cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ይዌድስዋ ቱዩብ

የዚህ ግሩፕ አላማ ብዙ ታሪክ እና ታምር ወደ አላቸዉ የተለያዮ ገዳማት /አድባራት በመሄድ መንፈሳዊ ህይወታችንን ማጠንከር እና ስለምንከተለዉ ሀይማኖትም በቂ የሆነ እዉቀት እንዲኖረን ለማረግ ነዉ 🙏 እንደ እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ🙏 ጉዞ ብቻ ሳይሆን በቻልነዉም ስለ ሀይማኖታችንን ያወቅነዉን አንዱ ለሌላዉ የሚያካፍልበት እና የምንማማርበት ቤት ይሆናል 🙏

Show more
Advertising posts
196Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

#እንኳን_አደረሠን_ ''ሥላሴ'' አዲስ ዝማሬ ከደቂቃወች በኋላ https://youtube.com/@yiwiedisiwatube-4311
Show all...
Watch "የጌታችንን ልደት ለምን እናከብራለን ጥያቄና መልስ||በሰባኬ ወንጌል ስንታየሁ በሪሁን" on YouTube https://youtu.be/JEf11QH36yY
Show all...
የጌታችንን ልደት ለምን እናከብራለን ጥያቄና መልስ||በሰባኬ ወንጌል ስንታየሁ በሪሁን

@ማኅቶት ቲዩብ - Mahtot Tube @Rama Tube ll ራማ ቲዩብ Zemari Tadewos @Felege Genet Media - ፈለገ ገነት ሚዲያ @አባ_ገብረ_ኪዳን_ግርማ @ዘማሪ ዲያቆን ሳምሶን ነጋሽ Zemari Deacon Samson Negash @ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን Mirtnesh Tilahun Official Page @ዘማሪ ዲያቆን ሳምሶን ነጋሽ Zemari Deacon Samson Negash @የዲ'ን ሄኖክ ኃይሌ ትምህርቶች

Watch "እሰይ ካሜንስትኾ|| እሰይ ተወለደ 🛑አዲስ የአገውኛ ዝማሬ|| ዘማሪት ሀብታምነሽ ጥላሁን||Esey Tewolede||Zemarit Habtamneshi Tilahun" on YouTube https://youtu.be/8Efv5CK3O8o
Show all...
እሰይ ካሜንስትኾ|| እሰይ ተወለደ 🛑አዲስ የአገውኛ ዝማሬ|| ዘማሪት ሀብታምነሽ ጥላሁን||Esey Tewolede||Zemarit Habtamneshi Tilahun

@ማኅቶት ቲዩብ - Mahtot Tube @Rama Tube ll ራማ ቲዩብ Zemari Tadewos @Felege Genet Media - ፈለገ ገነት ሚዲያ @አባ_ገብረ_ኪዳን_ግርማ @ዘማሪ ዲያቆን ሳምሶን ነጋሽ Zemari Deacon Samson Negash @ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን Mirtnesh Tilahun Official Page @ዘማሪ ዲያቆን ሳምሶን ነጋሽ Zemari Deacon Samson Negash @የዲ'ን ሄኖክ ኃይሌ ትምህርቶች

እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ ነውና እሱ ያደረገው ተአምር ምንም ቢሆን ከከሃሊነቱ አንጻር የሚጠበቅ ነገር ነው፡፡ ለደካማው የሰው ልጅ ኃይል ሠጥቶ የሚሠራውን ነገር ስንሰማ ግን ኃይሉ በሰው ድካም ሲገለጥ ስናይ የበለጠ እናደንቃለን፡፡ የቅዱሳን ተአምር መቼም ቢደረግ በእግዚአብሔር እጅ የተደረገ ነው፡፡ ‘ሁሉ በእርሱ ሆነ ከሆነውም አንዳችስ እንኳን ያለ እርሱ አልሆነም’ እንደሚል ድንግል ማርያም ያደረገችው ተአምር ሁሉ በእርሱ የተደረገ ነው፡፡ ተአምረ ማርያምም ራሱ ተአምረ ኢየሱስ ነው፡፡ እግዚአብሔር በድንግል ማርያም ተአምር ይሠራል ፤ ያለ ድንግል ማርያምም ተአምር ሊያደርግ ይችላል፡፡ ድንግል ማርያም ግን ያለ እግዚአብሔር አንዳች ተአምር ልትሠራ አትችልም፡፡ ክርስቶስ ‘ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉም’ ያለው ለዚህ ነው፡፡ (ዮሐ. 15፡5) ኦርቶዶክሳዊያን ስለ ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክዋን ፣ ዘለዓለማዊ ድንግልዋን ፣ መቼም መች መርገም ያልደረሰባት ንጽሕት መሆንዋ ፣ አማላጅነትዋን እናምናለን ፤ ከዚህ ፈቀቅ ሊያደርገን የሚሻ ቢኖርም እነዚህ የነገረ ማርያም መሠረተ እምነቶቻችን ናቸውና እስከ ሰማዕትነት ድረስ እንጸናለን፡፡ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ‘እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋል፤ ከዚህም የሚበልጥ ያደርጋል’ ‘የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ተራራ፦ ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም’ ብሎ ተናግሯል፡፡ (ዮሐ. 12፡14 ፤ ማቴ. 17፡20) ስለዚህ ‘ያመነች ብፅዕት’ የተባለችው ድንግል ማርያም (ሉቃ. 1፡45) በልጅዋ አነጋገር ክርስቶስ የሚያደርገውን ተአምር ታደርጋለች ፣ ከዚያም የሚበልጥ ታደርጋለች ፣ የሚሳናትም የለም፡፡ ተአምራትን የሚያነብ ሰው በእምነት ካላነበበው ብዙ መቸገሩ የማይቀር ነው፡፡ እውነት ለመናገር ይህ ከክህደት የተነሣ ብቻ ሳይሆን ከመንፈሳዊነት ደረጃችን ዝቅ በማለታችን የተነሣ የሚፈጠር ችግር ነው፡፡ በተአምራት መጻሕፍት ላይ ተደረጉ የሚባሉ ተአምራትን በእርግጠኝነት የሚያምን ልብ ቢኖረን ኖሮ ተአምራቱን እኛ ራሳችን ልንፈጽማቸው በቻልን ነበር፡፡ እኛ ግን እንኳንስ ተአምራቱን ልንፈጽማቸው ቀርቶ ተፈጽመዋል ብለን አምነን ለመቀበልም እንኳን ገና ነን፡፡ በዚህ የተነሣ የቅዱሳን ተአምራት ሲነበቡ ልባችን በጥርጣሬ ይናወጻል፡፡ ከኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ውጪ ያሉ ሰዎች ደግሞ ተአምራት ሲሰሙ ‘አቤት ተረት’ ለማለት ተነቦ እስከሚያልቅ ድረስ አይጠብቁም፡፡ በገድላትና ድርሳናት ላይ ያሉ ታሪኮችንና ተአምራትን ተረታ ተረት ናቸው ብሎ ለመደምደም ከቸኮልክ መጽሐፍ ቅዱስንም ማመንህ አስገራሚ ይሆናል፡፡ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስም ብዙ ለማመን የሚከብዱ ታሪኮች አሉበት፡፡ እባብ ከሰው ጋር ሲነጋገር ፣ አህያ ጌታዋን ስትመክር ፣ ኤልያስ ዝናብን እንደ ቧንቧ ውኃ ሲከፍትና ሲዘጋ ፣ ቁራ አስተናጋጅ ሲሆን ፣ ኤልያስ በእሳት ሰረገላ ሲሳፈር ፣ ዮናስ በአሳ አንበሪ ሆድ ውስጥ ሲጸልይ ፣ የኤልሳዕ አጥንት ሙት ሲያስነሳ ፣ የኤልያስ ልብስ ባሕር ሲከፍል ፣ የሙሴ በትር እባብ ሲሆን ፣ ጌታ በምራቁ ዓይን ሲፈጥር ፣ የአራት ቀን ሬሳ በስም ተጠርቶ ሲወጣ ፣ የጴጥሮስ ጥላ ሲፈውስ ፣ የጳውሎስ ጨርቅ ሙት ሲያስነሣ ተጽፎ ታገኛለህ፡፡ ይሄንን ሁሉ እግዚአብሔር ሁሉን ማድረግ ይችላል ብለህ በእምነት ካልተቀበልከው በስተቀር እንዴት ታደርገዋለህ? አንድ አባት ‘ዮናስን አሣ አንበሪ ዋጠው የሚለውን ታሪክ እንዴት ማመን ይቻላል?’ ተብለው ሲጠየቁ ‘የምናወራው ስለ እግዚአብሔር ከሆነ እንኳንስ ዓሣ አንበሪው ዮናስን ዋጠው ተብሎ ይቅርና ዮናስ ዓሣ አንበሪውን ዋጠው ቢባልም አምናለሁ’ ብለዋል፡፡ ‘አይ ይኼ እኮ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተጻፈ ነው’ ካልከኝ እግዚአብሔር መጽሐፍ ቅዱስ ተጽፎ ሲጠናቀቅ ሥራ አቁሞአል ማለት ነው? ‘እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ከእናንተ ጋር ነኝ’ ሲል አብረን አልሰማነውም? (ማቴ. 28፡19) ወደ ተአምረ ማርያም እንመለስና ለመሆኑ ተአምረ ማርያምን ማን ጻፈው? ከየት መጣ? ተአምረ ማርያም ላይ የሚነሡ ብዙ ጥያቄዎች ሁሉም የተሳሳቱ ናቸው ሊባል ይችላል? ብፁዓን አባቶች "ተአምረ ማርያም ላይ በሊቃውንት ጉባኤ በኩል ሥራዎች እየተሠሩ ነው" ሲሉ ምን ማለታቸው ነው? በቤተ ክርስቲያንዋ በኩልስ በአዋልድ መጻሕፍት ዙሪያ የሚነሡ ጉዳዮች የሉም? ሌሎች የሚያሳዩት ንቀትና ስድብ እንዳለ ሆኖ በአዋልድ በቤተ ክርስቲያንዋ እይታስ ምን እየተሠራ ነው? የዚህ ጽሑፍ ቀጣይ ክፍል ትኩረት ይሆናል፡፡ ክፍል ሁለት - ይቀጥላል ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ታኅሣሥ 12 2015 ዓ.ም. ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን አጥብቃችሁ ስለ እኔ ጸልዩልኝ! በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ [ዋጋን በምድር የሚያስቀር ውዳሴም ሆነ ሌላ] ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)
Show all...
በአጭሩ ዓረፍተ ነገሩ ሥጋ ወደሙን ዘወትር በመቀበል ሕይወት የሚኖርን ክርስቲያን የሚመለከት ቃል ነው፡፡ ይህ ክርስቲያን ፍጹም መንፈሳዊ ሕይወትን እየኖረ እንዳለ ምስክር የሚሆነው ሥጋ ወደሙን ከመቀበል የሚከለክለው ደዌ ወይም የታወቀ ምክንያት እንጂ አልቆርብም የሚል የኃጢአት ሰበብ አይደለም፡፡ እንዲህ ላለው ትጉሕ ቆራቢ ሰው ሁልጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያን እየገሠገሠ መቁረብ ልማዱ ነውና አስቀድሶ አለመቁረብም ኀዘን ይሆንበታል፡፡ ለዚህ ሰው መቅድመ ተአምረ ማርያም ያጽናናዋል፡፡ ‘የታወቀ ምክንያት ወይም ሕመም ስለከለከለህ ባለመቁረብህ አትዘን ቢያንስ ተአምርዋን ሰምተህ ሒድ ፤ በዚያ ዕለት ልትቆርብ ተመኝተሃልና ሰምተህ በመሔድህ ያን ቀን ብትቆርብ የምታገኘውን በረከት አላስቀርብህም’ ነው፡፡ ይህ ግን ንስሓ አልገባም አልቆርብም ተአምርዋን ሰምቼ ይበቃኛል የሚል ብልጣ ብልጥ ትዕቢተኛ ሰው የሚሠራ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ይህንን ዓይነቱን ሰው ከመቁረብ የሚከለክለው ‘የታወቀ ምክንያት ወይም ደዌ ሳይሆን’ የኃጢአት ፍቅር ነው፡፡ ሦስተኛው ጥያቄ ‘ለሥዕልዋ ያልሰገደ ከቆመበት ቦታ ይጥፋ የሚል እርግማን እንዴት በሐዲስ ኪዳን ይነገራል?’ ነው፡፡ ‘ለሥዕልዋ ስገዱ’ ማለት ለድንግል ማርያም ስገዱ ማለት ነው እንጂ እርስዋና ሥዕልዋን ነጣጥሎ ለማየት አይደለም፡፡ ምክንያቱም ቅዱስ ዮሐንስ ዘደማስቆ በእንተ ሥዕላት አምላካዊያት (On the Divine Images) ላይ ደጋግሞ እንደገለጸው በሥዕላት ፊት የሚደረግ ማንኛውም አክብሮትና ስግደት ለሥዕሉ ሳይሆን ለሥዕሉ ባለቤት ነው፡፡ ድርሳነ ሚካኤልም ‘ወሶበ ንሰግድ ቅድመ ሥዕላት አምላካዊያት አኮ ዘንሰግድ ለረቅ ወለቀለም ወለግብረ ዕድ’ ‘በእግዚአብሔር ሥዕል በተሳሉ በአምላካዊያት ሥዕላት ፊት ስንሰግድ የምንሰግደው ለወረቀቱ ለቀለሙ ወይንም ለሰው የእጅ ሥራ አይደለም’ ስግደትና ሥዕላትን በሚመለከት እነዚህን ቀደምት ጽሑፎች ይመልከቱ፡፡ ‘በሐዲስ ኪዳን እንዴት እርግማን እንሰማለን’ የሚለው ተቃውሞ ‘እንዲህ የሚያደርግ መንፈስ የተወጋ ይሁን’ ‘ወግቼዋለሁ’ ሲሉ ከሚውሉ ሰዎች አቅጣጫ መነሣቱ አሁንም አስደናቂ ነው፡፡ ከዚያ ውጪ ጉዳዩ የሚረገመው አካልና እርግማኑ ተገቢነት ላይ እንወያይ እንጂ ሐዲስ ኪዳን ላይ ጨርሶ የግዝት ቃል ሥራ አቁሞአል ማለት አይቻልም፡፡ ጌታ በለስዋን ‘ለዘላለም ፍሬ አይገኝብሽ ብሏታል’ /ማቴ. 21፡19/ ሐዋርያት ‘ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የማይወድ ቢኖር የተረገመ ይሁን’ ‘ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን’ ብለዋል፡፡ /ገላ.1፡8፣9/ እግዚአብሔር አያሰማን እንጂ በዕለተ ምጽአትም ‘እናንተ ርጉማን’ የሚለው ቃል የመጨረሻው ቃል ነው፡፡ ይህ ዓይነቱ ቃል ተራ እርግማን ሳይሆን በድርጊቱ የተገኙትን ከክርስትና ኅብረት የሚለይ በምድር ያሰረችው በሰማይ የታሰረ የሚሆንላት ቤተ ክርስቲያን የምትናገረው ቃለ ውግዘት (በግሪኩ Anathema) ነው፡፡ ይህም በተስፋ የምንጠብቃት መንግሥተ ሰማያት እስክትመጣና ‘ከእንግዲህ ወዲህ መርገም ከቶ አይሆንም፡፡ የእግዚአብሔርና የበጉም ዙፋን በእርስዋ ውስጥ ይሆናል ባሪያዎቹም ያመልኩታል ፊቱንም ያያሉ’ የሚለው ቃል እስከሚፈጸምልን ድረስ የሚቀጥል ነው፡፡ (ራእ. 22፡3) የመጨረሻው ነጥብ ‘የድንግል ማርያም ባሪያዎች ለመሆን እንሽቀዳደም እንጂ 16ቱን ትእዛዛት በመጠበቅ አይደለም እንዴት ይባላል?’ የሚለው ነው፡፡ መደጋገም ይሆንብኛል እንጂ አሁንም ጥያቄው ከእነርሱ መነሣቱ ያስደንቀኛል፡፡ ፕሮቴስታንቲዝም የትእዛዛት ተቆርቋሪ መሆን የጀመረው ከመቼ ወዲህ ነው? በማመን እንጂ ትእዛዝ በመጠበቅ አይዳንም በሚለው ትምህርት ምክንያት ስንት ውዝግብ አልተነሣም? ጳውሎስ የመገረዝን ሕግ ሥራ ለአሕዛብ ጽድቅ የግድ አስፈላጊ አይደለም ብሎ ያስተማረበትን ሮሜና ገላትያ ያለ አገባቡ በአጠቃላይ በጎ ሥራ አያፈልግም እንዳለ አድርገው በያዙት የተሳሳተ መረዳት ምክንያት በሰማይ በክብር አብረው የሚዘምሩትን ጳውሎስና ያዕቆብን ሳይጣሉ ያጣሏቸው እነርሱ አይደሉምን? አሁን ደግሞ ተአምረ ማርያምን ጎዳን ብለው እንዴት ትእዛዝ መፈጸም አያስፈልግም ትላላችሁ? ብለው ሲመጡ ማየት ምንኛ አስገራሚ ነው? በመሠረቱ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እነሱ እንደሚሉት ሥራ ብቻውን ያጸድቃል ብላ አምና አታውቅም፡፡ ልጆችዋንም እኔ በጎ ሥራ አለኝ በእርሱ እጸድቃለሁ ብለው እንዳያስቡ ታስጠነቅቃለች፡፡ ጸሎትዋም መዝሙርዋም ‘ምግባር የለኝም’ ነው፡፡ ‘እንበለ ምግባር ተራድእኒ ፍጡነ ፤ ምግባርየሰ ኃጢአተ ኮነ’ ‘እንበለ ምግባር ባሕቱ እመ ኢይጸድቅ አነ ፤ ቦኑ በከንቱ ኪዳንኪ ኮነ’ ‘በምን ምግባሬ ፊትሽን አየዋለሁ’ ‘እኔስ በምግባሬ ደካማ ሆኜያለሁ’ ወዘተ የሚሉት እልፍ ምስጋናዎች ቤተ ክርስቲያን ልጆችዋ በምግባሬ እጸድቃለሁ ብለው ተስፋ እንዳያደርጉና በክርስቶስ በማመናቸው (በሥጋ እንደመጣና ከድንግል ማርያም እንደተወለደ ማመንን ይጨምራል) እና በእግዚአብሔር ጸጋ ወይም ቸርነት እንደሚጸድቁ (እምነት + ሥራ + ጸጋ) ታስተምራለች፡፡ የድንግል ማርያም ባሪያዎች ለመሆን እንሽቀዳደም መባሉ የሚያበሳጨው ካለ መጽሐፍ ቅዱስ ‘ነገር ግን በፍቅር እርስ በእርሳችሁ እንደ ባሪያዎች ሁኑ’ ይላል፡፡ ገላ. 5፡13 እንኳንስ ለአምላክ እናት አጠገብህ ላለው ወንድምህም በፍቅር ባሪያ ብትሆን ትጠቀማለህ እንጂ አትጎዳም፡፡ ለድንግል ማርያም ባሪያዋና ታዛዥዋ ብትሆን ግን ብዙ ትጠቀማለህ፡፡ ክርስቲያኖች ሆይ ልንገራችሁ ሁሉን ትታችሁ ለድንግል ማርያም ብቻ ታዘዙ፡፡ የእርስዋ ትእዛዝ አንድ ነው ‘የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ’ ዮሐ. 2፡5 + ተአምራትን እንዴት እናያቸዋለን? + መጽሐፍ ቅዱስ ‘የሐዋርያት ሥራ’ን የመሰሉ ሰዎች በእግዚአብሔር ኃይል የሠሩትን ሥራ የሚተርኩ መጻሕፍት ያለበት መጽሐፍ ነው፡፡ ‘የእግዚአብሔርን ቃል የነገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ የኑሮአቸውን ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሏቸው’ በማለት ሕያዋን መጽሐፍት ወይም ተንቀሳቃሽ መጽሐፍ ቅዱስ /Living bible or moving bible/ ተብለው የሚጠሩትን የቅዱሳንን ሕይወት እንድናጠና እና በኑሮአቸው እንድንመስላቸው ያሳስበናል፡፡ (ዕብ. 13፡7) ቅዱስ ጳውሎስ ‘እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እናንተም እኔን ምሰሉ’ ብሎ እንደነገረን ክርስቶስን ለመምሰል የጳውሎስን የሕይወት ታሪክ ማጥናት የግድ አስፈላጊ ነው፡፡ (1ቆሮ. 11፡1) ራሱ ጳውሎስም ከእርሱ የቀደሙ የእምነት አርበኞችን አስደናቂ ታሪክ ከዘረዘረ በኋላ ‘ሁሉን እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛል’ ብሏል፡፡ (ዕብ. 11፡32) ጳውሎስ የቅዱሳኑን ታሪክ ለመተረክ ያጠረው ጊዜ እንጂ ፍቅር አልነበረም፡፡ እግዚአብሔር በቅዱሳኑ አድሮ ያደረገውን መስማትም የቅዱሳን ታሪክ አካል ነው፡፡ ‘በሐዋርያት እጅ ብዙ ድንቅና ምልክት ተደረገ’ ‘እግዚአብሔርም በጳውሎስ እጅ የሚያስገርም ተአምራት ያደርግ ነበር’ እንደሚል እግዚአብሔር በባሪያዎቹ እጅ ታላላቅ ተአምራት ያደርጋል፡፡ (ሐዋ. 2፡42 ፣ 19፡11) የእስራኤል ንጉሥ ‘ኤልሳዕ ያደረገውን ተአምር እስቲ ንገረኝ’ እያለ ግያዝን እየጠየቀ በደስታ ይሰማ እንደነበረ የእግዚአብሔር ቅዱሳን ያደረጉትን ተአምር መስማት ለምናምን ሰዎች እጅግ ደስ የሚያሰኝ ነገር ነው፡፡ (2ነገሥ. 8፡4)
Show all...
+ ተአምረ ማርያምና አንዳንድ ጉዳዮች + (ክፍል አንድ) ተአምረ ማርያምን በተመለከተ ሲነሡ የነበሩ ጉዳዮችን መቼም ሁሉም ሰው ያውቃቸዋል፡፡ ከመቅድሙ ጀምሮ ‘እንዴት ድንግል ማርያም ከዓለም አስቀድሞ ታስባ ትኖር ነበር ይባላል?’ ‘እንዴት ተአምርዋን የሰማ ሥጋውን ደሙን እንደተቀበለ ይሆንለታል ይባላል?’ ‘ለሥዕልዋ ያልሰገደ ከቆመበት ቦታ ይጥፋ የሚል እርግማን እንዴት በሐዲስ ኪዳን ይነገራል?’ ‘የድንግል ማርያም ባሪያዎች ለመሆን እንሽቀዳደም እንጂ 16ቱን ትእዛዛት በመጠበቅ አይደለም እንዴት ይባላል?’ የሚሉ ጥያቄዎች ከፕሮቴስታንቶች አንዳንዶቹ ሲያነሡ አይተናል፡፡ በዚህ ጽሑፍ የተነሡትን አንዳንድ ጥያቄዎች እንደመግቢያ እንመልከታቸውና በጉዳዩ ላይ ያለውን ዝርዝር ጉዳይና ዘላቂ መፍትሔ ደግሞ አስከትለን ለመዳሰስ እንሞክራለን፡፡ ‘‘እንዴት ድንግል ማርያም ከዓለም አስቀድሞ ታስባ ትኖር ነበር ይባላል?’’ የሚለው ጥያቄ ማንም ቢያነሣው ላያስደንቅ ይችላል፡፡ ‘ጸጋ ብቻ’ /Sola gratia/ በሚል አስተምህሮ እግዚአብሔር አስቀድሞ የወሰናቸው ሰዎች ብቻ እንደሚድኑ የሚያምነውን አስተምህሮ /Predestinationን/ እንደ መሠረተ እምነቱ የሚያስተምር ፕሮቴስታንቲዝምን የሚከተሉ የካልቪን ተከታይ የሆኑ ሰዎች /በእርግጥ አንዳንዶቹ አሁን አንቀበለውም እያሉ ነው/ እንዴት ቀድማ ታስባ ትኖራለች የሚል ጥያቄ ሲያነሡ መስማት ትንሽ ያስገርማል፡፡ እኛ ባናምንበትም እንዲያው ድንግል ማርያም ሌላው ቢቀር እነርሱ የሚያምኑበት ‘የPredestination አካል’ የምትሆንበትን ዕድል እንኳን ሊኖር እንደሚችል ቢያስቡ ጥሩ ነበር፡፡ ምክንያቱም የመጀመሪያዋ ክርስቲያን እንደመሆንዋ የተመረጡ /elect/ ከሚሏቸው ውስጥ በመቆጠር እድልዋ ቀዳሚ ናትና ከዓለም አስቀድማ ልትታሰብ ትችል ነበር፡፡ በመሠረቱ እንኳንስ ድንግል ማርያም ማንኛውም ፍጡር በአምላክ ሕሊና ታስቦ ይኖር ነበረ፡፡ ይህም ከፍጡሩ ማንነት አንጻር ብቻ ሳይሆን ከእግዚአብሔር ሁሉን አስቀድሞ ማወቅ ጋር የተያያዘ ጽንሰ ሃሳብ ነው፡፡ እንኳን ድንግል ማርያም እኛ ለሁላችን እንኳን ‘ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን ፤ በበጎ ፈቃዱ እንደ ወደደ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን’’ ተብሎ ተነግሮልናል፡፡ ኤፌ. 1፡4 የድንግል ማርያም ጎልቶ የሚነገረው ስለ አንድ ምክንያት ነው፡፡ እግዚአብሔር ከዓለም አስቀድሞ የሰው ልጅን መውደቅ የሚያውቅ እንደመሆኑ የሰውን ልጅም እንዴት እንደሚያድነው ያውቃል፡፡ እንዴት እንደሚያድነው ከዓለም አስቀድሞ ካወቀ ደግሞ በማዳኑ ሥራ ውስጥ እጅግ ወሳኝ የሆነችውን ድንግል ማርያምንም ከዓለም አስቀድሞ ያውቃታል ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ‘በክቡር የክርስቶስ ደም እንደ ተዋጃችሁ ታውቃላችሁ። ዓለም ሳይፈጠር እንኳ አስቀድሞ ታወቀ’ ብሎ ክርስቶስ በደሙ የሚያደርገው ቤዛነት ከዓለም መፈጠር በፊት እንደታወቀ ተናግሯል፡፡ 1ጴጥ. 1፡20 የክርስቶስ በከበረ ደሙ እኛን ማዳኑ ዓለም ሳይፈጠር ከታወቀ ከእርስዋ ሥጋና ደምን ነሥቶ የሚወለድባት ድንግል ማርያም በአምላክ ሕሊና የማትታሰብበት ምንም ምክንያት አይኖርም፡፡ በጉባኤ ኒቅያ ‘ጥበብ ጌታ ፈጠረኝ እግዚአብሔር የመንገዱ መጀመሪያ አደረገኝ’ የሚለውን አርዮስ የካደበት ምሳ. 8፡23 ላይ ያለው ቃል የተብራራው ‘ፈጠረኝ የሚለው ቃል የተዋሐደውን ሥጋ የሚያጠይቅ ነው’ (ወጥበብኒ ዘትብል ፈጠረኒ እግዚእ ያኤምር በእንተ ዘፈጠረ ለርእሱ ሥጋ በከርሰ ማርያም) ተብሎ ነው፡፡ /ሃይማኖተ አበው ዘቄርሎስ 76፡15/ ጥበብ ፈጠረኝ ማለትዋ ቅድመ ዓለም ሥጋን ስለመልበሱ የታወቀ መሆኑን የሚያስረዳ መሆኑ በኒቅያ ጉባኤ እንደ ማስረጃ ከቀረበ ድንግል ማርያም ከዓለም አስቀድሞ በአምላክ ሕሊና ታስባ ለመኖርዋም ትልቁ ማስረጃ ይኼው ጥቅስ ይሆናል፡፡ (ለዝርዝሩ ‘የብርሃን እናት’ ገጽ 324ን ይመልከቱ) ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ያሳተመው የብዙ ምሁራን የነገረ ማርያም ጥናቶች ስብስብ መጽሐፍ ስለዚህ ጉዳይ እንዲህ ይላል፡፡ ‘Mariology is a new creation or, perhaps, a new way of looking at creation. For this reason, the idea arose quite logically that Mary was chosen in eternity to be the Mother of God, and She is associated with Wisdom, who says in Proverbs 8:23 : Ages ago I was set up, at first, before the beginning of the earth’ ‘ነገረ ማርያም አዲስ ፍጥረት ወይም (ምናልባት) ሥነ ፍጥረትን በአዲስ መንገድ መመልከቻ መነጽር ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ማርያም የአምላክ እናት ለመሆን ቅድመ ዓለም የተመረጠች የመሆንዋ ሃሳብ ከበቂ አመክንዮ ጋር ይነሣል፡፡ እርስዋም ‘የመንገዱ መጀመሪያ አድርጎ ፈጠረኝ ፤ ምድርን ሳይፈጥር አስቀድሞ ከዓለም በፊት ሠራኝ’ ከምትለው ጥበብ ጋር ተያይዛ ትነሣለች’ /The Oxford Handbook of Mary, Oxford University, UK 2019 Press 2/ ሁለተኛው ጥያቄ ‘ተአምርዋን የሰማ ሥጋ ወደሙን እንደተቀበለ ይሆንለታል’ የሚለውን ቃል በመጥቀስ ‘እንዴት የክርስቶስ ሥጋና ደም ከተአምረ ማርያም ጋር ሊተካከል ይችላል?’ የሚል ጥያቄ ነው፡፡ ይህም ጥያቄ ከፕሮቴስታንት አቅጣጫ መነሣቱ በጣም አስገራሚ ነው፡፡ እኔ መረጃ አጥሮኝ ካልሆነ በቀር ከመቼ ወዲህ ነው አንድ ፕሮቴስታንት የሥጋ ወደሙ ተቆርቋሪ የሆነው? የአስተምህሮ ለውጥ ተደርጎ እንደሆነ አላውቅም፡፡ በብዙ ለዘመናት ጸንቶ እንደተቃወመው ግን ፕሮቴስታንቲዝም በክርስቶስ ሥጋና ደም አማናዊነት ጨርሶ አያምንም፡፡ ጌታችን ‘ይህ ሥጋዬ ነው ይህ ደሜ’ ነው ብሎ የሠጠውን ምሥጢረ ቁርባንም ‘አብሮ ከሚበላ የመታሰቢያ ማዕድነት ያለፈ ፋይዳ የለውም’ በሚል አቋም የፕሮቴስታንቱ ዓለም ከካቶሊክና ኦርቶዶክሱ ዓለም ጋር ሲሟገት የአምስት መቶ ዓመት ዕድሜውን እንዳሳለፈ ሁላችን የምንስማማባቸው የታሪክ መዛግብት ያስረዳሉ፡፡ እነርሱ እንደሚሉት ሥጋ ወደሙ ተራ የመታሰቢያ ማዕድ ከሆነ ደግሞ እውነትም ከመብላት መስማት የተሻለ ጥቅም አለውና ይህንን ቃል ሊቃወሙ የሚችሉበት መሠረት አይኖራቸውም፡፡ የተአምረ ማርያም መቅድም ግን ጉዳዩን የሚጀምረው ተአምርዋን መስማት ምንኛ ከሥጋ ወደሙ ያነሠ መሆኑን በመግለጽ ነው፡፡ ሰው ‘ሥጋውንና ደሙን ይቀበል ፤ ሥጋ ወደሙን ለመቀበል የሚከለክል የታወቀ ምክንያት ከገጠመው ግን ተአምርዋን ሰምቶ ይሒድ’ የሚለው ንግግር ሥጋ ወደሙን ለመቀበል የማይችል ሰው ተአምርዋን መስማት እንደሚችል ያስረዳል፡፡ ተአምረ ማርያም ከሥጋ ወደሙ እኩል ቢሆን ኖሮ ሰውዬውን ሥጋ ወደሙን ከመቀበል የከለከለው ምክንያት ተአምርዋንም ከመስማት ይከለክለው ነበር፡፡ ለምሳሌ ‘በአካል መጥተህ እንድታገኘኝ ነገር ግን በአካል ለመምጣት ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ባትችል ቢያንስ በስልክ ደውልልኝ ፤ ከደወልህልኝ እንደ መጣህ እቆጥረዋለሁ’ ብለህ ለወዳጅህ ነገርኸው፡፡ ይህ ዓረፍተ ነገር በአካል መምጣትና በስልክ መደወልን እኩል ያደርጋል ማለት አይደለም፡፡
Show all...
ነቢያት ጌታ "ይወርዳል ይወለዳል" ብለው የተናገሩት ትንቢት እንዲፈጸም ተመኝተው ጾሙ ጸለዩ:: እኛ ስለምን እንጾማለን? ክርስቶስ ተወልዶ ፣ ተጠምቆ ፣ አስተምሮ ፣ ተሰቅሎ ፣ ሞቶ ፣ ተነሥቶ ፣ ዐርጎ ፣ በአባቱ ቀኝ አይደለምን? አሁን ለምን እንጾማለን? ብለን እናስባለን:: ጌታ በእኔና አንተ ልብ ውስጥ እውነት ተወልዶአልን? እውነት የእኛ ልብ እንደ ቤተልሔም ግርግም ለክርስቶስ ማደሪያ ሆኖአል? ማደሪያ አሳጥተን ከእናቱ ጋር አልመለስነውም? የጥምቀቱ ትሕትና በእኛ ልብ መቼ ደረሰ? የስቅለቱ ሕማም መች በእኛ ሕሊና ተጻፈ? የትንሣኤው ተስፋ የዕርገቱ ልዕልና በእኛ ልቡና መቼ ዐረፈ? ስለዚህ ነቢያት "ውረድ ተወለድ" ብለው የጾሙትን ጾም እንጾማለን:: ጌታ ሆይ በእኔ ሕይወትም ውስጥ ውረድ ተወለድ የእኔን ሰውነት ማደሪያህ አድርገው:: ሕዋሳቶቼ ከኃጢአት አርፈው እንደ ቤተልሔም ግርግም ማደሪያህ ይሁኑ:: የቤተልሔም እንስሳት ትንፋሽ ገበሩልህ ፣ የቢታንያ ድንጋዮች ዘማሪ ቢጠፋ ሊዘምሩ ዝግጁ ነበሩ ፣ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ለክብርህ ተቀደደ ፣ ጨረቃ ላንተ ደም ለበሰች ፣ ፀሐይ ስላንተ ጨለመች ፣ ከዋክብት ለስምህ ረገፉ ፣ ዓለቶች ለፍቅርህ ተሰነጠቁ:: ከቤተልሔም እንስሳት ፣ ከቢታንያ ድንጋዮች ፣ ከቤተ መቅደስ መጋረጃ እኔ እንዴት አንሼ ልገኝ? የቢታንያ ድንጋይ ያወቀህን ያህል ሳላውቅህ ፣ የቤተ መቅደስ መጋረጃ የተረዳህን ያህል ሳልረዳህ እንዴት ልኑር? ዓለት ላንተ ሲሰነጠቅ የኔ ልብ ለምን ከዓለት ደነደነ? ጨረቃ ደም ስታለቅስ እኔ መከራህ ለምን አልተሰማኝም? ሙታን በሞትህ ሲነሡ እኔ ምነው ከኃጢአት ሞት መነሣት ተሳነኝ? ለዚህ ነው በእኔ ሕይወት ገና አልተወለድክም የምለው:: ስለዚህ ጌታ ሆይ የነቢያትህን ጾም ጸሎት ሰምተህ የወረድህ የተወለድህ ጌታ ሆይ በእኔም ሕይወት ውረድ ተወለድና እኔም ከመላእክት ጋር አብሬ ልዘምር ፣ ከሰብአ ሰገል ጋር ሥጦታህን ልቁጠር ፣ ከእረኞች ጋራ ልደነቅ:: ልደትህ ሳይገባኝ ምጽዓትህ እንዳይደርስብኝ እርዳኝ:: ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ጾመ ነቢያት 2015 ዓ.ም.
Show all...
+ አቤቱ ቅጣኝ ነገር ግን እንዳታዋርደኝ! + እግዚአብሔር ፍቅር ነው ፣ መሐሪ ነው ፣ ይቅር ባይ ነው፡፡ ፍቅር ይቆጣል ወይ? ይቅር ባይስ ይቀጣል ወይ? ብዙዎቻችን ስለ ክርስቶስ ሲነገረን መሐሪነቱና ፍቅሩ ብቻ ቢነገረን አንጠላም፡፡ ጨርሶ የማንፈራው እግዚአብሔር እንፈልጋለን፡፡ እንዲህ አታድርግ! የሚለን ሲመጣ ‘አትፍረድ’ እንላለን ፤ ቆይተን ግን የሰማዩን ዳኝም አትፍረድ ማለት ይቃጣናል፡፡ ቅጣት የሌለበት ክርስትና እንሻለን፡፡ ይህ ዓይነቱን ክርስትና ‘ጣፋጭ ክርስትና’ {የስኳር ክርስትና ይሉታል} ምንም ምሬት የሌለበት ሁሌም ማር ማር የሚል ሕይወት አድርገው ክርስትናን የሚሰብኩም ብዙ ናቸው፡፡ ‘አይዞህ ብትታመም ትፈወሳለህ ፣ ቤትህ ይሞላል ፣ ቀዳዳህ ይደፈናል ፣ ብትበድልም አትቀጣም’ ብቻ የሚሉ ስብከቶች የስኳር ክርስትና ስብከቶች ናቸው፡፡ ይህንን ብቻ የሚያጮሁ ሰዎች ክርስቶስ ‘የምድር ጨው ናችሁ’ ያለውን ትተው የምድር ስኳር ለመሆንና ዓለምን ለማስደሰት የሚፈልጉ ናቸው፡፡ በእርግጥ እግዚአብሔር ይቆጣል ወይ? አዎን ይቆጣል! እንዲህ ይላል መጽሐፉ ‘እግዚአብሔር ቀናተኛና ተበቃይ አምላክ ነው እግዚአብሔር ተበቃይና መዓትን የተሞላ ነው እግዚአብሔር ተቃዋሚዎቹን ይበቀላል፥ ለጠላቶቹም ቍጣውን ይጠብቃል። በቍጣው ፊት የሚቆም ማን ነው? የቍጣውንም ትኵሳት ማን ይታገሣል? መዓቱ እንደ እሳት ይፈስሳል፥ ከእርሱም የተነሣ ዓለቶች ተሰነጠቁ’ ናሆ 1፡1፣6 ‘‘ከቍጣው የተነሣ ምድር ትንቀጠቀጣለች አሕዛብም መዓቱን አይችሉም’’ ኤር 10፡10 ‘‘እኛ በቍጣህ አልቀናልና፥ በመዓትህም ደንግጠናልና’’ መዝ. 90፡7 እግዚአብሔር በተቆጣ ጊዜ የሚመልሰው የለም፡፡ ቅዱሳን የቁጣውን መጠን ስለሚያውቁ በትሕትና ይለምኑታል፡፡ ይሁንና መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር ቁጣ ደጋግሞ ቢነግረንም አንድ ሌላ ደስ የሚያሰኝ ነገርም ነግሮናል፡፡ የእግዚአብሔር ቁጣው ለዘላለም አይደለም፡፡ "ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" ይላል እንጂ "ቁጣው ለዘላለም ነውና" አይልም:: የእግዚአብሔር ቁጣ ጊዜያዊ ነው፡፡ ‘መሐሪ ነኝና ለዘላለም አልቆጣም’ ኤር 3፡12 ‘ቁጣው ለጥቂት ጊዜ ሞገሱ ግን ለሕይወት ዘመን ነው’ መዝ 29፡5 ‘ጌታ ለዘላለም አይጥልም ቢያሳዝንም እንደ ምሕረቱ ብዛት ይራራል ፤ የሰው ልጆችን ከልቡ አያስጨንቅም አያሳዝንምም’ ሰ.ኤር 3፡31 የፈጣሪን የነነደ የቁጣ እሳት ማጥፋት የሚቻለን በዕንባ ነው፡፡ በደላችንን አምነን ቅጣት ይገባናል ነገር ግን መሐሪ ነህና ማረን ማለት ይገባል፡፡ ንጉሥ ዳዊት ‘አቤቱ በቁጣህ አትቅሠፈኝ በመዓትህም አትገሥፀኝ’ ብሎ የፈጣሪን ቁጣ አበረደ፡፡ /መዝ 38፡1/ ነቢዩ ኤርያስም ‘አቤቱ ቅጣኝ ነገር ግን እንዳታዋርደኝ በመጠን ይሁን እንጂ በቁጣ አይሁን’ ብሎ ተለማመጠ፡፡ ኤር 10፡24 አንድ ሠዓሊ በጣም ብዙ ደክሞ የተጠበበትን ሥዕሉን የፈለገ ቢበሳጭ ለረዥም ጊዜ ያንን ሥዕል ለመሳል የተጠበበትን ጥበብ አስቦ ሥዕሉን ወደ እሳት አይጨምረውም፡፡ አባ ጊዮርጊስ እንዲህ ሲል ይለምናል ‘ሠዓሊ ሥዕሉን ያጠፋል ወይ? [ጌታ ሆይ እኔን ስትፈጥር የተጠበብክበትን] የቀደመ ጥበብህን አስብ እንጂ! አስበህም ማረኝ! [ያጠፋዖኑ ለሥዕሉ ሠዓሊ ፤ ኪነተከ ዘትካት ኀሊ] ይቅርታውን በንስሓ ለሚለምኑ ሁሉ ምሕረቱ ቅርብ ነው፡፡ በቀኝና በግራው ወንበዴዎች በተሰቀሉበት በዕለተ አርብ የግራው ወንበዴ ሲሰድበው ጌታ መልስ አልሠጠም፡፡ የቀኙ ወንበዴ ማረኝ ሲለው ግን ከአፉ ተቀብሎ በገነት ትሆናለህ አለው፡፡ ቁጣው የራቀ ምሕረቱ የበዛ እርሱ የራበው ሰው ለምግብ የሚቸኩለውን ያህል ይቅር ለማለት ይቸኩላል፡፡ ‘ምሕረትን ይወድዳልና ቁጣውንም ለዘላለም አይጠብቅም ተመልሶ ይምረናል ፤ ክፋታችንንም ይጠቀጥቃል ፤ ኃጢአታችንንንም በባሕሩ ጥልቅ ይጥለዋል’ ሚክ 7፡18 ልጆች ሳለን ጥፋት ስናጠፋ ከወላጆቻችን እንደበቃለን፡፡በተደበቅንበት ሰዓት ውስጣችን በፍርሃት ይርዳል፡፡ ‘ዛሬ ገደለኝ’ ‘ዛሬ መሞቴ ነው’ ብለን እንጨነቃለን፡፡ የሚደርስብንን ቅጣት እጅግ አጋንነን ከመፍራታችን የተነሣ መሬት ተሰንጥቃ ብትውጠን አንጠላም፡፡ በዚያ ሁሉ ጭንቀት ውስጥ ግን ወላጆቻችንም እስኪያገኙን ይጨንነቃሉ፡፡ እግዚአብሔርም እንዲህ ነው፡፡ አጥፍቶ በገነት ዛፎች መካከል የተሸሸገ አዳምን ወዴት ነህ ብሎ የፈለገ እርሱ እኛንም ይፈልገናል፡፡ አዳም ከገነት ሳይባረር ገነት ውስጥ እንደጠፋ ፈጣሪ ሳያባርረን ራሳችንን በኃጢአት ተሸማቅቀን ያባረርን እኛን ይፈልገናል፡፡ እርሱ ስለመጥፋትህ ይጨነቃል አንተ ‘ዛሬስ አይምረኝም’ ትላለህ፡፡ የሚገርመው በጥፋታችን ከተደበቅንበት ወላጆቻችን ካገኙን በኋላ ሁለተኛው ዙር ጭንቀታችን ‘ምን አጥፍተህ ነው የተደበቅከው’ መባል ነው፡፡ ጥፋታችንን ሲያውጣጡን እንንቀጠቀጣለን፡፡ ያጠፋነውን ስለምናውቀው ስንት እንደሚያስገርፈንም እናውቀዋለን፡፡ ‘ብትናገር ይሻላል? ግዴለህም!’ ብለው አግባብተውም አስፈራርተውም ወላጆቻችን ጥፋታችንን ያውጣጡናል፡፡ እየፈራን ያጠፋነውን ጥፋት ስንናዘዝ ግን ወላጆቻችን በጥፋታችን ቅጥል ብለው ‘አልመታህም ተናገር’ ያሉንን ረስተው የዱላ ዝናም ያዘንቡብናል፡፡ እግዚአብሔር ግን ጥፋትህን ስትነግረው ቁጣው የሚገነፍል አባት አይደለም፡፡ ’’ኃጢአታችንን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነፃን የታመነና ጻድቅ ነው’ 1ዮሐ 1፡9 ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ መጋቢት 18 2012 ዓ ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ፎቶ :- CMC ሚካኤል ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ዘንድ ጸልዩ! ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like እና Share ያድርጉ FB: https://www.facebook.com/officialHenokhaile/ Telegram: https://t.me/deaconhenokhaile Instagram: https://www.instagram.com/p/CBnMF0nnhcQ/?igshid=549jvl607bv4 Youtube: https://www.youtube.com/channel/UCOaVsWC05aUjeqIEW3fWj7g
Show all...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

🕊 ----------------------------------------------- እንኳን ለእናታችን ለእመቤታች ለቅድስት ድንግል ማርያም ለልጇ ለወዳጇ ለክብር ባለቤት ለጌታችን ለመድኃኒታች ለኢየሱስ ክርስቶስ ለስደታቸው መታሰቢያ ለፈቃድ ጾም [ለጽጌ ጾም] በሰላም አደረሰን። ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ 🕊    ወርኃ ጽጌ   🕊 በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስርአት መሰረት ከመስከረም ፳፮ [26] ቀን እስከ ሕዳር ፮ [6] ቀን ያለው ፵ [40] ቀን የእመቤታችን ና የልጇን ስደት በማሰብ ወርኃ ጽጌን [ዘመነ ጽጌን] ታከብራለች፡፡ ይህ ፵ [40] ቀን የእመቤታችንና የጌታችንና የአምላካችን ስደት የሚታሰብበት ዘመን ነው፡፡ ወቅቱ የአበባና የፍሬ ወቅት በመሆኑ እመቤታችን በአበባ ጌታን በፍሬ እየተመሰሉ ጌታችን በአምልኮት እመቤታችን በፈጣሪ እናትነቷ በተለየ ምስጋና ይመሰገናሉ ፡፡ በዚህ በወርኃ ጽጌ [በዘመነ ጽጌ] የሚጾሙ ክርስቲያኖች ሲኖሩ ጾሙን መንፈሳውያን ሰዎች ሳይታዘዙ በራሳቸው ፈቃድ የሚጾሙት ጾም በመሆኑ [የፈቃድ] የትሩፋት ጾም ይባላል፡፡ በቀኖና ቤተክርስቲያን ከታዘዙት ከ ፯ [7] ቱ አጽዋማት ውጪ የሆነ ትርፍ ጾም ማለት ነው፡፡ ከታዘዘው አትርፎ የጾመ ሰው የመጾሙን ዋጋ ያገኛል፡፡ ብዙ መንፈሳዊ ሥራ የሰራ ሰው ብዙ ክብር እንደሚያገኝ መጽሐፍ ይናገራልና፡፡ ‘’እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ሐጢአትዋ ተሰርዮላታል፡፡ ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል’’ [ሉቃ.፯፥፵፯] እንዲል፡፡ የጽጌን ጾም የሚጾሙ ሰዎች እመቤታችን ከልጇ ጋር በስደት የተቀበለችውን መከራና የደረሰባትን ሀዘን እየሰቡ በክብርም ከእመቤታችን ጋር ይተባበራሉ፡፡ ከእመቤታችን ጸጋንና በረከትን ያገኛሉ፡፡ ነገር ግን የጽጌን ጾም የሚጾሙ ሰዎች ለመመጻደቅ መጾም የለባቸውም፡፡ የማይጾሙ ሰዎችንም መንቀፍና መክሰስ የለባቸውም፡፡ የጽጌ ጾም እንዲጾም በቀኖና ቤተክርስቲያን ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ ተደርጎ ስላልተወሰነ የማይጾሙ ሰዎች ሕገ ጾምን እንዳፈረሱ አድርጎ መውሰድ ስሕተት ነው፡፡ ይልቁንም የሚጾሙ ሰዎች ቢችሉ መጾማቸው እንዳይታወቅባቸው ቢያደርጉ የተሻለ ነው፡፡ "ስትጾሙ እንደግብዞች አትጠውልጉ" [ማቴ.፮፥፲፮] የተባለው ለዚህ ዓይነቱ ጾም ነው፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡ ወለወላዲቱ ድንግል ፡ ወለመስቀሉ ክቡር ! [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ] ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
Show all...