cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Aleazer Melese

የእግዚአብሔርን ቃል መማር

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
211Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ሻሎም ቅዱሳን ➡ዛሬ ስለ አብና ወልድ የአካል ልዩነት እናያለን ዮሐንስ 8 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁶ የላከኝ አብ ከእኔ ጋር ነው እንጂ ብቻዬን አይደለሁምና እኔ ብፈርድ ፍርዴ እውነት ነው። ¹⁷ የሁለት ሰዎችም ምስክርነት እውነት እንደ ሆነ በሕጋችሁ ተጽፎአል። ¹⁸ ስለ ራሴ የምመሰክር እኔ ነኝ፥ የላከኝም አብ ስለ እኔ ይመሰክራል። ➡ኢየሱስ ብቻውን አይደለም አብ ከእርሱ #ጋር ነበረ። ➡ኢየሱስ በአካል ከአብ ባይለይ ኖሮ አብ ከኢየሱስ #ጋር ባልሆን ነበር። ➡ የሁለት ሰዎች ምስክርነት አስፈላጊ መሆኑን አይሁዳውያን ስለሚያውቁ #አንዱ ስለ ኢየሱስ የሚመሰክረው ➡ኢየሱስ ራሱ ሲሆን #ሁለተኛው መስካሪ ➡አብ ነው። ➡ኢየሱስ አብ አይደለም ። ➡አብ ኢየሱስ አይደለም ። Join and share ⏬⏬⏬ ⏬⏬⏬ t.me/aleazermelese
Show all...
ሻሎም ቅዱሳን ብዙ ጊዜ ➡ማርያም ከእግዚአብሔር አንሳ ከሰው ትበልጣለች ስሉ እንሰማለን ። ኦርቶዶክስ ወዳጆቻችን ለምን እንደዚህ ያወራሉ ? ➡መልሱ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት በሌላቸው መንፈሳዊ በሚመስሉ መጽሐፍቶች ስለተከበቡ ነው። ➡መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል ? #ኢየሱስ ክርስቶስ በማቴ 11:11 እውነት እላችኋለሁ ➡ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ➡ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሳም ። ይህ የሚያሳየው ማርያም ከሰው የማትበልጥ መሆኗን ነው። ➡ማርያም ከሴቶች መካከል የተባረከች እንጂ ከሴቶች ሁሉ የሚትበልጥ አይደለችም ። ⏬⏬⏬ share Join 👉👉👉👉👉 👉👉👉👉👉 👉👉👉👉👉 t.me/aleazermelese
Show all...
ሻሎም ቅዱሳን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞች ማርያም ከእግዚአብሔር የሚታንስ ከሰው የሚትበልጥ ነች ይላሉ ። ➡ኢየሱስ በማቴ 11:1 ከሴቶች ከተወለዱት #ከዮሐንስ የሚበልጥ የለም ብሏል ። ➡ማርያም ከዮሐንስ አትበልጥም። ➡ ማርያም ከእግዚአብሔር ታንሳለች ይላሉ እንጂ በብዙ የቤተክርስቲያንቱ መጽሐፍት ታላላቅ ብርሃናትን የፈጠረች ይላል ። ከዚህ ሰፋ አድርገን የሚናይ ይሆናል ። share አድርጉ join አድርጉ ⏬⏬⏬⏬ 👉@aleazermelese
Show all...
🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂 #ምሳሌ_6_21 #ሁልጊዜም_በልብህ_አኑረው_በአንገትህም_እሰረው። " ♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦ አንዳንድ በልማድ በውስጣችን የተሰገሰጉ ምንም አይነት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ የሌላቸው ነገር ግን መንፈሳዊ መስለው አብረውን አድገው ያረጁ ብዙ ልማዳዊ ነገሮች አሉ #ትልቁ ስህተት የሚጀምረው ደግሞ እነኚህን #በዘፈቀደ የተሰገሰጉ ልምምዶችና አስተምሮቶ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ለማረግ #መጽሐፍ_ቅዱስን በግድ ጠምዝዞ የምንፈልገውን እንዲል ማስገደድ ከባድ ስህተት ነው ፡፡ #እንደ_አንድ_ክርስቲያን እነኚህን አይነት ማስረጃ የሌላቸው ነገሮች ማጋለጥ እና እውነትን መግለጥ ግዴታዬ ነው ፡፡ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ በውይይት ወቅት #መስቀልን_በአንገት ስለማሰር ማስረጃ በማለት የሚያቀርቡት ክፍል ☞ ምሳሌ 6:21 በእርጋታ ለተመለከተው ክፍሉ ፍጹም ከዚ የተለየ ሐሳብ የያዘ ሆኖ እናገኘዋለን ፡፡ 📚 ከመጽሐፍ ቅዱስ አንድን #መስመር_ነቅሶ በማውጣት አሰተምሮ አይሰራም ፡፡ ቁጥር 21 ን ከ ቁጥር 20 ገንጥሎ በማውጣት የሌለ ሐሳብ መፍጠርም ስህተት ነው ለዚህ ነው ከፍ ብለን ቁጥሮቹን ከላችና ከታች ማየት የሚገባን እንዲህ ይላል 👇👇 ..............,,,,........,,,,.........,,,,,........ (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕ. 6) ---------- 20፤ #ልጄ_ሆይ_የአባትህን_ትእዛዝ ጠብቅ፥ #የእናትህንም_ሕግ አትተው፤ 21፤ #ሁልጊዜም_በልብህ አኑረው፥ #በአንገትህም_እሰረው። 22፤ ስትሄድም ይመራሃል፤ ስትተኛ ይጠብቅሃል፤ ስትነሣ ያነጋግርሃል። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••• እንግዲ የክፍሉን ሙሉ ሀሳብ ለማግኘት ከቁጥር 20 ጀምሮ ማንበብ ግድ ይላb ፡፡ ነገር ግን ቁጥር #21 ን ብቻ ገንጥሎ በማውጣት የመጽሐፉን ሙሉ ሐሳብ ማግኘት አይቻልም ስለዚህ ክፍሉ እንዲ ይላል 📌 የአባትህን ትዕዛዝ ጠብቅ 📌 የእናትህን ሕግ አትተው ይለንና ቁጥር 21 ላይ 🔍 ሁል ጊዜ በልብህ አኑረው በአንገትህም እሰረው ይላል ይህ ማለት ግን እንጨት ወርቅ ነሀስ ወይም ሌላ ነገር በመስቀል ቅርጽ ቀርጸህ አንገትህ ላይ አንጠልጥል ማለት አደለም ፡፡ ስለዚህ የእኔ ሙግቴ መስቀል በአንገት ለማሰር ብላቹ የምታቀርቡት #ማስረጃ ልክ ያልሆነና የመጽሐፉን ሐሳብ ካለመረዳት የተፈጠረ ስህተት ነው ፡፡ እኔም ልክ ያልሆኑ ሐሰቶችን በመጽሐፍ ቅዱስ እውነት መዝኜ አጋልጣለሁ እውነትን #እሰብካለሁ ፡፡ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ⏰ @Henock4 ⏰ ⏰ @adiskidanj ⏰ 💡💡💡💡💡💡💡💡💡💡
Show all...
ሻሎም ቅዱሳን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮና የመጽሐፍ ቅዱስ እውነት ! ➡ይህች ቤተክርስቲያን ኢየሱስ አማላጅ አይደለም ብላ ታስተምራለች። ➡ምዕመናን መጽሐፍ ቅዱስን እንድያነቡ አትፈቅድም ። የሚፈቀደው ሌሎች የቤተክርስቲያንቷን አስተምህሮ የያዙ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ያልሆኑ ትምህርቶችን ብቻ የሚያስተምሩ መጽሐፍትን እንድያነቡ ነው። ➡አንዳንድ መጽሐፍ ቅዱስን ለማንበብ ፍላጎት እና የማንበብ እድል ያገኙ ኢየሱስ አማላጅ ነው የሚለውን ሮሜ 8:34 አንብበው ጴንጤ እንዳይሆኑ ብለው ሮሜ 8:34 ስለ እኛ የሚፈርደው ኢየሱስ ነው ብለው ቀይረዋል ። ይህ አስተምህሮ እግዚአብሔር ያጸደቃቸውን ጻድቃንን ኢየሱስ ይኮንናቸዋል የሚል የሐሰት የክህደት አስተምህሮ ነው። ➡እግዚአብሔር ያጸደቀውን ኢየሱስ አይኮንንም ➡በክርስቶስ ላሉት ለጻድቃን ኩነኔ የለባቸውም ። በክርስቶስ ያሉት በኩነኔ አሉ ማለት የኢየሱስ መሞት መነሣት ወደ አብ ማረጉ ከንቱ ነው ማለት ነው። “እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም።” — ሮሜ 8፥1 Share Join t.me/aleazermelese
Show all...
ሻሎም ቅዱሳን ዛሬ ኢየሱስ እኔን ያየ አብን አይቷል ያለው ለምን እንደሆነ እናያለን ዮሐንስ 14 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁸ ፊልጶስ- ጌታ ሆይ፥ አብን አሳየንና ይበቃናል አለው። ⁹ ኢየሱስም አለው፦ አንተ ፊልጶስ፥ ይህን ያህል ዘመን ከእናንተ ጋር ስኖር አታውቀኝምን? እኔን ያየ አብን አይቶአል፤ እንዴትስ አንተ፦ አብን አሳየን ትላለህ? ¹⁰ እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ አታምንምን? እኔ የምነግራችሁን ቃል ከራሴ አልናገረውም፤ ነገር ግን በእኔ የሚኖረው አብ እርሱ ሥራውን ይሠራል። #እኔን___ያየ__አብን__አየ ምን ማለት ነው? ኢየሱስ አብ ነው ማለት ነው? የሐዋርያት (only Jesus) ተከታዮች ዮሐ 14:9 ሁሌ ስጠቅሱ ዋና ሀሳባቸው ➡ኢየሱስ አብን አሳየን ብለው ስጠይቁት እኔን ያየ አብን አይቷል ስላለ ኢየሱስ አብ ነው ማለት ነው ይላሉ ። ኢየሱስን ያየ አብን አይቷል ማለት ኢየሱስ አብ ነው ማለት አይደለም ምክንያቱም ኢየሱስ እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል ብሏልና ። ደቀመዛሙርትን የሚቀበል ኢየሱስን ይቀበላል ማለት ደቀመዛሙርት ኢየሱስ ናቸው ማለት አይደለም ። ➡እኔን ያየ አብን አይቷል ማለት ታድያ ምን ማለት ነው? “መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም፤ በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ እርሱ ተረከው።” — ዮሐንስ 1፥18 እግዚአብሔር አብን በሙሉ ክብሩ ያየ ሰው ስለሌለ አንዲያ ልጁ ኢየሱስ ተረከው። ➡ኢየሱስ እግዚአብሔር አብን ተረከ እንጂ ኢየሱስ ራሱ አብ አይደለም ። ➡ኢየሱስ አብ ብሆን ኖሮ አብን ተረከ ባልተባለ ነበረ። ፔጄን ለይክና ሼር አድርጉ t.me/aleazermelese
Show all...
ሻሎም ቅዱሳን #ታቦቱን#ከእንግዲህ_ወዲህ__አይጠሩም__ልብ_______አያደርጉትም። በሙሴ ጊዜ የተሰራው ታቦት በሰለሞን ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ አልመጣም ። ከንጉሥ ሰለሞን በኋላ እስከ ንጉሡ ኢዮስያስ ድረስ የኪዳኑ ታቦት በእስራኤል ነበረ። 2ዜና 35:3 ➡እስራኤላውያን በምድር በሚበዙበት ጊዜ ታቦት እንደማያስፈልግ በግልጽ ኤር 3:16 ይነግረናል ። የ Facebook ፔጄን ለይክ በማድረግ ወንጌልን ከእኔ ጋር በአንድነት እናገልግል። https://www.facebook.com/103767338553383/posts/253511483578967/?app=fbl Join t.me/aleazermelese
Show all...
🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂 #ምሳሌ_6_21 #ሁልጊዜም_በልብህ_አኑረው_በአንገትህም_እሰረው። " ♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦ አንዳንድ በልማድ በውስጣችን የተሰገሰጉ ምንም አይነት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ የሌላቸው ነገር ግን መንፈሳዊ መስለው አብረውን አድገው ያረጁ ብዙ ልማዳዊ ነገሮች አሉ #ትልቁ ስህተት የሚጀምረው ደግሞ እነኚህን #በዘፈቀደ የተሰገሰጉ ልምምዶችና አስተምሮቶ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ለማረግ #መጽሐፍ_ቅዱስን በግድ ጠምዝዞ የምንፈልገውን እንዲል ማስገደድ ከባድ ስህተት ነው ፡፡ #እንደ_አንድ_ክርስቲያን እነኚህን አይነት ማስረጃ የሌላቸው ነገሮች ማጋለጥ እና እውነትን መግለጥ ግዴታዬ ነው ፡፡ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ በውይይት ወቅት #መስቀልን_በአንገት ስለማሰር ማስረጃ በማለት የሚያቀርቡት ክፍል ☞ ምሳሌ 6:21 በእርጋታ ለተመለከተው ክፍሉ ፍጹም ከዚ የተለየ ሐሳብ የያዘ ሆኖ እናገኘዋለን ፡፡ 📚 ከመጽሐፍ ቅዱስ አንድን #መስመር_ነቅሶ በማውጣት አሰተምሮ አይሰራም ፡፡ ቁጥር 21 ን ከ ቁጥር 20 ገንጥሎ በማውጣት የሌለ ሐሳብ መፍጠርም ስህተት ነው ለዚህ ነው ከፍ ብለን ቁጥሮቹን ከላችና ከታች ማየት የሚገባን እንዲህ ይላል 👇👇 ..............,,,,........,,,,.........,,,,,........ (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕ. 6) ---------- 20፤ #ልጄ_ሆይ_የአባትህን_ትእዛዝ ጠብቅ፥ #የእናትህንም_ሕግ አትተው፤ 21፤ #ሁልጊዜም_በልብህ አኑረው፥ #በአንገትህም_እሰረው። 22፤ ስትሄድም ይመራሃል፤ ስትተኛ ይጠብቅሃል፤ ስትነሣ ያነጋግርሃል። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••• እንግዲ የክፍሉን ሙሉ ሀሳብ ለማግኘት ከቁጥር 20 ጀምሮ ማንበብ ግድ ይላb ፡፡ ነገር ግን ቁጥር #21 ን ብቻ ገንጥሎ በማውጣት የመጽሐፉን ሙሉ ሐሳብ ማግኘት አይቻልም ስለዚህ ክፍሉ እንዲ ይላል 📌 የአባትህን ትዕዛዝ ጠብቅ 📌 የእናትህን ሕግ አትተው ይለንና ቁጥር 21 ላይ 🔍 ሁል ጊዜ በልብህ አኑረው በአንገትህም እሰረው ይላል ይህ ማለት ግን እንጨት ወርቅ ነሀስ ወይም ሌላ ነገር በመስቀል ቅርጽ ቀርጸህ አንገትህ ላይ አንጠልጥል ማለት አደለም ፡፡ ስለዚህ የእኔ ሙግቴ መስቀል በአንገት ለማሰር ብላቹ የምታቀርቡት #ማስረጃ ልክ ያልሆነና የመጽሐፉን ሐሳብ ካለመረዳት የተፈጠረ ስህተት ነው ፡፡ እኔም ልክ ያልሆኑ ሐሰቶችን በመጽሐፍ ቅዱስ እውነት መዝኜ አጋልጣለሁ እውነትን #እሰብካለሁ ፡፡ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ⏰ @Henock4 ⏰ ⏰ @adiskidanj ⏰ 💡💡💡💡💡💡💡💡💡💡
Show all...
ሻሎም ቅዱሳን ስለ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅነት እያወረን ነው ሰሞኑን ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው ከማርያም ያለ ወንድ ስለተወለደ አይደለም ። ምክንያቱም ኢየሱስ በመለኮቱ ዘላለማዊ ነውና ። የኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅነት የመለኮት እንደሆነ በዮሐ 5:17 አይተናል ። አሁን የአብና የወልድ አንድነትን እንይ ኢየሱስ እኔና አብ አንድ ነን ብሏል ። ዮሐንስ 10 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³⁰ እኔና አብ አንድ ነን። ³¹ አይሁድ ሊወግሩት ደግመው ድንጋይ አነሡ። ³² ኢየሱስ፦ ከአባቴ ብዙ መልካም ሥራ አሳየኋችሁ፤ ከእነርሱ ስለ ማናቸው ሥራ ትወግሩኛላችሁ? ብሎ መለሰላቸው። ³³ አይሁድም፦ ስለ መልካም ሥራ አንወግርህም፤ ስለ ስድብ፤ አንተም ሰው ስትሆን ራስህን አምላክ ስለ ማድረግህ ነው እንጂ ብለው መለሱለት። ኢየሱስ እኔና አብ አንድ ነን ማለት ኢየሱስ ከአብ ጋር በመለኮት አንድ መሆኑን በመግለጽ አምላክ መሆኑን በመናገሩ ነው። አይሁዳውያን ኢየሱስ ሰው ብቻ ስለመሰላቸው አንተ ሰው ስትሆን ራስህን አምላክ ስለ ማድረግህ ነው ብለው ከሰሱት ኢየሱስ ሰው ብቻ ሳይሆን አምላክም ነው። የኢየሱስ እና የአብ አንድነት በመለኮት እንጂ በአካል አይደለም ። ኢየሱስ እና አብ በአካል አንድ አይደሉም ማለት ኢየሱስ አብ አይደለም ማለት ነው። አብ አባት ማለት ነው። ወልድ ልጅ ማለት ነው። የአባቴ ስም መለስ ይባላል ። መለስ የኔ አባት ነው ማለት እኔ መለስ ነኝ ማለት አይደለም ።በተመሳሳዩ ኢየሱስ የአብ ልጅ ነው ማለት ኢየሱስ አብ ነው ማለት አይደለም ። ይህንን መልዕክት በተለይ ለሐዋርያት(only Jesus ) ተከታዮች ሼር አድርጉላቸው ። @aleazermelese
Show all...
ሻሎም ቅዱስ ዛሬ ስለ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅነት መጽሐፍ ቅዱስ ምን እንደሚል እንመለከታለን። ብዙ ክርስቲያኖች ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ማለት ምን ማለት እንደሆነ አያውቁም ። ➡ኢየሱስ የእግዚአብሔር (አብ) ልጅ ነው ማለት ኢየሱስ አምላክ ነው ማለት ነው። ➡እኔ ሰውም የሰውም ልጅ እንደሆንኩ ኢየሱስም እግዚአብሔርም ነው የእግዚአብሔርም ልጅ ነው። ዮሐንስ 5 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁷ ኢየሱስ ግን፦ አባቴ እስከ ዛሬ ይሠራል እኔም ደግሞ እሠራለሁ ብሎ መለሰላቸው። ¹⁸ እንግዲህ ሰንበትን ስለ ሻረ ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ደግሞ ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር አስተካክሎ፦ እግዚአብሔር አባቴ ነው ስላለ፥ ስለዚህ አይሁድ ሊገድሉት አብዝተው ይፈልጉት ነበር። ይቀጥላል t.me/aleazermelese
Show all...
ሻሎም ቅዱሳን እንኳን ለጌታችን ለኢየሱስ የልደት መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን! በኢየሱስ መወለድ ብዙ ነገር ሆኗል *ኢየሱስ መወለድ የእግዚአብሔር ዘላለማዊ ፈቃዱ የተፈጸመበት ነው። እግዚአብሔር በሥጋ ተገልጾ ከሰው ጋር ኖሯል ። ኤማኑኤል “እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፥ ትርጓሜውም፦ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል ነው።” — ማቴዎስ 1፥23 ኢየሱስ በመወለዱ በጨለማ የሄደ ሕዝብ ብርሃንን አይቷል ።
Show all...
ሻሎም ቅዱሳን የቻናሌ ተከታታዮች ሰላምና ጸጋ ይብዛላችሁ ስለ ጠፋሁ ይቅርታ እጠይቃችኋለሁ ። በ Facebook page ስላለኝ ሁላችሁም ፔጄን መከታተል ትችላላችሁ ። ስለ እኛ ኢየሱስ በአብ ፊት ይታያል ምክንያቱም አማላጃችን ነውና። https://www.facebook.com/103767338553383/posts/244165611180221/?app=fbl
Show all...
ሻሎም ቅዱሳን ለእግዚአብሔር ልጆች በእግዚአብሔር ፍቃድ መኖር አማራጭ የሌለው ነገር ነው። ትዳር እግዚአብሔር ያቋቋመው ተቋም ነው። ሄዋን ለአዳም እንደሚታስፈልግ አውቆ ያመጠው እግዚአብሔር እንጂ ረዳት ትኑረኝ ብሎ አዳም ጠይቆ አይደለም ። አብርሃም ለልጁ ለይስሐቅ ሚስት እንድያመጣ ኃላፍነትን ስሰጠው እግዚአብሔር እንዴት እንመራው ማወቅ እንችላለን ይህ የሚያሳየው ለትዳራችን የእግዚአብሔር ፍቃድ ወሳኝ መሆኑን ነው። ሌላው ልባም ሴት/ወንድ ከእግዚአብሔር ዘንድ ነች/ነው ይላል ። ስለዚህ የእግዚአብሔርን ፍቃድ ለማወቅ ወደ እግዚአብሔር መጸለይ አለብን ።ጊዜው ስደርስ ለእኛ በሚገባው መንገድ ጌታ ያሳየናል ። @aleazermelese
Show all...
ሻሎም ቅዱሳን ዛሬ ትንሽ ስለ ወደፊት የትዳር ሕይወት እናውራ! ወጣትነት,,,,,ወደ,,ጓደኝነት,,,,,ጓደኝነት,,ወደ,,,እጮኝነት,,,,,,ከተፈራረረሙ,,,,,ወደ,,ትዳር አለም ይመራል ። እንደ ክርስቲያን ስለ እጮኝነት ስናስብ እጮኝነት ተራ ነገር አይደለም ።ችግኝ መትከልና እጮኛ መያዝ አንድ ናቸው ።አንድ አሪፍ ችግኝ ልታገኝ ትችላለህ ነገር ግን ችግኙን መቼና የት መትከል እንዳለብህ ጠንቅቀህ ማወቅ አለብህ ። እጮኛ ከመያዛችን በፊት ያፈቀረን ወይም ያፈቀርነው ሰውጋ ስንቀርብ ከመቅረባችን በፊት የእግዚአብሔር ፈቃድ መኖሩንና አለመኖሩን ቀድመን ማወቅ አለብን ። ካልሆነ እንተላለፋለን።።። ይቀጥላል 👉👉👉 @aleazermelese
Show all...
ሻሎም ቅዱሳን ይህ የዩትዩብ ቻናሌ ነው። https://m.youtube.com/watch?v=qJG8h5TFCFE
Show all...
ሻሎም ቅዱሳን በቻናሌ እየተባረካችሁና እየተጠቀማችሁ ያላችሁ ውድ የእግዚአብሔር ልጆች ቻናሌን ለጎደኞቻችሁ forward አድርጉላቸው ። t.me/aleazermelese
Show all...
ሻሎም ቅዱሳን ኢየሱስ ስለ ጸሎት ስያስተምር እንድህ ብሏል “አሕዛብም በመናገራቸው ብዛት እንዲሰሙ ይመስላቸዋልና ስትጸልዩ እንደ እነርሱ በከንቱ አትድገሙ።” — ማቴዎስ 6፥7 Network በማይሰራ ቤት 100 ጊዜ ብንደውል እንኳ እንደማይሰራ ሁሉ በክርስቶስ ሳናምንና በመንፈሱ ሳንመራ ብዙ ብናወራም/ብንጸልይም እግዚአብሔር አይሰማንም ። በከንቱ አትድገሙ network በሚሰራበት ካርድ ባለው ስልክ ለመደወል ሴክንዶች በቂ ናቸው ። መፍትሔው 👉በመንፈስ ቅዱስ ምሪት መመራት ብቻ ነው። ሮሜ 8 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁶ እንዲሁም ደግሞ መንፈስ ድካማችንን ያግዛል፤ እንዴት እንድንጸልይ እንደሚገባን አናውቅምና፥ ነገር ግን መንፈስ ራሱ በማይነገር መቃተት ይማልድልናል፤ ²⁷ ልብንም የሚመረምረው የመንፈስ አሳብ ምን እንደ ሆነ ያውቃል፥ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ስለ ቅዱሳን ይማልዳልና። Share Join 👉 @aleazermelese
Show all...
በእግዚአብሔር አካሄድ የሚሄድ ማለትም ከእግዚአብሔር ጋር መኖር የሚችል ሰው ከማንም ጋር መኖር አይከብደው። ከሐሜቴኛ ሰው ጋር እየኖረ ሐሜትን ለመቀነስ ሐሜት አያወራም ። ,,,,, ይቀጥላል 👇👇👇 @aleazermelese
Show all...
ሻሎም ቅዱሳን በሙሴ ሕግ ተሰጠን ጸጋና ሕይወት ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ተሰጠን። ጸጋ ነጻና በዋጋ የማይተመን ስጦታ ነው።ጸጋ በነጻ የተሰጠን ጸጋን መግዛት የሚንችልበት አቅም ለማናችንም ስለሌለ ነው።ጸጋን ለመቀበል ከስጦታው በፊት ሰጭውን ኢየሱስን መቀበልና ለእርሱ በእምነት መታዘዝ አለብን ።ጸጋ የእኛ ብቃት የሚታይበት ሳይሆን በእኛ ድካም የእግዚአብሔር ብርታት የሚታይበት ነጻ ስጦታ ነው። ይቀጥላል,,,,,, Join 👇👇👇👇 👇👇👇👇 @aleazermelese
Show all...
የወንድማችንን የኃይሌ የቴሌግራም ቻናልን ተቀላቀሉ t.me/VofGM
Show all...
"እግዝሐብሄርን የሚያመልክ ሰው ከጠላት ያመልጣል" የሚለው አባባል የተለመደ ቢሆንም፤ "እግዝሐብሄርን የሚያመልክ ጠላቱን ይለውጣል።" የሚለውን መርሳት አይገባንም። አንደኛው መገለጫችን ጠላትን ወዳጅ ማድረግ መቻላችን ነው።
Show all...
Show all...
እግዚአብሔር የሚከብረውን ነገር ካደረግህ ተጠቃሚና ጠቃሚ ሰው ትሆናለህ ።
Show all...
#እግዚአብሔር____________ያለህ__ነገር___ስትታዘዘው___ይሆንልሃል ! Join ⏬⏬⏬ 👇👇👇👇 t.me/aleazermelese
Show all...
📌📌📌እንኳን ለጌታችንና ለመድሃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት መታሰቢያ በዓላ አደረሳቹሁ፡፡ ✝כי־ילד ילד־לנו בן  נתן־לנו ותהי המשרה על־שכמו ויקרא #שמו פלא יועץ אל #גבור אביעד #שר־שלום ✝parvulus enim natus est nobis filius datus est nobis et factus est principatus super umerum eius et vocabitur nomen eius Admirabilis #consiliarius #Deus #fortis Pater #futuri saeculi Princeps #pacis ✝ For a Child hath been born to us, A Son hath been given to us, And the princely power is on his shoulder, And He doth call his name #Wonderful, C#ounsellor, Mighty #God, Father of #Eternity, #Prince of #Peace. ✝ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ #መካር፥ ኃያል #አምላክ፥ የዘላለም #አባት፥ የሰላም #አለቃ ተብሎ ይጠራል።" (ትንቢተ ኢሳይያስ 9:6) ✍ዓለማችን ከተፈጠረችበት ጊዜ እንስቶ ብዙ በተለምዶ ድንቃድንቅ ነገሮችን በድንቃድንቅ መዝገብ ላይም አስፈራላች፡፡ እነዚህ ሊrድ ሰው ችሎታ(የእግዚአብሔር ልዩ ስጦታ) መከናወን ሲገኝ የተቀረው አእላፍ ህዝብ ለማጨብጨብና ለማድነቅእንደውም ለሙገሳ መውጣት የተለመደ ነው፡፡እነዚህ ድንቃድንቅ ተብዬዎች ሁላ ሊሆን የማችሉ ሰይሆኑ በብዙ ሰዎች ሊደረጉ የለማይችሉ የመሆኑ ሚስጥር በአድናቂዎችም እንዲሁም በተደናቂው ልቦና የተቀመጠ ገሃድ ነው፡፡ ነገ ሌላ ሰው መጥቶ ሊሽረው ከቀደመው የበለጠውን ሊቀበል አለና፡፡ፈጽሞ ከዚህ በተለየ መልኩ ዓለማችን ከ2000 ዓመታት በፊት ልትረሳው ፈጽሞ የማትችለውን በሌላ በማንም ሊደፈ፣ሊደገምና እና ሊሆን የማይችል እንጻራው ያልሆነ እውነት በገሃድ አስተናግዳላች፡፡ይህም የኢየሱስን ልደት ነው፡፡በዓለማችን በ1 ማ.ሰከንድ በአቭሬጅ 9 ህጸናት ይወለዳሉ፡፡መወለድ ብርቅ አደለም ከምክኒያቶቹ አንዱ ደግሞ ሳይወለድ ወደዚህ ዓለም የገባ ስለሌለ ይሆናል፡፡ የክርስቶስን ልደት ከኛ እእንደ ሊሆን ፈጽሞ የማይችልበት ምክኒያቶች አእላፍ ቢሆኑም እርሱ በእናቱ ድንግል ማርያም ሆድ ውስጥ ሆኖም ዓለምን ያስተዳድር ነበር፡፡ ይህም የሚገረማቸው እና እንድት እንዲህ ይሆናል የሚሉ ሰዎች በአምላክ ሁሉን መቻል የማያምኑና አምላክ ማንነቱ ስያሜው እንደሆነ ለሁሉ የታወቀ ሀቅ ነው፡፡እኛ ሰዎች ብዙ ጊዜ ስማችን እና ማንነታችን የሁለት ዓለም ያህል ወይም የህልምና የእውን ያህል የመነነ ስለሆነ ለአምላክ የስም መጠሪዎች ብዙ ትክረት አንሰጠም፡፡ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ላቅርብ “ሀብትን ተመኝተው ሀብታሙ ብለው ስም ስለሰየሙት እና አልቀና ብሎት ዘመኑ በሙሉ በድህነት ስለጨረሰው ምስኪን ኢትዮጲያዊ” ይህኔ ነው የስም ተቃራኒ በትክክል የኖረ ሰው፣ ብዙ ማንሳት ይቻላል፡፡ ነገር ግን በሁሉም ሃይማኖት ዘንድ አምለክ ተብሎ ለሚታመነው የሚሰጠው ስያሜ ከማንነቱ የመነጩ እንጂ በእምላኪዎቹ ስምምነት የሚመጣ አይደለም፡፡አምላክ (ኤልሻዳይ)ሁሉን ቻይ ነኝ ሲል ደግሞ ችሎም ስናይ እኛ ደግሞ ሁሉን ቻይ(ኤልሻዳይ) ነው እንላለን፡፡በጥቅሉ የአምላክ ስሞች መጠሪያ ብቻ ሳይሆኑ ማንነቶቹ ናቸው፡፡ስለዚህ ስለተወለደው ስለዚህ መሲህ ስሞች ከመወለዱ ከ1500 ዓ.ቅ.ክ ራሱ አግዚአብሔር ለነብዩ ኢሳያስ የተናገረውን የሚወለደውን ህጻን ስሞች በትኩረት ማየት አስፈላጊ ነው፡፡ በዚህ ጹሁፌ ከውቅያኖስ በማንኪያ አንዲሉ የሀገሬ አበው ጥቂት ሰው ሆኖ እንደ ሰው ተወልዶ ወደ ምድር ስለመጠው እውነተኛ አምላክ እናትታለን፡፡ 1) #ድንቅ (פֶּלֶא) (wonder) ✍ይህ (פֶּלֶא)ፒላህ የሚለው የዕብራይስጥ ቃል a miracle:--marvelous thing, የሚገረም ነገር ወይም ድርጊት አመልካች ቃል ሲሆን በመጸሐፍ ቅዱስ 13 በሚሆኑ ቦታዎች የእግዚአብሐርን እጅግ አስገራሚ ስራዎች ለመግለጽ ውላል፡፡ዘጽ 15፡11 ፣መዝ 77፡11፣14፣ 78፡12 ፣ 88፡10 ፣ 89፡5 ፣ 119፡129 ኢሳ 25፡1፣ 29፡14…. እንደሚታወቀው የእግዚአብሔር ስራ በቃል መግለጽ የሚቻል አይደለም ነገር ግን እንዱ ልጁ ግን ገልጾታል፡፡መቼ ብለን ስንጠይቅ መጸሀፍ ቅዱስ ኢየሱስ በምድር በነበረበት በ33 ዓመት ተኩል ቆይታው እንደሆነ የየሐ 1፡18፣ 14፡9-11 ላይ ይነግረናል፡፡ስንጠቀልለው ድንቅ የሚለው ስም የእግዚአብሔር ድርጊት ወይም ተግባር ወይም ስራ ኢየሱስ ክርስቶስ ማንነቱ እንደሆነ ይገልጽልናል፡፡ 2) #መካር(יָעַץ )( Counsellor ) יָעַץ yaw-ats' ያውአተስ የሚለው የዕብራይስጥ ቃል determine, devise, guide, purpose በአማረኛው ደግሞ በሚናገረው ቃል ዓላማ ያለው አቅጣጫ የሚመራ የሚል ትርጉም ይሰጣል፡፡ ተመልከቱ ይህ ቃል በመጸሀፍ ቅዱስ ላይ በአትኩሮት የሚያሳየን እግዚአብሔር በዘላለም ዕቅድ ዓለምን በምክሩ ሲመራ እንደነብርና አባቶቻችንንም በድንቅ ሁኔታ አቅጣጫ እያሳየ ሲመራቸው የነበረው እና እንደ እግዚአብሔር ምክር ይታይ የነበሩ የአንዳንድ ሰዎች ምክር ተጠቅሳል፡፡ይህም በእስራኤል የምድረበዳ ቆይታ የተገለጠው የደመናና የእሳት አምድ ዘላለማዊውን ምሪት ራሱ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደነበር በተለያዩ ቁና መጽሀፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮቶችና ጥቅሶች ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ይህም ስም ለህጸኑ መሰጠቱ እርሱ ራሱ እግዚአብሔር እንደሆነ በግልጽ ያሳየናል፡፡ 3) #ኃያል_አምላክ (גִּבֹּר גִּבּוֹר אֵל) (The mighty God) ✍ይህኔ ነው ህጸን ሆነ ግን አምላክ ነው ይለናል፣ ኤል אֵל የሚለው የዕብራይስጥ ቃል የተኛው አማልክት ማለትም እውነተኛውንም ወይም ያህዌን ሀሰተኛውን ወይም ጣዖትን ለማመልከት በመጽሀፍ ቅዱስ የገባ ቃል ነው፡፡ ጣዖታት አምላክ ተደርገው በአምላኪዎቻቸው ዘንድ ቢቆጠሩም እውነታው ግን አይደለም ኃያል ሊሆን ለራሳቸው የሰው ወይም የአምላኪዎቻቸው እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ናቸው፡፡ 4) #የዘላለም_አባት (עַד אָב) עַד אָב ad awb (አድ አወብ) የሚለው የዕብራስጥ ቃል ሁለት ትርጉሞችን የሚሰጥ ይሆናል፡፡ 4.1) #አባት_የዘላለም (The father of eternity)፡- ✍ይህኛውም ትርጉም ያዘለው እውነት በቁጥር መግለጽ ለማይቻለው፣ መጀመሪያና መጨረሻ ለሌለው እና ከአእምሮ በላይ ለሆነው ቀመር-ዘላለም አባቱ የተወለደው ህጸን እንደሆነ ነው፡፡ይህንን ለመረዳት የሚከብድ ሚስጥር በአዲስ ኪዳን ቆላ 1፡15-16፣ዕበ 1፡1-3….ወዘተ በግልጽ በስጋ የተገለጠው ህጸኑ ኢየሱስ ራሱ ለፍጥረታት አባት(ባለቤት) ወይም ፈጣሪ እንደሆነ ከ1500 ዓ.ቅ.ክ የተነገረው ትንቢት በግልጽ ያስረዳናል፡፡ 4.2) #የዘላለም_አባት(The everlasting father)፡- ✍ይህኛው ቃል በውስጡ ያዘለው ትርጉምና እውነቱ የተወለደው ኢየሱስ አባትነቱ የዘላለም ነው የሚል ነው፡፡ይህም የማይቃረጥ ዘላቂና ቀጠይነቱ አሳሳቢ የማይሆን እንደሆነ በቁና መጽሀፍ ቅዱሳዊ እውነት ተረጋግታል፡፡ 5) #የሰላም_አለቃ (The Prince of Peace)( שַׂר שָׁלֹם ) שַׂר שָׁלֹם ሳር-ሻሎም የሚለው የዕብራይስጡ ቃል ነጣጥለን ብንመለከታቸው ትርጉሙን ይበልጥ ለመረዳት ይቀለናል፡፡ ַ שַׂר sar ሳር የሚ
Show all...
ክርስቲያናዊ ዓቅብተ እምነት ************* “አፖሎጀቲክስ” የሚለው የእንግሊዘኛ ቃል አፖሎጊያ ከሚል የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጓሜውም “በመከላከል መናገር” እንደ ማለት ነው፡፡ በጥንታዊቷ ግሪክ የሕግ ስርኣት ውስጥ ሁለት ቁልፍ የሆኑ ቃላት ጥቅም ላይ ይውሉ ነበር፤ የከሳሽ ወገን ንግግር “ካታጎሪያ” በመባል የሚታወቅ ሲሆን የተከሳሽ ወገን ምላሽ ደግሞ “አፖሎጊያ” በመባል ይታወቃል፡፡ “አፖሎጊያ’ የሚለው ቃል በአዲስ ኪዳን ውስጥ በተደጋጋሚ ተጠቅሷል። በሐዋርያት ሥራ 26፡2 ላይ ሐዋርው ጳውሎስ ተከሶ በፊስጦስና አግሪጳ ፊት በቀረበ ጊዜ ተጠቅሞበታል፤ እንዲሁም በፊልጵስዩስ 1፡7፣ 1፡16 እና 1ጴጥሮስ 3፡15 ላይ እናገኘዋለን፡፡ ዓቅብተ እምነት ከነገረ መለኮት የጥናት ዘርፎች መካከል አንዱ ሲሆን መረጃዎችን በተቀናበረ ሁኔታ በመጠቀም ለሃይማኖታዊ አስተምህሮ ጥብቅና መቆም ነው፡፡ የአንድ ሃይማኖት አስተምህሮ ትክክል መሆኑንና እምነቱን መምረጥ ከሰው አመክንዮአዊ አስተሳሰብ ጋር የማይጣረስ መሆኑን ለማሳየት የሚደረግ ጥረትም ነው፡፡ ስለዚህ ዓቅብተ እምነት ሰዎች አስተሳሰባቸውን እንዲለውጡ የማሳመን ሥራ ነው፡፡ ክርስቲያናዊ ዓቅብተ እምነት ክርስቲያናዊ ሥነ መለኮት (Christian Theology)፣ ተፈጥሯዊ ሥነ መለኮት (Natural Theology) እና ፍልስፍናን በማጣመር ክርስቲያናዊውን አስተምህሮ ከውጪያዊ ጥቃቶችና የተሳሳቱ ትርጓሜዎች ለመከላከል ይጥራል፣ እንዲሁም የሌሎች ንፅረተ ዓለማት አስተምሕሮዎችን ይመረምራል፡፡ የክርስቲያን ዓቅብተ እምነት ታሪክ **************** የክርስቲያን ዓቅብተ እምነት ታሪክ ከመጀመርያው ክፍለ ዘመን የሚጀምር ቢሆንም እንደ አንድ የጥናት ዘርፍ የጎለበተውና ወጥ የሆነ መልክ የያዘው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ነው፡፡ ክርስቲያናዊው ዓቅብተ እምነት በተለያዩ የዕድገት ደረጃዎች ውስጥ አልፏል፡፡ ክርስትና በተጀመረበት ዘመንና ተከትለው በነበሩት ጥቂት ክፍለ ዘመናት መካከል ክርስቲያኖች በሮማ መንግሥት ከፍተኛ ስደት ይደርስባቸው ነበር፡፡ ይህንን ስደት ለመቀስቀስና ለማጽደቅ ተቃዋሚዎች የተለያዩ የሐሰት ክሶችን ይጠቀሙ ነበር፡፡ ኔሮ የተባለው የሮም ንጉሥ ክርስቲያኖች ላይ ስደት ለማስነሳት በ64 ዓ.ም. ለስድስት ተከታታይ ቀናት በመንደድ የሮምን ከተማ አብዛኛውን ክፍል ያወደመውን የእሳት አደጋ ያቀጣጠሉት ክርስቲያኖች እንደሆኑ በሐሰት እንደወነጀላቸው ታሲተስ የተባለ ሮማዊ ጸሐፌ ታሪክ ዘግቧል፡፡ የጌታን እራት በቀጥታ በመተርጎም ክርስቲያኖች የሰው ሥጋ እንደሚበሉም ተከሰው ነበር፡፡ እንዲሁም ክርስቲያኖች “ወንድምና እህት” በማለት እርስ በርሳቸው የመጠራራት ልማድ ስለነበራቸው ይህንንም በቀጥታ በመተርጎም የዝምድና ጋብቻ (incest) እንደሚፈጽሙ ተወርቶባቸዋል፡፡ የይሁዲ ኃይማኖት፣ ኖስቲዝምና የግሪክ ፍልስፍና የክርስትናን አስተምህሮ የሚገዳደሩ አስተሳሰቦችም ነበሩ፡፡ እነዚህን የመሳሰሉ ውንጀላዎችንና ስም ማጥፋቶችን እንዲሁም አስተምሕሯዊ ተግዳሮቶችን ለመከላከል የጥንት የቤተ ክርስቲያን አበው የተለያዩ ጽሑፎችን መጻፍ አስፈልጓቸው ነበር፡፡ በጥቅሉ ሲታይ የአበው ጽሑፎች ሦስት ዓላማዎችን ያነገቡ ነበሩ። እነርሱም፦ 1. ክርስትናን ከሐሰት ክሶችና ውንጀላዎች መከላከል 2. የብሉይ ኪዳን ትንቢቶች ፍጻሜ ላይ በመመሥረት የክርስትና አስተምህሮ እውነት መሆኑን ማስረዳት 3. ክርስትና የግሪክ ፍልስፍና ላዕላይና ምልዓት መሆኑን ማስረዳት ናቸው፡፡ የኋለኞቹ ክርስቲያን ዓቃቤ እምነታውያን ሥራዎች የተለያዩ የክርስትና አስተምሕሮዎችን ከተቃዋሚዎች በመከላከልና ስለ እግዚአብሔር መኖር አመክንዮአዊ ማስረጃዎችን በማቅረብ ላይ ያተኮሩ ናቸው። ይቀጥላል ...
Show all...
Share for your friends
Show all...
ፊልጵስዩስ 4 ⁶ ጌታ ቅርብ ነው። በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ። ⁷ አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል።
Show all...
ባቸው ሁኔታዎች ውስጥ እንድናልፍ በመፍቀድ ከዚህ እውነታ ጋር ፊት ለፊት እንድንላተም ብሎም እውነታውን እንድንቀበል ያደርጋል፡፡ እግዚአብሔር ሕግን የሰጠን ወደዚህ እውነት እንድንደርስ ነው። ስለዚህ በአክብሮት እና በጥንቃቄ እንዲህ ማለት እንችላለን፡- እግዚአብሔር ሕግን እንድንጠብቀው ሳይሆን እንድንጥሰው ነው የሰጠን። ሕጉን መፈጸም እንደማንችል በእርግጥ ያውቃል፡፡ ስረ-መሰረታችን እጅግ የተበላሸና እና ከእኛ አንዳች በጎ ነገር እንደማይገኝ ያውቃል (ሮሜ 7፡18)፡፡ ማንም በእግዚአብሔር ፊት በሕግ በኩል ሊጸድቅ አይችልም፡፡ ሕግ ሊያጽድቀን የተሰጠ ሳይሆን “በደል እንዲበዛ” የተሰጠ ነውና (ሮሜ 5፡20)፡፡ ሕግ የተሰጠው እንድንፈጽመው ሳይሆን ሕግ ተላላፊዎች መሆናችንን ለማስረዳት ነው፡፡  “...በሕግ ባይሆን ኃጢአትን ባላወቅሁም ነበር፤ ሕጉ፦ አትመኝ ባላለ ምኞትን ባላወቅሁም ነበርና። ኃጢአት ግን ምክንያት አግኝቶ ምኞትን ሁሉ በትእዛዝ ሠራብኝ፤ ኃጢአት ያለ ሕግ ምውት ነውና። እኔም ዱሮ ያለ ሕግ ሕያው ነበርሁ፤ ትእዛዝ በመጣች ጊዜ ግን ኃጢአት ሕያው ሆነ እኔም ሞትሁ፤” (ሮሜ. 7:7-9)፡፡ ሕግ፣ እውነተኛውን ተፈጥሮአችንን ከተደበቀበት ጎሬ አውጥቶ ወደ አደባባይ ያወጣዋል፡፡ በሚያሳዝን ሁኔታ ለራሳችን ያለን ግምት የተጋነነ እና እጅግ ኩሩዎች ስለሆንን እግዚአብሔር ይህን ውሸት ገልጦ ለማሳየት እና ሃጢአተኞች እና ደካሞች መሆናችንን ለማስረዳት ሕግን ይጠቀማል፡፡  ሕጉ እንደምንተላላፈው እየታወቀ የተሰጠ እንጂ ይፈጽሙታል በሚል ተስፋ የተሰጠ አይደለም፡፡ ለመጠበቅ በምናደርገው ትግል ውስጥ ተላልፈነው ስናበቃ በውስጣችን ያለውን ማንነት ከገለጠ የሕግ አላማ ተሳካ ማለት ነው፡፡ ሕጉ፣ “በእምነት እንጸድቅ ዘንድ ... ወደ ክርስቶስ የሚያመጣ ሞግዚታችን...” ነው (ገላ. 3፡24)። አዳነው ዲሮ ዳባ @aleazermelese
Show all...
1 Respond to this post by replying above this line New post on ወንጌል በድረ-ገፅ አገልግሎት  ከተስፋቢስነትህ ጋር ፊት ለፊት ተፋጠሃል? by tsegaewnet ብዙ ክርስቲያኖች ራሳቸውን በድንገት ወደ በሮሜ 7 ውስጥ በሚገኘው አይነት የሕይወት ልምድ ሲገቡ ቢያገኙም ለምን እንደገቡ ግን መገንዘብ ሲቸግራቸው ይታያል፡፡ በተስፋ እና ድል የተሞላውን የሮሜ 6 ምዕራፍ ካነበቡ በኋላ በፊታቸው በሮሜ 7 ላይ እንደተጠቀሰው አይነት የሕይወት ልምምድ ሊገጥማቸው እንደሚችል ከቶዉኑም አይጠብቁም፡፡ ይህን አስበው ብዙ ሳይቆዩ ራሳቸውን በዚህ ታሪክ ውስጥ ያገኙታል፡፡ ለዚህ ክስተት ማብራሪያው ምንድን ነው?   በመጀመሪያ፣ በሮሜ 6 ላይ የተገለፀው እና እኛ ከክርስቶስ ጋር የመሞታችን ሃቅ ላለን የኃጢአት ጥያቄዎች ሁሉ በቂ ምላሽ በመሆኑ ላይ ምንም ብዥታ ሊኖረን አይገባም፡፡ ሞታችን እና ከሞታችን ጋር ተያያዥ የሆኑ ጉዳዮች በምዕራፉ በተሟላ ዝርዝር ባለመቅረቡ በምዕራፍ 7 ውስጥ ለቀረበው መንፈሳዊ እውነታ እንግዶች እንድንሆን ሊያደርገን ይችላል፡፡ ሮሜ 7 በሮሜ 6፡14 ውስጥ የተገለጸውን እውነት በጥልቀት እንድንረዳ እና በቂ ግንዛቤ እንድንይዝ የሚረዳን ምዕራፍ ነው፡፡ ጥቅሱ እንዲህ ይነበባል፡- “ኃጢአት አይገዛችሁምና፤ ከጸጋ በታች እንጂ ከሕግ በታች አይደላችሁምና።” እዚህ ላይ ያለው ትልቁ ችግር በርካታ ክርስቲያኖች ከሕግ መፈታት (ሮሜ 7፡6) ወይም አርነት መውጣት ማለት ምን ማለት እንደሆነ አለመገንዘባቸው ነው፡፡ ይህን ለመረዳት አስቀድመን የሕግን ምንንነት ማወቅ ይገባናል፡፡ ጸጋ ማለት እግዚአብሔር ለእኔ የሚያደርገው ነገር ሲሆን ሕግ ደግሞ እኔ ለእግዚአብሔር የማደርገው ነገር ነው። እግዚአብሔር እንድፈጽመው ወይም እንዳደርገው የሚጠይቀኝ ቅዱስና እና ጻድቅ ፍላጎቶች አሉት፤ እርሱም ሕግ ይባላል። ሕግ ማለት እግዚአብሔር እንድፈጽመው ከእኔ የሚጠብቀው ቅዱስ ፍላጎት ከሆነ ከሕግ አርነት ወይም ነጻነት መውጣት ማለት ደግሞ እግዚአብሔር ይህን ቅዱስ ፍላጎቱን እኔ እንዳሟላ መጠበቅ ትቶ ራሱ አሟልቷል ማለት ነው፡፡ ሕግ እግዚአብሔር ለእርሱ አንድ ነገር እንዳደርግ እንደሚጥብቅ የሚገልጽ ከሆነ፤ ከሕግ ነጻ መውጣት ደግሞ ከእኔ ምንም እንደማይጠብቅ ያመለክታል። እናም በጸጋው እሱ ራሱ ያደርገዋል።  እኔ (ማለትም በሥጋዬ) የሕግን ትዕዛዝ ለመፈጸም ከቶ አልችልም (ሮሜ 7፡14)፡፡ በዚህ በሰረት በሮሜ 7 ላይ ያለው ሰው ችግር በስጋው ለእግዚአብሔር የሕግን ትዕዛዝ ለመፈጸም መታገሉ መሆኑን እንረዳለን። በእንዲህ ሁኔታ (ማለትም በሥጋህ) የሕግን ትዕዛዝ በመፈጸም እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት በምትንቀሳቀስበት ቅስበት ራስህን ከሕግ በታች ታደርጋለ፡፡ ከዛም የሮሜ 7 ሰውዬን የሕይወት ልምምድ መለማመድ ትጀምራለህ፡፡   እዚህ ላይ አንድ ነገር በጊዜ ግልጽ መሆን አለበት፡፡ ችግሩ እኔ እንጂ ሕጉ አይደለም፡፡ “...ሕጉ ቅዱስ ነው ትእዛዚቱም ቅድስትና ጻድቅት በጎም ናት” ( ሮም 7:12 )፡፡ በሕጉ ላይ ምንም ችግር የለም፣ ችግሩ እኔ ጋር ነው። የሕግ ፍላጎቶች ጽድቅ ናቸው፤ ነገር ግን እንዲፈጽማቸው የተጠየቀው ሰው ዓመፀኛ ነው። ችግሩ፣ ሕጉ የጠየቀው ጥያቄ ተገቢ አለመሆኑ ሳይሆን ፈጻሚው አካል ሊያደርጋቸው አለመቻሉ ነው፡፡  "ከኃጢአት በታች ልሆን የተሸጥሁ" ሰው ነኝ (ሮሜ. 7:14)፡፡ ኃጢአት በእኔ ላይ የበላይ ነው (ይገዛኛል)። ሕግ ከእኔ የሚጠይቀው አንዳች ነገር እስከሌለ ድረስ ጤነኛ መስዬ መኖር እችላለው፤ ሕጉ እንዳደርገው የሚፈልገው ነገር በተገለጠ ጊዜ ግን የእኔም አመጻ (ሃጢአት) አብሮ ይገለጣል፡፡ የተደበቀው ማንነቴ ወደ ብርሃን ይወጣል፡፡ ደንባራ አገልጋይ ቢኖርህና ያለሥራ ተቀምጦ ቢውል ደንባራነቱ ከእርሱ ጋር ቢሆንም ማንነቱ ሳይገለጥ ይቆያል፡፡ ቀኑን ሙሉ ምንም ሳያደርግ ከተቀመጠ ምንም የጠቀመህ ነገር ባኖርም ቢያንስ ግን ሲደናበር ከሚያጠፋው ጥፋት ተጠብቀሃል፡፡ “ጊዜ አታባክን፤ ተነሳና አንድ ነገር አድርግ” ያልከው እለት ወዲያውኑ የተደበቀው ችግር መገለጥ ይጀምራል፡፡ ገና ሲነሳ ከወንበሩ ጋር እግሩ ይላተማል፣ ጥቂት እንደተራመደ በመንገዱ ላይ ካለ ነገር ጋር ይጋጫል፤ ብዙ ሳይቆይ ሲደናበር ውድ እቃህን ከእጁ ላይ ጥሎ ይሰብርብሃል፡፡ እንዲሰራ ሳትጠይቀው ቀርተህ ቢሆን ምንም እንኳ ሊጠቅምህ ባይችልም ይህን ሁሉ ችግር አይፈጸምም፡፡ እንዲያደርግልህ የጠየከው ጥያቄ ከሌለ ደንባራነቱ በጭራሽ አይታወቅም፡፡ ተነስቶ እንዲሰራ መጠየቁ ትክክል ቢሆንም የተጠየቀው ሰው ግን ጥያቄዎን በአግባቡ ለመፈጸም የማያስችል መሰረታዊ ችግር አለበት፡፡ ተቀምጦም ሆነ ሲሰራ ሰውየው ያው ደንባራ ነው፡፡ ነገር ግን ደንባራነቱን የገለጠው ትዕዛዙን ተከትሎ ነው፡፡ ሁላችንም በተፈጥሮ ኃጢአተኞች ነን። እግዚአብሔር ከእኛ ምንም ካልጠየቀ፤ እኛም ሆነ በእኛ ውስጥ ያለው ነገር ሁሉ ጥሩ መስሎ ሊኖር ይችላል፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ከእኛ አንዳች ነገር በጠየቀ ጊዜ (ሕግ) ሃጢአተኛ ተፈጥሮአችን ራሱን መግለጥ ይጀምራል፡፡ በሌላ አነጋገር ሕጉ ድካማችንን በግልጽ ያሳያል። ዝም ብለህ እንድቀመጥ ከፈቀድክልኝ፣ ሁሉ ነገር ሰላም ሊመስል ይችላል፡፡ እንድሰራ ባዘዝከኝ ጊዜ ግን፣ ጥፋቴን መመልከት ትጀምራለህ፡፡ ሁለተኛ እድል ብትሰጠኝም ማጥፋቴን አልተውም፡፡ ቅዱሱን የእግዚአብሔርን ሕግ ለመፈጸም ስነሳ የሚፈጠረውm ይኸው ነው፡፡ ሕጉ በውስጤ ያለውን ማንነቴን መግለጥ ይጀምራል፡፡ እግዚአብሔር እኔ ማን እንደሆንኩ ያውቃል፡፡ ከራስ ጸጉሬ እስከ እግሬ ጥፍሬ በኃጢአት የተሞላሁ እንደሆነም  ያውቃል፡፡ ምንም ማድረግ እንደማልችል ለሱ የተሰወረ ሃቅ አይደለም፡፡ ችግሩ እኔ ይህን ሃቅ አለማወቄ ነው። እኔን ጨምሮ ሰዎች ሁሉ ኃጢአተኞች እንደ ሆኑ መሰረታዊ ግንዛቤ ቢኖረኝም ፍጹም ተስፋ ቢስ ሃጢአተኛ መሆኔን ግን በቀላሉ አልገነዘብም፡፡ ለአብነት፣ ራሴን ከአንዳንድ “የከፉ” ሃጢአተኞች ይልቅ የተሻልኩ አድርጌ ልመለከት እችላለው፡፡ በመሆኑም፣ እግዚአብሔር ፍጹም ተስፋ ቢስ እና ደካማ እንደሆንኩ ወደምገነዘብበት ሁኔታ ሊያመጣኝ ይፈልጋል፡፡ የሕግን ትዕዛዝ ከመፈጸም አኳያ ምን ያህል ጎስቋሎች ወይም ደካሞች እንደሆንን የምንለውን ያህል እውነታውን አናውቀውም፡፡  እናም፣ እግዚአብሔር ከዚህ መራር እውነታ ጋር እንድንፋጠጥ እና እንድንቀበል አንድ መሳሪያ አዘጋጅቷል፤ ያም መሳሪያ ሕግ ይባላል፡፡ በሕጉ ባይሆን ኖሮ ምን ያህል ደካሞች እና ተስፋ ቢሶች መሆናችንን ባላወቅን ነበር፡፡ ጳውሎስ እዚህ ደረጃ ላይ ደርሶ ነበር። በሮሜ 7፡7 ላይ፣ “...በሕግ ባይሆን ኃጢአትን ባላወቅሁም ነበር፤ ሕጉ፦ አትመኝ ባላለ ምኞትን ባላወቅሁም ነበርና” በማለት ይህን መረዳቱን ግልጽ ያደርግልናል፡፡ ከሌሎቹ ትዕዛዛት አንጻር ጳውሎስ የነበረው የሕይወት ልምምድ ምን ይምሰል ምን፣ ማንነቱን ያውቅ ዘንድ ፊት ለፊት የተላተመው ከአሥረኛው ትእዛዝ ጋር እንደነበር ተገልጿል፡፡ በዚህ ትዕዛዝ አማካኝነት ጳውሎስ ከድካሙ እና ተስፋቢስነቱ ጋር ፊት ለፊት ተፋጠጠ! አብዝተን ሕጉን ለመጠበቅ በሞከርን ቁጥር አብዝተን በመውደቅ ሕይወታችን ለሮሜ 7 ልምምድ ቅርብ መሆኑን እየተረዳን እንመጣለን፡፡ የዚህ አላማው፣ በራሳችን የሕጉን ትዕዛዛት ልንፈጽም የማንችል ተስፋ ቢሶችና ደካሞች መሆናችንን ማስገንዘብ ነው፡፡ ከላይ እንደተገለጸው እግዚአብሔር ይህን ማንነታችንን ጠንቅቆ ያውቀዋል፤ እኛ ግን አናውቅም፡፡ ስለዚህም እግዚአብሔር እጅግ አስቸጋሪ እና ህመም ባለ
Show all...
እውቀትን የሚፈልግ ሰው ግዜውን በጥያቆዎች መረብ ያጠምዳል ይላሉ ጠቢባን። በዚህ ሃሳብ እኔም እስማማለው። በተለይ ስለ እግዝሐብሔር መጠየቅ ያስደስተኛል። ጌታ ሁሉን አዋቂና ሁሉን ቻይ አምላክ ነው። ታናናሾችን እንዴት አድርጎ፡- እንደሚመልስ፥እንደምያሳድግ፥ እንደሚንከባከብና ለፍሬ እንደምያበቃ ያውቅበታል። በሌላ በኩል ደሞ ይሄው አንዱ ጌታ ሐጥያትን የማይወድ፥ ውሸትን  የሚጸየፍ፥ የሚቆጣ፥ የሚቀጣ ደግሞም የሚምር ና የእንደገና እድል የሚሰጥ አምላክ ነው። "እውነት እና ውሸት" ይላል ውስጤ። ሁለት ወር ሆነኝ ይህን ማጤንና መጠየቅ እንደዚሁም ከራሴ ህይወት ጋር ማስተያየቱን የተያያዝኩት። በዚህ ሓሳብ ውስጥ እያለው የ እግዝሐብሔር እውነትና የአዳም ውሸት ታወሰኝ።... ጌታ ሁሉን ያውቃል። አዳም እንደሚወድቅም ጠንቅቆ ያውቃል። ሆኖም ግን አዳም እንዳይስት አስጠነቅቆ መከረው እንጂ አላስገደደውም።  ምክንያቱም ሰው በአፈጣጠሩ እግዝሐብሆርን ስለሚመስል፣ ተገዶ የሚኖር ሳይሆን ወዶና ፈቅዶ የሚኖር ነው። ለሚፈልገው ነገር ለመኖር ራሱን ልያስገድድ ይችል ይሆናል እንጂ ማንም ልያስገድደው የሚችል ፍጡር አይደለም። የተፈጠረው ፈጣርውን ስለሚወድና ሊገዛለት ስለሚፈልግ እንጂ ተገዶ እንዲኖርለት አልተፈጠረም።... ሁሉን አዋቂው ጌታ ማንነቱ እውነተኛ ፍቅር ስለሆነ የፈጠረውን ሰው ሙሉ ፈቀድ ሰቶታል።.... ሆኖም ግን አዳም እንደታቀደለት ሳይሆን በፈለገውና በመረጠው መንገድ ነጎደ! እውነቱንና ፍቅሩን ያላወቀው አዳም ጥፋቱን በሌላ ጥፋት ለመሸፈን ሲሞክር ሸሸ።... ሌላ ሩጫ.... የገባበት የውሸት አለም ለእውነት ያለውን አይን አጠልሽቶበታል።..... እውነት ግን አዳም እንዳሰበው አይነት ገዳይ አልነበረም። እውነት ለሌላው ሟች ነው። እውነት distructive ሳይሆን constructive ነው። ይሁንና አዳም ሸሸ!...ወደ ውሸት አለም ሲገባ የሚወደውን ጌታ ጭምር መሸሸግ ጀመረ።...ጌታን ቢወደውም፤ እይታው ስለተጋረደበት ሽሽትን አማራጩ አደረገ። ፍቅር ይፈልገው ጀመር!...""አዳም!"..አዳም,....አአአ...ዳዳ...ምም....ወዴት ነህ?" እውነትና ፍቅር የሆነው ሁሉን አዋቂ ጌታ ጮክ ብሎ ተጣራ። "የት ነህ?" አለ። እውቀቱን በፍቅር በመያዝ ፍቅሩ ጎልቶ እየታየ የከዳውን ልጅን እየፈለገ ዛሬ በማለዳ ከእንቅልፌ ስናቃ ይችን ሓሳብ ነበር እያመነዠኩ የነቃውት። ባጋራቹ ይጠቅማል ብዬ በማሰብ በዝይች ሰሌዳ ከተብኳት.... ጥያቆው ይሄ ነው " ጌታ ሁሉን እያወቀ ለምን የት ነህ አለው?" ሁሉን አዋቂው ጌታ ስለ አንድ ጉዳይ ሲጠይቅህ ለመመለስ ከመፍጠንህ በፊት ማን እንደ ጠየቀህና ጠያቂው ለምን እንደ ጠየቀህ ለማወቅ ግዜ ውሰድ። የምናመልከው አምላክ ለጥያቄያችን ብቻ መልስ የሚሰጥ ጌታ አይደለም። ጠያቂም ነው።..."እግዝሐብሄር ግን ሁሉን እያወቀ ለምን ይሆን የሚጠይቀን?" በንጹ ልብህ የሆነውን ሁሉ እንድትነግረው ፥ ጉብዝናህን ብቻ ሳይሆን ድካምህንም እንድታሳየው ስለሚፈልግ ይጠይቅሃል። ችግርህን መናገር ከቻልክ መፍቴውን በቀላሉ ደረስክበት እንደሚባለውም ነው። የሆነ ግዜ አልበርት ኤንስታይን እንዲህ ብሎ ነበር:- ችግርህን ጠንቅቀህ አወክ ማለት 50% መፍቴ አግኝተሃል ማለት ነው። ጌታም አዳምን የጠየቀው፡ ቶሎ ራሱን በነጻነት እንድያሳየው እንጂ ልያጠፋው አልነበረም።...እንድትነግረው እንጂ ልያዋርድህ አይጠይቅህምና። ወዳጄ:- ለመዋሸትህ የትኛውንም ያክል ምክንያትህ ትልቅ ሆኖ ቢታይህም ከእውነት የሚበልጥ ነገር እንደሌለ አውቀህ ፈጠን ብለህ ከሚፈልግህ ጌታ ጋር ታረቅ።  ውሸት ሕይወትን የምታበላሽ መርዝ ናትና!!
Show all...
ሻሎም ቅዱሳን እንዴት ሰነበታችሁ ! ዛሬ የሚንማማረው #Tile_ብልሃትን__ከዮሴፍ__ሕይወት ዘፍጥረት 41 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ከሁለት ዓመት በኋላም ፈርዖን ሕልምን አየ፥ እነሆም፥ በወንዙ ዳር ቆሞ ነበር። ² እነሆም፥ መልካቸው ያማረ ሥጋቸውም የወፈረ ሰባት ላሞች ከወንዙ ወጡ፥ በውኃውም ዳር በመስኩ ይሰማሩ ነበር። ³ ከእነርሱም በኋላ እነሆ መልካቸው የከፋ ሥጋቸውም የከሳ ሌሎች ሰባት ላሞች ከወንዝ ወጡ፥ በእነዚያም ላሞች አጠገብ በወንዙ ዳር ይቆሙ ነበር። ⁴ መልካቸው የከፋ ሥጋቸውም የከሳ እነዚያም ላሞች መልካቸው ያማረውን ሥጋቸው የወፈረውን ሰባቱን ላሞች ዋጡአቸው። ፈርዖንም ነቃ። ⁵ ደግሞም ተኛ ሁለተኛም ሕልምን አየ፤ እነሆም በአንድ አገዳ ላይ የነበሩ ያማሩና መልካም የሆኑ ሰባት እሸቶች ወጡ፤ ⁶ እነሆም ከእነርሱ በኋላ የሰለቱና በምሥራቅ ነፋስ የተመቱ ሰባት እሸቶች ወጡ፤ ⁷ የሰለቱትም እሸቶች ሰባቱን ያማሩና የዳበሩ እሸቶች ዋጡአቸው። “ፈርዖንም ነቃ፥ እነሆም ሕልም ነበረ። በነጋም ጊዜ ነፍሱ ታወከችበት ወደ ሕልም ተርጓሚዎች ሁሉ ወደ ግብፅ ጠቢባንም ሁሉ ልኮ ወደ እርሱ ጠራቸው፤ ፈርዖንም ሕልሙን ነገራቸው፥ ነገር ግን ከእነርሱ ለፈርዖን የሚተረጕም አልተገኘም።” — ዘፍጥረት 41፥8 በዚህ ምዕራፍ የተገለጸው ሀሳብ የግብፅ ንጉሥ ፈርዖን ከባድ ሕልም አይቶ ሕልሙን ለሕልም ተርጓሚዎች ብነግርም በግብጽ ምድር ካሉ ተርጓሚዎች አንድም ከባዱን ሕልም ልተረጉም አልቻለም ። በዚህ ሁኔታ ንጉሡ በመረበሹ ቤተመንግሥት በጣም ተጨንቋል ።ከ2 ዓመት በፊት ከዮሴፍ ጋር ታስሮ ሕልሙን ፈቶለት የወጣ የንጉሥ ጠጅ አሳላፊ ነበረ።ይህ ጠጅ አሳላፊ ንጉሡ ዮሴፍን ጠርቶ ብነግርለት ሕልሙን ልፈታ እንደሚችል ነገረለት። ከዚያ ዮሴፍ እንድህ አለው ። “ዮሴፍም ለፈርዖን እንዲህ ብሎ መለሰ፦ ይህ በእኔ አይደለም፤ እግዚአብሔር ግን ለፈርዖን በደኅንነት ይመልስለታል።” — ዘፍጥረት 41፥16 ንጉሡ ሕልሙን ከነገረለት በኋላ ዮሴፍ ተረጎመለት። እንድህ ስል ዘፍጥረት 41 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁶ ሰባቱ መልካካሞች ላሞች ሰባት ዓመታት ናቸው፥ ሰባቱም መልካካሞች እሸቶች ሰባት ዓመታት ናቸው ሕልሙ አንድ ነው። ²⁷ ከእነርሱም በኋላ የወጡት የከሱትና መልከ ክፋዎቹ ሰባት ላሞች ሰባት ዓመታት ናቸው፥ የሰለቱትና የምሥራቅ ነፋስ የመታቸው ሰባቱም እሸቶች እነርሱ ራብ የሚሆንባቸው ሰባት ዓመታት ናቸው። ለዘህ ችግር ምን መፍትሔ ያስፈልጋል ? ዘፍጥረት 41 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³³ አሁንም ፈርዖን ብልህና አዋቂ ሰውን ይፈልግ፥ በግብፅ ምድር ላይም ይሹመው። ³⁴ ፈርዖን በምድር ላይ ሹማምትን ይሹም፤ በሰባቱም የጥጋብ ዓመታት ከሚገኘው ፍሬ በግብፅ ምድር ሁሉ ከአምስት እጅ አንደኛውን ይውሰድ። ³⁵ የሚመጡትን የመልካሞቹን ዓመታት እህላቸውን ያከማቹ፤ ስንዴውንም ከፈርዖን እጅ በታች ያኑሩ፥ እህሎችም በከተሞች ይጠበቁ። ³⁶ በግብፅ ምድር ስለሚሆነው ስለ ሰባቱ ዓመታት ራብ እህሉ ተጠብቆ ይኑር፥ ምድሪቱም በራብ አትጠፋም። ³⁷ ነገሩም በፈርዖንና በሎሌዎቹ ፊት መልካም ሆነ። ብልህ ሰው ተሾሞ ይህንን ችግር ልፈታ እንደሚችል ለንጉሡ ዮሴፍ ከነገረለት በኋላ የንጉሡ ምላሽ,,, ዘፍጥረት 41 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³⁸ ፈርዖንም ሎሌዎቹን እንዲህ አላቸው፦ በውኑ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበትን እንደዚህ ያለ ሰው እናገኛለንን? ³⁹ ፈርዖንም ዮሴፍን አለው፦ እንደ አንተ ያለ ብልህ አዋቂም ሰው የለም፥ እግዚአብሔር ይህን ሁሉ ገልጦልሃልና። ⁴⁰ አንተ በቤቴ ላይ ተሾም፥ ሕዝቤም ሁሉ ለቃልህ ይታዘዝ፤ እኔ በዙፋኔ ብቻ ከአንተ እበልጣለሁ። ንጉሥ ፈርዖን ዮሴፍን እንደአንተ ያለ ብልህ ሰው የለም ብሎት ሾመው። #ብልህ__ሰው 1,በየትኛውም እንቆቅልሽ አይሸበርም። 2,የትኛውንም እንቆቅልሽ በእግዚአብሔር ጸጋ ልፈታ ይችላል ። 3,በፈታው እንቆቅልሽ በምድር ባለው ሕይወት የተሳካ ኑሮ ይኖራል እግዚአብሔርን ያስከብራል። እግዚአብሔር ብልህ ሰው ያድርጋችሁ። share Join @aleazermelese
Show all...
ሻሎም ቅዱሳን በቻናሌ ከዚህ በኋላ ብዙ ርዕሰ ጉዳዮችን ስለማነሳ ብዙ ትምህርት ስለሚትቀስሙ ቻናሌን ለጓደኞቻችሁ share እንድታደርጉስል በጌታ ፍቅር እጠይቃችኋለሁ ።
Show all...
Sign in and get access to detailed information

We will reveal these treasures to you after authorization. We promise, it's fast!