኋላ ... የማንነት ለውጥ እንደተደረገልን፣ አዲስ ሕይወት እንደተቀበልን እና ጸጋው በእምነት እንዳዳነን ይገልጻል። የዚህ ታላቅ ለውጥ መሰረት እግዚአብሔር ለእኛ ያለው ትልቅ ፍቅር እና የምሕረት ብልጥግናው እንደሆነ ጽፎልናል።                   ✍️messager kaleb
Show all...
👍 2
.                ለጌትነቱ                  °°°°°°°°        ዘማሪት ዮርዳኖስ ዮሐንስ        °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°   Amazing Cover Song     share♻️share♻️share♻️         🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣👇 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚  🎼  ✨ @Yemezimur_Maikel ✨  ✨ @Yemezimur_Maikel
Show all...
.               ትልቅ ነህ                 °°°°°°°°°          ዘማሪ ቢኒያም ዮናስ          °°°°°°°°°°°°°°°°°°° Amazing Kingdom Sound Worship      share♻️share♻️share♻️         🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣👇 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚  🎼  ✨ @Yemezimur_Maikel ✨  ✨ @Yemezimur_Maikel
Show all...
የዚህ ዘመን አንዱ ችግር.. ‼️ "እኔኮ በእናቴ ፀሎት ነው የምኖረው" የሚል ብዙ ሰው በተለይ ብዙ ወጣት አለ። አንዳንዱማ በቃ የምትፀልይ እናት ካለች የሱ ፀሎት ቢቀርም ኖርማል ነው ብሎ ወስዶታል። የሆነ መልካም ነገር በህይወቱ ሲደረግ የእናቴ ፀሎትኮ ይልሃል። ከሆነ አደጋ ቢተርፍ እኔኮ በእናቴ ፀሎት ነው የምኖረው ይልሃል። እኔኮ የእናቴን የፀሎት ፍሬ እየበላሁ ነው ይልሃል። አዎ እናትህ ልጄን አደራ ብላ  ፀልያለች ተሰምቷልም እግዚአብሔር ይመስገን። ግን እግዚአብሔር ዘንድ በቀጥታ አንተ እንደመቅረብ ፈንታ እናትህ የአንተ ተወካይ ሆና እስከመቼ?..  እናትህ ለአንተ ፀለየች፤ አንተም ለልጆችህ የምትፀልይ አባት ሁን እንጂ። አዎ ፀሎት በእግዚአብሔር መንፈስ እንጂ በኔ ፅሁፍ አይመራም አውቃለሁ። ግን ፀልይ ዘምር ማለት ክርስቲያናዊ የመፅሐፍ ቅዱስ መሰረት ያለው ምክር ነውና በእናቴ ፀሎት ነው የምኖረው እያልህ ራስህን አለመፀለይን አታለማምድ። እናትህ ትፀልያለች እግዚአብሔር ይባርካት አንተም ፀልይ!..  ለነገሩ አሁን አሁንኮ የኛ ፀሎት የማይሰማ ይመስል የሆነን አገልጋይ ፀልይልኝ ማለት እየተስተዋለ ነው። እግዚአብሔር ይርዳን! ©amen gospel
Show all...
ሐሙስ =ሐ... ሙስ = ሙስሊም ወገኖቻችንን በወንጌል የምንደርስበት ቀን ነው
Show all...
ረቡዕ = ቡናችንን ለወንጌል ዛሬ ረቡዕ ሚያዝያ 9 በአንጾኪያ ሙቭመንት የወንጌል የቀን ስያሜ:- ረቡዕ = ቡ ="ቡናችንን ለወንጌል" የሚል ነው ስለዚህ እያንዳንዱ አማኝ በቀን ውስጥ የሚኖረውን የቡና እና ሻይ ጊዜ ( የዕረፍት ጊዜ)  ስለ  ትንሳኤው ሚመሰክርበት ቀን ነው ! "ሁላችንም የትንሳኤው ምስክሮች ነን " ትንሳኤው ስለ ኃጢአታችን በመስቀል ላይ በሰውነቱ ውስጥ ያለውን ደም ሁሉ አፍስሶ ቆዳው ከአጥንቱ ጋር ተጣብቆ  የሞተው እየሱስ፤ እኛን ስለማጽደቅ በሦስተኛው ቀን ከሙታን  ተነስቷል እኛም በእሱ ከሙታን መነሳት በማመናችን በኃጢያታችን እና በበደላችን ከሞትንበት ከእግዚአብሔር የራቀ ፣ ክብር የሌለው  ህይወት ተነስተን ህያዋን ሆነናል !! ዛሬም በኃጢአት፣ በበደል ፣ በሰይጣን እና በአለማዊ የህይወት ስርዓት እየተመላለሳችሁ ከእግዚአብሔር ህይወት ርቃችሁ ( ሙት ህያው ለሆናችሁ) ከሙታን የተነሳውን እየሱስን በማመን ከሞት ፣ ከጨለማ ህይወት ፣ ከዘላለም ፍርድ ከእግዚአብሔር ቁጣ  እንድትድኑ እንመሰክርላችኃለን :: አማኞች የትንሳኤው ምስክር ነኝ እያላችሁ ኮሜንት አድርጉ ሼር በማድረግ አብረን እንመስክር የትንሳኤው ምስክር ነኝ
Show all...